en
Feedback
ይኸነው የሸበሉ ( ክንዴ )

ይኸነው የሸበሉ ( ክንዴ )

Open in Telegram

ለአማራ ህዝብ እውነተኛ መረጃ በማቀበል ድምፅ ለመሆን !!

Show more
1 323
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-2530 days
Posts Archive
ብዛትና ጥራት ? የአማራው የህልውና ትግል ትልቁ ችግር የታጋይ ብዛት ማነስ ሳይሆን ብዛት ያለውን ታጋይ ወደ ወታደራዊና ፖለቲካዊ ሀይል የመቀየር ብቃት ማጣት ነው። የመጀመሪያው ችግር በአለም አቀፍ ደረጃ ዝቅ ብለን እንድንታይ ያደረገን የፖለቲካ ትርክትን ወደ አለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ጥያቄነት መለወጥ አለመቻል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በብዛት በየጫካው የተበተነውን ሀይል በአንድ ወጥ፣ ዲሲፕሊን ባለውና ዘመናዊ የጦርነት ስልትን በሚከተል ማዕከላዊ አመራር ስር ማሰለፍ አለመቻል ነው። የአማራ ፋኖ በየቀጠናው ሁልጊዜም ስልጠና፣ ማደራጀትና ማስታጠቅ ላይ መሆኑን ሳይ የአማራ ድል ቅርብ መሆኑን ያበስረኛል። ሆኖም ግን የውጤታማ ጦርነት ወሳኝ መለኪያው የሰራዊት ብዛት ሳይሆን የጦር ሀይሉ ጥራት፣ ስልጠና፣ አመራርና የትጥቅ ብቃት ነው። በወታደር ብዛት ቢሆን ኖሮ ደረግም አይወድቅም ነበር ፥ ጃል አብይም እስካሁን አማራን ጨፍጭፎ ባጠናቀቀ ነበር። ባለፉት 3 የጦርነት ዓመታት የተረዳሁት ነገር በፋኖ ስም የተሰባሰበው ሀይል አብዛኛው በየአካባቢው የተነሳ ጀግና ሕዝባዊ አርበኛ ( Patriot-Fighter ) ሲሆን፣ መሰረታዊ የትግል መንፈስና ቆራጥነት አለው። ይሁን እንጂ ዘመናዊና የተወሳሰቡ ወታደራዊ ኦፕሬሽኖችን ለመምራት የሚያስችል ወጥነት ያለው የፕሮፌሽናል ጦር ( Professional Army ) ስልጠና፣ ዲሲፕሊንና ዶክትሪን ( Doctrine ) ይጎድለዋል። እንደ ምሳሌ ብንመለከት የሱዳኑ አማፂ RSF ትግል ሲጀምር ከ50,000 ልዩ ሀይል በታች ይዞ ወደ ትግል ቢገባም ከፊል መደበኛ፣ ከፍተኛ ልምድና ስልጠና ባላቸው ሀይሎች ላይ የተመሰረተ ስለነበር እንደምናየው ውጤታማ እየሆነ ነው። የትግራይ ሀይሎችም ቢሆኑ ከፍተኛ የመደበኛ ወታደራዊ ልምድና ጠንካራ ማዕከላዊ አመራር ከጀርባ አላቸው። ይህም በትንሽ ሀይል እንኳ ቢሆን በትላልቅ ውጊያዎች ላይ ፈጣን፣ ስልታዊና ወሳኝ ድሎችን ለማስመዝገብ አስችሏቸዋል። አለፍ ሲልም በጣም ተፈሪ እንዲሆኑ ጭምር አስቸሏቸዋል። ጥራትና ግዳጅ የመፈፀም ብቃትን እንተወውና የሠራዊት ብዛትን እንኳ ብንመለከት ማዕከላዊ ኮማንድ ከሌለህ 1,000,000 ሰራዊት በተለያዩ የዞንና የጎጥ አመራሮች ስር ከተዋቀሩ ይህ ሀይል በፍፁም ለአንድ ወጥ ስልታዊ ዓላማ ሊውል አይችልም። እያንዳንዱ ክፍለ ሃገር ወይም ዞን የራሱን የአካባቢ ትግል፣ የራሱን ጦርነትና የራሱን የውጊያ ህግጋት ይከተላል። ይህ ደግሞ የጠላትን ሀይል ለመበተን ከመቻል ይልቅ የፋኖን ሀይል እንዲበታተን ያደርጋል። ፋኖ በባህሪው