en
Feedback
ዛ አንቀጽ

ዛ አንቀጽ

Open in Telegram

የክርስትና ልቡ የተሰቀለውን ክርስቶስን ተመልክቶ በተጠሩለት የቅድስና ጥሪ መጓዝ ነው የዚህም ቴሌግራም ቻናል ዓላማ ከፊት ለፊታችን የተሰቀለውን ቸሩ አባት ክርስቶስን እንዳንረሳ በማስታወስ በቅዱሳን ፍኖት ለእግዚአብሔር ደጅ ማብቃት ነው።

Show more
1 047
Subscribers
No data24 hours
-17 days
-1530 days

Data loading in progress...

Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
May '26
May '26
+1
in 0 channels
April '26
+7
in 0 channels
Get PRO
March '26
+7
in 1 channels
Get PRO
February '26
+9
in 0 channels
Get PRO
January '26
+17
in 0 channels
Get PRO
December '25
+29
in 0 channels
Get PRO
November '25
+15
in 0 channels
Get PRO
October '25
+19
in 0 channels
Get PRO
September '25
+18
in 0 channels
Get PRO
August '25
+20
in 0 channels
Get PRO
July '25
+38
in 0 channels
Get PRO
June '25
+34
in 1 channels
Get PRO
May '25
+247
in 1 channels
Get PRO
April '25
+377
in 1 channels
Get PRO
March '25
+26
in 0 channels
Get PRO
February '25
+14
in 0 channels
Get PRO
January '25
+60
in 0 channels
Get PRO
December '24
+126
in 0 channels
Get PRO
November '24
+91
in 0 channels
Get PRO
October '24
+341
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
11 May0
10 May+1
09 May0
08 May0
07 May0
06 May0
05 May0
04 May0
03 May0
02 May0
01 May0
Channel Posts
የክርስቶስ ሰላም ይብዛላችሁ !! በእግዚአብሔር ስም እንደምን አላችሁ ውድ የዛ አንቀጽ ቤተሰቦች? በዚህ አንድ ዓመት ከግማሽ ከእናንተ ጋር የተዋወቅንበት ሳናቋርጥም ዘውትር ዕለተ ዓርብ ፥ ዕለተ መድ
የክርስቶስ ሰላም ይብዛላችሁ !! በእግዚአብሔር ስም እንደምን አላችሁ ውድ የዛ አንቀጽ ቤተሰቦች? በዚህ አንድ ዓመት ከግማሽ ከእናንተ ጋር የተዋወቅንበት ሳናቋርጥም ዘውትር ዕለተ ዓርብ ፥ ዕለተ መድኃኒት በተለያየ ሕብረ አምሳል ከዕለቱ ስንክሳር እንዲሁ ከሰንበት መዝሙር ጋር እያስማማን የነገር ሁሉ ማዕከል የሆነውን የክርስቶስን ሕማም ስለእኛ ሲል የደረሰበትን መከራና የተቀበለውንም ሞት በአንክሮ ፥ በተዘክሮ ሁነን በጾም እየዘከርን ከዚህም ጋር በመንፈሳዊ ሕይወታችን እንበረታ ዘንድ በተለያዩ ዓምዳዊ ጽሑፎች እየተመካከርን ቆይተናል። አሁን ደግሞ ለተወሰኑ ወራት የጀመርኳቸውን ተግባራት ለማጠናቀቅና ራሴንም ለመመልከት የጽሞና ግዜ ስላስፈለገኝ በጸሎት በቆማችሁ ግዜ ሁሉ እኔን ታናሽና ኃጥዕ ወንድማችሁን ክንፈዑራኤል እያላችሁ ታስቡኝ ዘንድና እንደጀመርን ሁሉ ዘውትር ዕለተ ዓርብ በጌታ ፍቅር እየዋላችሁ ለተቸገሩ ሁሉ እንደአቅማችሁ ቸርነትን ታደርጉ ዘንድ በትህትና እጠይቃለሁ !! ቸር ያቆየን !! "እኛ ግን የማንጠቅም ባሪያዎች ነን ፤ ልናደርገው የሚገባንን አድርገናል።" ሉቃስ ፲፯ ፥ ፲ ዛ አንቀጽ የካቲት / ፬ / ፳፻፲፰

2
ዘሰንበት መዝሙር ወብዙኃን ኖሎት ፤ መጽኡ ወስዕኑ ከሢቶታ ለዕብን ፤ እምአፈ አዘቅት እስከ ይመጽእ ያዕቆብ ፤ ዘክቡት ውስተ ሐቌሁ ዘሀሎ ይሠጎ ፤ እምሰብእ ከሠተ ወአስተየ መርዔቶ ። ወከማሁመ መጽኡ
ዘሰንበት መዝሙር ወብዙኃን ኖሎት ፤ መጽኡ ወስዕኑ ከሢቶታ ለዕብን ፤ እምአፈ አዘቅት እስከ ይመጽእ ያዕቆብ ፤ ዘክቡት ውስተ ሐቌሁ ዘሀሎ ይሠጎ ፤ እምሰብእ ከሠተ ወአስተየ መርዔቶ ። ወከማሁመ መጽኡ ብዙኃን ነቢያት ፤ ወስዕኑ ከሢቶታ ለጥምቀት እስከ ይመጽእ ፤ ዓቢይ ኖላዊ እምሰማይ ከሠተ ፤ ወአጥመቀ ብዙኃነ አሕዛበ ፤ በውስቴታ መንክር ተአምሪሁ ለመድኃኒነ ። በከመ ወጽአት በትር እምሥርወ ዕሤይ ፤ በአምሳለ በትረ ያዕቆብ በዘይርዒ አባግዒሁ ፤ ይእቲኬ ማርያም ይእቲ ። ወበእንተ ዘይቤ ትወጽእ በትር ወየዓርግ ጽጌ ፤ ውእቱኬ ዋህድ ውእቱ ፤ ውእቱኬ ወልደ አምላክ ውእቱ። ትርጉም ብዙ እረኞች [በጎቻቸውን ውሃ ሊያጠጡ] ወደ [ጉድጓድ] መጡ ሆኖም የመዝጊያውን ድንጋይ አንከባለው ከጉድጓዱ ደረሰው በጎቻቸውን ማጠጣት አልተቻላቸውም [እስራኤል የተባለ] ያዕቆብ ግን [ድንጋዩን አንከባሎላቸውን ከጉድጓድ ውሃ እንዲቀዱ] ድረስ እንዲሁ የወገቡ ፍላጭ [የአብራኩ ክፋይ] የሆነ ከእርሱ ዘር ሰው ይሆን ዘንድ ያለው [ክርስቶስ] ከተዘጋው ጉድጓድ በጎቹን [የሚያሰማራቸውን] አጠጣቸው። ብዙ ነቢያት [ልክ እንደ ብዙ እረኞች] መጡ ሆኖም ብርቱ እረኛ [ክርስቶስ] እስኪመጣ ድረስ ጥምቀት [ልጅነት] መግለጥ [መስጠት] አልተቻላቸውም ።