መራኁት
Open in Telegram
መራኁት ማለት መፍቻ፣ መክፈቻ፣ ቁልፍ ማለት ነው። ጥያቄዎቻችንን ቋጠሮአችንን በአባቶች ትምህርት እየፈታን አብረን እንጓዛለን። Tiktok: @mera_hut YouTube: @merahuut https://t.me/merahutchat
Show more5 996
Subscribers
-124 hours
-127 days
-2830 days
Posts Archive
5 996
የኔ ተወዳጆች እንደምን አላችሁ፣ ፋርማሲ እና መድኃኒት አከባቢ የምትሠሩ ይህቺን መድኃኒት በፍጥነት ልታገኙልኝ ትችሉ ይሆን?
እግዚአብሔር ያክብርልኝ።
5 996
ከአንድ ወንድሜ ጋር ስንወያይ ብልጭ ያለችልኝን ሐሳብ ላጋራችሁማ።
ልጆች እያለን ማደግ የምንፈልግበት ብቸኛ ምክንያት ልጅነታችንን በነጻነት ለማጣጣም ነበር። ሕጻናት ሆነን ስለማደግ የምናስበው ሳድግ በነጻነት ከጓደኞቼ ጋር እየተጫወትኩ አመሻለሁ፣ ሳድግ ሁሉንም መጫወቻዎች ገዝቼ እጫወታለሁ፣ ሳድግ ሱቅ ውስጥ ያሉትትን ከረሜላዎች እንዳለ ገዝቼ እበላለሁ እና በመሳሰሉት የልጅነት ምኞቶቻችን ዙሪያ ነጻነትን በመሻት ነበር እድገት የምንፈልገው። ማደግ ማለት ልጅነትን ገድሎ መቅበር ማለት እንደሆነ አስበነውም አናውቅ። አይገርማችሁም ቅድስናም እንደዛው ነው። ዛሬ ላይ ብዙዎቻችን የተሻለ መንፈሳዊ ሕይወትን የምንፈልገው የምርም በመንፈሳዊ ሕይወታችን ለማደግ ሳይሆን ሥጋዊ መሻቶቻችንን በተለይም ከንቱ ውዳሴን ለማጣጣም ነው።
ጥሩ ጸሎተኛ፣ ተአምር አድራጊ፣ ጎበዝ ሰባኪ፣ ተወዳጅ ድምጻዊ ዘማሪ፣ የመጻሕፍት ደራሲ፣ ሌላም ሌላም መሆን የምንፈልገው "አቤት እገሌ" እንዲባልልን፣ ከሰዎች ተሽለን መታየትን ስለምንፈልግ፣ የሚሰጠን attention፣ የምናገኛው ክብር ገና በመንፈሳዊነት ያልጠነከረች ሥጋዊነት የጸናባት ነፍሳችንን ስለሚያጓጓት ብቻ ነው እንጂ ከማደግ ጋር ተያይዞ የሚመጣውን የሕይወት ውጣ ውረድ እና መንፈሳዊ ፈተና ታግሎ የማሸነፍ ፍላጎቱም አቅሙም ስላለን አይደለም።
መቀደስ ግን ፈቃደ ሥጋን(ኃጢአትን) ገድሎ መቅበር ነው። በልጅነት የጓጓንለትን ነገር ሁሉ መናቅ፣ የተመኘነውን ክብር እና ዝና መሸሽ፣ ያንን የተመኘንበትን ዘመን ወደኋላ ተመልክቶ በራስ መሳቅ፣ "አይ አለማወቄ" ማለት ነው። ለቅድስና ያለን ፍቅር ለሥጋዊ መሻቶቻችን unlimitted access ለማግኘት ከመሻት የመነጨ መሆኑ ቀርቶ ክርስቶስን መናፈቅ ሲሆን ብቻ ትክክል ይሆናል። ቅዱሳኑም የበለጡን ቅድስናን በመፈለግ ሳይሆን ቅድስናን በሻቱበት ምክንያት ነው። መቀደስንማ ማን ይጠላል። ሐሳቤ ገብቷችሁ ይሆን?😊
5 996
ከአንድ ወንድሜ ጋር ስንወያይ ብልጭ ያለችልኝን ሐሳብ ላጋራችሁማ።