እውነተኛ የሽምቅ ተዋጊ ( Guerrilla Fighter ) ቢሆንም በመዋቅርና በዓላማ ግን ለአጭር ጊዜ ምላሽ የሚሰጥ አርበኛ እየሆነ መጥቷል። የሽምቅ ውጊያ ስኬታማ የሚሆነው ትንንሽና ተንቀሳቃሽ ሀይሎች ትልልቅ የጠላት ሀይሎችን በደፈጣ ሲመቱና በጥቂት መስዕዋትነት ብዙ ጉዳት ማድረስ ሲቻል ነው። ዘመናዊ የመገናኛ ዘዴዎች ፣ ጠንካራ አዋጊዎች በሌሉበት ሁኔታና ዘመናዊ የድሮን መከላከያ ባልታጠቅንበት ወቅት ግዙፍ የፋኖ ሀይልን ለሽምቅ ውጊያ ማዋል ሎጂስቲክስን ከማወሳሰብ በተጨማሪ ለዘመናዊ የድሮን ጥቃትም ያጋልጠዋል። ይህ በእንዲህ እያለ ግዙፍ የፋኖ ሠራዊት ውጊያ ላይ ሲሆን የምግብ፣ የመድሃኒት፣ የትጥቅና የጥይት አቅርቦት የሚያስፈልገው ፍላጎት ከአገዛዙ የጦር ሠራዊት በላይ ይሆናል። ያለ ጠንካራ የኋላ ደጀን (Backend Support)ና የተቀናጀ የሎጅስቲክስ ሰንሰለት (Supply Chain) እንዲህ ያለ ግዙፍ ቁጥር ያለው የፋኖ ሀይል በአጭር ጊዜ ውስጥ በሀብት እጥረት ሽባ ይሆናል። በተጨማሪም እያንዳንዱ አካባቢ በራሱ ደጀን የአካባቢው ሕዝብ ላይ እንዲመሰረት መደረጉ የአካባቢውን ማህበረሰብ ኢኮኖሚያዊና ሰብዓዊ ቀውስ ውስጥ ይከተዋል። ከዚህ በተጨማሪ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሀይል ቢኖርም እንኳ ያለ በቂ ጥይትና ከባድ መሳሪያ በአገዛዙ የሚፈጸመውን የድሮን ጥቃትና በታንክ የተደገፈ ጥቃት መመከት ስለማይቻል በአነስተኛና ተንቀሳቃሽ ሀይል የደፈጣ ውጊያዎችን ማስቀጠልና እንደ አስፈላጊነቱ Conventional ውጊያን ማስቀረት አሁንም ቢሆን አዋጭ ይመስለኛል። የሱዳኑ አማፂ RSF በዋናነት በከተሞችና ውስብስብ በሆኑ አካባቢዎች ፈጣን፣ ተንቀሳቃሽና አጥቂ ቡድኖችን እየተጠቀመ ውጤታማ ሲሆን አይተነዋል። ይህም የጠላትን ከባድ መሳሪያና የአየር ኃይል የበላይነት ለመቋቋም የሚያስችል የሽምቅና የከተማ ጦርነት ስልት ነው። የፋኖ ትግልም ስኬታማ እንዲሆን ከተፈለገ ከቁጥር ብዛት ይልቅ ወደ ተንቀሳቃሽነት (Mobility)ና ፈጣን ስልታዊ ድብደባ (Surgical strike ) መቀየር ይኖርበታል ባይ ነኝ። በመጨረሻም ይህንን ብዛት ያለው የፋኖ ሀይል ወደ ወሳኝ የስትራቴጂያዊ ጥቅም ሊቀይረው የሚችለው አንድ ወጥ ድርጅትና አንድ ወጥ ሠራዊት እንዲሁም ታማኝ መሪ መፍጠር ሲቻል ብቻ መሆኑ ቁልጭ ብሎ ይታየኛል።

የ19 ዓመት ልጅ ካለደ*ፈርኩ ያለው የ50 ዓመት ሚሊሻ እናቷን..... ! በሰሜን ጎጃም ዞን ሰሜን አቸፈር ወረዳ ይስማላ ከተማ ላይ ልጇን በሚሊሻ አላስደፍርም ያለች እናት በሚሊሻ ተገደለች። ድርጊቱ የተፈፀመው ትላንት ጥቅምት 9 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 አካባቢ በተለምዶ ከምፕ ( የደርግ ካምፕ ) ተብሎ የሚጠራው አካባቢ ነው። ሚሊሻው ከአሁን በፊት 7 ዓመታትን በመከለከያ ተቋም አገልግሎ የነበረና አሁን በድጋሜ የብልፅግና ጦር ጋር የተቀላቀለ የጡት ቆራ*ጮች ተላላኪ ነው። ባደረግነው ማጣራት ገዳዩ ለጊዜው ወደ ጫካ ዞር ብሎ እንዲቆይ በመመካከር አመለጠን የሚል ድራማ ሰርተዋል። ሟቿ ተጨማሪ የ4 ዓመት ህፃን አላት። ይስማላ ከተማ ውስጥ ያለው አጠቃላይ የአገዛዙ ሀይል 70 እንደሆና ከጥቂት አድማ ብተናዎች ውጭ አብዛኛዎቹ ሚሊሻ እንደሆኑና እራሱን መከላከያ ብሎ የሚጠራው ቡድን ለፓትሮል በቀን አንድ ጊዜ ከሊበን ተነስቶ ቃኝቶ ከመመለስ ውጭ በከተማዋ እንደሌለም አረጋግጠናል። በነገራችን ላይ ባለፈው ከባህርዳር የመጡ መንግስቱ አማረ የሚባለው የክፍለ ጦር መሪ ይመራቸው የነበሩ ፋኖዎች አልጋ ይዘው ከተኙበት የተገደሉትም ይስማላ ነው።

የመሳፍንት መንግስቴ ውጣ ውረድና የትግሉ አቅጣጫ ጥያቄ ! ​ ​የአፋብኃ ቴዲ ዕዝ 1ኛ ክፍለ ጦሩ አርበኛ መሳፍንት መንግስቴ የደረሰበት መከራ በእጅጉ ያሳዝናል። ከቀድሞው የወያኔ አገዛዝ ጀምሮ እስከ አሁን ባለው የኦህዴድ አስተዳደር ድረስ ለአማራ ህዝብ ሲል ብቻ ሲታሰር ሲፈታ እንደቆዬ ሁላችንም የምናውቀው ነው። ትንሽ ነፃነት አገኘ ከተባለም ነፍጥ አንስቶ ጫካ ከገባ በኋላ ነበር። ይባስ ብሎ ለአማራ ሕዝብ የህልውና ትግል ሲል የሞቀ ቤቱን፣ ሚስቱንና ልጆቹን ጥሎ በከፍተኛ ክፍለ ጦር ኃላፊነት ተሰጥቶት ሥራ ላይ እያለ "የአካሄድ እንዲስተካከል" በመጠየቁ ብቻ የክፍለ ጦሩ ሰብሳቢ የግል እስረኛ ከሆነ ወራት አልፎታል። ይህ በእውነት አሳዛኝ ነው። የብልፅግናን ዋና ካድሬ 1.35 ሚሊዮን ብር ተደራድሮ የሚለቅ double agent አመራር ስለ መሳፍንት እገታ justification ሊሰጠኝ እንደማይችል አውቃለሁ። ድሮም አዲስ አበባ ሪል ስቴት ላይ ቤት ገዝቶ ሚስቱንና ልጆቹን የላከን የፋኖን አመራር ለአማራ ህልውና ወይስ ለብልፅግና ህልውና ነው የሚታገለው ? ብሎ የማይጠይቅ የበታች ተዋጊ ሞቱ ደመ-ከልብ ሆኖ ከመቅረት ውጭ ሌላ የሚፈይደው ነገር የለም። የእውነት የሰራው ወንጀል ሰርቶ ተጠያቂነትን ለማምጣት ቢታሰር ምንኛ ደስ ባለኝ ነበር ፤ ግን እውነታው ሌላ ነው። እኛም 1ኛ ክፍለ-ጦር ላይ ያለው የሲሲሊ ማፍያዎችን የሚያስንቅ ወንጀል በክፍለ ጦሩ አመራሮች ብልሹነት የመጣ ስለሆነ አንድም በግምገማና በሪፎርም ይስተካከላል ፤ ነገሩ ቢከፋም ታች ያለው ንፁህ ታጋይ በእምቢተኝነት ጭምር ኃላፊዎችን በራሱ በማደራጀት ነገሮች ይስተካከሉ ይሆናል ብለን ብንጠብቅም ሳይሳካ ቀርቶ ስንቶች የተሰውለት የህልውና ትግል መልኩን እንዲቀይር አስገዳጅ ሁኔታ እየፈጠረ መሆኑን ተረድተናል። ​ስለ እውነት በ1ኛ ክፍለ ጦር ውስጥ ያሉት የትግል አጋሮች በተለይም ከአንሙት ያዛቸው ብርጌድ ውጭ ያሉ አባላት፣ የወጡለትንና እየተዋደቁለት ያለውን ዋና ዓላማ በትክክል ያውቁታል ወይ? ትግሉ የት እየሄደ እንደሆነስ ይገመግማሉ ወይ? ከዚህ በኋላ በዚህ ቀጠና ላይ ያደረጉትን ፣ እየተደረጉ ያሉትንና ሊደርጉ የታሰቡትን ፀያፍ አካሄዶች ጭምር ለሰፊው የአማራ ህዝብ በጨዋነት እናሳውቃለን። በባህር ዳር ከተማ ከአድማ ብተና ጋር በመቆራኘት የሚሰሩትን የማፍያነት ተግባራትና ደረቅ ወንጀሎች እንዘረዝራለን። አጋሰስነትን ተፀየፉ ወገኖች ! ምንጊዜም ውግንናችን ለህዝባችን ይሁን !