እርሱ ግን ከሠማይ ገለጣት ፥ ያላመኑትን ብዙዎች [ከቀኝ ጎኑ በፈሰሰ ውሃ ] አጠመቀ በውስጡም የመድኃኒታችን ድንቅ ስራ [ምስጢር] ተአምር ተከናወነ ። በጎችን ከሚጠብቅ ያዕቆብ በትር ምሳሌ አንጻር ከዕሤይ ስር በትር ወጣ [የዚህ ፍጻሜው] ድንግል ማርያም ሆነች [እነዚህ በትሮች ሳይተክሏቸው ፥ ውኃ ሳያጠጧቸ አብበው እንደተገኙ ድንግል ማርያምም ያለወንድ ዘር ጌታ አስገኝታለችና]። በትር ይወጣል ፥ አበባም ያስገኛል ያልነው እርሱ አንድያ የአምላክ ልጅ [ኢየሱስ ክርስቶስ] ነው።
497
3
እግዚአብሔር እረኛዬ ነው .m4a
414
4
ስስት የሞተበት ቀን ዕለተ ዓርብ እኛን ከመውደዱ የተነሳ አባቱ ያለስስት ለመስቀል ሞት አሳልፎ የሰጠው አንድያ ልጅ ፥ ለሚወዱት ሁሉ ያለስስት ቅዱስ መንፈሱን ለሚያፈስ ባለጸጋ ፥ በእምነት ለቀረቡ ሁ
ስስት የሞተበት ቀን ዕለተ ዓርብ እኛን ከመውደዱ የተነሳ አባቱ ያለስስት ለመስቀል ሞት አሳልፎ የሰጠው አንድያ ልጅ ፥ ለሚወዱት ሁሉ ያለስስት ቅዱስ መንፈሱን ለሚያፈስ ባለጸጋ ፥ በእምነት ለቀረቡ ሁሉ ያለስስት ስጋውን ለመብል እንዲሁ ደሙን ለመጠጥ የሰጠ መድኃኔዓለም ስለኛ የደረሰበትን ሕማምና የተቀበለውን ሞት እያሰብን ካለን ነገር ላይ ያለስስት ለመስጠት የምንነሳበት ቀን እነሆ !! የእውነተኛ ክርስትና ማረጋገጫው መልካም እረኝነት መሆኑ ይታወቅ ዘንድ ለቅዱስ ጴጥሮስ የምትወደኝ ከሆነ ግልግሎቼን ጠብቅ ብሎ በፍቅር ቃል አባብሎ አስተምሮታል። ፍቅርን የተማረ ፥ ፍቅር የገባው ማንም የሌሎችን ሕሊና ከመጠበቅ አንስቶ ራሱ እስኪሰጥ ድረስ እረኝነቱን በስራ ማሳየት አለበት። የእነ ሙሴን ፣ የነ አብርሃምን ፣ የነ ይስሐቅን ፣ የነ ያዕቆብን ፣ የነ ዳዊትን ፣ የነ ኤልሳዕን እረኝነት ታሪክ ላጠና ሁሉ በብሉይ ኪዳን እረኝነት በእግዚአብሔር ዓይን ምን ያህል ትልቅ ቦታ እንዳለው ይረዳል። ቅዱስ ጎርጎርዮስ "እረኝነት ከቅዳሴ በኋላ ያለ ቅዳሴ" በማለት በክርስትና ውስጥ እረኝነት ፍቅር የሚፈተትበት ቅዳሴ እንደሆነ በድርሳኑ አስተምሮናል ። ዛሬም ጥር ፳፱ በአክሱም ምድር በማህበረ ዴጌ የነበረ ስስታሙ ሳይዳ እንግዳ ሆኖ ለተገለጠላቸው ለጌታ በተሸረፈ ጽዋ እየሰጠ አለፍ ሲልም እየከለከለ ፥ አንተ ደሃ እያለ እየሰደበ ጌታን ሲያሳዝን መቆዩት አላወቀም ነበር። ሁሉ በተሰበሰበበት ያቺ የተሸረፈች ጽዋ እስክትመሰክርበትና በሰው ፊት ተዋርዶ እስኪሞት ስስታምነቱ አልጠቀመውም። ጸሎት ጌታዬ ፥ አምላኬ ፥ መድኃኒቴ ኢየሱስ ክርስቶስ ከፍቅርህ የተነሳ ለስምህ የወንጌል አርበኛ አድርገኝ ፥ በስስት የደረቀ ቅርንጫፍ እንዳልሆን በቅዱስ ደምህ አረስርሰኝ ፥ ለምግባርና ለትሩፋት እንድበቃ በክቡር ሥጋህ አለምልመኝ !!