ልጆች እያለን ማደግ የምንፈልግበት ብቸኛ ምክንያት ልጅነታችንን በነጻነት ለማጣጣም ነበር። ሕጻናት ሆነን ስለማደግ የምናስበው ሳድግ በነጻነት ከጓደኞቼ ጋር እየተጫወትኩ አመሻለሁ፣ ሳድግ ሁሉንም መጫወቻዎች ገዝቼ እጫወታለሁ፣ ሳድጉ ሱቅ ውስጥ ያሉትትን ከረሜላዎች እንዳለ ገዝቼ አበላለሁ እና በመሳሰሉት የልጅነት ምኞቶቻችን ዙሪያ ነጻነትን በመሻት ነበር እድገት የምንፈልገው። ማደግ ማለት ልጅነትን ገድሎ መቅበር ማለት እንደሆነ አስበነውም አናውቅ። አይገርማችሁም ቅድስናም እንደዛው ነው። ዛሬ ላይ ብዙዎቻችን የተሻለ መንፈሳዊ ሕይወትን የምንፈልገው የምርም በመንፈሳዊ ሕይወታችን ለማደግ ሳይሆን ሥጋዊ መሻቶቻችንን በተለይም ከንቱ ውዳሴን ለማጣጣም ነው። ጥሩ ጸሎተኛ፣ ተአምር አድራጊ፣ ጎበዝ ሰባኪ፣ ተወዳጅ ድምጻዊ ዘማሪ፣ የመጻሕፍት ደራሲ፣ ሌላም ሌላም መሆን የምንፈልገው "አቤት እገሌ" እንዲባልልን፣ ከስዎች ተሽለን መታየትን ስለምንፈልግ፣ የሚሰጠን attention፣ የምናገኛው ክብር ገና በመንፈሳዊነት ያልጠነከረች ሥጋዊነት የጸናባት ነፍሳችንን ስለሚያጓጓት ብቻ ነው እንጂ ከማደግ ጋር ተያይዞ የሚመጣውን የሕይወት ውጣ ውረድ መንፈሳዊ ፈተና ታግሎ የማሸነፍ ፍላጎቱም አቅሙም ስላለን አይደለም። መቀደስ ግን ፈቃደ ሥጋን(ኃጢአትን) ገድሎ መቅበር ነው። በልጅነት የጓጓንለትን ነገር ሁሉ መናቅ፣ የተመኘነውን ክብር እና ዝና መሸሽ፣ ያንን የተመኘንበትን ዘመን ወደኋላ ተመልክቶ በራስ መሳቅ፣ "አይ አለማወቄ" ማለት ነው። ለቅድስና ያለን ፍቅር ለሥጋዊ መሻቶቻችን unlimitted access ለማግኘት ከመሻት የመነጨ መሆኑ ቀርቶ ክርስቶስን መናፈቅ ሲሆን ብቻ ትክክል ይሆናል። ቅዱሳኑም የበለጡን ቅድስናን በመፈለግ ሳይሆን ቅድስናን በሻቱበት ምክንያት ነው። መቀደስንማ ማን ይጠላል። ሐሳቤ ገብቷችሁ ይሆን?😊
5 996
ተወዳጆች ሆይ እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ትንሣኤ እና እርገት መታሰቢያ ጾም፤ ጾመ ፍልሰታ በሰላም አደረሳችሁ።
የምር ፍሬ የምናፈራበት ጾም እንዲሆን እንድንተጋ በፍቅር አሳስባለሁ። ሰዓታቱን፣ ኪዳኑን ቅዳሴውን የሰርክ ጉባኤውን ከጌታችሁ ለመገናኘት ተጠቀሙበት😊
ደካማ ወንድማችሁን ብስራተ ገብርኤል'ን በጸሎታችሁ ማሰብ ደግሞ አትዘንጉ።
5 996
ከወንድሜ ዲ/ን እንዳለው እና ከውድ ወንድሜ ጸጋ ሥላሴ ጋር በመሆን ባለፈው ዓመት የሠራነውን ይህንን መዝሙር ተጋበዙልኝማ😊
https://youtu.be/K4AYaq1n7t4?si=eGhtK1Ce9oohbENG
5 996
Repost from ሐዋርያዊ መልሶች
ጌታ ኢየሱስን እንደምውደው በውስጤ አይሰማኝም..??
