en
Feedback
ደቂቀ አትናቴዎስ

ደቂቀ አትናቴዎስ

Open in Telegram

"ግራ ሊያጋቡን ለሚጥሩት ምላሻችን ይህ ነው።" ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ

Show more
212
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
April '25
April '25
+180
in 0 channels
March '250
in 0 channels
Get PRO
February '25
+32
in 0 channels
Channel Posts
ኢየሱስ ክርስቶስ በብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ውስጥ የሌለን ቃል እንዳለ አርጎ ጠቅሷልን ?      ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ስብከቱ ሰማዕያኑ የሚያስተምረውን ትምህርት ይበልጥ ይገነዘቡት ዘንድ ፣ በጥያቄ ሊፈትኑት የሚፈልጉት አይሁድም መልሱ እንዲረ'ዳቸው ከብሉይ ኪዳን መጻሕፍት እየጠቀስ ያስተምር ነበር።      ሆኖም በክርስትና ላይ ስህተት በጌታ ቃል ውስጥም ግድፈት ለማግኘት የሚተጉ አምላክ የለሾችና ተንባላት ጌታችን ከብሉያት መጻሕፍት ጠቅሶ ያስተማረባቸውን የወንጌል ክፍላት በብዙ ሲተቹ እና ሲያብጠለጥሉ ማየት የተለመደ ነው። ስለሆነም በዚች አጭር መጣጥፍ አምላክ የለሾች እና ተንባላት ደጋግመው ከሚያነሱት መሰል ሙግት መሐከል ለአንዱ ምላሽ የምንጽፍ ይሆናል - መልካም ቆይታ !      ፍቁረ እግዚእ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ በወንጌሉ እንዳሰፈረው በአይሁድ የዳስ በዓል ኋለኛው ቀን ፈጣሬ ኩሉ ዓለማት ኢየሱስ ክርስቶስ "ቆሞ፦ ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ። በእኔ የሚያምን መጽሐፍ እንዳለ፥ የሕይወት ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል ብሎ ጮኸ።" (ዮሐ 7:37-38)      አስተውላችሁ ? ከላይ ባሰፈርነው የወንጌል ክፍል ላይ ኢየሱስ ክርስቶስ ከመጻሕፍት ብሉያት ጠቅሶ ተናግሯል ፤ ነገር ግን ጌታችን የጠቀሰው አንቀጽ በየትኛውም የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ላይ ቃል በቃል ተጽፎ አይገኝም። ይህን እውነት ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ የዮሐንስ ወንጌልን ባብራራበት ድርሳን ላይ " ... ነገር ግን መጽሐፍ የቱ ጋር ነው ' የሕይወት ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል ' የሚለው ? የቱም ጋር። ... " በማለት ገልጾታል። [1]       ታዲያ አምላክ የለሾችና ሙሐመዳውያን ይህን በመያዝ "ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐ 7:38 ላይ የትኛውን መጽሐፍ ነው የጠቀሰው ? በመጽሐፍ ላይ ቃል በቃል ያልሰፈረን ነገርስ እንዴት ' መጽሐፍ እንዳለ ' በማለት ይናገራል ?" የሚል ሙግት ያቀርባሉ ፤ ታዲያ የእኛስ መልስ ምንድን ነው ?      ለቀረበው ሙግት ምላሽ ከመስጠታች በፊት ሙግቱ በውስጡ ያነገበውን ስሁት እሳቤ አርመን እንለፍ ፤ ይኸውም የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትን እና የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስን ንግግር ዘመናዊ በሆነ አንድን ጥቅስ የመጥቀሻ መንገድ መመዘን ነው።      በዘመናችን አንድ ሰው የሌላን አካል ንግግር ወይንም ጽሐፍ መጥቀስ ከከጀለ ቃል በቃል ወስዶ ፣ በትምሕርተ ጥቅስ ከቦ እንደሚያሰፍር የአዳባባይ ሚስጢር ነው ፤ ሆኖም በዚህ ዓይነት የአጠቃቀስ መንገድ በአንደኛው ክፍለ ዘመን የተጻፋትን የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትንም ሆነ የጌታችን ንግግር ለመመዘን መሞከር አግባብ አይደለም ሥነ አመክንዮአዊ ሕጸጽም ነው - 'የአናክሮኒዝም ሕጸጽ (Fallacy Of Anachronism)' በመባል ይታወቃል።        የአናክሮኒዝም ሕጸጽ ማለት ቁሶችን ፣ ሰዎችን ፣ ክስተቶችን እና ቃላትን በተሳሳተ የታሪክ ጊዜ ውስጥ ማስቀመጥ ማለት ነው ፤ ይህም የታሪክ የጀርባ አጥንት የሆነውን ቅደም ተከተላዊነት የሚቃረን ነው [2]። ስለዚህ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሆነ የሐዲስ ኪዳን ጸሐፊዎች አሁን ላይ አንድን ጥቅስ በምንጠቅስበት መንገድ ሁል ጊዜ ቃል በቃል የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን እንዲጠቅሱ መጠበቅ ትክክል አይደለም።      አንዳንድ ጊዜ የሐዲስ ኪዳን ጸሐፊዎች መጻሕፍተ ብሉያትን ቃል በቃል አይጠቅሱም ፤ ይልቁን በአንድ ርዕሰ ዙሪያ  በመጻሕፍተ ብሉያት ውስጥ የሚገኘውን አጠቃላይ አስተምህሮ ለሐዲስ ኪዳን በሚሆን መልኩ በአንድ ዓ.ነገር ወይንም ሀረግ ይገልጹታል እንጂ። [3]      ይህ ዓይነቱ የመጥቀሻ መንገድ ከጥንታዊ የሥነ - ጽሑፍ ልምዶች ጋርም አብሮ የሚሄድ ሲሆን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ በተገለጠበት ዘመን እንዲሁም ከዚያ አስቀድሞ በነበሩ ጸሐፊዎች እና ተናጋሪዎች ዘንድ መጻሕፍት ውስጥ በረጅሙና በሰፊው የተበተኑ አንቀጾችን በአጭር ዓረፍተ ነገር ለመግለጽ ጥቅም ላይ ይውል ነበር። [4]        ለአብነትም አርስቶትል በ Nichomachean Ethics , Book 10 , Chapter 2 , Section 3 ላይ ከ ፕሌቶ ጠቅሶ የጻፈውን እንመልከት ፤ እንዲህ ሲል :-     «የደስታ ሕይወት ይላል ፕሌቶ ካለ ጥበብ ይልቅ ከጥበብ ጋር ይበልጥ አስደሳች ነው።»     Barthélemy Saint-Hilaire ከላይ በሰፈረው አንቀጽ ዙርያ በጻፈው ማስታወሻው ላይ ፕሌቶ ቃል በቃል እንደልተናገረው እንዲሁም አርስቶትል ቃል በቃል ከፕሌቶ እየጠቀሰ እንዳልሆነ ይልቁንም የፕሌቶን ጽንሰ ሃሳብ በአንድ ላይ ጨምቆ እየገለጸ እንደሆነ አመልክቷል ፤ ይህም ይህን መሰሉ የመጥቀሻ መንገድ የተለመደና ምንም ችግር የሌለበት እንደሆነ ያሳያል። [5]      በዚህም አቡ ቀለምሲስ “ይህን ግን በእርሱ የሚያምኑ ሊቀበሉት ስላላቸው ስለ መንፈስ ተናገረ፤ ኢየሱስ ገና ስላልከበረ መንፈስ ገና አልወረደም ነበርና።” (ዮሐ 7፥39) እንዳለ ፤ “በእኔ የሚያምን መጽሐፍ እንዳለ፥ የሕይወት ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል” የሚለው የጌታችን ቃል በብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ውስጥ በመንፈስ ቅዱስ መውረድ አማኞች ስለ ሚቀበሉት ጸጋ የሚናገሩ ጥቅሶችን ጠቅለል አድርጎ በአንድ ዓ.ነገር የሚገልጽ ነው ማለት ነው። (መዝ 51:6-7 ፣ ምሳ 4:23 ፣ 21:1፣ ኢሳ 58:11 ፣ 12:3 ፣ 44:3 ፣ ኤር 17:8 ፣ ሕዝ 36 :25-27 ፣ ዘካ 13:1)     በመጨረሻም ይህን መሰሉ የዮሐ 7:38 አረዳድ የቀደሙ የቤተ ክርስቲያን አባቶች  ይጠቀሙበት እንደነበረ ልብ እንዲባል አሳስባለሁ ፤ ለምሳሌ ያህል ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድሪያ የዮሐንስ ወንጌልን በተረጎመበት ድርሳኑ ዮሐ 7:38 ትን ሲያብራራ ያሰፈረውን መመልከት ይቻላል ፤ እንዲህ ሲል :-    «ከዚህ በተጨማሪ መድኃኔዓለም ይህን ቃል በራሱ ንግግር ላይ መጠቀሙን መገንዘብ መልካም ነው ፤ አስቀድሞ በመለኮታዊ መጻሕፍት ላይ በቀጥታ እንደሰፈረው አይደለም ይልቁንም በፍቺው መሰረት በመተርጎም ነው እንጂ። ምክንያቱም  እግዚአብሔርን የሚወድ እና የሚያከብር እንደሚጠጣ ገነት ውኃውም እንደማያቋርጥ ምንጭ እንደሚሆን አግኝተናልና።» [6]                   አሜን ጌታ ኢየሱስ ሆይ ና !           ✍ በዘአትናቴዎ የተጻፈ [https://t.me/ZeathanAmharic] 🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱 1).Homily on The Gospel Of John by St.John Chrysostom 2). Historians' Fallacies : Toward A Logic Of Historical Thought by David hackett 3). New Testament use of the old testament by Roger Nicole 4). The quotation of The new testament from old by Johnson Franklin , pp.103 5). Ibid 6). Commentary On The Gospel Of John By St.Cyril Of Alexandria , Chapter 10 , pp.545

2
ማርቆስ 2:26 ከ 1ሳሙ 21:1-9 ጋር ይጋጫልን ? (ክፍል 2)      ... ተመሳሳይ የሆነ የአጻጻፍ መንገድ በሌላ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ውስጥም የምናገኝ ሲሆን ለአብነትም ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ዕብራውያን በጻፈው መልዕክቱ ላይ ያሰፈረውን እንመልከት ፤   "የሳሌም ንጉሥና የልዑል እግዚአብሔር ካህን የሆነ ይህ መልከ ጼዴቅ አብርሃም ነገሥታትን ገድሎ ሲመለስ ከእርሱ ጋር ተገናኝቶ ባረከው ፤ ለእርሱም ደግሞ አብርሃም ከሁሉ አስራትን አካፈለው። የስሙም ትርጓሜ በመጀመሪያ የጽድቅ ንጉሥ ነው፥ ኋላም ደግሞ የሳሌም ንጉሥ ማለት የሰላም ንጉሥ ነው። " (ዕብ 7:1-2)    በዚህ መልእክቱ ሐዋርያው ዘፍጥረት ምዕራፍ 14 ላይ ያለውን ታሪክ አንስቶ  የጻፈ ሲሆን በዚያ ጊዜ ግን አብርሃም ይጠራ የነበረው "አብራም" ተብሎ እንጂ "አብርሃም" ተብሎ አልነበረም። ይህም ቅዱስ ጳውሎስ prolepsis ን ተጠቅሞ ስለ አባታችን አብርሃም እንዳጻፈ ያስገነዝባል።    ምናልባት ከላይ እንዳሰፈርነው ይጋጫሉ የተባሉት ጥቅሶች እንደማይጋጩና /ሎቱ ስብሐት/ጌታችንም እንዳልተሳሳተ ከተረዳን በኋላ ግን ጌታችን ጊዜውን ለማመልከት ሽቶ ከሆነ ስለምን አብያታርን መጥቀስ አስፈለገው? በዚያን ዘመን ሊቀ ካህን የነበረው አቢሜሌክን ማንሳቱ አይቀለምን ?  የሚል ጥያቄ አዕምሯችን ውስጥ ከመጣ እነዚህን ሁለት ምክንያቶችን ግምት ውስጥ ማስገባት ተገቢ ነው። 1፦ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የምናገኛቸው መጻሕፍት በተጻፉበት ዘመን እንዲህ እንዳሁኑ በምዕራፍና ቁጥር የተከፋፈሉ አልነበረም። በምዕራፍና ቁጥር የተከፋፈሉት ከጊዜ በኋላ ሲሆን ከዚያ አስቀድሞ ግን ወጥ የሆኑ ጽሑፎች ብቻ ነበሩ።[3]     በዚህም ከአንድ መጽሐፍ ጠቅሶ ማስተማር የወደደ ሰው ሁለት አማራጮች ነበሩት፦   - አንድም ጥቅሱን በቀጥታ መጥቀስ   - ወይንም ደግሞ ጥቅሱ የሚገኝበትን አካባቢ መጥቀስ      ለእነዚህ ሁለቱ አማራጮች ከራሱ ከጌታችን ትምህርት እንደ ምሳሌ እንጥቀስ፦      የመጀመሪያውን አጠቃቀስ ስንመለከት ፤ ፈሪሳውያን ወደ ጌታ ቀርበው “ሰው በሆነው ምክንያት ሁሉ ሚስቱን ሊፈታ ተፈቅዶለታልን?” ብለው በጠየቁት ጊዜ ጌታችን ዘፍ 2:24 ላይ ያለውን ጥቅስ ቀጥታ በመጥቀስ እንዲህ ሲል መለሰላቸው፦ “ፈጣሪ በመጀመሪያ ወንድና ሴት አደረጋቸው፥ ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል፥ ከሚስቱም ጋር ይተባበራል፥ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ፡ የሚለውን ቃል አላነበባችሁምን?" [ ማቴ 19 : 1-6]    ሁለተኛውን የመጽሐፍ ቅዱስ የአጠቃቀስ መንገድ ስንመለከት ደግሞ ትንሳኤ ሙታን የለም የሚሉ ሰዱቃውያን ወደ ጌታችን ቀርበው "ሰባት ባሎችን ያገባች ሴት በትንሳኤ ቀን ለማንኛቸው ትሆናለች?" ብለው በጠየቁት ጊዜ ጌታችን ከመጽሐፍ ጠቅሶ የመለሰላቸውን እናገኛለን ፤     ክርስቶስ ለሰዱቃውያኑ ጥያቄ ሲመልስ ያደረገው ነገር ሊያነሳው ካሰበው ሀሳብ አካባቢ የሚገኝ ለሰሚዎቹ በጣም ቅርብ የሆነ ሀሳብን እንደ መሪ መጠቀም ነው። ለዚህም ነው እንዲህ በማለት የመለሰላቸው ፤ "ስለ ሙታን ግን እንዲነሡ እግዚአብሔር፦ ‘እኔ የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ፡’ እንዳለው በሙሴ መጽሐፍ በቍጥቋጦው ዘንድ የተጻፈውን አላነበባችሁምን? ”      ከክርስቶስ መልስ ማስተዋል እንደምንችለው ጌታችን ‘እኔ የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ፡’ የሚለውን ሀሳብ ለማሳየት እንደ መሪ ማጣቀሻ የጠቀሰው የቁጥቋጦውን ታሪክ ነው። የቁጥቋጦው ታሪክ በሁሉም የታወቀ ስለሆነ የት ነው ‘እኔ የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ፡’ ያለው? የሚል ጥያቄ የሚያነሳ ሰው የቁጥቋጦው ታሪክ የሚገኝበትን ክፍል ሂዶ ሲያነብ ይህንን ጥቅስ ያገኘዋል ማለት ነው።      ጌታችን በማር 2:26 የተጠቀመው ሁለተኛውን የማጣቀሻ መንገድ ሲሆን በ 1ኛ ሳሙኤል ምዕራፍ 21 ላይ እንደሰፈረው ለዳዊት የመስዋዕቱን እንጀራ የሰጠው ሊቀ ካህኑ አቢሜሌክ በሁለቱ የሳሙኤል መጽሐፍት ለመጀመሪያ ጊዜ ስሙ የተጠቀሰው በዚሁ ምዕራፍ ሲሆን የአገልግሎቱ መጨረሻ የተነገረው ደግሞ ቀጥሎ ባለው ምዕራፍ 22 ላይ ነው።     በተቃራኒው ሊቀ ካህኑ አብያታር ከምዕራፍ 22 ጀምሮ በነብዩ ዳዊት ህይወት ሙሉ የምናገኘው ሲሆን ከአቢሜሌክ ይልቅ አብያታር በሰዎች ዘንድ ይበልጥ ታዋቂ ነው። ስለሆነም ጌታችን ይህንን ክስተት ለማስረዳት ኲነቱ በተፈጸመ ጊዜ አብያታር ሊቀ ካህን ያልነበረ ቢሆንም ነገር ግን ታሪኩን በቀላሉ ለማግኘት እንዲያግዝ ስለ አብያታር የሚያወሳውን ክፍል በመጥቀስ ጌታችን ለፈሪሳውያኑ ምላሹን ሰጣቸው ማለት ነው። 2፦ ጊዜውን ለማሳየት ከሆነ ስለምን አብያታርን መጥቀስ አስፈለገው? ለሚለው ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ ፈሪሳውያን በማር 2:24 “እነሆ፥ በሰንበት ያልተፈቀደውን ስለ ምን ያደርጋሉ?" በማለት የጠየቁት በግብዝነት ለህጉ እኛ ቀናኢ ነን ለማለት ሲሆን ይሄ ከእኛ በላይ ቀናኢ የለም የሚለውን ትምክህታቸውን ከእነሱ በላይ ቀናኢ በሆነው በአብያታር ዘመን በህግ ያልተፈቀደው ተከውኗል ነገር ግን አብያታር እንደናንተ አልከሰሰም የሚለውን ለማሳየት አብያታርን ጠቅሷል ማለት ነው። [4]              አሜን ጌታ ኢየሱስ ሆይ ና !                 ✍ በ'አናሲሞስ ተጻፈ [https://t.me/ZeathanAmharic] 🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱 3). Norman L. Geisler and William E. Nix ; A General Introduction to the Bible ; 234 - 236 4). Maurice Casey ; Aramaic source of Mark goslel ; 151