447
5
ጸሎተ ዮናስ በመከራዬ ሳለሁ ወደ አምላኬ ወደ እግዚአብሔር ጮኽሁ እርሱም ሰማኝ ፤ በሲኦልም ሆድ ውስጥ ሆኜ ጮኽሁ ፥ ቃሌንም አዳመጠ። ወደ ጥልቁ ወደ ባሕሩ ውስጥ ጣልኸኝ ፥ ፈሳሾችም በዙሪያዬ ነበሩ
ጸሎተ ዮናስ በመከራዬ ሳለሁ ወደ አምላኬ ወደ እግዚአብሔር ጮኽሁ እርሱም ሰማኝ ፤ በሲኦልም ሆድ ውስጥ ሆኜ ጮኽሁ ፥ ቃሌንም አዳመጠ። ወደ ጥልቁ ወደ ባሕሩ ውስጥ ጣልኸኝ ፥ ፈሳሾችም በዙሪያዬ ነበሩ ፤ ማዕበልህና ሞገድህ ሁሉ በላዬ አለፉ። እኔም ከዓይንህ ፊት ተጣልሁ ፤ ነገር ግን ወደ ቅዱስ መቅደስህ ደግሞ እመለከታለሁ አልሁ። ውኆችም እስከ ነፍሴ ድረስ ከበቡኝ ፤ ጥልቁ ባሕር በዙሪያዬ ነበረ ፤ የባሕሩ ሣር በራሴ ተጠምጥሞ ነበር። ወደ ተራሮች መሠረት ወረድሁ ፤ በምድርና በመወርወሪያዎችዋ ለዘላለም ተዘጋሁ ፤ አንተ ግን አቤቱ አምላኬ ሕይወቴን ከጕድጓዱ አወጣህ። ነፍሴ በዛለችብኝ ጊዜ እግዚአብሔርን አሰብሁት ፤ ጸሎቴም ወደ አንተ ወደ ቅዱስ መቅደስህ ገባች። ከንቱነትንና ሐሰትን የሚጠብቁ ምሕረታቸውን ትተዋል። እኔ ግን በምስጋና ቃል እሠዋልሃለሁ ፤ የተሳልሁትንም እከፍላለሁ። መድኃኒት ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።"
543
6
ዘሰንበት መዝሙር እሙነ ኮነ ልደቱ ፤ ለመድኃኒነ ክርስቶስ (እ)። እምሰማያት ወረደ ፤ ወእመላእክት ተአኵተ ፤ ወእማርያም ተወልደ (እ)። በቤተ ልሔም ተወልደ ፤ ወበናዝሬት ተሐፅነ ፤ ወአስተርአየ ገ
ዘሰንበት መዝሙር እሙነ ኮነ ልደቱ ፤ ለመድኃኒነ ክርስቶስ (እ)። እምሰማያት ወረደ ፤ ወእመላእክት ተአኵተ ፤ ወእማርያም ተወልደ (እ)። በቤተ ልሔም ተወልደ ፤ ወበናዝሬት ተሐፅነ ፤ ወአስተርአየ ገሃደ (እ)። ውእቱ አክሊለ ሰማዕት ፤ ውእቱ መድኃኔ ነገሥት ፤ ኖላዊሆሙ ለአሕዛብ ። እሙነ ኮነ ልደቱ ፤ ብርሃነ ኮነ ምጽአቱ ፤ ለመድኃኒነ ክርስቶስ። ትርጉም የመድኃኒታችን [ኢየሱስ] ክርስቶስ ልደቱ እውነት ሆነ ይኽውም ከሰማያት [ከክብሩ] ወረዶ [ትሑት ከሆነች እናቱ ] ከማርያም ተወለደ [በዛን ምሽትም] በመላእክት [አንደበት] ተመሰገነ ። በቤተልሔም ተወልዶ በናዝሬት አደገ ፥ በግልጥ ታየ እርሱም የሰማዕታት [ምስክሮች] አክሊል [ሽልማት ጌጣቸው] ፥ የነገሥታት መድኃኒት [ትምክህታቸው] ፥ በስሙ ላመኑ ለብዙዎችም ጠባቂ እረኛቸው እርሱ [ኢየሱስ ክርስቶስ] ነው። መወለዱ እውነት ሆነ ፥ በመድኃኒታችን [በኢየሱስ] ክርስቶስ በመምጣቱም ብርሃን [እውቀት ፥ ምስጢር] ተገለጠ።