የስልጤና የወሎ ህብረት ጋብቻ በመካነ ሰላም ! ወሎን ሰሜን ኦሮሚያ አደርጋለሁ ብሎ ለተነሳው የኦሮሙማው አገዛዝ መሳሪያ እየሆኑ ያሉት የስልጤ ብሔርተኞች ወሎ ውስጥ የሃይማኖት ግጭት ለመፍጠር እየተፍጨረጨሩ ነው። አማራ ክልል ውስጥም ሆነ ኦሮሚያ ውስጥ በግፍ የሚጨፈጨፉ አማራዎች ሀይማኖት አላቸው። ታዲያ ስንት ሺህ ሙስሊም በወለጋና መተከል በአማራነቱ ሲጨፈጨፍ ትንፍሽ ያላሉት የስልጤ ብሔርተኞችና ወሎ ህብረቶች መካነ-ሰላም ውስጥ ከአገዛዙ ጦር ጋር የነበሩ 4 ሰዎች ተገድለው ማን እንደመታቸው እንኳ በውል ሳይጣራ ተንደርድረው ክርስቲያን ሙስሊምን ጨፈጨፈ የሚል አጀንዳ ተሸክመው እያጯጯሁ ነው። ይሄ አጀንዳ ዞሮም የሚበላው ያው ማህበረሰቡን እንደሆነ እንኳ አይረዱም። ባህር ዳር ለሚኖር ሙስሊም እዚሁ ካለው ክርስቲያን ይልቅ ወራቤ ያለ ሙስሊም ሊቀርበው አይችልም። ሞጣ ላይ የተለመደችው ከአክቲቪስት እስከ ሚኒስተሮች የተሳተፉባትን ፕሮፓጋንዳ ለመድገም እየተንደፋደፉ ነበር አልተሳካም። ለወደፊቱም አይሳካም። በእምነት ስም ተኮፉሶ አማራን ዋጋ እያስከፈለ ያለ አካልም በዚህ መንገድ አይቀጥልም። ነጭ ቦኔት በለው ጥቁር ቀሚስ ወይም ነጭ ቀሚስ ያለቦታው ከዋለ አያድነውም። ከአሁን በፊት አገዛዙ የአርበኛ አበበ ፋንታውን አባት ሙስሊም ሚሊሻዎችን ልኮ ቤተክርስቲያን ውስጥ ቢያስገድልም የሀይማኖት ጦርነት ሳይነሳለት ቀረ። ምክንያቱም ገዳዩ ሙስሊምም ይሁን ክርስቲያን የአገዛዙ ሚሊሻ እንጅ የትኛውንም የእምነት ተቋም አይወክልም ብለን ስለተቀበልን። ሁሉም ቀርቶ ሙስሊሙ መሀመድ ተሰማ የሚመራው ጦር ስንት የቆሎ ተማሪዎችን ሲረሽን የአገዛዙ ጦር ግፍ ፈፀመ እንጅ ሙስሊሙ ጄነራል የክርስቲያን ተማሪዎችን ጨፈጨፈ የሚል ዜና አልተሰራም ለወደፊትም አይሰራም። ከዚህም በኋላ ፀረ-አማራ ሆነህ ከአገዛዙ ጋር አንሶላ ስትጋፈፍ እርምጃ ቢወሰድብህ ሮጦ የሃይማኖት ምሽግ ውስጥ መግባት ተቀባይነት የለውም። ሙስሊም ሚሊሻም ሆነ ክርስቲያን ሚሊሻ ያው ሚሊሻ ነው። በተለይ ደቡብ ወሎ በጣም ብዙ ሚሊሻ አለና ገና ሲደመሰስ ጄኖሳይድ ሊባል ነው እንዴ? አረጋ ከበደን ለመደምሰስ የወጣ ፋኖ አብዱ ሁሴንን ይምረዋል ወይ? ያለፈበት አሮጌ የፖለቲካ ፋሽን አያድንህም ነው የምልህ ከገባህ ! ደነዝ !