98
3
በዚህም በማር 2:26 ላይ የሰፈረው የጌታችን ቃል የአብያታርን ሊቀ ካህንነት ወደ ኋላ አምጥቶ ሊቀ ካህን ባልነበረት ጊዜም ጭምር በማዕረጉ ጠርቶ እየገለጸው እንጂ ንጉሥ ዳዊት ከካህናት በቀር ማንም ይበላው ዘንድ ያልተፈቀደን የመሥዋዕት እንጀራ በበላ ጊዜ አብያታር ሊቀ ካህናት ነበር እያለ አይደለም።       ይህም ከላይ ካስቀመጥነው ምሳሌ አንጻር ስህተት የሌለበት የአነጋገር መንገድ እንደሆነ ግልጽ ነው - «Prolepsis» በመባልም ይታወቃል።    «Prolepsis» የአጻጻፍ እንዲሁም የአነጋገር መንገድ ሲሆን አንድ ድርጊት ባልተጸፈመበት ዘመን እንደተፈጸመ ቆጥሮ መናገርን የሚያመለክት ነው ፤ ይኸውም አንድን ስም ወይም ማዕረግ አንድ አካል በዚያ ስም ወይም ማዕረግ ባልተጠራበት ጊዜ ጭምር ዓውሎ መጠቀምን የሚያካትት ነው። ይቀጥላል ....              አሜን ጌታ ኢየሱስ ሆይ ና !                 ✍ በ'አናሲሞስ ተጻፈ [https://t.me/ZeathanAmharic] 🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱 1). ምኒሊክ አባታቸው ሲሞቱ ከ11 ዓመት ያልበለጡ ልጅ ነበሩ የሚለው ከዚሁ ከጳውሎስ ኞኞ መጽሐፍ ተነስተን የምንደርስበት ድምዳሜ ሲሆን ይኸውም እንደሚከተለው ነው፦               ምኒሊክ አባታቸው ከሞቱ በኋላ በአጼ ቴዎድሮስ የቁም እስረኛ ሆነው 10 ዓመት ቆይተዋል (ገጽ 16) በኋላም እስረኛ ሆነው ከቆዩበት ከመቅደላ ሲያመልጡ 21 ዓመታቸው ነበረ (ገጽ 19)። እነዚህን ቁጥሮች ስናቀናንስ ምኒሊክ አባታቸው ሲሞቱ 11 ዓመታቸው የነበረ መሆኑን እንረዳለን። 2). Daniel B.Wallace ; Mark 2:26 and the Problem of Abiathar
76
4
ማርቆስ 2:26 ከ 1 ሳሙ 21:1-9 ጋር ይጋጫልን ? (ክፍል 1)     ለስም አጠራሩ ክብር ምሥጋና ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሰንበት ከሐዋርያቱ ጋር በእርሻ መካከል ሲያልፍ ሐዋርያቱ ከእሸቱ ይቀጥፋ ጀመር ፤ ይህን የተመለከቱት ፈሪሳውያንም “እነሆ፥ በሰንበት ያልተፈቀደውን ስለ ምን ያደርጋሉ?” በማለት ወቀሳ ያዘለ ጥያቄ ለጌታችን አቀረቡ። ለፈሪሳውያኑ ወቀሳ ያዘለ ጥያቄም ጌታችን ልበ አምላክ ዳዊት ያደረገው በማውሳት እንዲህ ሲል ምላሽ ሰጠ ፤     “ዳዊት ባስፈለገውና በተራበ ጊዜ፥ እርሱ አብረውት ከነበሩት ጋር ያደረገውን፥ አብያተር ሊቀ ካህናት በነበረ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ቤት እንደ ገባ፥ ከካህናት በቀር መብላት ያልተፈቀደውን የመሥዋዕትን እንጀራ እንደ በላ፥ ከእርሱም ጋር ለነበሩት እንደ ሰጣቸው ከቶ አላነበባችሁምን?” (ማር 2:25-26)     ታዲያ ይህ በማር 2:23-28 ላይ ሰፍሮ የሚገኘው የክርስቶስ ምላሽ 1ኛ ሳሙ 21:1-9 ላይ ካለው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ጋር ይጋጫል የሚል ጠንከር ያለ ሙግት የሚሰነዝሩ ሰዎች አሉ ፤ ግን እንዴት ? ነገሩ እንዲህ ነው !     በማር 2:25 ላይ ልበ አምላክ ዳዊት ከካህናት በቀር ማንም ሊበላ የማይቻለውን የመሥዋዕት እንጀራ የተመገበበትን ዘመን ለማመልከት ”አብያታር ሊቀ ካህናት በነበረ ጊዜ” በማለት ኢየሱስ ክርስቶስ ዳዊት ለካህናት ብቻ የተፈቀደውን እንጀራ የበላበትን ጊዜ አመልክቷል።      ሆኖም ወደ ኋላ መለስ ብለን ዋናው ክስተት ሙሉ በሙሉ የሰፈረበትን 1ሳሙ 21:1-9 ስናነብ ሊቀ ካህን የነበረው አብያታር ሳይሆን የአብያታር አባት አቢሜሌክ እንደሆነ እንገነዘባለን ፤ ከዚህ በመነሳት በመጽሐፍ ቅዱስ ግጭት አልባ መሆን የማያምኑ ሰዎች የሚጠይቁት ጥያቄ ”ዳዊት ከካህናት በቀር ማንም ይበላ ዘንድ ያልተፈቀደውን እንጀራ ሲበላ ሊቀ ካህናት የነበረው ማን ነው ? አብያታር ወይንስ አቢሜሌክ ? ” የሚል ነው።    ከላይ ለሰፈረው ጥያቄ መልስ ከመጻፋችን በፊት እንደ መነሻ ይሆነን ዘንድ አንድ ጥያቄ ጠይቀን ምላሹንም ጠቁመን እንጀምር ፤ አንድ አንባቢ የጳውሎስ ኞኞ'ን "አጤ ምኒሊክ " የተሰኘ መጽሐፍ ካነበበ በኋላ በማስታወሻ ደብተሩ ላይ የሚከተለውን አሰፈረ እንበል ፤ እንዲህ ሲል :-   "ንጉሥ ምኒሊክ አባቻቸው ኃይለ መለኮትን በህመም ምክንያት በሞት የተለዩት ገና በልጅነታቸው ዓርብ ጥቅምት 30 ቀን 1848 ዓ.ም ነው።"    ሆኖም ለሌሎች ይህ የአንባቢው ማስታወሻ ከታሪክ መጽሐፍቶች ጋር ይልቁንም ከጳውሎስ ኞኞ መጽሐፍ ጋር የሚጋጭ ሊመስል ይችላል ፤ ምክንያቱም የጳውሎስ ኞኞ'ን መጽሐፍ ያነበበ ሰው ምኒሊክ አባታቸው ሲሞቱ ከ11 ዓመት ያልዘለሉ ልጅ እንጂ ንጉስ እንዳልነበሩ ይረዳልና።[1]    ታዲያ እናንተ ምን ታስባላችሁ ? ምንስ ይመስላችኋል ? የአንባቢው ማስታወሻ ጳውሎስ ኞኞ ከጻፈው ጋር ይጋጫልን ? በፍጹም ! በእርግጥ አባታቸው ባረፋ ጊዜ አፄ ምኒሊክ ንጉስ አልነበሩም ይህ ማለት ግን  አንባቢው የከተበው ማስታወሻ ስህተት ነው  ማለት አይደለም ፤ ምክንያቱም አንባቢው በማስታወሻው አፄ ምኒሊክ አባታቸው በሞቱ ጊዜ መኖራቸውን አመለከተ እንጂ በዚያን ጊዜ ንጉስ መሆናቸውን የሚያንጸባርቅ ሃሳብ አላሰፈረምና።     ከላይ ይጋጫሉ ተብለው የቀረቡት ጥቅሶችም ከዚህ የሚለዩ አይደሉም። 1ኛ ሳሙኤል ምዕራፍ 21ን ከቁጥር አንድ ጀምረን እስከ ምዕራፍ 22  ድረስ ስናነብ ዳዊት ወደ ሊቀ ካህኑ አቢሜሌክ ወደ ኖብ እንደሄደ በዛም ለካህናት ብቻ የተፈቀደውን የመስዋዕት እንጀራና የጎልያድን ሰይፍ ከአቢሜሌክ እንደተቀበለ ፥ አቢሜሌክም እኒህን ለዳዊት ሲሰጥ በአካባቢው ኤዶማዊው ዶይቅ እንደነበረና እንዳዬ ፤ ይህን ያየውን ነገርም ለሳኦል እንደተናገረ ፤ ሳኦልም በኖብ ከተማ ያሉትን ካህናት በሙሉ እንዲገደሉ እንዳደረገ እና ይህ ሁሉ ሲኾን አቢያታርም በዚያው እንደነበረና እንደ እድል አምልጦ ወደ ዳዊት እንደሸሸ እናነባለን።      በዚህም አስቀድመን እንዳልነው ይህ ሁሉ ሲኾን አብያታር በዚያ ነበረ ፤ ደግሞም ይኸው አብያታር ከአባቱ መሞት በኋላ በንጉሥ ዳዊት የንግሥና ዘመን ሊቀ ካህን ሁኖ አገልግሏልና ይህንን ይዞ ድርጊቱ በተፈጸመበት ጊዜ በህይወትና በቦታው መኖሩን ለመግለጽ ሲል ጌታችን "...አብያተር ሊቀ ካህናት በነበረ ጊዜ ..." በማለት ተናገረ ማለት ነው።   "አብያታር ሊቀ ካህናት በነበረ ጊዜ" የሚለው ሀረግ ጥንት በተጻፈበት በግሪኩ ቋንቋ "ἐπὶ Ἀβιαθὰρ ἀρχιερέως" የሚል ሲሆን አወቃቀሩም ἐπί + genitive noun ነው። በተመሳሳይ አወቃቀር የተቀመጡ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎችን ስንመለከት ጊዜን ለማመልከት የዋሉ እንደሆኑ እንረዳለን። ለአብነትም የሚከተሉትን ጥቅሶች እንመልከት :-    “#በነቢዩ _በኤልሳዕ_ ዘመንም [ ἐπὶ Ἐλισαίου τοῦ προφήτου ... ] በእስራኤል ብዙ ለምጻሞች ነበሩ፥ ከሶርያዊው ከንዕማን በቀር ከእነርሱ አንድ ስንኳ አልነጻም።" (ሉቃስ 4፥27)    “ከእነርሱም አጋቦስ የሚሉት አንድ ሰው ተነሥቶ በዓለም ሁሉ ታላቅ ራብ ሊሆን እንዳለው በመንፈስ አመለከተ፤ ይህም #በቀላውዴዎስ_ቄሣር_ዘመን ሆነ [ ... ἥτις ἐγένετο ἐπὶ Κλαυδίου] ።” (ሐዋ 11፥28)     የእነዚህ ሁለት ጥቅሶች የግሪክ አወቃቀር ከ ማር 2:26 ጋር ተመሳሳይ ሲሆን የመጣው የኤልያስን ነብይነት ወይንም የቀላውዴዎስን ቄሳርነት ለማሳየት ሳይሆን ዘመኑን ለማመልከት ነው ። በተመሳሳይ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "አብያታር ሊቀ ካህናት በነበረ ጊዜ" ሲል የአብያታርን ሊቀ-ካህንነት ሳይሆን እርሱ በነበረበት ዘመን የተፈጠረውን ክስተት የሚያሳይ ነው።      ለዚህም ነው በዘመናችን የሚገኙ አንዳንድ የሐዲስ ኪዳን ሊቃውንት ማር 2:26 ላይ ያለው ሀረግ መተርጎም ያለበት "በሊቀ-ካህናቱ በአብያታር ዘመን" ተብሎ ነው የሚሉት።[2]  በዚህም መንገድ ተርጉመው ያስቀመጡ በርካታ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች ሲኖሩ  የተወሰኑትን ለመጥቀስ ያክል ፦   "በሊቀ ካህናቱ በአብያታር ዘመን ወደ እግዚአብሔር ቤት ገብቶ ፣ ካህናት ብቻ እንዲበሉት የተፈቀደውን የተቀደሰ ህብስት ራሱ በልቶ አብረውት ለነበሩትም ሰዎች ሰጣቸው።" (አ.መ.ት)    "In the days of Abiathar the high priest, he entered the house of God and ate the consecrated bread, which is lawful only for priests to eat. And he also gave some to his companions " (NIV)    "how he entered the house of God, in the time of Abiathar the high priest, and ate the bread of the Presence, which it is not lawful for any but the priests to eat, and also gave it to those who were with him?” (ESV)     "how he entered the house of God in the time of Abiathar the high priest, and ate the consecrated bread, which is not lawful for anyone to eat except the priests, and he also gave it to those who were with him?" ( NASB)
77
5
🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱 [1] ዘምዘም (زمزم‌‎) በመካ ሳኡዲ አረቢያ መስጂድ አል-ሐራም ውስጥ የሚገኝ የውኃ ጉድጓድ ሲሆን በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ የአብርሃም ልጅ እስማኤል ከእናቱ አጋር ጋር በበረሃ ሳለ በተአምር የፈለቀ ነው ተብሎ ይታመናል።
173
6