በሕይወታችን ውስጥ ከሚገጥሙን ውድ ነገሮች ውስጥ.. የውዶች ውድ ብዬ የማስበው ኢየሱስን መውደድ ነው.. ኢየሱስን መውደድ ማለት በምድርም በሰማይም ባለጠጋ መሆን ነው.. ልብህን ይሞላዋል.. ጌታህን የሚያስናፍቅ ታላቅ ሥጦታ ነው..
ታድያ ግን እንዲህ ያለው የመንፈስ ስጦታ በተለይም በኃጢአትና በዲያቢሎስ ፈተና ከውስጣችን እየተሰወረ ሊሄድ ይችላል.. በዚህን ጊዜ ማድረግ ያለብን ነገር መዝሙረኛውም እንደሚለው “ቆይቶ እግዚአብሔርን ደጅ መጥናት” ማለትም መላልሶ “ጌታ ሆይ ፍቅርህን ስጠኝ” እያሉ በትዕግሥት መለመን.. ንስሐ እና ቅዱስ ቁርባን አለማቋረጥ..
አንዴ ፍቅሩን መጨመር ሲጀመር ግን ፕሊስ በጥንቃቄ ያዙት.. በተለይ ከጸሎት፣ ከቅድስና፣ ሌሎች ሰዎችን ከመውደድ እንዲሁም ከትህትና ባለመራቅ..
@Apostolic_Answers
5 996
ብጹዕ አቡነ ቀውስጦስ ነፍሴ አጥብቃ ከምትወዳቸው የቤተክርስቲያናችን አባቶች ውስጥ ግንባር ቀደም ናቸው። እንደተለመደው የዚህን ወር አስራታችንን ሕንጻ ብቻ ሳይሆን ሰው ለመገንባት በማሰብ እሳቸው ለሚያሠሩት የአብነት ትምህርት ቤት እያሰባሰብን ነው። ግባችን 200ሺ ብር ማሰባሰብ ነው። 1ሺ ብር መስጠት የሚችሉ 200 ሰዎች አልያም 200 ብር መስጠት የሚችሉ አንድ ሺ ሰዎች ብቻ ነው የምፈልገው😊
screenshot እና ክርስትና ስም በውስጥ ብትልኩ በአባቶቻችን ጸሎት ትታሰባላችሁ😊
የትኖራ ቅዱስ ሚካኤል እና ቅዱስ ጊዮርጊስ 1000596467605
Yetnora kidus Michael betekristian
5 996
ተወዳጆች እንደምን አላችሁ እንኳን አደረሳችሁ😊 ሐምሌ ሰባት ሥሉስ ቅዱስን የምናከብርበት ቀን በመሆኑ ትልቁ ትኩረታችን እዛ ላይ ቢሆንም ታላቁ ቅዱስ አባት አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የእረፍቱ በዓል የሚከበርበት ዕለት ነው። ለእመቤታችን ባለው ጥልቅ ፍቅር እና ዛሬም ድረስ በፍቅር በምናነባቸው የጸሎት መጻሕፍቱ ልባችን ውስጥ ልዩ ስፍራ ያለው አባት ነው። በሚገባው ልክ ባንዘክረው እና አንዳች ልናደርግለት ባንችል እንኳ ቢያንስ በጸሎታችን ጊዜ ስሙን ጠርተን በመማጸን፣ የቻልን መልክኡን በመድገም ድርሳኑን በማንበብ ቀኑን እናሳልፍ። በርሱ ልብ ውስጥ የገዘፈ የእመቤታችን ፍቅር እንደው በጥቂቱ በእኛ ልብ ቢበቅል፤ ቅዱሱን መዘከር ይገባል😊 እነሆ ስለርሱ የተዘመሩ መዝሙር፣ ተጋበዙልኝ።