ለትግሉ ስኬት ቁልፍ :- - ምሁራዊ ልዕልና - ፖለቲካዊ ራዕይ - ወታደራዊ ፅናት - አማራዊ ወንድማማችነት ​የአማራ ሕዝብ የትግል አቅጣጫ ግቡን መምታቱ የሚያረጋግጠው የአዲሱ የአማራ ትውልድ የትግል መሪ ምሁራዊ ልዕልና፣ ፖለቲካዊ ራዕይና ወታደራዊ ፅናት እንዲሁም ከሴራ የፀዳ አማራዊ ወንድማማችነትን አጣምሮ የያዘ ከሆነ ብቻ ነው። አርበኛ ዘመነ ካሴ ባውቄ የአማራ ህዝብ ጭቆናን በፖለቲካዊ ትንተና ብቻ ማስወገድ እንደማይቻል ቀድሞ በመረዳትና በመንቃት ከኤርትራ በረሃ የጀመረውን ትጥቅ ትግል ለአሁኑ ትግል መሠረት የጣለ ብቻ ሳይሆን የቅንጦት ወንበርንና የዩኒቨርስቲ ሜዳልያን በወርወር ለአማራነት ሲባል መሳሪያ አንስቶ ጎረቤት አገር ድረስ መሰልጠንና መታጠቅ እንደሚቻል ያሳየ ደፋር ጀግና ነው። ለውጥ ከተባለው የ2010 ዓ.ም ነውጥ በኋላም የወጣቶችን በየሰፈሩ በማደራጀት ስልጠና ሲጀምር እንዲህ እንዳሁኑ ሚሊዮኖች ከጎኑ ሊሆኑ የማይሳካ መስሏቸው የተሳለቁበትም ነበሩ። አርበኛው ቀድመው ከነቁ የተወሰኑ ወጣቶች ጋር ሰብሰብ ብሎ ሲሄድም ኦቦ ተመስገን ጥሩነህ "እጀባ የሚመስል ነገር አየሁ " በማለት በብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ወጥቶ "ህግ ማስከበር ዘመቻ" የሚባል በማወጅ አልተሳካለትም እንጅ ህልሙን ለማጨናገፍ ጦርነት የከፈተው ገና በ2013 ዓ.ም ነበር። ሌላውን ያው የምናውቀው ነው። በኋላም አብዛኞቹ የአማራ ታጋይ ነን የሚሉ አካላት የግል ጥቅማቸውን ከአማራ ህዝብ ጥቅም አስቀድመው ራሱን " ብልፅግና " ከሚለው አገዛዝ ጋር ተሻርከው የስልጣንና ገንዘብ ማማ ላይ ሲወጡ አርበኛ ዘመነ ካሴ ግን ውግንናውን በድጋሜ ለአማራ ሕዝብ ብቻ በማድረግ የአማራ ሕዝባዊ ኃይል ፋኖን መሥርቶ ስልጠናና ትጥቅ አሰባሰበ። ያን ጊዜም አብይ አህመድ "ጥቁር ክላሽ ሳይ ያመኛል" አለ እና ዘመቻውን አጠናክሮ ቀጠለበት። ክብር ለሰማዕታት ወንድሞቻችን ይሁንና በ55 ጥቁር ክላሽ የታመመው ጃል አብይ አሁን በሚሊዮን የሚቆጠር ጥቁር ክላሽ አስታጥቆን የበለጠ ህመሙን ያባባሰው ራስ አርበኛ ዘመነ ካሴ ነው። ራስ አርበኛ ዘመነ ካሴ በውቄ የጎጃምን ፋኖ በመምራት በጦር ሜዳ የብልፅግናን ማዕረግ የተሸከሙ ኮለኔሎችንና የጦር መኮንኖችን ከአፈር በመደባለቅ ትግሉን በአንድ ወጥ ድርጅት ሥር ለማድረግ ሲል እራሱን ዝቅ በማድረግ ከወንድሞቹ ጋር በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ኮማንድ ሥር ተጠርንፎ እየሠራ ይገኛል። ይህ ትህትናን የተላበሰ ታጋሽነትና የጋራ አመራርን