የቀድሞው አብዱ አደም የአሁኑ ዘማሪ ተስፋ ሚካኤል (ክፍል 1)     « ... እኔ ክርስቲያን ለመሆን ያላሰብኩኝ ሰው ነኝ ፤ በጣም የምሰግድ ፣ ቁርአን የምቀራ ፣ ቤተሰቦቼ በሙሉ ሙስሊም የሆኑ ሰው ... ነገር ግን ኃይሌን መታኝ በማያደማ መዶሻ ... የእግዚአብሔር ቃል መዶሻ ነው አያደማም ፣ የእግዚአብሔር ቃል ሰይፍ ነው ሲቆርጥህ አይታይም። ክፉውን ነገር ከአንተ ቆርጦ ሲጥል አይታይም ግን ሰይፍ ነው። እና ያ ቃል ነው እኔ ቀጥቅጦኝ እንደዚህ ያደረገኝ ፣ እኔን የመለሰኝ ... »   ዘማሪ ተስፋ ሚካኤል      ከዚህ በታች የምንጽፈው ቃለ ምልልስ እግዚአብሔር አምላክ ከእስልምና በድንቅ አጠራሩ ጠርቶ ወደ ክርስትና ከመጣው ከዘማሪ ተስፋ ሚካኤል [አብዱ አደም] ጋር የተደረገ ቆይታ ሲሆን ከአንድ ዓመት በፊት በንቁ ቲዩብ ላይ በድምጽ ተቀድቶ ከተለቀቀው ቃለ ምልልስ ለጽሐፍ በሚሆን መልኩ ተስተካክሎ የተወሰደ ነው።                                  መልካም ንባብ ! ጠያቂ :- ጥሪያችንን አክብረህ ስለመጣህ በጣም እናመሰግናለን ፤ በመጀመሪያ ተስፋ ሚካኤል ማን ነው ? የት ተወለደ ? የት አደገ ? የሚለውን አክለህ ራስህን ብታስተዋውቀን ። ዘማሪ ተስፋ ሚካኤል :- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! እናንተም የእኔ ታሪክ የሚጠቅመው ሰው አለ ብላችሁ ስለጋበዛችሁኝ አመሰግናለሁ - እግዚአብሔር ያክብርልኝ።      ስሜ ተስፋ ሚካኤል ይባላል ፣ የትውልድ ስፍራዬ ቤጊ ኮቦር የሚባል ሲሆን እስከ ሰባት ዓመቴ ድረስ የኖርኩት እዚያ ነው። ሰባት ዓመት ሲሞላኝ ከቤተሰቦቼ ጋር ወደ ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል አሶሳ ሄጄ በዚያ አብዛኛውን የልጅነት ጊዜዬን አሳልፌያለሁ።        እንዲሁም ቤተሰቦቼ በሙሉ ሙስሊም ስለ ነበሩ ያደኩት የእነርሱን መንገድ በመያዝ እስልምናን እየተከተልኩ ነው። ጠያቂ :-  በእስልምና ውስጥ በነበርክበት ጊዜ ምን ያህል በእምነቱ ገፍተህ ሄደሃል? ቁርአንስ ቀርተህ ነበር ? ዘማሪ ተስፋ ሚካኤል :- አስቀድሜ እንደ ገለጽኩት ቤተሰቦቼ ሙስሊሞች በመሆናቸው እኔም በእስልምና ውስጥ ነው ታንጼ ያደኩት ።       ነገር ግን እድሜዬ ለትምህርት ሲደርስ ቀጥታ ወደ ትምህርት ቤት አልተወሰድኩም ፣ ምክንያቱም የምንኖረው ገጠር ውስጥ ነበርና ቤተሰቦቼን በእረኝነት እንዲሁም በመላላክ አግዝ ስለ ነበረ ማለት ነው ፤ ታዲያ በዚያ ሰዓት በምንኖርበት አካበቢ ወዳሉ ደረሣ ቤቶች እየሄድኩ ቁርአን እቀራ ነበር።       ሆኖም የቤተሰቦቼ ኑሮ ዝቅተኛ ስለነበር በመሐል እያቋረጥኩ እየተማርኩ እያቋረጥኩ እየተማርኩ የተወሰነ ጊዜ ቆየሁ ፤ በኋላ ላይ ግን የምንኖረው ገጠር ውስጥ ስለ ነበረ ደግሞም እንደሚታወቀው የገጠር ኑሮ ምቹ ስላልሆነ ያዘነበልኩት ወደ እረኝነቱ ነበርና ቤተሰቦችን በሥራ ለማገዝ ስል ሙሉ በሙሉ አቋርጫለሁ።      ያኔ አብዱ ይባል ነበር ስሜ ... ጠያቄ :- አሃ ... ተስፋ ሚካኤል አልነበረም ? ዘማሪ ተስፋ ሚካኤል :- አዎ ተስፋ ሚካኤል የተባልኩት ከተጠመኩ በኋላ ነው ፤ ሳልጠመቅ በፊት አብዱ አደም እባል ነበር። ጠያቄ :- ታዲያ ተስፋ ሚካኤል እንዴት ከእስልምና ጥርጥር ወደ ሌለባት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ሊመጣ ቻለ ? ዘማሪ ተስፋ ሚካኤል :- የመጣሁት የእግዚአብሔር ቸርነት ሆኖልኝ ነው።      ሙስሊም በነበርኩበት ጊዜ የቤተሰቦቼን ፍኖት ተከትዬ ስለሄድኩኝ እኔም እንደ እነርሱ ክርስቲያኖችን እጠላ ነበር ፣ በእረኝነት ስፍራ እንኳ ከክርስቲያን ልጆች ጋር አልውልም ነበር። በእኛ አካባቢ በብዛት ባይኖርም አልፎ አልፎ ቀሳውስትን ስናገኝ ቤተ ክርስቲያን ስናይ በጣም ነበር የምንጠላቸው ... አሁን ላይ ሳስበው ግን እግዚአብሔር እኛ በጠላነው ልክ የእርሱ ፍቅር ይጨምራል ።       ያኔ ለክርስቲያኖች በጣም ጥላቻ ነበረኝ ክርስቲያን የሚለው ስም ሲጠራ ራሱ በጣም ነበር የሚከብደኝ ... እግዚአብሔር ግን ከዚያ አረንቋ ከድቅድቁ ጨላማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን ሊያመጣኝ ሲፈልግ መንገድ አለውና የእኔን ጥላቼ እርሱ በፍቅር እየለወጠ በፍቅር ይስበኝ ነበር። በአንድ ወቅት ታመምኩኝ ፣ በየዓመቱ ያመኝ ነበርና ፤ በዚያ ሰዓት አንድ ባሕታዊ  ከጋራ አባ ሞቲ ቀጥሎ ካለው ተራራ ሥር ጸበል አፈለቀ ሲባል ሰማን። ባሕታዊ መሆኑን ያወኩት አሁን ነው ፣ ብቻ ጸጉሩ ረጅም የሆነ ሰው ከተራራ ሥር ዘምዘም አፍልቋል ሲባል ነው የሰማነው።[1]      ቤተሰቦቼ ይህን በሀገራችን ያወጣልን አላህ ይመስገን እያሉ እዚያ ወሰዱኝ ፤ እኔም ሰባት ቀን እንደተጠመኩኝ ተፈወሰኩኝ ።         የሚያሰደንቀው ነገር ግን በዚያ ሙስሊሞችም ክርስቲያኖችም ሲጠመቁ ይፈወሱ ነበር ፤ በመሐል ግን ግጭት ተፈጠረ ክርስቲያኖችም የእኛ ነው ሙስሊሞችም የእኛ ነው ይሉ ነበርና ፣ በዚህም ምክንያት ጸበሉ ደረቀ።       ለእኔ ግን የፈውስ ምክንያት ሆኖኝ  እግዚአብሔር በዚህ ሰዓት ለክርስትናዬ መነሻ የሚሆን አንድ ነገር በውስጤ እንዳኖረ አምናለሁ። እንዲሁም ከመጠመቄ በፊት በምታመምበት ሰዓት በእረኝነት ስፍራ ላይ ሳለሁ የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ድምጽ በቅርብ ይሰማ ነበር ፣ በተለይ በዐብይ ጾም የቅዳሴው ዜማ  ልቤን በጣም ያራራ ነበር ፣ ምንድን ነው ይህ ድምጽ ? እያልኩም አስብ ነበር ፣ የቅዳሴውን ድምጽ ስሰማም ዕንባ ዝም ብሎ በጉንጮቼ ይፈስ ነበር - በዚህም በኩል እግዚአብሔር አንድ ነገር በልቤ ውስጥ ያኖረ ይመስለኛል። ጠያቄ :- እሺ ወንድሜ ከባሕታዊ ዘንድ ሄደህ በጸበል እንደተፈወሰክ ነገረኸናል። ከዚያስ ምን ተፈጠረ ? እንዴትስ ወደ ክርስትና ልትመጣ ቻልክ ? ዘማሪ ተስፋ ሚካኤል :- ባሕታዊው እዚያ ቆሞ የሚያጠምቅ አልነበረም ፤ ጸበሉን በራዕይ አይቶ በመምጣት መንገዱ እንዲመነጠር አደረገ እንጂ። ከዚያ በኋላ ሙስሊሙም ክርስትያኑም እየተጠመቀ ይድን ነበር ፤ ነገር ግን እዚያው ቆሞ ሚያጠምቅ ካህን አልነበረም።      ጸበሉ የሚወርደው ከተራራ ላይ ነበር ፤ ቁልቁል ወርዶ ሰውነታችን ላይ ሲያርፍ አንዳች ነገር ይሰማናል። ጸበሉን ተጠምቀን ራሱ ወደ ሌላ ቦታ አይሄድም እዚያው ጋር ተሽከርክሮ የሆነ ጉርጓድ ውስጥ ይገባል -  ለዓይን በጣም ተአምር የሆነ ነገር ነበር።       እኔም ተጠምቄ ከተፈወስኩ በኋላ ራሱ የቀጠልኩት በእስልምና ውስጥ ነው - ሙስሊም ነኝ ብዬ ስለማስብ ማለት ነው ።       በዚህ ሁኔታ ውስጥም ወደ ሦስት ዓመት ገደማ ያህል ቆየሁ። አብሬም የመዳኔን ነገር ረሳሁ እግዚአብሔር ግን በህልም ብዙ ነገሮችን ይነግረኝ ጀመር ፤ ሁልጊዜ ተኝቼ ድምጽ ይሰማኛል ፣ ከአንድም ሦስት ጊዜ ህልም አየሁ።      እኔ ነብይ ወይንም ጻዲቅ ሆኜ አይደለም ፤ እግዚአብሔር ጻዲቅ ለሆነ ሰው ብቻ ሳይሆን ለጥፋተኛውም ከጥፋቱ ይመለስ ዘንድ ራዕይ ሊያሳየው ይችላልና - ለእኔም ህልም ያሳየኝ ከጥፋቴ እንድመለስ ነው ብዬ አስባለሁ። ጠያቄ :- ያየኸው ህልም ምን ነበር ? ይቀጥላል ....                 አሜን ጌታ ኢየሱስ ሆይ ና !         ✍ በዘአትናቴዎ ወደ ጽሑፍ የተቀየረ [https://t.me/ZeathanAmharic]
158
7
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምስክርነት እውነት ነው ወይስ አይደለም ? (ክፍል 2)     ...ሁለተኛው ብዙ ሰዎች መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ግጭት አለ ሲሉ ግምት ውስጥ የማያስገቡት ነገር ቃላት ወይንም ዓ.ነገሮች በተለያየ ሁኔታ ውስጥ የተለያየ ትርጉም ሊኖራቸው እንደሚችል ነው ፤ ማለትም አንድ ነገር በተለያየ ሁኔታ ውስጥ እውነትም ውሸትም ሊሆን እንደሚችል አለ መረዳታቸው ነው።       ለምሳሌ ቅዱስ ጳውሎስ በሮሜ 8:8 ላይ "በሥጋ ያሉት እግዚአብሔርን ደስ ሊያሰኙት እንደማይችሉ ..." በማለት የተናገረ ሲሆን በገላ 2:20 ላይ ደግሞ እርሱ አሁን በሥጋ የሚኖረው ኑሮ በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለው እምነት የሚኖረው ኑሮ እንደሆነ ገልጿል። ሆኖም እዚህ ጋር አንድ ሰው ቃላት በተለያየ አውድ ውስጥ የሚኖራቸውን የትርጉም ልዩነት ካልተረዳ ሁለቱ ጥቅሶች ሚጋጩ ሊመስለው ይችላል።      ሆኖም ጥቅሶቹን በአውዳቸው ስናነብ በገላ 2:20 ላይ ቅዱስ ጳውሎስ "በሥጋ" ሲል በምድር ላይ በህይወት እያለ ፣ ነፍሱ ከሥጋው ሳትለይ በህይወት እየኖረ መሆኑን ለማመልከት ሲሆን በሮሜ 8:8 ላይ ግን "በሥጋ" ሚለው በአዉዱ ከእግዚአብሔር ተልይቶ በራስ ፍቃድ የሚኖር የኃጢአት ህይወትን የሚያመለክት ነው።       በዚህም የቅዱስ ጳውሎስ ቃል እርስ በርሱ የሚጋጭ ሆኖ ሳይሆን "በሥጋ" የሚለውን ሀረግ በሁለት ዓ.ነገር ውስጥ በተለያየ መንገድ ተጠቅሞ ነው።        በተመሳሳይ ጌታችን መድኋኒታች ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐ 5:31 ላይ "እኔ ስለራሴ ብመሰክር ምስክሬ እውነት አይደለም" ሲል ከአይሁድ አንጻር ፣ በዘመኑም ከነበረው ሥርዓት አኳያ የተናገረ ሲሆን በዮሐ 8:14 ላይ ግን "እኔ ስለራሴ ብመሰክር ከወዴትም እንደመጣሁ አውቃለሁና ምስክርነት እውነት" ብሎ ሲናገር እንደ አምላክነቱ ፣ ከማንነቱ አንጻር ነው። ግን እንዴት?       በአይሁድ ሕግ ስለ አንድ ነገር እውነትነት ለማረጋገጥ የአንድ አካል ምስክርነት ብቻ በቂ አይደለም ፤ ሁለት ወይንም ሦስት ምስክሮች ሊኖሩ ግድ ይላል (ዘዳ 19:15)።      በዚህም በዮሐ 5:31 ላይ ጌታችን "እኔ ስለራሴ ብመሰክር ምስክሬ እውነት አይደለም" ብሎ ሲናገር "በእናንተው ሕግ መሰረት ስለእኔ ማንነት ምስክር እኔ ብቻ ብሆን ኖሮ ምስክርነቴ እውነት ባልሆነ ነበር ፣ ነገር ግን ስለ እኔ መጥምቁ ዮሐንስ ፣ እግዚአብሔር አብ እና መጻሕፍት መስክረዋልና ልትቀበሉኝ ይገባል" ማለቱ ነው ፤ ለዚም ነው "እኔ ስለራሴ ብመሰክር ምስክሬ እውነት አይደለም" ካለ በኋላ እንዲህ ብሎ መናገሩ :-               "እኔ ስለ እኔ ስለ ራሴ ብመሰክር ምስክሬ እውነት አይደለም፤ስለ እኔ የሚመሰክር ሌላ ነው፥ እርሱም ስለ እኔ የሚመሰክረው ምስክር እውነት እንደ ሆነ አውቃለሁ።...እናንተ ወደ ዮሐንስ ልካችኋል እርሱም ለእውነት መስክሮአል። ...እኔ ግን ከዮሐንስ ምስክር የሚበልጥ ምስክር አለኝ፤ አብ ልፈጽመው የሰጠኝ ሥራ፥ ይህ የማደርገው ሥራ፥ አብ እንደ ላከኝ ስለ እኔ ይመሰክራልና።...እናንተ በመጻሕፍት የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ይመስላችኋልና እነርሱን ትመረምራላችሁ፤ እነርሱም ስለ እኔ የሚመሰክሩ ናቸው፤" (ዮሐ 5:19 -33, 36-39)         በተቃራኒው በዮሐ 8:14 ላይ "እኔ ስለራሴ ብመሰክር ከወዴትም እንደመጣሁ ወዴትም እንድሄድ አውቃለሁና ምስክርነት እውነት ነው" ብሎ ሲናገር ፣ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "አንተ ስለ ራስህ ትመሰክራለህ ፣ ምስክርነት እውነት አይደለም "( ዮሐ 8:13) ብለው ለወቀሱት አይሁዶች ፣ ከየት እንደመጣ ፣ ወዴትም እንደሚሄድ ያውቃልና የርሱ ምስክርነት እውነት እንደሆነ እየገለጸላቸው ነው።     ማለትም አምላክ ስለ አንድ ነገር ቢናገር ፣ በአይሁዳዊያን ዘንድ ንግግሩን እንደ እውነት ለመቀበል ምስክር አያስፈልጋቸውም ፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር ምስክር አያስፈልገውምና። በተመሳሳይ ክርስቶስ ከሰማይ ወርዶ ስለእኛ ሲል ሥጋን የተዋሐደ ፣ ደግሞም ሞትን ድል አርጎ ወደ ሰማይ የወጣ አምላክ ነው ና ምስክሩ እውነት እንደሆነ እንዲሁም የሌሎች ምስክር እንደማያስፈልገው እየነገራቸው ነው።         ለዚህም ነው "እኔ ስለራሴ ብመሰክር ምስክሬ እውነት አይደለም" ካለ ብኋላ ፣ ይህ ቃል ለእነርሱ ሲባል የተነገረ እንጂ ጌታችን እንደ አምላክነቱ የሌሎች ምስክርነት እንደማያስፈልገው ለማስረዳት “እኔ ግን ከሰው ምስክር አልቀበልም፥ እናንተ እንድትድኑ ይህን እላለሁ እንጂ።”(ዮሐ 5፥34) በማለት የተናገረው።         በመጨረሻም ይህ የትርጓሜ መንገድ ክርስቲያኖች ከሙስሊሞች ሙግት ለማምለጥ ሲሉ የፈጠሩት ሳይሆን እስልምና ከመነሳቱ ከብዙ አመታት በፊት በቤተ ክርስቲያን የነበረ ፣ በቤተ ክርስቲያንም አባቶች ዘንድ ተቀባይነትን ያገኘ ትርጓሜ እንደሆነ ልብ እንዲባል አሳስባለሁ ። ለአብነትም  በ 4 ተኛ ክፍል ዘመን የኖረ የቤተ ክርስቲያን ሊቅ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ  የጻፈውን ባስተውሎት አንብቡት።     « 'ምስክሬ እውነት አይደለም' ሲል እነርሱ ስለእርሱ ያላቸውን አመለካከት ና በእርሱ ላይ የሚያነሱትን ክስ እየነቀፈ ነው ፤ ነገር ግን "ስለራሴ ብመሰክር ምስክሬ እውነት ነው" ብሎ ሲናገር ፣ ስለነገሩ ምንነት ይህም ስለራሱ ሲናገር እንደ እግዚአብሔርነቱ ሊያምኑት እንደሚገባ እያስረዳ ነው ። » [1]         አሜን ጌታ ኢየሱስ ሆይ ና !        ✍ በዘአትናቴዎስ የተጻፈ     [https://t.me/ZeathanAmharic] 🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱 2) Homily on the Gospel of John by st.john Chrysostom
130
8