https://youtube.com/watch?v=Zlbt_aqUuVY&si=sP1_0Os2-w3Bwr3l
5 996
ትናንት በነበረን መጽሐፍ ምረቃ ያልተገኛችሁ ብዙ አምልጧችኋል😒 የዛሬው ደግሞ ይብሳል ቦሌ መድኃኔዓለም አሁን 8 ሰዓት ይጀመራል፣ እመኑኝ እንዲያመልጣችሁ አትፈልጉም😊
5 996
#ለመጽሐፍ_ምርቃቱ_ቀን_5_ቀናት_ብቻ_ቀሩት_ሐምሌ_4_2018_ከቀኑ_7፡00 ጀምሮ_በቅድስት_ሥላሴ_ዩኒቨርሲቲ_ሕንጻ_አራተኛ_ፎቅ_ላይ_ኹላችሁም_ተጋብዛችኋል። በዚያ ቀን ቀጠሮ ይዛችሁ እንድትገኙልኝ ስል በአክብሮት ጋበዝኋችሁ🙏
ለቅምሻ ያህል ከኦርቶዶክሳዊ ነገረ ሥላሴ፦
ቅዱስ አትናቴዎስ “የተለያዩ የአካል ክፍሎች ተሰብስበው ሙሉ አካልን እንደሚገነቡ፣ ሙሉ አካልም የተለያዩ ክፍሎች ውሑድ እንደ ኾነው፣ እያንዳንዱ ክፍልም የሙሉ አካሉ ክፍል ነው፡፡ ይህ ግን ስለ አምላክ ካለን ሐሳብ እጅጉን የራቀ ነው፡፡ እግዚአብሔር ምሉዕ ነው፤ የተለያዩ የአካል ክፍሎች ወይም ልዩ ልዩ የኾኑ ንጥረ ነገሮች ውሑድ አይደለም፤ ነገር ግን እርሱ ራሱ የዓለምን ሥርዓት የሠራ ነው፡፡ አምላክ የአካል ክፍሎች አለው ሲሉ ምን ዓይነት የማይረባ ነገር አምላክን ተቃርነው እንደሚናገሩ ተመልከቱ፡፡ እርሱ ከአካል ክፍሎች ከተገነባ፣ በእርግጠኝነት እርሱ ራሱን አይመስልም፣ ከማይመሳሰሉ የአካል ክፍሎችም የተገነባ ነው የሚለውን ሐሳብ ያስከትላል፡፡ እርሱ ፀሐይ ከኾነ ጨረቃ አይደለም፤ ጨረቃ ከኾነ ምድር አይደለም፤ ምድር ከኾነ ባሕር መኾን አይችልም፤ ወዘተ፡፡ … ዓይን የመስሚያ አካል አይደለም (ጆሮ)፣ የኋለኛው (የመስሚያ አካል) እጅ አይደለም፣ ሆድም ደረት አይደለም፣ እንደገና አንገትም እግር አይደለም፣ ነገር ግን እያንዳንዱ የራሱ ሥራ አለው፤ አንዱ ነጠላ ሰውነት ከእነዚህ ክፍሎች የተገነባ ነው፡፡ … ይህን ለአምላክ የሚሰጡ ከኾነ የሚከተሉትን ያመጣል፡- አንደኛ ከላይ እንዳየነው እርሱ ራሱን አይመስልም ያሰኛል፤ ኹለተኛ ተፈጥሮአዊ በኾነ ኹኔታ የአካል ክፍሎች እንደሚከፋፈሉት እርሱንም እንደገና እንዲከፋፈል