የመቀበል ብስለት፣ የፋኖን እንቅስቃሴ ከግለሰቦች ፍላጎት በላይ ለሆነው የሕዝብ ዓላማ ማስገዛት መቻሉን የሚያሳይ ሲሆን፣ ይህ የመሪነት ብቃት ለትግሉ ስኬት ቁልፍ ማሳያም ነው። ይሄን የመሰለ ምሁርና የፀና ታማኝ የአማራ ህዝብ ወታደር በጎጃም ብቻ ታጥሮ እንዲቀርና ትግሉን ካሁን በፊት በሴራ ተኮለሽተው እንደቀሩት 1966፣ 1983 ፣ 1997፣ 2010 ዓ.ምና አብን ትግሎች ለማድረግ ከባንዳ እስከ ነጭ ከፍተኛ ሴራ ቢጎነጎንም ከባለፈው በመማር ሁሉንም ወጥመዶች በመበጣጠስ ይሄው ለዚህ አድርሶታል። ከዚህ በኋላ መሪውን እንደ ንብ የመጠበቅ፣ ድርጅቱንና የትግሉን ራዕይ በወታደራዊ ዲሲፕሊን የመጠበቅ የመላው የአማራ ህዝብና የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ኃይል ሰራዊት አደራ ነው። ታማኙ መሪየ ድል ካንተ ጋ እንደምትሆን የስሜን ያህል እርግጠኛ ነኝ !

የጤና ባለሙያዎች ፣ መምህራን እና ወላጆች ጥንቃቄ ! አለማቀፍ ህግን የማያውቀው አገዛዙ ባለፉት ሁለት ዓመታት የተለማመደውን ተቋማትን በድሮን የማውደም ኦህዴዳዊነት በ2018 ዓ.ም ጤና ጣቢያና ጤና ባለሙያዎችን በመጨፍጨፍ "ሀ" ብሎ ጀምሮታል። ትላንት በሰሜን ወሎ ዞን ጉባላፍቶ ወረዳ ሳንቃ ከተማ ጤና ጣቢያ ላይ የተደረገው የድሮን ጥቃት የአገዛዙን የ2018 ዕቅድ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው። ትምህርት የሚለውም ነገርም ነገ ተማሪዎች ሰብሰብ ብለው እንዲጠብቁት መሆኑን ደግሞ ነገ ትምህርት ቤት እስከ መምህራኑ ይጨፈጨፉ ይሆን የሚለው ስጋት ያዘኝ። አገዛዙ በወሎ ግንባር የደረሰበትን ሽንፈት መቋቋም ሲያቅተው በወልድያ ዙሪያ የቆሰሉ ፋኖዎች አሉ የሚል መረጃ ከባንዳዎች ስላገኘ ብቻ በአካባቢው ባለ የህክምና ጣቢያ እርዳታ ሊደረግላቸው ይችላል ብሎ በመገመት ጤና የሳንቃ ጤና ጣቢያን በድሮን በመደብደብ አንድም ፋኖ ሳያገኝ ሀኪሞችንና ንፁህ ታካሚዎችን ጨፍጭፏል። የሚገርመው እኮ አገዛዙ ቁስለኛ ፍለጋ ድሮን ያሰማራው በሺህ የሚቆጠሩ ምርኮኞች በፋኖ እጅ እያሉ ነው። ለመሆኑ የአገዛዙ ጦር ሲቆስል የሚታከመው በህዝብ ጤና ተቋማት ያውም በነፃ አይደለም ወይ? አገዛዙ አንድ የፋኖ ቁስለኛ የሆነ ሆስፒታል ገብቷል የሚል ወሬ ቢሰማ ሆስፒታሉን በሙሉ በቱርክና ኢራን ድሮኖች እንደሚያጋየው ይሄ የታወቀ ነገር ነው። ትምህርት ቤቶችንም እንደለመደው ነገ ማውደም ይጀምራል። አገዛዙ የትኛውንም ተቋም ከማውደም ወደኋላ አይልም። ጤና ጣቢያ በድሮን እየደበደበ ትምህርት ላስተምር ሲል መጠርጠር አይከፋም ብየ ነው !