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምስክርነት እውነት ነው ወይስ አይደለም ? (ክፍል 1)          የመጽሐፍ ቅዱስን የአምላክ ቃል እንደሆነ የማያምኑ ሰዎች ፣ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ግጭት አለ ሲሉ መስማት የተለመደ ነው ፤ ታዲያ አለ ያሉት ግጭት ያሳዩ ዘንድ በምንጠይቃቸው ጊዜ አዘውትረው ከሚጠቅሷቸው ጥቅሶች መሐከል ዮሐ 5:31 እና ዮሐ 8:14 ይገኙበታል።         ዮሐ 5:31 ላይ ጌታችን መድኋኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "እኔ ስለራሴ ብመሰክር ምስክሬ እውነት አይደለም " ሲል የተናገረው ቃል በዮሐ 8:14 ላይ"እኔ ስለራሴ ብመሰክር ከወዴትም እንደመጣሁ ወዴትም እንዲሄድ አወቃለሁና ምስክርነቴ እውነት ነው "  ካለው ጋር ይጋጫል ብለው ያስባሉና ፤ እውን ሁለቱ የጌታችን ቃላቶች ይጋጫሉን ? በፍጹም !           በዮሐ 5:31 እና ዮሐ 8:14 መሐከል አለ ለተባለው ግጭት መልስ ከመስጠታችን በፊት ፣ ስለምን ይህ ግጭት ተፈጠረ ? ብዙ ሰዎች መጽሐፍ ቅዱስን ሲያነቡ ለምን ሚጋጩ ሚመስሉ ሃሳቦችን ያገኛሉ ? የሚለው ሃሳብ ላይ የተወሰነ ብንወያይ ጥሩ ይመስለኛል።        መጽሐፍ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝተው ቅዱሳን ሰዎች የጻፋት እንደመሆኑ ግጭቶችን በኩር በሆኑት እደ ክታባት ላይ አናገኝም ፤ ሆኖም መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ግጭቶች ባይኖሩም እንኳን የሰው ልጅ ከራሱ ስህተት ና ከአረዳድ ችግር የተነሳ ግጭትዎችን መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሊያገኝ ይችላል ፣ ይህም የመጽሐፍ ቅዱስ ችግር ሳይሆን የአንባቢው ችግር ነው ፤ ማለትም ጥቁር መነጸር አርጎ ነጭ ወረቀትን የሚመለከት ሰው ፣ ለምን ወረቀቱ ጥቁር ሆነ ? ብሎ ቢጠይቅ ስህተቱ ከሰውየው እንጂ ከወረቀቱ እንዳልሆነ ሁሉ ማለት ነው።        በዚህም ብዙዎች መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ግጭት አለ ብለው ሲናገሩ የሚሰሯቸውን ሁለት ዋና ዋና ስህተቶችን አንስተን የተወሰነ እንበል ።          የመጀመሪያው ስህተት አንድን ጥቅስ ከአውዱ ውጭ መውሰድ ነው ፤  ጥቅሶች ለማን ፣ መቼ ፣ ለምን ና በማን እንደተነገሩ ሒሳብ ውስጥ ካላስገባን ምናልባትም መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ግጭት ያለ ሊመስለን ይችላል ።      ለምሳሌ ዘፍ 1:1 የእግዚአብሔርን ህልውና ፍጥረትን መፍጠሩን በማስታወቅ ይገልጻል ፤ ሆኖም ይህ ጥቅስ መዝ 14:1 ላይ "አምላክ የለም " ከሚለው ጥቅስ ጋር ይገጫል ብለን መናገር እንችል ይሆናል ፤ ነገር ግን መዝ 14:1 ን በአውዱ ስናነብ ጥቅሱ አምላክ የለም እያለን ሳይሆን የማያምኑ ሰዎች የሚሉትን እየነገረን እንደሆነ እንረዳለን ፣ ጥቅሱ ሙሉው ሲነበብ "ሰነፍ በልቡ አምላክ የለም ይላል"  የሚል ነውና።       ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ አንድ ጥቅስ ከአውድ ውጭ ገንጥሎ መውሰድ የሚያስከትለውን ችግር እንዲህ በማለት ገልጾታል :-      "ለማን እና በምን ምክንያት እንደተነገሩ በደንብ ሳናመዛዝን ከአውድ ውጭ በቀላሉ እንደተባሉ  ብቻ የምንወስድ ከሆነ ...ሁለቱም (ጥቅሶች) ሐሰት ይሆናሉ። "[1]  ይቀጥላል!           አሜን ጌታ ኢየሱስ ሆይ ና !            ✍ በዘአትናቴዎስ የተጻፈ [https://t.me/ZeathanAmharic] 🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱 1)Homilies on the Gospel of John by st.John chrysostom
118
9
ማቴ 23:35 ከ 2 ዜና 20:24 ጋር ይጋጫልን ?     ጥንት አዳም ርስቱ ትሆን ዘንድ በተፈጠረች ገነት ጸጋ እግዚአብሔርን ለብሶ ይኖር ነበር ፤ በበደለ ጊዜ ግን መጽሐፍ እንደሚል ጸጋ እግዚአብሔር ራቀው [1]። ሆኖም ከጸጋ እግዚአብሔር የተራቆተ ፣ ባሕርዩ የጎሰቆለ ሰውነት ቢይዝም የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ በልቦናው ሕግ ያውቅ ነበር።     ታዲያ የሰዎች ልቦና ወደ ኃጢአት ማጋደሉ በጨመረና ከእግዚአብሔር ይበልጡን እየራቁ  በመጡ ጊዜ እግዚአብሔር በሚታይ ህግ ፣ በሚታይ መስዋዕት ፣ ... ወዘተ ራሱን ለእኛ ይገልጥ ዘንድ ወደደ። ከእነዚህ ከሚታዩና አምላክ ራሱን ለሰው ልጅ ከገለጠባቸው መንገዶች መሐከል አንዱ መጽሐፍ ቅዱስ ነው።       በእርግጥ መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ራሱን ለእኛ የገለጠበት አንዱ መንገድ እንጂ ብቸኛው መንገድ አይደለም። በመሰረቱ መጽሐፍ ቅዱስ በቤተክርስቲያን ውስጥ ያለውን ህያው ቅዱስ ትውፊት (the living holy tradition) ከፊሉን በጽሑፍ የያዘ ሲሆን ይህም መጽሐፍ ቅዱስን በምናነብበት ጊዜ በቤተክርስቲያን ባለው ሕያው ትውፊት መሰረት ሊሆን እንደሚገባ ያጠይቃል።      መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ራሱን ለእኛ የገለጠበት አንዱ መንገድ ነው ካልን በዚህ መጽሐፍ ውስጥ እርስ በርሱ የሚቃረን ወይንም የሚጋጭ ሀሳብ ሊኖር እንደማይገባ ግልጽ ነው።      ስለ ግጭት/ተቃርኖ ስናነሳ አስቀድመን "በሁለት ሀሳቦች መካከል ተቃርኖ ተፈጥሯል የምንለው እንዴት ነው?" የሚለውን ሀሳብ ማጥራት ይኖርብናል። ሁለት ሀሳቦች (ንግግሮች) እርስ በእርሳቸው ይጋጫሉ ሚባለው በተመሳሳይ ጊዜ እና ሁኔታ/ግንኙነት የተነገሩ ሲሆን ነው።      ስለዚህ ቀጥለን የምናየውንም ሆነ በሌላ ክፍል የምንመለከታቸውን የመጽሐፍ ቅዱስ ግጭት ተብለው የሚነሱ ሙግቶች ከላይ ባሰፈርነው የግጭት ፍቺ መሰረት ምንመዝን ይሆናል።      ለዛሬ ሙስሊም ወገኖች የመጽሐፍ ቅዱስ ይጋጫል ለማለት በተደጋጋሚ ከሚያነሷቸው  ሙግቶች ውስጥ አንዱን ምንመለከት ይሆናል። ሙግቱም እንደሚከተለው ይነበባል ፦      "ማቴዎስ 23:35 ላይ ኢየሱስ ክርስቶስ  ዘካርያስ የበራክዩ ልጅ እንደሆነ በቤተመቅደስና በመሰዊያው መካከልም ደሙ እንደፈሰሰ የተናገረ ሲሆን በ 2ኛ ዜና 24:20-21ላይ ስንመለከት ግን ዘካርያስ የዮዳሄ ልጅ እንደሆነ በአዳባባይም እንደተገደለ ተገልጿል።    ታዲያ የዘካርያስ አባት ስም ማነው ዮዳሔ ወይንስ በራክዩ ? ደግሞስ ዘካርያስ በአደባባይ ወይንስ ቤተ መቅደስ እና በመሠዊያው መካከል ነው የሞተው ?"       አስቀድመን ከላይ እንዳብራራነው መጽሐፍ ቅዱስ በቤተክርስቲያን ውስጥ ያለው የህያው ትውፊት አካል እንደመሆኑ ቃሉን ስንረዳም ሆነ ስናብራራ ከዚህ ከቤተክርስቲያን ህያው ትውፊት አንፃር ሊሆን ይገባል።         2ኛ ዜና 24:20-21 ያለውን ክፍል በተመለከተ ከምዕራፍ 23 ጀምሮ ስለ አባቱ ስለ ዮዳሄ እየተረከ መጥቶ ካህኑ ዮዳሄ ከሞተ በኋላ ልጁ ዘካርያስ ሕዝቡን በመገሰጹ ሕዝቡ ሁሉ ተማምለውበት በንጉሱ በኢዮአስ ትእዛዝ በእግዚአብሔር ቤት አደባባይ እንደተገደለ የሚናገር ነው። ማቴዎስ 23:35 ላይ የምናገኘው ንግግር ግን 2ኛ ዜና 24:20-21 ያለውን የሚያወሳ ሳይሆን ራሱን ችሎ ስለሌላ ኩነት የሚገልጽ ነው።      በቤተክርስቲያን ህያው ትውፊት ውስጥ እንደምናገኘው የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ አባት ካህኑ ዘካርያስ በቤተመቅደስ እና በመሰዊያው መሐከል በአገልግሎት ላይ ሳለ የሄሮድስ ሠራዊት ስለ ልጁ ብለው ገድለውታል [2] ፤ በተጨማሪም የካህኑ ዘካርያስ አባት በራክዩ እንደሚሰኝ በዚሁ ትውፊት ውስጥ የምናገኘው እውነታ ነው [3]።      በዚህም በ 2 ዜና 24:20-21እና በማቴዎስ 23:35 ላይ የሚገኙት ሁለት ደማቸው የፈሰሰ አባቶች የተለያዩ አካላት እንጂ አንድ አይነት ሰዎች አይደሉም ፤ በሁለቱም ታሪኮች ውስጥ ያሉት አባቶች ስማቸው 'ዘካርያስ' መሆኑ ስለ አንድ ሰው የሚያወራ ነው የሚል ድምዳሜ ላይ አያደርስምና። ይህ ዓይነቱ  አመክንዮ ሕጸጽ ያለበት ሲሆን የአሻሚነት ሕጸጽ (Fallacy of Equivication)[4] ከተሰኘው ሥነ አመክንዮአዊ ሕጸጽ ሊመደብ የሚችል ነው።      በመጨረሻም ሁለቱ ታሪኮች ስለ አንድ ሰው እየተረኩ እንዳልሆነ ከተረዳን በመነሻችን ሁለት ሀሳቦች የሚቃረኑ ናቸው ለማለት ያስችለን ዘንድ ባስቀመጥነው መስፈርት ሙግቱን ስናነጥረው ገፈታ ሁኖ ከላይ እንደሚቀ'ር ግልጽ ነው።             አሜን ጌታ ኢየሱስ ሆይ ና !               ✍ በ'አናሲሞስ ተጻፈ [https://t.me/ZeathanAmharic] 🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱 [1] ዘፍጥረት 3:7 [2] ወንጌል ቅዱስ አንድምታ ፤ ገድለ ዮሐንስ መጥምቅ ፤ Origen ; commentary on the gospel of Matthew [3] ወንጌል ቅዱስ አንድምታ ፤ St. Didymus the blind , commentary on Zechariah [4] የአሻሚነት ሕጸጽ፦ የሚባለው በሁለት ምንባባት ውስጥ የሚገኙ አንድ አይነት ቃላትን በተመሳሳይ ትርጓሜ ከመተርጎም የሚመጣ ስሑት እሳቤ ነው።
144
10
በዚህም የእስልምናው መምህር በአሸዋ ላይ የተገነባው ሙግታቸው የእውነት ነፋስ በነፈሰ ጊዜ እንዳይፈርስባቸው ሲሉ ፣ ያቀረቡት ሙግት ውሃ ማያነሳ ፣ ሚዛን ማይደፋ እንደሆነ ግልጽ ነው ፤ በተቃራኒው ከላይ እንዳብራራ ነው በራእይ 2:23 ላይ " ኵላሊትና ልብን የምመረምር እኔ እንደሆንሁ ያውቃሉ " በማለት የተናገረው ለስም አጠራሩ ክብር ምሥጋና ይግባውና መድኋኔ ዓለም  ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሆነ ማያሻማ ነውና አምላካችን ሁሉን አዋቂ ስለመሆኑ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ምስክር አለን ማለት ነው። ... ይቀጥላል ።           አሜን ጌታ ኢየሱስ ሆይ ና !          ✍ በዘአትናቴዎስ የተጻፈ [https://t.me/ZeathanAmharic] 🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱 1. " ... As if the ignorance of the teacher is the glory of disciples."  [The Fathers of the church ; St.Jerome commentary on Matthew , Translated by Thomas P.Scheck ,pp.278] 2. እውን ኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክ ነውን ? ፣ በኡስታዝ ወሒድ ኡመር ዐቃቤ ኢስላም ፣ ገጽ.124 - 125 3.Ancient Christian Commentary on scripture ; New Testament Hebrew , Translated by Thomas C.oden , pp.58 4. እውን ኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክ ነውን ? ፣ በኡስታዝ ወሒድ ኡመር ፣ ገጽ 125
256
11
ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁሉን አዋቂነት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ (ክፍል 2)       ... ሆኖም ይህ እውነት ያልተዋጠላቸው ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ሁሉን አዋቂ አይደለም ከሚለው እሳቤያቸው ጋር አልሄድ ያላቸው ሰዎች ፣ አባ ጄሮም መናፍቁ አርዮስን ሲወቅስ " የመምህሩ አላዋቂነት የደቀ መዛሙርቱ ክብር ይመስል ... " [1] እንዳለ ኢየሱስ ክርስቶስ ሁሉን አዋቂ አይደለም ብለው በመቅጠፋቸው ሚያገኙት ክብር ያለ ይመስል ፣ የጌታችንን ቃል ለማጣመም ይሞክራሉ ። ለአብነትም አንድ የእስልምና መምህር " ኩላሊትንና ልብን የምመረምር እኔ እንደሆንሁ ያውቃሉ " የሚለውን የጌታ ቃል ለማጠመም የጻፉትን እንመልከት ፤       " መዝሙር 7:9 ኤርሚያስ 11:20 ኤርሚያስ 17:10 ላይ ኩላሊትን እና ልብን የምመረምር አንዱ አምላክ ያህዎህ ስለሆነ ጥቅሱ ላይ " የአምላክ ልጅ እንዲህ ይላል " ስለሚል አንዱ አምላክ በልጁ እየተናገረ ነው ... "ራእይ" አምላክ ለኢየሱስ እንዲናገር የሰጠው ከሆነ እና አምላክ " አምላክ በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን " ካለ " ኵላሊትን እና ልብን የምመረምር እኔ እንደሆንሁ ያውቃሉ " የሚለው የላከው ንግግር እንጂ የራሱ ንግግር አይደለም ። ... " [2]       አስተዋላችሁ ! ኡስታዝ እያሉን ያሉት መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር በልጁ እንደ ተናገረ መግለጹ ፣ " ኵላሊትንና ልብን የምመረምር እኔ እንደሆንሁ ያውቃሉ " የሚለው የኢየሱስ ክርስቶስ ንግግር የአብ እንጂ የወልድ እንዳልሆነ  ያሳያል ነው ፤ ሆኖም እዚህ ጋር ኡስታዝ  እግዚአብሔር በልጁ ተናገረን ማለት ምን ማለት እንደሆነ የተገነዘቡ አልመሰለኝም ።      ለአፍታ አብ በልጁ ተናገረን ማለት ምን ማለት እንደሆነ ከማየታችን በፊት  የኡስታዝ ሙግት ስህተት እንደሆነ እንረዳ ዘንድ  የእሳቸውን እሳቤ ይዘን ጥቂት እንጓዝ ፤ ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ራእይ 2:23 ላይ ልብና ኩላሊትን እንደሚመረምር የተናገረው ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሆነ በቁጥር 18 ላይ " የእግዚአብሔር ልጅ እንዲህ ይላል " ብሎ መግለጹ ንግግሩ የአብ እንጂ የወልድ እንዳልሆነ ያሳያል ካልን ፣ በአውዱ ላይ የእግዚአብሔር ልጅ ኵላሊትንና ልብን እንደሚመረምር ከገለጸ በኋላ " ድል ለነሣውና እስከ መጨረሻም ሥራዬን ለጠበቀው እኔ ደግሞ ከአባቴ እንደተቀበልሁ በአሕዛብ ላይ ... " (ራእ 2:26-27) ብሎ ተናግሮአልና በእርሳቸው አመክንዮ ከሄድን " ከአባቴ " ብሎ የተናገረው በልጁ አብ ነው ልንል ነው ማለት ነው ።       እንግዲህ በኡስታዝ እሳቤ ከተመራን ምን ዓይነት ስህተት ውስጥ እንደምንገባ አስተዋላችሁ ? እንደ እርሳቸው ሙግት ከተረዳን " አብ ማንን ነው አባቴ ብሎ የጠራው ? ወይስ አብ ራሱን ነው አባቴ ብሎ የሚጠራው ? " የሚሉትን ጥያቄዎች እንዴት ነው መመለስ የምንችለው ? ፣ እንደዚህስ ብሎ መረዳት ትክክል ነው ብላችሁ ታስባላችሁ ? አይ እንደርሱ እኮ አይደለም ፣ " ከአባቴ " ብሎ የተናገረው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ካልን በራእይ ዮሐንስ ምዕራፍ ሁለት አውድ መሰረት በቁጥር 23 ላይ " ኵላሊትንና ልብን የምመረምር እኔ እንደሆንሁ ያውቃሉ " ያለው እንዲሁም በቁጥር 26 ላይ  " ... ከአባቴ ... " በማለት የተናገረው ፣ በቁጥር 18 ላይ የእግዚአብሔር ልጅ ተብሎ የተጠራው ኢየሱስ ክርስቶስ ነውና ጌታችን ሁሉን አዋቂ እንደሆነ ተናግሮአል ማለት ነው ።        