504
7
https://youtu.be/a1k0q25BmKc?si=MjkqQtJHGEai4ta0
https://youtu.be/a1k0q25BmKc?si=MjkqQtJHGEai4ta0
467
8
መልአከ ሰላምነ.m4a
513
9
ዕለተ መድኃኒት ዕለተ ዓርብ ከመላእክት ይልቅ የኛን ደካሞችን ስጋ ለተዋሕዶ የመረጠውን የአምላኮች አምላክ ፥ በመላእክት አንደበት የሚመስገን እርሱ ስለኛ ክብር በአይሁድ አንደበት የተሰደበ ምስጉን እ
ዕለተ መድኃኒት ዕለተ ዓርብ ከመላእክት ይልቅ የኛን ደካሞችን ስጋ ለተዋሕዶ የመረጠውን የአምላኮች አምላክ ፥ በመላእክት አንደበት የሚመስገን እርሱ ስለኛ ክብር በአይሁድ አንደበት የተሰደበ ምስጉን እረኛ ፥ ሁሉን ከእግሮቹ በታች የተገዙለት ሲሆን ስለኛ ፍቅር በአይሁድ እግር የተረገጠ የዓለም መድኃኒት በዚህች ቀን መሞቱንና መከራ መቀበሉን በአንክሮ በተዘክሮ እያሰብን በጾም እንውላለን !! ዕለተ ዓርብ ጌታ መከራ በሚቀበልበት ግዜ መላእክቱ እንደ ሻሽ ሲነጠፉ ዓለም ትቀደስ ዘንድ ፥ እኛ እንከብር ዘንድ ጌታ ያፈሰሰውን ክቡር ደም በብርሃናውያን ጽዋ ተቀብሎ በዓለም ላይ የረጨ ጌታ ያንንም ቦታ ቅድስት ቤተክርስቲያንን የምትታነጽበት ቅዱስ ቦታ ያደረገለት ፥ ለለመኑት ሁሉ ፈጥኖ የሚደርስ የሰዎችን የችግር ቋጠሮ ሚፈታ ፥ ለወዳጆቹ ሁሉ ምስጢር ገላጭ የዋህ መልአክ እንደ ቅዱስ ዑራኤል ማን አለ ?? በዕለተ ዓርብ ጌታን ያከበረ ፥ ጌታም የወደደው ይህ ድንቅ መልአክ ዛሬ የሹመት በዓሉ ነው !! ኪዳን ዘሰርክ ጸሎት ሳናቋርጥ አርምሞ ጽርዓት በሌለበት ቃል ሊቃነ መላእክት ለሚያመሰግኑህ ለአንተ ከምስጋና የሚበልጥ ምስጋናን እናቀርብልሃለን ያውም መላእክት የሚያመሰግኑት ምስጋና ነው። አቤቱ አንተን በማኅሌት ያመሰግኑሃል ያንተ ምክር ፥ ያንተ ቃል ፥ ያንተ ጥበብ ፥ ያንተ መጎብኘት የላክኽው ወልድ ከቀድሞ ጀምሮ ካንተ ጋር የነበረ ዓለም ሳይፈጠር ያልተፈጠረ ባሕርየ ሰብእን ለማዳን በሥጋ የተገለጸ ቃል ልጅህ ወዳጅህ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከኃጢአት ቀንበር ነጻ አደረገን አቤቱ ስለዚህ እኛ አገልጋዮችህ እናመሰግንሃለን !!