አቢሲኒያ ባንክ እንዲህ እንረዳው ! ከሰሞኑ ከአቢሲኒያ ባንክ ጋር ተያይዞ ባነሳሁት መረጃ ላይ ከአንዳንድ የባንኩ ኃላፊዎች ጋር ትክክለኛ ያሉትን መረጃ አድርሰውኛል። በነገራችን ላይ በባንኩ ላይ አማራ ጠሎች የነከሱበትን ጥርስና ያለበትን ጫና ለመረዳትም ችያለሁ። በመረጃየ ላይም እነ ስንቄ ባንክ ትናንት ተወልደው በባዶ ድድ ሲንከተከቱ ተመልክቼ እስከ ጥግ መረጃውን ለማወቅ ጥረት አድርጌ በደንብ ተረድቻለሁ። የተረዳሁትንም ለማከብራችሁ ቤተሰቦቼ በድጋሚ ለማስረዳት መጥቻለሁ። በመጀመሪያ የእኔ ሀሳብም በዋናነት ትኩረት ያደረገው የባንኩ ሰራተኞች financial security ላይ እንጅ ህዝባዊ አገልግሎቱን ወይም የንግድ ተቋም እስከሆነ ድረስ የባንኩ ተጠቃሚነት ላይም አላተኮርኩም ነበር። አቢሲኒያ ባንክ ጋር በዋናነት የተነሳው ነገር Digitalization ጋር ተያይዞ በመጡ Computerized በሆኑ አገልግሎቶች ምክንያት ነው። ከ Digitalization ጋር ተያይዞ ያለው አደገኛ ስጋት ምናልባት ወደፊት የሰዎችን ስራ ሙሉ በሙሉ ኮምፒውተሮች እና ሮቦቶች ተክተው በመስራት የሰዎችን ስራ በመንጠቅ ስራ አጥነትን እንዳያስፋፉ ነው። እዚህ የምኖርበት አሜሪካም አንድ ባንክ ውስጥ ቢበዛ 5 ወይም 6 ሰራተኞች ነው የምታገኙት ምክንያቱም ሁሉም ነገር computerized ነው። ኢትዮጵያም ውስጥ ድሮ ገንዘብ በስልክ ሲተላለፍበት ከነበረው ዘምኖ ሁሉም በሚባል ደረጃ ሞባይል ባንኪንግ ተጠቃሚ እየሆነ ነው። ይሄ ማለት ቀስ በቀስ ባንክ ውስጥ የተቀመጡ ሰራተኞች ያለስራ መዋል ይጀምራሉ ማለት ነው። ለትርፍ የተቋቋመ ባንክ ሰራተኛን እንዲሁ አስቀምጠህ ክፈል ብለን ማስገደድም እንዳይሆንብን መልሼ ቆም ብየ እንዳስብ ተገድጃለሁ። እስከአሁን ባለው ሁኔታ ግን ሰራተኞችን ቦታ በማሸጋሸግና ወደ ቀበሌ አውርዶ በመመደብ እንጅ በማባረር ደረጃ ምንም አይነት ስራ እንዳልተሰራ መስራትም እንደማይፈልጉ ከገለፁልኝ በኋላ ስራውን የማይሰራ ሰራተኛ ግን ችግር ውስጥ ሊገባ እንደሚችል አልሸሸጉኝም። ስለሆነም አቢሲኒያ ባንክም የላቁ ቴክኖሎጅዎችን መጠቀም በመጀመሩ paperless banking (ከወረቀት ንክኪ ነፃ) የሆነ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። ከዚህ ጋር ተያይዞ የባንክ ብዛት ያላቸው ሰራተኞች ባንክ ውስጥ መቀመጥ የግዴታ የማይሆንበት ጊዜ እየመጣ ነው ማለት ነው። በዚህ ደረጃ እንረዳው። ከዚያ ውጭ ስሙ አቢሲኒያ፣ አርማው አደይ አበባ፣ ባለአክሲዮኖች የኛ፣ ሰራተኞችም የእኛ፣ ተጠቃሚው ህዝብም የእኛ ነው። የአዋሽ እና ስንቄ ባንክን አማራ ጠልነት ግምት ውስጥ አስገብታችሁ የባንኩን ህልውና እንዴት እናስቀጥለው፣ ሰራተኞችንስ እንዴት ማብዛት ይቻላል የምትሉ አማራዎች ካላችሁ:- - የድርጅቶቻችሁን እና የግል አካውንታችሁን በአቢሲኒያ ባንክ አድርጉ - ከውጭ ዶላር የምትልኩ አማራዎች በአቢሲኒያ ባንክ ላኩ - የእቁብና እድር አካውንታችሁን በአቢሲኒያ ባንክ አድርጉ - ATM የአቢሲኒያን ማሽን ተጠቀሙ ከዚያ ውጭ የብልፅግና ባንክ (cbe) እና ሸኔ ባንክ (አዋሽ) እየተጠቀሙ ባንካችን ተነካ ማለት "ጉራ ብቻ" ያስብላል። ስለ ሁሉም ይቅርታ !