ታዲያ ቅዱስ ጳውሎስ " “ሁሉን ወራሽ ባደረገው ደግሞም ዓለማትን በፈጠረበት በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን፤” (ዕብ 1፥2) ብሎ ሲናገር ምን ማለቱ ነው ? ይህ ቃል የአብ አካላዊ ቃል ከቅድስት ድንግል ተወልዶ ፣ ሥጋችንን ተዋሕዶ ወደ ምድር በመምጣት እንደ ተናገረን ፣ ከአባቱ ጋር አንድ የሆነ ፈቃዱን እንደ ገለጠለን ፣ የምሥራችን የሆነ ቅዱስ ወንጌሉን እንዳስተማረን የሚያመለክት እንደሆነ ቅዱስ ቄርሎስ አብራርቶ አስተምሯል ።     " በዘመናት መጨረሻ ወልድ ራሱ በራሱ ተናግሮናልና ፤ በነቢያት መካከለኝነት  ወይንም በቅዱሳን ድምጽ ሳይሆን ወልድ ዋሕድ እንደ እኛ ሆኖ በመወለድ በራሱ ተናገረን ። እኛም አብ በልጁ ተናገረን እንላለን እንጂ ፣ መካከል ላይ ይሆን ዘንድ በተመረጠ ዕሩቅ ብእሲ ወይንም የራሱን ሳይሆን የሌላን መልእክት በሚያስታውቀን አካል አይደለም ። ይልቁንም ወልድ በራሱ ድምጽ ፣ በራሱ ሰውነት በኩል ተናገረን ፤ ትስብእት የወልድ ዋሕድ እንጂ የሌላ የማንም አይደለምና። " [3]      የሚያስደንቀው ግን ኡስታዝ ያቀረቡት ሙግት ፣ እንደ እምቧይ ካብ በቀላሉ እንደሚፈርስ ስለገባቸው ይመስላል ፣ ቀጠል አድርገው  የመጽሐፍ ቅዱስን ቃል ከአዉድ ውጭ በመጥቀስ ለመቅጠፍ የሞከሩት ፤ እንዲህ በማለት :- " ሙሴ :- " እኔ አምላካችሁ ያህዌህ እንደ ሆንሁ " ብሏል :- ዘዳግም 29:2 ሙሴም የእስራኤል ልጆችን ሁሉ ጠርቶ አላቸው :- ዘዳግም 29:6 " እኔ አምላካችሁ ያህዌህ እንደ ሆንሁ " ታውቁ ዘንድ እንጀራ አልበላችሁም ፣ የወይን ጠጅና የሚያሰክረውን መጠጥ አልጠጣችሁም። ዐውደ ንባቡ ላይ "ይላል" የሚል የለም። አይ ሙሴ ፍጡር ፣ ሰው ፣ ነቢይ መሆኑን ስለተገለጸ አምላክ በእርሱ በኩል እየተናገራ ነው " ካላችሁ እንግዲያውስ ኢየሱስ ፍጡር ፣ ሰው ፣ ነቢይ መሆኑን ስለተገለጸ አምላክ በእርሱ በኩል እየተናገራ ነው " [4]      ለአንድ ጥያቄ መልስ ሊሆኑ የሚችሉ ከሁለት በላይ ምርጫዎች እያሉ ፣ ለራስ እሳቤ መደገፊያ ይሆን ዘንድ ሁለት ምርጫ ብቻ እንዳለ አድርጎ በማቅረብ መላሹን አጣብቂኝ ውስጥ ለመክተት የሚደረግ ሙከራ ሥነ አመክንዮአዊ ሕጸጽ ሲሆን የሃሰት አጣብቂኝ ሕጸጽ (False Dilemma Fallacy) በመባል ይታወቃል። የእስልምናው መምህርም የመጽሐፍ ቅዱስን ቃል ከአውዱ ውጪ ገንጥለው በማውጣት ፣ ወይ ሙሴ አምላክ ነኝ ብሏል ወይንም አምላክ በእርሱ እየተናገረ ነው የሚሉ ምርጫዎችን ብቻ በማቅረብ ክርስቲያኖችን አጣብቂኝ ውስጥ ለመክተት ሞክረዋል ፤ ሆኖም ጥቅሱን በአውዱ ካነበብነው  ሙሴ  እኔ እግዚአብሔር አምላክ ነኝ እያለ ሳይሆን እግዚአብሔር በሞዓብ ምድር ከእስራኤላውያን ጋር ያደረገውን የቃል ኪዳን ቃሎች እየተናገረ ነው ፤ “እግዚአብሔር በኮሬብ ካደረገው ቃል ኪዳን ሌላ በሞዓብ ምድር ከእስራኤል ልጆች ጋር ያደርገው ዘንድ ሙሴን ያዘዘው የቃል ኪዳኑ ቃሎች እነዚህ ናቸው። " (ዘዳግም 29፥1) እንዲል መጽሐፍ ።      ዳግመኛም በዐውዱ " ይላል " የሚል ቃል ቢኖርም ባይኖርም ፣ አስቀድሞ ሙሴ ይናገር ዘንድ ያለው ነገር እግዚአብሔር ከሕዝበ እስራኤል ጋር ያደረገውን ቃል ኪዳን እንደሆነ መገለጹ ፣ የቃሉ ባለቤት ማን እንደሆነ ግልጽ አድርጎ ያስገነዝበናል ። ተመሳሳይ የሆነ ሃሳብ በዘጸ 6:6 ላይም የሚገኝ ሲሆን እግዚአብሔር  “ስለዚህም ለእስራኤል ልጆች እንዲህ በላቸው፦ እኔ እግዚአብሔር ነኝ፥ ከግብፃውያንም ባርነት አወጣችኋለሁ፥ ከተገዥነታቸውም አድናችኋለሁ፤ በተዘረጋ ክንድ በታላቅ ፍርድም እታደጋችኋለሁ፥  (ዘጸ 6፥6) በማለት ሙሴን እንዳዘዘው ተጽፏል ፤  ታዲያ በቁጥር 9 ላይ " ሙሴም ይህን ለእስራኤል ልጆች ተናገረ " ይላልና ሙሴ እኔ እግዚአብሔር ነኝ በማለት ራሱን አምላክ እያደረገ ነው ማለት እንችላለን? መልሳችሁ " አይ አይደለም ፤ እግዚአብሔር እንዲናገር ያዘዘውን እየተናገረ ነው እንጂ " ከሆነ ዘዳ 29:6 ላይ ያለውንም በዚሁ መንገድ ልንረዳ ይገባናል ማለት ነው ።
220
12
"ጥልቅንና ልብን መርምሮ ያውቃቸዋል ፤ ምክራቸውንም ሁሉ ያውቃል ፤ እግዚአብሔር የልቡና አብን ሁሉ ያውቃል ፤ የዓለምንም ምልክት ያያል። ያለፈውንም የሚመጣውንም እርሱ ይናገራል ፤ የተሰወረውንም ፍለጋ ይገልጣል ። ከምክርም ሁሉ የሚያመልጠው የለም ፤ ከነገሩ ሁሉ አንድ ቃል ስንኳ የሚሰወረው የለም ። " (ሲራክ 42:18-20)       ለስም አጠራሩ ክብር ምሥጋና ይግባውና ጌታችንና መድኋኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም የአምላክን ሁሉን አዋቂነት የሚያሳይ አገላለጽ ተጠቅሞ ፣ " ኩላሊትንና ልብን የምመረምር እኔ እንደሆንሁ ያውቃሉ ፣ለእያንዳዳችሁም እንደ ሥራችሁ እሰጣችኃለሁ ። [2] ማለቱ እርሱ ሁሉን አዋቂ እንደሆነ ያስገነዝባል። በተለይ  አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት እንዳመለከቱት ጌታችን በራእ 2:23  " ኩላሊትንና ልብን የምመረምር እኔ እንደሆንሁ ያውቃሉ ፣ ለእያንዳንዳችሁም እንደሥራችሁ እሰጣችኋለሁ " ብሎ ሲናገር  በትንቢተ ኤርሚያስ ላይ እግዚአብሔር አምላክ  “እኔ እግዚአብሔር ለሰው ሁሉ እንደ መንገዱ፥ እንደ ሥራው ፍሬ እሰጥ ዘንድ ልብን እመረምራለሁ ኵላሊትንም እፈትናለሁ።” (ኤር 17፥10) ሲል የገለጸውን  ዓ.ነገር ተጠቅሞ (paraphrase አድርጎ) እየተናገረ ሊሆን ይችላል ። [3] በዚህም እኛ ክርስቲያኖች ኢየሱስ ክርስቶስ ሁሉ አዋቂ ነው ብለን ለማመናችን በቂ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ አለን ማለት ነው።     ሆኖም ይህ እውነት ያልተዋጠላቸው ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ሁሉን አዋቂ አይደለም ከሚለው እሳቤያቸው ጋር አልሄድ ያላቸው ሰዎች ፣ አባ ጄሮም መናፍቁ አርዮስን ሲወቅስ " የመምህሩ አለማወቅ የደቀ መዛሙርቱ ክብር ይመስል... "[4] እንዳለ ኢየሱስ ክርስቶስ ሁሉን አዋቂ አይደለም ብለው በመቅጠፋቸውው ሚያገኙት ክብር ያለ ይመስል ፣ የጌታችንን ቃል ለማጣመም ይሞክራሉ ። ... ይቀጥላል ።        አሜን ጌታ ኢየሱስ ሆይ ና !      ✍ በዘአትናቴዎስ የተጻፈ [https://t.me/ZeathanAmharic] 🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱 1.How to not to be wrong : the power of mathematical thinking by Jordan Ellenberg 2. " ልብንና ኩላሊትን እመረምራለሁ ሲል የምታስቡትን አውቃለሁ ማለቱ ነው ፤ በጥንታዊው ዓለም ኩላሊቶች የስሜቶቻችንና የፍላጎቶቻችን መኖሪያ ፣ ልባችን ደግሞ የፍቃዳችንና የሃሳባችን ማደሪያ እንደሆኑ ይታመን ነበርና። " [Revelation of Jesus christ, commentary on The book of Revelation by Ranko Stefanovic , pp.129] 3.Revelation ; Ance Anchor by Craig R.Koester ,pp.300 4." ... As if the ignorance of the teacher is the glory of disciples. " [ The fathers of the church ;  st .Jerome commentary on Matthew , translated by Thomas P.scheck ,pp.278 ]
192
13
ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁሉን አዋቂነት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ (ክፍል 1)      ዘግይታም ቢሆን በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ላይ ተሳታፊ የሆነችው ልዕለ ኃያሏ ሀገር አሜርካ ፤ ጦርነቱን ለማሸነፍ ፣ ናዚዎችንም ድል ለመንሳት ያስችላት ዘንድ ፣ ጦር ሜዳ ላይ ከሚደረገው ውጊያ በስተጀርባ ሆነው በተቸራቸው ጸጋ ፣ ባላቸውም መክሊትና ሙያ የሚያግዙ ሰዎችን በመመልመል እንዲሁም  በቡድን መልክ በማዋቀር የጠላትን እንቅስቃሴ የማስተንተን ፣ የራስንም አቅም የማጎልበት ሥራ ትሰራ ነበር ።     አሜርካ ትጠቅሙኛላችሁ ፣ በውጊያውም ላይ ታግዙኛላችሁ ብላ ከጠራቻቸው ፣ በቡድን መልክም ካዋቀረቻቸው ሰዎች መሐከል በሒሳብ እውቀታቸው የተመሰከረላቸው ፣ በስሌት ችሎታቸው አንቱ የተባሉ ሰዎች ይገኙበት ነበር ። እነዚህ የሂሳብ ሊቃውንት በማንሐተን ከሚገኘው ኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ ጥቂት ራቅ ብሎ በተገነባው አፓርትመንት ውስጥ የጥናት እና የምርምር ቦታ ተዘጋጅቶላቸው በጦርነቱ ውስጥ የአሜሪካ ወታደሮችን የሚያግዙ ፣ የጠላትን ጦር ሚያዳክሙ ስትራቴጂዎችን እና የሒሳብ ቀመሮችን ያዘጋጁ ነበር ።     ታዲያ አንድ ቀን የሀገሪቱ የጦር ጀነራሎች የውጊያ ጀቶቻቸው በናዚ ጦር እንዳይመቱ ለማድረግ ፣ የተተኮሱባቸውንም ጥይቶች እንዲቋቋሙት ለማስቻል ሁሉንም ተዋጊ ጀቶች በብረት ለመለበጥ አሰቡ ፤ ሆኖም ተዋጊ ጀቶቹ  ሙሉ በሙሉ በብረት ከተለበጡ ክብደት ስለሚጭምሩ ለመብረር እንደሚቸገሩና በቀላሉ ለመንቀሳቀስ ከባድ እንደሚሆንባቸው ፣ ብዙ ነዳጅም እንደሚጠቀሙ ስለሚያውቁ መፍትሔ ፍላጋ ሐሳባቸውን ይዘው ወደ ሀገሪቱ የሒሳብ ጠበብት ቡድን ዘንድ ጎራ አሉ ።     የሒሳብ ሊቃውንቱም ችግሩን አይተውና ተገንዝበው ፣ ተዋጊ ጀቶቹን ሙሉ በሙሉ በብረት ከመለበጥ ይልቅ በናዚ ጦር በብዛት የተመታ ክፍላቸውን በመለየት እርሱን ክፍል ብቻ በብረት መለበጥ ይሻላል የሚል ሃሳብን አቀረቡ ። በዚህም ከውጊያ የተመሉሱ ጀቶች ላይ በብዛት በየትኛው ክፍል ላይ እንደተመቱ ማጥናት ጀመሩ ፤ በጥናታቸውም ተዋጊ ጀቶቹ ከሞተር ክፍላቸው ይልቅ የእቃና የሰው ማስቀመጫ ክፍላቸው ላይ በይበልጥ እንደተመቱ ተገነዘቡ።        ከውጊያ በተመለሱት ጀቶች ላይ ባደረጉት ጥናት ተመስርተው የብረት ልበጣው የሚያስፈልገው የእቃ ማስቀመጫው ክፍል ላይ ነው በማለት አብዛኛው የሂሳብ ሊቃውንት ደመደሙ ፤ ሆኖም በሒሳብ ጠበብቱ ቡድን ውስጥ የሚገኘው የሒሳብ ሊቅ አብርሃም ዋልድ ከእነርሱ በተቃራኒ የብረት ልበጣው የሚያስፈልገው ከእቃ ማስቀመጫው ክፍል ይልቅ በሞተሩ ላይ ነው ብሎ ሐሳብ ሰጠ። የዋልድ ሃሳብ ያልገባቸው ጠበብትም " እንዴት ? ከሞተሩ በላይ እኮ የእቃ ማስቀመጫ ክፍል ነው ብዙ ጥይት ያስተናገደው ፣ " በማለት ለዋልድ ጥያቄ አቀረቡለት ። ዋልድም ለቀረበለት ጥያቄ እንዲህ በማለት ምላሽ ሰጠ :-    " የብረት ልበጣው የጥይት ቀዳዳዎች በሌሉበት ክፍል እንጂ የጥያት ቀዳዳዎች ባሉበት ክፍል መከናወን የለበትም ፤ ምክንያቱም እኛ ማሰብ ያለብን የእቃ ማስቀመጫ ክፍላቸውን ተመተው ስለተመለሱት ጀቶች ብቻ ሳይሆን ሞተራቸውን ተመተው መመለስ ስላልቻሉትም ጭምር ነውና። " [1]     የአብርሃም ዋልድ ሃሳብ በጦር ሜዳ ላይ ተዋጊ ጀቶች ምን እንደሚገጥማቸው ለመረዳት ከጦርነት ከተመለሱት ጀቶች ይልቅ ሳይመለሱ የቀሩ ጀቶች ዋቢ መደረግ እንደሚገባቸው አጽኖት የሚሰጥ ነው ፤ ነገር ግን እዚህ ጋር አንድ ጥያቄ እንጠይቅ ዘንድ ይገባል ፣ ይኸውም " ዋልድ በቀላሉ የተረዳውን ነገር በችሎታቸው ተመርጠው ፣ ከፍተኛ ዕውቀት አላቸው ተብለው የመጡት ሌሎቹ የሒሳብ ሊቃውንት እንዴት ሳይረዱት እና ሳያገናዝቡት ቀሩ ? " የሚል ነው።     ከዋልድ በቀር ሌሎቹ የሒሳብ ሊቃውንት ትክክለኛውን የመፍትሔ ሃሳብ ያላገኙበት ምክንያት ከውጊያ የተመለሱት ጀቶች ፣ ሙሉ በሙሉ ተዋጊ ጀቶች በጦርነት ውስጥ ምን እንደሚገጥማቸው ያስረዳሉ ብለው ማሰባቸው ነው ፤ ማለትም ጥናቱን ሲያካሂዱና ከጥናቱ ውጤት ተነስተው ድምዳሜ ላይ ሲደርሱ እውነታውን አስቀድመው አእምሮአቸው ውስጥ ባለው እሳቤ እየቃኙት ስለነበረ ትክክለኛውን መፍትሔ ማግኘት አልቻሉም።      በተመሳሳይ በዘመናችን የሚገኙ የእስልምና ዐቃቢያን ጌታችንንና መድኋኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁሉን አዋቂ እንዳልሆነ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል ብለው ሲያስተምሩ ፣  ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የኢየሱስ ክርስቶስን ሁሉን አዋቂነት የሚመሰክሩ ጥቅሶችን ሲያጣምሙ ሳይ ፣ ምናልባት መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኘውን እውነት መነበብ በሚገባው መንገድ ሳይሆን አእምሮአቸው ውስጥ ባለው ኢየሱስ ክርስቶስ ዕሩቅ ብእሲ ነው /ሎቱ ስብሐት / በሚለው እሳቤ መነጸርነት እያነበቡት ይሆን ብዬ አስባለሁ ።      ይህ አንድ ከእኛ እሳቤ ጋር የሚጻረር ነገር ስናገኝ እውነታውን በቁሙ ከመቀበል ይልቅ ፣ መረጃ እና ማስረጃዎችን ለእኛ እሳቤ በሚመች መልኩ በማጣመም ትክክለኛ ትርጉማቸውን የማደብዘዝ ሙከራ በስነ ልቦና ጥናት ውስጥ የማረጋገጫ አድሏዊነት (confirmation bias) ተብሎ ይጠራል ፤ ምናልባት ሙስሊም ዐቃቢያ እንዴት ነው ስለክርስቶስ ሁሉን አዋቂነት የሚመሰክሩ ጥቅሶችን ለማጣመም የሞከሩት ? ጥቅሶቹስ የጌታችንን ሁሉን አዋቂነት ከመጀመሪያውኑ ያስረዱ ነበርን ? ሚል ጥያቄ አእምሮአችሁ ውስጥ ከተፈጠረ አንድ ምሳሌ ልስጣችሁ ።      በራእየ ዮሐንስ ላይ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በትያጥሮን ለሚገኘው የቤተ ክርስቲያን መልአክ[2] መልእክትን እንደ ላከ "እንደ እሳት ነበልባል የሆኑ ዓይኖች ያሉት በእቶንም የነጠረ የጋለ ናስ የሚመስሉ እግሮች ያሉት የእግዚአብሔር ልጅ እንዲህ ይላል"(ራእ 2:18) በሚለው ቃል ግልጽ ተደርጎ ተቀምጦልና ፤ በመልእክቱም ጌታችን የቤተ ክርስቲያኒቱን መልአክ ስለፍቅሩ እና በየጊዜ እየበዛ ስለመጣው መልካም ተግባሩ ካመሰገነው በኋላ ፣ ቀጥሎም ነቢይ ሳትሆን ነኝ ያለችውን ፣ ክርስቲያኖችን ወደ ጣኦት አምልኮ የመራችውን ኤልዛቤልን ስለተዋት እንደሚነቅፈው ገለጸለት ፤ አክሎም " ያቺን ሴት ኤልዛቤልን " (ራእ 2:20) እንዲሁም በኃጢአቷ የተቋደሱትን ንሰሐ ካልገቡ ቅጣት እንዲሚከተላቸው ፣ መከራ እንዲሚጠብቃቸው ከገለጸ በኋላ በቅጣቱ ና በሚመጣው መከራ "አብያተ ክርስቲያናትም ሁሉ " ምን እንደሚረዱ ሲያመለክት " ኩላሊትንና ልብን የምመረምር እኔ እንደሆንሁ ያውቃሉ ፣ ለእያንዳንዳችሁም እንደ ሥራችሁ እሰጣችኋለሁ " በማለት ተናገረ። (ራእ 2:23) ይህ የጌታችን ንግግር ግልጽ በሆነ ሁኔታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሁለን አዋቂ እንደሆነ የሚያሳይ ነው ፣ ግን እንዴት ?      በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር አምላክ በአእምሯችን ያሰብነውን ፣ በልባችን የቋጠርነውን የሚያውቅ ሁሉን አዋቂ እንደሆነ ከሚገልጽባቸው መንገዶች መሐከል ፣ እርሱ ልባችንን እና ኩላሊታችንን የሚመረምር መሆኑን በመግለጽ ነው (1ነገ 8:40 ፣ 1ሳሙ 16:7 ፣ 1ዜና 28:9 ፣ መዝ 7:10 ; 44:21 ; 139:1-6,23 ፣ ኤር 11:20) ፤ ምንም እንኳን ነቢያት እና በእግዚአብሄር የተመረጡ ቅዱሳን ከአምላክ ዘንድ በተሰጣቸው ጸጋ ሰዎች የሚያስቡትን ማወቅ የሚቻለቸው ቢሆንም ፣ አፋቸውን ሞልተው ግን "እኔ ልብንና ኩላሊትን እመረምራለሁ ፣ ለሁሉም እንደየስራው እሰጣለሁ" ማለት ግን አይችሉም ፤ ለዚህም ነው ኢያሱ ሲራክ ስለ አምላካችን እግዚአብሔር እንዲህ ብሎ መናገሩ :-