እናደርገዋለን፡፡” ይላል፡፡ በመኾኑም እግዚአብሔር የአካል ክፍሎች አሉት ማለት ተገቢ አለመኾኑን ይህ ሊቅ ያትታል፡፡ እኛ ጋር ያሉ የአካል ክፍሎችን ለእግዚአብሔር ሰጥቶ መናገር ወይም ለእግዚአብሔር አካሉን ከፋፍሎ ዐይኑ የኾነ የአካል ክፍሉ ነው፣ ጆሮውም የኾነ የአካል ክፍሉ ነው፣ እጁም የኾነ የአካል ክፍሉ ነው … እያልን ልንከፋፍል አይገባም ነው ሊቁ የሚለን፡፡
ለቅምሻ ያህል ከዐይነ ልቡና መጽሐፌ፦
ቃል ሥጋ ሲኾን፣ ቃልነቱን ለቆ ሥጋ ወደ መኾን አልተለወጠም፤ ይህማ ቢኾን ፈጣሪ ፈጣሪነቱን ለቆ ፍጡር ኾነ ያሰኛል። እንዲህ ይኾናል ብሎ ማሰብ አእምሮ ካለው ከማንም የሚጠበቅ አይደለም። በመጽሐፍ "እኔ እግዚአብሔር አልለወጥም" ብሎ ራሱ ባለቤቱ እንደ ተናገረው በአምላክ ዘንድ ውላጤ ፈጽሞ የለም፤ ሊኖርም አይችልም። ፈጣሪን ፍጡር ወደ መኾን ይለወጣል ብሎ የሚያምን ሰው ፈጣሪ የለም ብሎ ከሚያምን ጋር ነው ቍጥሩ ሊኾን የሚችለው። በሌላ በኲል ሥጋም ቃልን ወደ መኾን መለወጥ አይችልም። ምንም እንኳን ለፍጥረት ለውጥ ቢስማማውም በምንም መንገድ ቢኾን ፍጡር በራሱ ፈጣሪ ወደ መኾን ሊለወጥ አይችልም። ፍጡር ፈጣሪ ወደ መኾን ይለወጣል ብሎ ማሰብም ፈጣሪም ፍጡር ወደ መኾን ይለወጣል ብሎ ከማሰብ በላይ ስሕተት ነው። ፍጡር ፈጣሪ ወደ መኾን መለወጥ ከቻለ ለፍጡር የተቻለ ለፈጣሪ አይቻልም ይባል ዘንድ ተገቢ ስላልኾነ ፈጣሪም ይለወጣል ብሎ በተዘዋዋሪ እንደ ማመን ነው። በእርግጥስ ፍጡር ፈጣሪ ወደ መኾን መለወጥ ከቻለ ቀድሞ ፈጣሪ የነበረው አዲስ ከሚመጣው "ፈጣሪ" ጋር እንዴት ሊኾን ኖሯል? ይህን ውዥንብርና የተምታታ አስተሳሰብ ከየልቡናችን ልናስወግድ ይገባል። ቃል ሥጋን በተዋሐደ ጊዜ ቃልነቱን ለቋል፤ ሥጋም ቃልን በተዋሐደ ጊዜ ሥጋነቱን ለቋል የሚል ቢኖር ፈጽሞ የተወገዘ ነው። ከላይ ያነሣነውን መሠረት አድርጎ መቃርስ እንዲህ ይላል፦ "ሰውም ቢኾን አምላክነቱን አልለቀቀም፤ አምላክነቱን ለቀቀ ማለት አይገባም፤ በተዋሕዶ አንድ በኾኑት (በመለኮትና በትስብእት) መለወጥ፣ ባሕርይን መልቀቅ የለም፤ በአለበት በተዋሕዶ ጸንቶ ይኖራል እንጂ።" እንዲል። ሃይ. አበ.ዘመቃርስ 98፥15።
Share በማድረግ ወደ ብዙኀን አድርሱልኝ🙏