620
10
https://youtu.be/ECrBLfBMSxQ?si=fwgowRychbjSk8o_
https://youtu.be/ECrBLfBMSxQ?si=fwgowRychbjSk8o_
563
11
የጥር ወር የመጽሐፍ ጥቆማ ርዕስ :- የነገረ መለኮት መግቢያ ጸሐፊ :- ረ/ፕ ቀሲስ ግርማ ባቱ ገጽ ብዛት :- 316 ምድብ :- ለሁሉም የሚሆን ይዘት :- ትምህርተ ሃይማኖት መጽሐፋ ገበያ ላይ ስላ
የጥር ወር የመጽሐፍ ጥቆማ ርዕስ :- የነገረ መለኮት መግቢያ ጸሐፊ :- ረ/ፕ ቀሲስ ግርማ ባቱ ገጽ ብዛት :- 316 ምድብ :- ለሁሉም የሚሆን ይዘት :- ትምህርተ ሃይማኖት መጽሐፋ ገበያ ላይ ስላለ እየገዛን እናብብ !! ስለ ጌታ ፍቅር ለአንድ ወዳጅ @za_anqets በማጋራት የቤተሰብ አባላት ያድርጉ !! ዛ አንቀጽ ጥር / ፲፰ / ፳፻፲፰
660
12
ዘሰንበት መዝሙር ሖረ ኢየሱስ በትፍሥሕት ውስተ ከብካብ፤ እንዘ ይገብር ተአምረ ወመንክረ ፤ በውስተ አሕዛብ አርአዮሙ ስብሐቲሁ ፤ አምኑ ቦቱ አርዳኢሁ ፤ ወይቤሎሙ ቅድሑ ማየ ፤ ወምልዕዎን ለመሳብክት
ዘሰንበት መዝሙር ሖረ ኢየሱስ በትፍሥሕት ውስተ ከብካብ፤ እንዘ ይገብር ተአምረ ወመንክረ ፤ በውስተ አሕዛብ አርአዮሙ ስብሐቲሁ ፤ አምኑ ቦቱ አርዳኢሁ ፤ ወይቤሎሙ ቅድሑ ማየ ፤ ወምልዕዎን ለመሳብክት እስከ አፉሆን፤ ጥዒሞ አንከረ ሊቀ ምርፋቅ፤ በረከተ ዘአምላክ ገብረ፤ ቤዛነ ተስፋነ ወልደ አምላክ፤ ወለማይኒ ረሰዮ ወይነ። ትርጉም ወደ ሰርግ ቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ [ከእናቱና ከደቀመዛሙርቱ ጋር] በደስታ ሔደ[የእርሱ ድንቅ አድራጊነት ፥ የእናቱ አማላጅነት የሚገለጥበት የመጀመርያው የተአምራት ቀን ነውና]። እዛም እያለ በብዙህ ሰዎች መካከል ድንቅ ተአምርን አድርጎ ጌትነቱን ገለጠ ፥ ደቀ መዛሙርቱም [አይተው] አመኑበት። ጌታችንም እንዲህ ብሎ አዘዛቸው ውኃ ቀድታችሁ እስከ አፏቸው ድረስ ምሏቸው [እነርሱም እንደተባሉት አደረጉ] የሰርጉ አሳዳሪ የሆነው አለቃም አምላክ ያበረከተውን ፥ ከውኃነት የተለወጠውን ወይን ቀምሶ አደነቀ። ውኃውን ወደ ወይን የለወጠ እርሱ የአምላክ ልጅ [ኢየሱስ ክርስቶስ] ተስፋችን ፥ ቤዛችን ነው።
543
13
ኑ ተቀደሱ.m4a
536
14
ዛሬ የሕጻናት በዓል ነውና የዛሬውን ምሳችንን የቻልነውን ያክል ከረሜላና ብስኩት ገዝተን መንገድ ላይ ወድቀው ለሚለምኑ ሕጻናት እንመጽውት !! የተለመደውን ምግብና ፍርፋሪ እንጂ ለአፋቸው ጣፋጭ የሚሰጣቸው የለምና ።
626
15
ዛሬ ዕለተ አርብ ነው !! እንደ ጀመርን ዕለተ አርብ የመድኃኔዓለምን ሕማሙን ፤ ስለእኛ የተቀበለውን ስቃይና መከራ ወገባችንን ታጥቀን በጾም እንዘክራለን !! ለኛ ለኃጥዓን ተስፋችን ፥ ለተነሳህያን