190
14
ጥያቄ መጠየቁ ኢየሱስ ክርስቶስን /ሎቱ ስብሐት/ አላዋቂ ያሰኘዋልን ? (ክፍል 4)       በመጨረሻም ከላይ ያሰፈርነውን ማብራሪያ እና ምሳሌ ችላ ብለው አሁንም በቀደመ ነገራቸው በመጽናት "ኢየሱስ ክርስቶስ ጥያቄ በመጠየቁ ሁሉን አዋቂ ሊባል አይገባውም" በማለት ለሚከራከሩ አሕዛብ እስቲ የራሳቸውን የአመክንዮ መንገድ ተጠቅመን ሙግቱን ወደ እነርሱ እናዝረው።       በቁርአን ውስጥ አላህ የተለያዩ አካላትን ፣ መላእክትን እንዲሁም ነቢያትን ጥያቄ እንደጠየቀ ተጽፎአል ፤ ታዲያ በራሳቸው በሙስሊሞች እሳቤ ከሄደን አላህ የማያውቀውን ነገር ለማወቅ ሲል ነው ሚጠይቀው ማለት ነው - በዚህም አላህ ሁሉን አዋቂ ተብሎ ሊጠራ አይገባውም። ለአብነትም እነዚህን የቁርአን ክፍሎችን እንመልከት :-        * አላህ ኢብሊስ ስለምን ለአደም እንደማይሰግድ አያውቅም። قَالَ يَا إِبْلِيسُ مَا لَكَ أَلَّا تَكُونَ مَعَ السَّاجِدِينَ (አላህም) «ኢብሊስ ሆይ! ከሰጋጆቹ ጋር የማትኾን ላንተ ምን ምክንያት አለህ» አለው፡፡(ሱራ15:32)      * አላህ ሙሐመድ ያሰበውን አያውቅም። أَمْ حَسِبْتَ أَنَّ أَصْحَابَ الْكَهْفِ وَالرَّقِيمِ كَانُوا مِنْ آيَاتِنَا عَجَبًا የዋሻውና የሰሌዳው ባለቤቶች ከተዓምራቶቻችን ሲሆኑ ግሩም መሆናቸውን አሰብክን (ሱራ18:9)       * አላህ ኢሳ ምን እንደተናገረ ወይንም እንዳስተማረ አያውቅም። وَإِذْ قَالَ اللَّهُ يَا عِيسَى ابْنَ مَرْيَمَ أَأَنتَ قُلْتَ لِلنَّاسِ اتَّخِذُونِي وَأُمِّيَ إِلَٰهَيْنِ مِن دُونِ اللَّهِ ۖ قَالَ سُبْحَانَكَ مَا يَكُونُ لِي أَنْ أَقُولَ مَا لَيْسَ لِي بِحَقٍّ ۚ إِن كُنتُ قُلْتُهُ فَقَدْ عَلِمْتَهُ ۚ تَعْلَمُ مَا فِي نَفْسِي وَلَا أَعْلَمُ مَا فِي نَفْسِكَ ۚ إِنَّكَ أَنتَ عَلَّامُ الْغُيُوبِ አላህም፡- «የመርየም ልጅ ዒሳ ሆይ! አንተ ለሰዎቹ፡- እኔንና እናቴን ከአላህ ሌላ ሁለት አምላኮች አድርጋችሁ ያዙ ብላሃልን» በሚለው ጊዜ (አስታውስ)፡፡ «ጥራት ይገባህ፤ ለእኔ ተገቢዬ ያልኾነን ነገር ማለት ለኔ አይገባኝም፡፡ ብዬው እንደ ኾነም በእርግጥ ዐውቀኸዋል፡፡ በነፍሴ ውስጥ ያለውን ሁሉ ታውቃለህ፡፡ ግን አንተ ዘንድ ያለውን አላውቅም፡፡ አንተ ሩቆችን ሁሉ በጣም ዐዋቂ አንተ ብቻ ነህና» ይላል፡፡(ሱራ 5:116)      * አላህ ኢብራሂም ይመን ፣ አይመን አያውቅም። وَإِذْ قَالَ إِبْرَاهِيمُ رَبِّ أَرِنِي كَيْفَ تُحْيِي الْمَوْتَىٰ ۖ قَالَ أَوَلَمْ تُؤْمِن ۖ قَالَ بَلَىٰ وَلَٰكِن لِّيَطْمَئِنَّ قَلْبِي ۖ قَالَ فَخُذْ أَرْبَعَةً مِّنَ الطَّيْرِ فَصُرْهُنَّ إِلَيْكَ ثُمَّ اجْعَلْ عَلَىٰ كُلِّ جَبَلٍ مِّنْهُنَّ جُزْءًا ثُمَّ ادْعُهُنَّ يَأْتِينَكَ سَعْيًا ۚ وَاعْلَمْ أَنَّ اللَّهَ عَزِيزٌ حَكِيمٌ ኢብራሂምም «ጌታዬ ሆይ! ሙታንን እንዴት ሕያው እንደምታደርግ አሳየኝ» ባለ ጊዜ (አስታውስ፡፡) አላህ ፡- «አላመንክምን» አለው፡፡ «አይደለም (አምኛለሁ)፤ ግን ልቤ እንዲረጋ» ነው አለ፡፡ (አላህም)፡- «ከበራሪዎች (ከወፎች) አራትን ያዝ፡፡ ወደ አንተም ሰብስባቸው፡፡ (ቆራርጣቸውም)፤ ከዚያም በየኮረብታው ሁሉ ላይ ከነርሱ ቁራጭን አድርግ፡፡ ከዚያም ጥራቸው፤ ፈጥነው ይመጡሃልና፡፡ አላህም አሸናፊ ጥበበኛ መኾኑን ዕወቅ» አለው፡፡(ሱራ 2:260)       "የቆጡን አውርድ ብላ የብብቷን ጣለች" እንደሚባለው ፣ ሙስሊሞች የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ሁሉን አዋቂነት እንሞግታለን ብለው የራሳቸውን አምላክ አላዋቂ አርገውት አረፉ።           አሜን ጌታ ኢየሱስ ሆይ ና !             ✍ በዘአትናቴዎስ የተጻፋ [https://t.me/ZeathanAmharic]
348
15
ጥያቄ መጠየቁ ኢየሱስ ክርስቶስን/ሎቱ ስብሐት/ አላዋቂ ያሰኘዋልን ? (ክፍል 3)         ለ. "የዳሰሰኝ ማን ነው ?" (ሉቃ 8:45)         ለስም አጠራሩ ክብሩ ምሥጋና ይግባውና ጌታችንና መድኋኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከጌርጌሴኖን ወደ ገሊላ በተመለሰ ጊዜ "ሁሉ ይጠብቁት ነበርና ሕዝቡ ተቀበሉት።" (ሉቃ 8:40)        በዚያን ሰዓትም ኢያኢሮስ የሚባል የምኩራብ አለቃ የነበረ ሰው ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ መጣ ፤ ከእግሩም ላይ ወድቆ አስራ ሁለት ዓመት የሞላት ብቸኛ ሴት ልጁ ለሞት እስክትቀርብ ድረስ ታማለችና ወደ ቤቱ ገብቶ ይፈውሳት ዘንድ ለመነው። የለመኑትን ማይነሳ፣ የጠየቁትን የማይረሳ ፈጣሬ ኩሉ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስም ከምኩራብ አለቃው ጋር ወደ ቤቱ ይሄድ ዘንድ ተነሣ "ሲሄድም ሕዝቡ ያጨናንቁት ነበር።"(ሉቃ 8:42)      አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱን አስከትሎ ከኢያኢሮስ ጋር ወደ እርሱ ቤት እየሄደ ሳለ ፣ አስራ ሁለት ዓመት ሙሉ ደም ሲፈሳት የነበረች ፣ ባለመድኋኒቶች ጋር ሄዳ ልትፈወስ ያልቻለች አንዲት ሴት "በልብዋ፦ ልብሱን ብቻ የዳሰስሁ እንደ ሆነ፥ እድናለሁ”(ማቴ 9፥21) እያለች መጣች። "በኋላውም ቀርባ የልብሱን ጫፍ ዳሰሰች የደምዋም ፈሳሽ ... ቆመ።"(ሉቃ 8:44) በዚያን ጊዜ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "ማን ነው የዳሰሰኝ ?" ሲል ጠየቀ።     አስተውሉ ! እንግዲህ መፍቀሬ ሰብእ ኢየሱስ ክርስቶስ የዳሰሰው ማን እንደሆነ መጠየቁን ተመልክተው ነው አንዳንዶች የዳሰሰው ማን እንደሆነ አያውቅም ብለው የደመደሙት ፤ ነገር ግን ድምዳሜያቸው አውዱን ያላገናዘበ ነው። ምክንያቱም የመጽሐፍ ቅዱስን ቃል ለመረዳት አውዱን ግምት ውስጥ ማስገብት ተገቢ ነውና።        ለምሳሌ እግዚአብሔር አምላክ ለነቢዩ ኢሳይያስ በረጅምና ከፍ ባለ ዙፋን ላይ ሆኖ ፣ የልብሱም ዘርፍ መቅደሱን ሞልቶት ፣ ሱራፌልም ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እያሉ እያመሰገኑት በተገለጠለት ጊዜ "ማንን እልካለሁ? ማንስ ይሄድልናል?"(ኢሳ6፥8) ሲል ተናግሮአል። ታዲያ ይህ ይዘን እግዚአብሔር ማንን እንደሚልክ አያውቅም እንላለን? በፍጹም ! ይልቁንም አውዱን ተመልክተን እግዚአብሔር ኢሳይያስን ለተልእኮ ያዘጋጀውና ፍቃደኛ ያደርገው ዘንድ "ማንን እልካለሁ? ማንስ ይሄድልናል?" እንዳለ እንረዳለን እንጂ።      በተመሳሳይ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "የዳሰሰኝ ማን ነው?" ብሎ ሲጠይቅ ብንመለከት ፣ "የጅብ ችኩል ቀንድ ይነክሳል" እንደሚባለው ቸኩለን ማን እንደዳሰሰው አያውቅም በማለት ስህተት ውስጥ ከምንገባ አውዱን አመዛዝነን ስለምን ይህን መሰሉን ጥያቄ ተናገረ ሚለውን መገንዘብ ይበጃል።      በሙሴ ሕግ መሰረት አንዲት ደም የሚፈሳት ሴት ንጽሑ አይደለችም ተብሎ ይታመናል ፤ በዚህም ከማንም ሰው ጋር አካላዊ ንክኪ እንድታደርግ አይፈቀድላትም ነበር (ዘሌ15:25-30)። ይህም ጌታችን ከህመሟ የፈወሳት ሴት ለአስራ ሁለት አመት ያህል ከሰው ርቃና ተገ'ላ እንዲሁም ከአካላዊ ንክኪ ተቆጥባ እንደኖረች ያመለክታል ፤ ለዚህም ነው ከኋላው ሆና ፣ ራሷን ደብቃ ክርስቶስን መንካቷ።        ታዲያ እቺ ሴት ለብዙ ዓመታት በማኅበረሰቡ ተገ'ላ ስትኖር ከሥጋ ሕመሟ በተጨማሪ ምን ያህል ሥነ ልቦናዋ ሊጎዳ ፣ ልቧ ሊቆስል እንደሚችል መገመት አያዳግትም። በዚህም "የዳሰሰኝ ማን ነው?" የሚለው የጌታችን ጥያቄ በመለኮታዊ ሥልጣኑ የሥጋ ህመሟን እንደፈወሰላት ሁሉ በቃሉ ደግሞ የልቧን ቁስል ይፈውስላት ዘንድ የቀረበ ነው።       ሊቁ "ተአምሩ ተደብቆ አልቀረም ፤ መድኃኒታችን ሁሉን ቢያውቅም እንኳ እንደማያውቅ ሆኖ 'የዳሰሰኝ ማን ነው?' ሲል ጠይቋልና።"[8] እንዳለ ፣ ለስም አጠራሩ ክብር ምሥጋና ይግባውና ኢየሱስ ክርስቶስ ማን እንደዳሰሰው የጠየቅበት ምክንያት ለአስራ ሁለት ዓመት ደም ሲፈሳት የነበረችው ሴት ተደብቃ የልብሱን ጫፍ እንድትነካ ያደረጋትን ሐፍረት እና ፍርሐት አሸንፋ የተደረገላትን ነገር ከሰው ሁሉ ፊት እንድትመሰክር ነው።       ለዚህም ነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማን እንደዳሰሰው በጠየቀ "ጊዜ፥ ጴጥሮስና ከእርሱ ጋር የነበሩት፦ አቤቱ፥ ሕዝቡ ያጫንቁሃልና ያጋፉህማል፤ የዳሰሰኝ ማን ነው ትላለህን?" እንዳሉት ፣ ጌታም "አንድ ሰው ዳስሶኛል፥ ኃይል ከእኔ እንደ ወጣ እኔ አውቃለሁና" ብሎ እንደ መለሰላቸው በወንጌል ተጽፎ የምናነበው ፤ ይኸውም ሴቲቱ መጥታ ትመሰክር ዘንድ ነው - "ሴቲቱም እንዳልተሰወረች ባየች ጊዜ እየተንቀጠቀጠች መጥታ በፊቱ ተደፋች፥ በምን ምክንያትም እንደ ዳሰሰችው ፈጥናም እንደ ተፈወሰች በሕዝቡ ሁሉ ፊት አወራች።"(ሉቃ 8:45-47) ብሎ ቅዱስ ሉቃስ በወንጌሉ እንደ ጻፈ።         ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ የማቴዎስ ወንጌልን በተረጎመበት ድርሳኑ ኢየሱስ ክርስቶስ "የዳሰሰኝ ማን ነው?" የሚል ጥያቄ የጠየቀው ስለ ሦስት ምክንያቶች እንደሆነ አብራሮቶ አስተምሯል ፤ እንዲህ በማለት :-      "ስለምን ወደ ፊት አመጣት ? በመጀመሪያ የሴቲቱን ፍርሐት ያርቅላት ዘንድ ነው። ... ሁለተኛው ደግሞ ልትደበቅ እንደማትችል ሲያሳያት ነው። ሦስተኛ ሌሎች እንደ እርሷ እምነት እንዲኖራቸው የእርሷን እምነት አሳያቸው ፤ ... እንዲሁም እምነቱ ሊሸረሸር እና ተስፋውን ሊያጣ የነበረውን የምኩራብ አለቃ በሴቲቱ አጸናው። እነዚያ የመጡት 'መምህሩን አታድክመው ልጅህ ሞታለች' ብለውታልና በቤትም ውስጥ የነበሩት 'ተኝታለች' ባላቸው ጊዜ ስቀዋልና የልጅቱ አባት ተመሳሳይ ሐሳብ አድሮበት ይሆናል። በዚህም ከፊቱ ያለውን ድክመት ያርቅለት ዘንድ ሴቲቱን ወደ ፊት አመጣት።"[9] ይቀጥላል...                   አሜን ጌታ ኢየሱስ ሆይ ና !               ✍ በዘአትናቴዎስ የተጻፈ [https://t.me/ZeathanAmharic] 🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱 8).Commentary On The Gospel Of Luke By St.Cyril Of Alexandria 9).Commentary On The Gospel Of Matthew By St.John Chrysostom
272
16
     ጥያቄ መጠየቁ ኢየሱስ ክርስቶስን /ሎቱ ስብሐት/ አላዋቂ ያሰኘዋልን ? (ክፍል 2)      ምናልባት ከላይ ያሰፈረነው ማብራሪያ ግልጽ ካልሆነላችሁ ጌታችንና መድኋኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትምህርቱን የሚሰሙትን ፣ ከተዓምራቱ የሚካፈሉትን ሰዎች ጥያቄ ሲጠይቃቸው የማያውቀውን ነገር ለማወቅ ሳይሆን ሊያስተምር በፈለገው ትምህርት አውድ ፣ ባደረገውና ሊያደርገው ባለው ተዓምር ምንነት መሰረት ለተለያዩ ምክንያቶች መሆኑን ትገነዘቡ ዘንድ በብዛት በአሕዛብ ከሚነሱ መሰል ጥያቄዎች ሁለቱን አንስተን እንመልከት።        ሀ. "ወዴት አኖራችሁት ?" (ዮሐ 11:34)       ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነቱን ገልጦ በመናገሩ አይሁድ ሊገሉት ሽተው ነበርና ከዮርዳኖስ ወንዝ ማዶ ተሻገረ ፤ በዚያም በነበረበት ጊዜ በቢታንያ የሚኖረው የማርያምና የማርታ ወንድም አልዓዛር ታመመ ፤ "ስለዚህ እኅቶቹ ጌታ ሆይ የምትወደው ታሞአል ብለው ወደ እርሱ ላኩ " (ዮሐ 11:2)።      መልእክቱ የደረሰው መፍቀሬ ሰብእ ኢየሱስ ክርስቶስም የአልዓዛር ህመም ለእግዚአብሔር ልጅ ክብር እንጂ ለጥፋት እንዳማይሆን ያውቃልና በነበረበት ስፍራ ለሁለት ቀን ያህል ቆየ ። ከዚያም "ወደ ይሁዳ እንሂድ" ብሎ ለደቀ መዛሙርቱ ነገራቸው ። እነርሱ ግን ከጥቂት ቀናት በፊት አይሁድ ሊገሉት ይፈልጉ እንደነበር በማስታወስ ላለመሄድ አንገራገሩ።       ጌታም የጉዞውን ምክንያት ለዘብ ባለ አነጋገር [4] "ወዳጃችን አልዓዛር ተኝቷል ነገር ግን ከእንቅልፋ ላስነሳው እሄዳለሁ" በማለት አልዓዛርን ከሞት ሊያስነሳው እንደሚሄድ ገለጸላቸው ፤ ሆኖም ደቀ መዛሙርቱ የኢየሱስ ክርስቶስን ቃል አልተረዱትም ነበር ። አልዓዛር መደበኛ እንቅልፍ የተኛ መስሏቸው "ጌታ ሆይ ተኝቶ እንደሆነ ይድናል አሉት። ... እንግዲህ ያንጊዜ ኢየሱስ በግልጥ አልዓዛር ሞተ እንድታምኑም በዚያ ባለመኖረ ስለ እናንተ ደስ ይለኛል ነገር ግን ወደ እርሱ እንሂድ አላቸው ።" (ዮሐ 11:12-14)       አስራ አምስት ምዕራፍ ያህል ለኢየሩሳሌም ወደ ምትቀርበው ቢታንያ በተቃረበ ሰዓት ፣ ማርታ የኢየሱስ ክርስቶስን መምጣት ሰምታ ልትቀበለው ወጣች ። ባገኘችውም ጊዜ "ጌታ ሆይ አንተ በዚህ ኖረህ ብትሆን ወንድሜ ባልሞተም ነበር " ስትል ወቀሳ ያዘለ ቃል ተናገረችው ። ጌታችንም "ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳን ሕያው ይሆናል ሕያው የሆነ የሚያምንብኝም ሁሉ ለዘላለም አይሞትም  ይህን ታምኚያለሽ ? " (ዮሐ 11:25-26) በማለት እርሱ " የሞትና የሲዓል መክፈቻ"(ራዕ 1:18) ያለው መሆኑን ገለጸላት ፣ ይህንንም እንደምታምን በጠያቃት ጊዜ  የእርስዋ መልስ አዎንታዊ ነበር።      ማርታም ከለቀስተኞች ጋር የነበረችው እኅቷን በስውር መምህሩ እንደመጣ ነግራ ጠራቻት ፤ ማርያምም ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፈጥና መጣች ፣ እያለቀሰችም ከእግሩ ሥር ወደቀች ። ጉንጮቿን በእንባ እያጠበች እንደ እኅቷ "ጌታ ሆይ አንተ በዚህ ኖረህ ብትሆን ወንድሜ ባልሞተም ነበር አለችው። ኢየሱስም እርስዋ ስታለቅስ ከእርስዋም ጋር የመጡት አይሁድ ሲያለቅሱ አይቶ በመንፈሱ አዘነ በራሱም ታወከ " እንባውንም አፈሰሰ። "ወዴት አኖራችሁት?" በማለትም አልዓዛርን የቀበሩበትን ቦታ ጠየቃቸው።      አስተውሉ ! እንግዲህ አልዓዛር የት እንደተቀበረ መጠየቁ ነው ኢየሱስ ክርስቶስ /ሎቱ ስብሐት/ የዕውቀት ተከፍሎ አለበት እንዲሉ ያደረጋቸው ፤ ነገር ግን ሊቁ "ጥያቄ መጠየቁ ስለእኛ እንደ እኛ የሆነ የእርሱን አላዋቂነት አያሳይም"[5] እንዳለ ፣ ክርስቶስ  የአልዓዛር የመቃብር ስፍራ የት እንደሆነ መጠየቁ አልዓዛር የት እንደተቀበረ አያውቅም የሚል ድምዳሜ ላይ አያደርሰንም።       ለምሳሌ ነነዌ እንደ ትንቢቱ ቃል ባለመጥፋቷ የተቆጣው ዮናስን እግዚአብሔር "በውኑ ትቆጣ ዘንድ ይገባልን?"(ዮናስ 4:4) ሲል ጠይቆታል ፤ ሆኖም ይህን ተመልክተን እግዚአብሔር አምላክ ዮናስ ስለምን እንደተቆጣ አያውቅም አንልም ። ይልቁንም አውዱን ተመልክተን ዮናስ ራሱን እንዲመለከትና የቆመበትን እንዲመረምር ሲል የጠየቀው ነው ብለን እንረዳዋለን እንጂ።       ቅዱስ ቄርሎስ ኢየሱስ ክርስቶስ "ወዴት አኖራችሁት ?" ብሎ መጠየቁን ተመርኩዘው ሁሉን አዋቂ አይደለም ሊሉት ለሚቃጣቸው "የአልዓዛርን መሞት በሌላ ሀገር ሆኖ ያወቀ እርሱ እንዴት የመቃብሩን ስፍራ ላያውቅ ይችላል ?" በማለት ይሞግታል ። አክሎም ጌታችን አልዓዛር የት እንደተቀበረ የጠየቀበትን ምክንያት እንዲህ በማለት አብራርቶ ገልጾታል :-     "ደግሞም እንደዚህ በማለቱ ብዙዎችን ከእርሱ ቀድመው እንዲሄዱ አዘጋጃቸው ሊያደርግ የፈለገውን ነገር ያሳያቸው ዘንድ። ... በዚህም ጥያቄው ብዙዎች ወደ መገለጡ ይሰበሰቡ ዘንድ እንዲሁም ቀድሞ በስብሶ የነበረው ወደ ሕይወት የመመለሱን ዜና ከሌሎች ይልቅ ጠላቶቹ ራሳቸው ይመሰክሩ ዘንድ ነው።"[6]      ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም ከቅዱስ ቄርሎስ ትርጓሜ ጋር በሚስማማ መልኩ ክርስቶስ የአልዓዛርን የመቃብር ስፍራ የመጠየቁ ምክንያት ልያደርገው ያለውን ተአምር ከጥርጣሬ ለማራቅ እንደሆነ ገልጿል[7]።  ይቀጥላል...                         አሜን ጌታ ኢየሱስ ሆይ ና !               ✍ በዘአትናቴዎስ የተጻፈ [https://t.me/ZeathanAmharic] 🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱 4). ለዘብ ባለ አነጋገር ስንል ለአድማጭ በማይጎረብጥ እና በማያስደነግጥ መልኩ ማለታችን ነው ፤ ይህ ዓይነቱ አነጋገር «ephumism» በመባል የሚታወቅ ሲሆን አስደንጋጭና ከባድ የሆኑ ክስተቶችን ቀለል ባለ መንገድ መግለጽን የሚያመለክት ነው። 5). St.Cyril commentary on The Gospel of John 6). Ibid 7). St.John Chrysostom Homily on The Gospel of John
240
17
በዚህም መፍቀሬ ሰብእ ኢየሱስ ክርስቶስ በሐዲስ ኪዳን በመዋዕለ ስብከቱ ጥያቄዎችን ሲጠይቅ የማያውቀው ነገር ኖሮ ያንን ለማወቅ ሳይሆን ትምህርቱን የሚከታተሉት ሰዎች ትምህርቱን እንዲገነዘቡ ፣ ሊከናውን ስላለውም ነገር ትኩረት እንዲያደርጉ እንዲሁም ለተለያዩ ምክንያቶች ነው ። ይህን እውነት ፍቁረ እግዚእ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ኢየሱስ ክርስቶስ ያደረገውን ተዓምር ተመልክተው ብዙዎች በተከተለቱ ጊዜ ፊልጶስን "እነዚህ እንዲበሉ እንጀራ ከወዴት እንገዛለን ?" ብሎ እንደጠየቀው ካሰፈረልን በኋላ የጌታችን ጥያቄ ከአላወቂነት የመነጨ እንዳልሆነ ሲያስረዳንን "ራሱ ሊያደርገው ያለውን ያውቅ ነበርና ሊፈትነው ይህን ተናገረ። "(ዮሐ 6:5-6) ብሎ መጻፋ ፍንትው አድርጎ ያሳያል። ይቀጥላል....             አሜን ጌታ ኢየሱስ ሆይ ና !               ✍ በዘአትናቴዎስ የተጻፈ [https://t.me/ZeathanAmharic] 🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱 1). ገድለ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ እና ገድለ አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ፣ ገጽ.64-67 2). ድርብ መለኪያ (Double Standard) ማለት (ሥነ አመክንዮአዊ ሕጸጽ) ሲሆን አንድን መርሕ ለሁለት አካላት በተለያየ መልኩ መጠቀም ማለት ነው ። 3).Against The Arians , 3:27;37
260
18
ጥያቄ መጠየቁ ኢየሱስ ክርስቶስን /ሎቱ ስብሐት/ አላዋቂ ያሰኘዋልን ? (ክፍል 1)     በአንድ ወቅት በአፄ ዳዊት ዘመነ መንግሥት አንድ አይሁዳዊ ሰው በቤተ ክርስቲያን ምእመናን ላይ ተነሣ፡፡ " ኑ በመጻሕፍት ቃል እንከራከር ፤ ከረታችሁኝ ወደ ሃይማኖታችሁ  አስገቡኝ ፤ ከረታኋችሁም ወደ  ሃይማኖቴ ትገባላችሁ " በማለትም የእንሟገት ጥሪ አቀረበ።       የአይሁዳዊው ነገር ከጆሮው የደረሰው  ንጉሥ ዳዊትም የካህናት አለቆችን ፣ ንቡራነ እድን እንዲሁም በአገሩ ያሉ የመጻሕፍት አዋቂዎችን ሁሉ በመሰብሰብ ከአይሁዳዊው ጋር ይሟገቱ ዘንድ ቀን ቆረጠ ፤ በተቆረጠውም ቀን ንጉሡ ባለበት አይሁዳዊው በአንድ ጎን ማኅበረ ካህናቱ ደግሞ በሌላኛው ጎን ቆሙ ፣ ሊደረግ ላለውም ተዋሥኦ ተሰናዱ።      ንጉሡም ሁሉም ቦታ ቦታውን እንደያዘ ፣ ተሟጓቾች ለመሞገት ሕዝበ ክርስቲያኑም ለማዳመጥ ዝግጁ እንደሆነ ካስተዋለ በኋላ አይሁዳዊው እንዲጀምር ያለውንም ጥያቄ እንዲያቀርብ ትዕዛዝ ሰጠ ፤ አይሁዳዊውም የተሰጠውን ትእዛዝ ተከትሎ እንዲህ ሲል ጥያቄውን አቀረበ ፤      "እናንተ  የእግዚአብሔር ልጅ ነው የምትሉት ክርስቶስ እውን የእግዚአብሔር ልጅ ቢሆን ኖሮ አልአዛር የተቀበረበትን ቦታ ባወቀ ነበር ፣ ወንጌላችሁ ' ኢየሱስ ቢታንያ  በደረሰ ጊዜ አልዓዛርን ወደት  ቀበራችሁት አለ ' ይላልና፡፡ እግዚአብሔር ግን የሚሰወረው ሥራ የለም ፣ ሁሉ በዐይኖቹ ፊት የተገለጠ ነውና ። እነሆ እኔ በኦሪት ያይደለ በወንጌላችሁ ክፍል ነገርኋችሁ ፤ በሉ መልሱልኝ ፡፡"      ንጉሡም የአይሁዳዊውን ጥያቄ በአንክሮ ካደመጠ በኋላ ለቀረበው ጥያቄ ምላሽ እንዲሰጡ በዚያ ለተሰበሰቡት የቤተ ክርስትያን ሊቃውንት ነገራቸው ፤ ሆኖም ማኅበረ ካህናቱ ለጥያቄ ምላሽ መስጠት አልተቻላቸውም ነበር። ይህን ያስተዋሉት የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችም በዘመኑ የነበሩትን መናፍቃን በመከራከርና አስተምሮ በመርታታቸው ‹ኢትዮጵያዊው ቄርሎስ› የሚል ስም የተሰጣቸውን አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ለቀረበው ጥያቄ ምላሽ ይሰጡ ዘንድ ከመሐከላቸው ፈለጓቸው ፤ ነገር ግን ሊያገኟቸው አልቻሉም - አባ ጊዮርጊስ ታመው ከቤታቸው ቀርተው ነበርና።     ሊቃነ ካህናቱ በአንድ ላይ ሆነው ስለ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ለንጉሡ ነገሩት ፣ ከእርሳቸውም በቀር ማንም ይህን ጥያቄ ሊመልስ እንደማይችል አሳሰቡት ፤ ንጉሡም ያመጧቸው ዘንድ የቤተ መንግሥቱን ሹማምንት ወደ አባ ጊዮርጊስ ቤት ላከ ፡፡ የቤተ መንግሥቱም ሹማማንት በአልጋ ተሸክመው አወጧቸው ፣ አምጥተውም በመካከላቸው አስተኟቸው።      አባ ጊዮርጊስም የአይሁዳዊውን  ቃል ሰምተው ከጨረሱ በኋላ እንዲህ ሲሉ አስደናቂ ምላሽን ሰጡ ፤     " እኔም በእኔ ወንጌል አልከራከርህም ፤  በአንተ ኦሪት ነው እንጂ ። ' ትንቢት ለምኲራብ ሃይማኖት ለቤተ ክርስቲያን ነውና ምኲራብ ዘርን ዘራች ቤተ ክርስቲያን ምርቱን ሰበሰበች  ምኲራብ ግምጃን  ሠራች ቤተ ክርስቲያን ለበሰችው ' ። (ሃይ.አበው. ምዕ 66. ቁጥ 21)      አይሁዳዊ ሆይ እስቲ በል መልስልኝ  አዳምን በገነት  ' ወዴት ነህ ? '(ዘፍ 3:9) ፣ አብርሃምንም ' ሚስትህ ሣራ ወዴት  ናት? '(ዘፍ 18:9) ያለው ማን ነው?  ሰይጣንንስ ' ከወዴት መጣህ? '(ኢዮብ 1:7) ያለው  ማን ነው? በሌላም የመጽሐፍ ክፍል ' አክአብን ማን ያስትልኛል ? ' ይላል፡፡ እግዚአብሔር ነው ትላለህ? ወይስ ሌላ ? "      አይሁዳዊው የአባ ጊዮርጊስን ሙግት ማፍረሰው አቃተው ፣ በዚህም ራሱን ከፍ ከፍ ባደረገባቸው እንሟገት ብሎ በተነሣሣባቸው ምዕመናን ፊት ምላሽ አጥቶ የሽንፍት ካባን ተከናነበ።[1]      በእርግጥ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጭ ለተጠየቀው ጥያቄ ሰፋ ያለ ማብራሪያ አልሰጡም ፣ ነገር ግን በምላሻቸው " እሾህን በእሾህ ... " እንደሚባለው ፣ በአይሁዳዊው ጥያቄ ውስጥ ያለውን ድርብ መለኪያ (Double standard) [2] በማመላከት ፣ " በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር አዳም ወዴት እንዳለ መጠየቁ አዳም የት እንዳለ አያውቅም ካላስባለው ፣ አንዲያ የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው ፈጣሬ ኩሉ ዓለማት ኢየሱስ ክርስቶስም አልዓዛር የት እንደተቀበረ መጠየቁ አልዓዛር የት እንደተቀበረ አያውቅም ሊያስብለው አይችልም ። " የሚል መከራከሪያ አቅርበዋል።      በእውነቱ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ የሰጡት ምላሽ ከበቂ በላይ ቢሆንም በዘመናችን የሚገኙ አሕዛብ እንዲሁም የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት ሚክዱ መናፍቃን መድኃኔዓለም አልዓዛርን "ወዴት አኖራችሁት ?" (ዮሐ 11:34) ብሎ መናገሩን እንዲሁም አስራ ሁለት ዓመት ሙሉ ደም ሲፈሳት የነበረችው ሴት የልብሱን ጫፍ ነክታ በተፈወሰች ጊዜ " የዳሰሰኝ ማን ነው ?" (ሉቃ 8:44-48) ብሎ መጠየቁን በማንሳት ሁሉን አዋቂነቱን ለመካድ ይዳዳቸዋልና በዚህ ዙሪያ ጥቂት እንበል።      ኢየሱስ ክርስቶስ መልካም መምህር ነው ፤ እንደ መልካም መምህርነቱም ሚያስተምረው ትምህርት ለመረዳት ቀለል ያለ ይሆን ዘንድ ጥያቄ ይጠይቃል ። ጥያቄ ሲጠይቅም የማያውቀን ነገር ለማወቅ ወይንም ያልተረዳው ነገር ኖሮ ለመገንዘብ ሳይሆን ሰማዒው በትኩረት እንዲያደምጥ እና ጥልቅ መረዳትን እንዲይዝ ሲል ነው።        ለምሳሌ አንድ የሒሳብ መምህር ስለ መሰረታዊ የሒሳብ ቀመር ሲያስተምር ተማሪዎችን " 2+2 ስንት ነው ? " ብሎ ሊጠይቃቸው ይችላል ። ይህ ማለት ግን መምህሩ የጥያቄውን መልስ አያውቀውም ማለት አይደለም ፣ በተቃራኒው መምህሩ የጥያቄውን መልስ ቢያውቀውም "2+2 ስንት ነው ? "ብሎ ተማሪዎችን መጠየቁ ትምህርቱ ላይ ትኩረት ያደርጉ ዘንድ እንዲሁም ስለ መሰረታዊ የሒሳብ ቀመር ከፍ ያለ መረዳት ይኖራቸው ዘንድ ነው።                 በተመሳሳይ ቅዱስ አትናቴዎስ "አንድ ሰው ሚጠይቀው ስለማያውቅ ብቻ አይደለምና ፣ ነገር ግን ዕውቀቱ ያለው ሰው ስለ ሚያውቀው ነገር ሊጠይቅ ይችላል ።" [3] እንዳለ ፣ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ስብከቱ ጥያቄዎችን ሚጠይቀው /ሎቱ ስብሐት/ የዕውቀት ገድብ ኖሮበት ሳይሆን ደቀ መዛሙርቱ እንዲሁም ከእርሱ ዘንድ ትምህርት የሚማሩ ሰዎች ጥልቅ መረዳት እንዲኖራቸው ፣ እምነታቸውንም እንዲመሰከሩ እንዲሁም ጥያቄው በቀረበበት ሁኔታና በተጠየቀው ሰው ማንነት መሰረት ለተለያየ ዓላማ ነው።       ለአብነትም ደቀ መዛሙርቱን " ሰዎች እኔ ማን እንደ ሆንሁ ይላሉ ? " (ማር 8:27) ብሎ መጠየቁ ቀጥሎ ለሚነግራቸው ነገር ሲያዘጋጃቸው ነው ፣ ሊፈትነው ለመጣው ሕግ አዋቂ "በሕግ የተጻፈው ምንድር ነው ? እንዴት ታነባለህ ?" (ሉቃስ 10:26) የሚል ጥያቄ ማቅረቡ ለሚናገረው ነገር ትኩረት ያደርግ ዘንድ ነበር ። በተጨማሪም የካህናት አለቆችና ጻፎችን " ግንበኞች የናቁት ድንጋይ እርሱ የማዕዘን ራስ ሆነ ተብሎ የተጻፈው ይህ ምንድር ነው ? " (ሉቃ 20:17) ብሎ ሲጠይቃቸው ጥልቅ ወደ ሆነ መረዳት ያሻግራቸው ዘንድ አስቦ ነው ።