ዛሬ ዕለተ አርብ ነው !! እንደ ጀመርን ዕለተ አርብ የመድኃኔዓለምን ሕማሙን ፤ ስለእኛ የተቀበለውን ስቃይና መከራ ወገባችንን ታጥቀን በጾም እንዘክራለን !! ለኛ ለኃጥዓን ተስፋችን ፥ ለተነሳህያን ርስታችን ፥ የቅዱሳን ክብራቸው ፥ የጻድቃን መድኃኒታቸው ፥ የሰማዕታት ሽልማታቸው እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነውና። በማየ ዮርዳኖስ ከሰማይ በመጣ ምስክር የምወደው ልጄ ይህ ነውና እርሱን ስሙት የተባለ አምላክ ወልደ አምላክ ፥ የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ ብላ እናቱም ምስክር የሰጠችለት ወልደ ማርያም ፥ በዛሬዋ ዕለትም ይህን የተማረ ሕጻን ቅዱስ ቂርቆስ እኔም በዕለተ ዓርብ የተሰቀለው የክርስቶስ ባርያው ነኝ በማለቱ አንገቱ እስኪሰጥ የደረሰበት የምስክርነት ቀን ነው። በዚህ ዘመን የእግዚአብሔር ቃል እንደ ማነቃቂያ ንግግር በተቆጠረበት ፥ የእግዚአብሔር ቃል ከሚሰሙትና ከሚያነቡት ጋር መዋሐድን በተወበት ፥ የእምነት ሕይወት በራቀበት ፥ ፍቅር እንደ በረዶ በቀዘቀዘበት ግዜ የተሰቀለውን ክርስቶስ እንደማሰብ አበረታች መድኃኒት የለም። ቅዱሳኑ ሕመማቸውን የረሱበት ፥ አስፈሪ ነገስታትን ድል ያደረጉበት ፥ ሞትን እንደ ክብር የቆጠሩበት ምስጢር የመስቀሉ ነገርን ግዜ ሰጥተው ስለተማሩ ፥ የጌታን መከራ እንደ አቅማቸው ስለተለማመዱና ስላሰቡ ነው። ጸሎት ጌታዬ ፥ አምላኬ ፥ መድኃኒቴ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ በዘመኔ ሁሉ ሕማምህንና ሞትህን ከቃል አልፌ በስራ ፥ በእውነትና በፍቅር እሰብከው ዘንድ እርዳኝ ።ማረኝ ኃጢያተኛ ነኝና ፤ በኃጢያቴ ምክንያት ያጣሁትን ልጅነት ፥ ሕይወት ትመልስ ዘንድ ስለእኔ እርቃንህን መሰቀልህን አስብ ዘንድ እርዳኝ። ራሴን መግዛት ላልቻልኩት ለእኔ ምሕረትን አድርግልኝ ፥ ስጋዊ ፍትወታት ላቆሰሉኝ ለእኔ መድኃኒት ስጠኝ ፥ በሕግ በስርዓት ተወስኜ እኖር ዘንድ ፍቅርህን በልቤ አኑርልኝ ።
1 151
16
No text...
703
17
ዘሰንበት መዝሙር ንጉሥኪ ጽዮን ፤ ለትውልደ ትውልድ መጽአ ኀቤነ ፤ ዘኪያሁ ይሴፈዉ ሰማያት ወምድር ፤ ዕበይ ለነገሥት ብርሃኖሙ ለእለ ይጸመድዎ ፤ አክሊለ ሰማዕት ሠያሜ ካህናት ፤ ዓምዳ ወድዳ ለቅድ
ዘሰንበት መዝሙር ንጉሥኪ ጽዮን ፤ ለትውልደ ትውልድ መጽአ ኀቤነ ፤ ዘኪያሁ ይሴፈዉ ሰማያት ወምድር ፤ ዕበይ ለነገሥት ብርሃኖሙ ለእለ ይጸመድዎ ፤ አክሊለ ሰማዕት ሠያሜ ካህናት ፤ ዓምዳ ወድዳ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ፤ በቤተ ልሔም ተወልደ ወበናዝሬት ተሐፅነ ፤ ኢተዘኪሮ አበሳነ ኢኀደገነ ፍሥሐ ኮነ ፤ ዘውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ። ትርጉም ጽዮን [ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አንድም ነፍሴ) ሆይ ንጉሥሽ ክርስቶስ ሰማያውያን መላእክት እንዲያዩት ፥ ምድራውያን ደቂቀ አዳም እንዲያድናቸው ተስፋ የሚያደርጉት እርሱ ወደ ሁላችን መጣ። እርሱ ለነገሥታት ክብራቸው ፥ በስሙ ለሚጠመዱ ተስፋ ብርሃናቸው ፥ የሚያገለግሉትን ካህናትን የሚሾማቸው ነው።ቅድስት ለምትሆን ቤተ ክርስቲያንም መሠረቷና ጉልላቷ እርሱ ነው ። እንዲህ ክብር ያለው የክብር ባለቤት በቤተልሔም ተወለደ ፥ በናዝሬት አደገ ይህ ሳያንስ በደላችንን አስቦ እንደወጡ ይቅሩ ፥ እንደተበተኑ ይኑሩ ብሎ አልተወንም ይልቁን ተድላ ፥ ደስታችን ሆነ ይህንን ያደረገ ንጉሥ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
974
18
https://openinyoutu.be/mfdR1BGDsCY?si=pHmTm0RWT8SZj4Ad
https://openinyoutu.be/mfdR1BGDsCY?si=pHmTm0RWT8SZj4Ad
547
19
የተሰቀለውን ሳየው.m4a
623
20
የትህትና ቀን ዕለተ አርብ ስለኛ ፍቅር በመስቀል የተሰዋ ፥ እንደ ተሸለተ በግ እርቃኑን የዋለ ፥ በግፍ ሲጎትቱት በፍቅር የተከለ ፥ መከራ ሲያጸኑበት አፉን መድኃኔዓለም ስላደረገልን ውለታ ሁሉ በአን
የትህትና ቀን ዕለተ አርብ ስለኛ ፍቅር በመስቀል የተሰዋ ፥ እንደ ተሸለተ በግ እርቃኑን የዋለ ፥ በግፍ ሲጎትቱት በፍቅር የተከለ ፥ መከራ ሲያጸኑበት አፉን መድኃኔዓለም ስላደረገልን ውለታ ሁሉ በአንክሮ ፥ በተዘክሮ ሁነን ይህች ቀን እንዘክራለን ። ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊትም ዕለተ አርብን በትንቢት መነጽሩ አይቶ ሲናገር እንዲህ አለ "ብዙ ውሾች ከብበውኛልና ፥ የክፋተኞች ጉባኤም ያዘኝ ፥ እጆቼንና እግሮቼን ቸነከሩኝ ፥ አጥንቶቼ ሁሉ ተቈጠሩ ፥ እነርሱም አዩኝ ተመለከቱኝም።ልብሶቼን ለራሳቸው ተከፋፈሉ ፥ በቀሚሴም ላይ ዕጣ ተጣጣሉ"አለ ። ነቢየ ልዑል ኢሳይያስ በትንቢቱ "ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም ፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት ፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም።" ብሎ አሰምቶ ተናገረ ። ጸያሔ ፍኖት ቅዱስ ዮሐንስ ጌታን በዮርዳኖስ ወንዝ ባየው ግዜ ልጎነበስ ፥ የጫውን ጠፍር እንኳን ልነካ ፥ ጫማውን ልሸከም የማይገባኝ ብሎ ከተቀበለው በኋላ ስለሁሉ ደስታ ጌታን አጥምቆታል ሲያጠምቀውም "ብርሃንን የምትገልጽ የብሩክ ልጅ አንተ እንደ መልከጼዴቅ ሹመት ለዘላለም ካህን ነህ" እያለ ነበር። ይህ መጥምቀ መለኮት ጌታ ካጠመቀው በኋላ የዕለተ አርብ የጌታ ውሎ ተገልጾለት "የዓለምን ኃጢያት የሚያሶግድ የእግዚአብሔር በግ እነሆ " በማለት ጌታን መድኃኒትነት ለዓለም ያስተዋወቀ የእውነት ምስክር ሆነ። ብዙዎች ሊያዩት ሽተው ያላዩትን መድኃኒት ከፊታችን ተሰቅሎ ሳለ ዛሬስ ዓይናችን ማንን እያየ ይሆን?? ጸሎት ጌታዬ ፥ አምላኬ ፥ መድኃኒቴ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ በፍቅርህ ተመልከተኝ ፥ እኔ ባሪያህ በሥራዬ ሁሉ ደካማ ነኝና ከእንግዲህ ወዲህ ክፉ እንዳልናገር አፌን ፈውስልኝ ፥ ክፉ እንዳላይ ዓይኔን ፈውስልኝ ፥ ክፉ እንዳይሠሩ ነፍሴንና ሥጋዬን ሁሉ ፈውስልኝ ።
657