233
19
"   ... በመጠቅለያ ተጠቅልሎ ነበር ፤ በትንሣኤው ግን የመቃብርን በፍታ አንስቷል።     በግርግምም ተኝቶ ነበር ፤ ሆኖም በመላእክት ከፍ ከፍ ተደርጎ ፣ በኮከብ ታውጆ ፣ በሰብአ ሰገልም ተሰግዶለታል ።    ... ወደ ግብጽ ተሰዷል ፤ የግብጽን ጣዖታት ግን አጥፍቷል ።      በአይሁዳውያን ዓይን መልክ እና ውበት አልነበረውም ፤ ለዳዊት ግን ከሰው ሁሉ በላይ ውብ ነው ፣ በተራራ ላይም እንደ መብራቅ አብርቶ ከፀሐይም በላይ አንጸባርቋል ፤ በዚህም ለሚመጣው ምሥጢር አነሳስቶናል ።     ሰው እንደመሆኑ ተጠምቋል ፤ ሆኖም አምላክም ነውና ኃጢአትን አስወግዷል - እርሱ መንጻት አስፈልጎት አይደለም ውሃን ይቀድስ ዘንድ ነው እንጂ ።     ሰው እንደመሆኑ ተፈትኗል ፤ ነገር ግን አምላክም ነውና ድል ነስቷል - በእውነቱ አይዟችሁ ይለናል እርሱ ዓለምን አሸንፏልና ።     ተርቧል ፤ ሺህዎችን ግን መግቧል - በእርግጥም እርሱ ከሰማይ የወረደ የሕይወት እንጀራ ነው ።         ተጠምቷልም ፤ ሆኖም ' ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ ' ሲል ተናግሯል - አዎ ከአመኑት ሆድ የሕይወት ውሃ ወንዝ እንደሚፈልቅ ቃል ገብቷል ።      ደክሞትም ነበር ፤ እርሱ ግን ለደከማቸውና ሸክም ለከበዳቸው እረፍት ነው ።     ተኝቷል ፤ ነገር ግን በባሕር ላይ ተራምዷል - በእውነቱ ነፋሱን ገስፆ ጴጥሮስን መስመጥ በጀመረ ጊዜ አድኖታል ።      ግብር ከፍሏል ፤ ሆኖም ከአሳ ውስጥ ነው - አዎ እርሱ ለሚሹት ንጉሳቸው ነውና።       ሳምራዊ የሆነ ጋኔንም ያለበት ተብሎ ተጠርቷል ፤ እርሱ ግን ከኢያሪኮ ወደ ኢየሩሳሌም ሲወርድ በወንበዴዎች እጅ የወደቀውን አድኖታል ፣ አጋንንትም መስክረውለታል ፣ እርሱም አጋንንትን አውጥቷቸዋል ። ሌጌዎን የተባለ ርኩስ መንፈስንም ባሕር ውስጥ አስጥሟል ፣ የአጋንንትም አለቃ እንደ መብረቅ ከሰማይ ሲወድቅ አይቷል ።     ሰዎች ሊወግሩት ድንጋይ አንስተውበታል፤ እርሱ ግን ተሰወረባቸው ።     ጸልዮ ነበር  ፤ እርሱ ግን ጸሎትን ይሰማል ።     አልቅሷል ፤ እርሱ ግን እንባን ያብሳል ።     ሰው ነውና አልዓዛርን የት እንደ ቀበሩት ጠይቋል ፤ ነገር ግን አምላክም ነውና አልዓዛርን ከሞት አንስቶታል ።     በጣም በርካሽ ዋጋ ልያውም በሠላሳ ብር ብቻ ተሽጧል ፤ እርሱ ግን በጣም ውድ በሆነ በደሙ ዋጋ ዓለምን ተቤዥቷል ።       እንደ በግ በሸላቾቹ ፊት ተነድቷል ፤ እርሱ ግን  የእስራኤል ብሎም የዓለም ሁሉ እረኛ ነው።         እንደ በግ ዝም ብሏል ፤ እርሱ ግን በምድረ በዳ በሚጮኽ ሰው ድምፅ የታወጀ ቃል ነው ።      ቆስሏል ደቋልም ፤ እርሱ ግን ሁሉንም ደዌና ህመም ፈውሷል ።      በእንጨት ላይ ተሰቅሎ ተቸንክሯል ፤ እርሱ ግን በህይወት ዛፍ እኛ አድሶናል ፣ አብሮት የተሰቀለውን ወንበዴ እንኳን አድኖታል ፣ የሚታየውንም ዓለም በጨላማ ጠቅልሎታል።      ሆምጣጤ እና ሀሞት ይጠጣ ዘንድ ሰጥተውታል ፤ ማንን ? ውሃን ወደ ወይን የቀየረውን ፣ መራራውን ያሸነፈውን እንዲሁም እጅግ ጣፋጭ እና ፈጽሞ ያመረ የሆነው እርሱን ።     ነፍሱን አኑሯታል ፤ ነገር ግን ሊያነሳትም ሥልጣን አለው ። የቤተ መቅደሱ መጋረጃ ተቀዶ የገነት በሮች ተከፍተዋልና ፣ ዓለቶች ተሰነጣጥቀው ሙታን ተነሥተዋልና ።     ሞቶ ነበር ፤ እርሱ ግን ሕይወትን ይሰጣል ፣ በሞቱም ሞትን ሽሯል ።     ተቀብሮም ነበር ፤ ግን ደግሞ ተነሥቷልም።     ሙታን ካሉበት ስፍራም ወርዷል ፤ ነገር ግን ነፍሳትን ይዞ ወጥቷል ። ወደ ሰማይም ዐርጓል ዳግመኛም በሕያዋን እና ሙታን ላይ ይፈርድ ዘንድ ይመጣል ... " [13]       አሜን ጌታ ኢየሱስ ሆይ ና !        ✍ በዘአትናቴዎስ የተጻፈ 🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱 1).https://jamesclear.com/great-speeches/the-danger-of-a-single-story-by-chimamanda-ngozi-adichie 2).Gregory of Nazianzus on The Trinity and The Knowledge of God by Christopher A.Beeley , pp.122 3).Commentary on The Epistle of Hebrew by St.john Chrysostom 4).ተንከተም በሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ ፣ ገጽ . 193 5).Against The Arians 3:29 6).ሃይማኖተ አበው 78:26 7).Oration 29:19 8).Ibid 9).Commentary on The Gospel of Matthew by S.t John Chrysostom 10).The case for Jesus Christ by Brant Pitre , pp.118 11).The Jewish Annotated New Testament by Amy-Jill Levine and Marc Zvi Brettler , pp.16,69 12).Commentary On The Gospel of St.Matthew by st.john Chrysostom 13). Oration 29:19-21
210
20
ዳግመኛም በወንጌል ተጽፎ እንደምናነበው ጌታችንና መድኋኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በታንኳ ላይ ሆኖ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር  በገሊላ ባሕር እየተጓዘ ነበር ፤ በጉዞውም ወቅት ጌታችን ተኝቶ ነበር ፣ ጥቅት ቆይቶም ታንኳይቱ በዓውሎ ነፍስ መናጥ ጀመረች ፣ ውሃም ወደ ታንኳይቱ ይገባ ነበር ። በዚህ የተደናገጡት እና የተጨነቁት ሐዋሪያት መምህራቸውን " አቤቱ አቤቱ ጠፋን አድነን " እያሉ ቀሰቀሱት ። እርሱም ተነሥቶ ደቀ መዛሙርቱን ስለ እምነታቸው ጉድለት ከወቀሣቸው በኋላ ነፋሱን እና ባሕሩን ገሰፀ ታላቅ ጸጥታም በባሕሩ ላይ ሰፈነ ፤ " ሰዎቹም :- ነፋሳትና ባሕርስ ስንኳ የሚታዘዙለት ይህ እንዴት ያለ ሰው ነው ? እያሉ ተደነቁ " (ማር4:35-41 ፣ ማቴ 8:23-27 ፣ ሉቃ 8:22-25) ።       እዚህ ጋር አንድ ሰው የክርስቶስን በታንኳ ውስጥ ሳለ መተኛት አንስቶ "ኢየሱስ ክርስቶስ ስለተኛ አምላክ ሊሆን አይችልም ፤ አምላክ አይተኛም አይንቀላፋምና " በማለት ሊናገር ይችላል ። ሆኖም ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ " መተኛቱና አፍአዊ ገጽታው ሰው መሆኑን ቢያሳይም ፣ ባሕሩና ጸጥታው ግን አምላክነቱን ይገልጻል ። "[9] ብሎ እንደተናገረ ወንጌላውያኑ የጌታችንን መተኛት ብቻ ሳይሆን ማዕበሉንም መገሰጹን ጽፈውልናልና የሥግው ቃልን ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው መሆን ልንረዳ ይገባል።    ምናልባት እዚህ ጋር "የክርስቶስ መተኛቱና ማንቀላፋቱ ሰው መሆኑን ፣ ባሕርን መገሰጹ ደግሞ አምላክነቱን ያሳያል የምትለን ከሆነ በበትር የኤርትራን ባሕር ለሁለት የከፈለውም ሙሴ አምላክ ነው ማለት እንችላለን ? የክርስቶስ ተአምር ከሙሴ ተአምር በምን ይለያል ? " የሚል ጥያቄ አእምሮአችሁ ውስጥ ሊመጣ ይችላል ፤ በእርግጥ ተአምር መስራት ብቻ አምላክነትን አያሳይም ። ነገር ግን እዚህ ጋር ጌታ ያደረገው ተአምር ከመደበኛ ተአምር ከፍ ያለ ነው ፤ ግን እንዴት ?      ምን መሰላችሁ ? በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር በተደጋጋሚ ኃይሉን ከሚገልጽባቸው መንገዶች መሐከል ሁለቱን ታላላቅ ፍጥረታት " ነፋስና ባሕርን " እንደሚቆጣጠር በመግለጽ ነበር ፤ ጻዲቁ ኢዮብ "በኃይሉ ባሕርን ጸጥ ያደርጋል "(ኢዮብ 26:12) ማለቱ ለዚሁ ነው ።[10] ከዚህም በላይ በሚያስደንቅ መልኩ በመዝሙር 107 ላይ እግዚአብሔር ሕዝቡን ባሕርን በመገሰጽና ማዕበልን ጸጥ በማድረግ እንዲሚያድናቸው ተጽፎ እናገኛለን ፤ "በመርከቦች ወደ ባሕር የሚወርዱ፥ በታላቅ ውኃ ሥራቸውን የሚሠሩ፥ እነርሱ የእግዚአብሔርን ሥራ፥ በጥልቅም ያለችውን ድንቁን አዩ። ተናገረ፥ ዐውሎ ነፋስም ተነሣ፥ ሞገድም ከፍ ከፍ አለ። ወደ ሰማይ ይወጣሉ ወደ ጥልቅም ይወርዳሉ፤ ነፍሳቸውም በመከራ ቀለጠች። ደነገጡ እንደ ስካርም ተንገደገዱ፥ ጥበባቸውም ሁሉ ተዋጠች። በተጨነቁ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፥ ከመከራቸውም አዳናቸው። ዐውሎንም ጸጥ አደረገ፥ ሞገዱም ዝም አለ። ዝም ብሎአልና ደስ አላቸው፤ ወደ ፈለጉትም ወደብ መራቸው። " (መዝ 107:23-30)      ከላይ የሰፈረውን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል  በትኩረት ካነበባችሁት እግዚአብሔር በዚህ መዝሙር እንደ አደርገው የተጻፈው ነገር ጌታችን በታንኳ ላይ ሳለ ባሕርን በመገሰጽ ማዕበሉን ጸጥ በማድረግ ከፈጸመው ተግባር ጋር ፍጹም ተመሳሳይ ነው ፤ የታሪክ አውቃቀሩና አገላለጻቸውም አንድነት አላቸው ። ምክንያቱም መዝሙረኛው መርከበኞች በመርከብ ላይ እንደሆኑ እንደነገረን ሁሉ ወንጌልም ደቃ መዛሙርቱ በታንኳ ላይ እንደነበሩ ገልጾልናልና፣ በመርከቢቱ ላይ ከባድ አውሎ ነፋስና ሞገድ እንደተነሳ እንዲሁም መርከበኞቹ በፍርሃት ነፍሳቸው እንደ ቀለጠ እንደ ተጻፈ ሁሉ በታንኳይቱም ላይ በሆነው ከባድ ማዕበልና መናወጥ የተነሳ ሐዋሪያት በፍርሃት እንደራዱ ተቀምጦልናልና ።         እንዲሁም መርከበኞቹ በፍርሃት ወደ እግዚአብሔር ቢጮኹ አምላክ ማዕበሉን ጸጥ እንደ አደረገውና ዐዉሎ ነፋሱና ሞገዱም ዝም እንዳለ እንደተጻፈ ሁሉ በፍርሃት ውስጥ የነበሩት ሐዋሪያት ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቢጮኹ ጌታ ማዕበሉን ጸጥ እንዲል በማድረግ በባሕሩ ላይ ታላቅ ዝምታ አስፍኗል ፤ ታዲያ መዝሙረኛው ስለ እግዚአብሔር የተናገረውና በወንጌል ስለጌታችን የተጻፈው እንዲህ መመሳሳሉ ግጥምጥሞሽ ይሆንን ?  በፍጹም ![11]      ይልቁንም ወንጌላውያኑ ጌታ ኢየሱስ ያደረገው ተአምር መደበኛ ምልክት ሳይሆን እርሱ ራሱ እግዚአብሔር አምላክ እንደ መሆኑ በባሕርና ነፋስ ላይ ባለው ሥልጣን የከወነው እንደሆነ ሊያሳውቁን ወደው ነው እንጂ ። ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ የማቴዎስ ወንጌልን በተረጎመበት ድርሳኑ የጌታችን ተአምር እርሱ ከነቢዩ ሙሴ በላይ የሆነ አምላክ መሆኑን እንደሚያሳይ እንዲህ በማለት ገልጿል :-     " ይህም የእርሱን የበላይነት ያሳያል ፤ ሙሴ በአንድ ወቅት ተመሳሳይ ነገር አድርጓልና። አንደኛው ተአምራትን እንደ ባሪያ ሲያደርግ ሌላኛው ደግሞ እንደ ጌታ ይፈጽማልና ፤ በዚህም ሙሴ እንደ አደረገው በትሩን አልዘረጋም ፣ እጁንም ወደ ሰማይ አላነሳም ፣ ጸሎትም አላስፈለገውም ። ነገር ግን ጌታ ባሪያውን ፣ ፈጣሪ ፍጥረቱን እንደሚያዝ በቃሉና በትእዛዙ ብቻ ጸጥ አደረገው። " [12]        እንግዲህ በነጠላ ታሪካዊ አረዳድ ተመርኩዘን ወንጌልን ምናነብ ከሆነ ጌታ በሥጋው ያደረጋቸውን ነገሮች እያነሳን አምላክነቱን ለመካድ የሚቃጣን ሲሆን መጽሐፍ ቅዱስ መነበብ ባለበት መንገድ ካነበብን ግን በመተኛቱና በታንኳ ላይ በመጓዙ ፍጹም ሰው መሆኑን እንደተገነዘብነው ሁሉ ባሕርን በመገሰጹና ማዕበሉን ጸጥ በማድረጉ ደግሞ አምላክነቱን ተረድተን እንደ ሐዋርያት "ነፋስም ባሕርም የሚታዘዙለት ይህ ማን ነው ? "(ማር 5:41) በማለት መደነቅ እንጀምራለን ።        በመጨረሻም እጅግ ውብ በሆነው እና  ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ በተናገረው ቃል መጣጥፋችንን ከመቋጨታችን በፊት ከላይ በሰፊው የተወያየንበትን ጉዳይ ፍሬ ሃሳብ ላስታውሳችሁ ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ማለት ሰው የሆነ አምላክ ነው ፣ ሰው እንዳመሆኑ ያደረጋቸው ነገሮች በሙሉ (እንደ መብላት ፣ መተኛት ፣ መራብ ያሉትን ማለት ነው) ስለእኛ መዳን ሲል ያድረጋቸው ናቸውና እርሱ ለእኛ ያለውን ፍቅር የሚያሳዩ እንጂ አምላክነቱ የሚቃረኑ አይደሉም ። መብላቱ ፣ መተኛቱ ፣ መጠጣቱ ፍጹም ሰው መሆኑን እንደሚያሳይ ሁሉ ወደር የማይገኝላቸው ተአምራቱና ቃላቱ ደግሞ አምላክነቱን ያስረዳሉ ። ስለሆነም ጌታችን በሥጋው ያድረጋቸው ነገሮች አምላክነቱ የሚጋፋ አይደሉም ማለት ነው ።
169