ህክምና የሚከለክል አገዛዝ ! እንኳን ከህዝብ ልብ የተፋቀው የኦሮሙማው አገዛዝ ይቅርና የትኛውም ህዝባዊ መንግስት ቢሆን እንኳ መውደቁ አይቀርም። ስለ ክቡር ክርስቲያን ታደለ ፍትህን ከኦሮሙማው አገዛዝ መጠየቅ ጉንጭ አልፋነት ነው። ኦሮሙማው በታሪኩ ፈሪ ነው። ፈሪ ደግሞ ከያዘህ አይምርህም። ፈሪው ኦሮሙማ ደግሞ ትችትንም የሚቋቋምበት የስነ-መንግስት ልምምድ የለውም። ትላንት የከብት ጭራ እየተከተለ የመጣ ለአገሪቱ እንግዳ ለሆነ አካል ስለ ኢትዮጵያዊነት ባህልና ወግም ግድ የለውም። ወዳጆቹም በሆዳቸው የወደቁ ራስ ጠል አማራዎች እንጅ እንደነ ክርስቲያን ታደለ አይነት ፅኑ አማራዎች አይደሉም። በአጭሩ ይሄ የፈሪዎች ስርዓት ማስወገድ እንጅ ለምነህ ፍትህ አታገኝም። የፍርድ ቤት ውሳኔ እንኳ አልተሰጠበትም። ምስክር ነን የሚሉ አማራዎች " ከመጋረጃ ጀርባ ተደብቀን መመስከር አለብን፤ ማንነታችን ከታወቀ አማራ ክልል የሚኖሩ ዘመዶቻችን ያልቃሉ።" በማለታቸውና ይሄን የህግ አካሄድ ደግሞ ጠበቃዎች ስለተቃወሙ የውሸት ክሱ እንኳ ውሳኔ አልተሰጠበትም። እንኳን አንድ ሀሙስ የቀረው ኦሮሙማው ይቅርና ሰማይ መሬቱ ሲሰግድላቸው የነበሩት ጃንሆይም ሆነ የአፍሪካ ባለገናናው ጦር ደርግም ወደቅዋል። ያን ጊዜ ፍትህን በእጃችን እንፅፋለን። ስነ ስርዓትን የሚያውቅ መንግስት ቢሆን ኑሮ እንኳን ክቡር ክርስቲያን ታደለ ቀርቶ የሰው ልጅ ሁሉ ህክምና መከልከል የለበትም ነበር። ወንድማለም ባለህበት ሰላም ሁንልኝ ! #እኔም ክርስቲያን ታደለ ነኝ !

ኢንጅነር ክበር ተመሰገን የማይረሳው ጀግና ! " ደምበጫ የባለጌ መቅጫ " የተባለው እንዲሁ አይደለም። ደምበጫ ሲነሳ ጠላት ሱሪው ላይ የሚሸናው ጀግንነትን በተግባር ስለሚያውቀው ነው። ከብዙ የአማራ ጀግኖች መካከል የመስከረም 5/2016 ዓ.ም አንድያ ነፍሱን ለአማራ ህዝብ አሳልፎ የሰጠውን ሰማዕቱ ኢንጂነር ክበር ተመስገንን እናስበው። ከአባቱ ከአቶ ተመስገን አሰግሀኝ ከእናቱ ከእማሆይ ሞሲት ምህረቴ ነሀሴ 16/ 1964 ዓ.ም ደምበጫ ከተማ ተወለደ። ኢንጅነር ክበር ተመስገን 1997 - 2002 ዓ. ም በዩኒቨርስቲ ቆይታው በሲቪል ኢንጂነሪንግ በከፍተኛ ውጤት ከተመረቀ በኋላ በግል ተቋራጭነት በግንባታው ዘርፍ የራሱን አሻራ አሳርፏል። በማህበራዊ ህይወቱም በደምበጫ ቅዱሰ ሚካኤል ቤተክርሰቲያን የሰንበት ትምህርት ቤት አገልጋይ የነበረና በፀባዩ አንቱ የተባለ ሰው ነበረ። ኢንጅነሩ ግፍንና ግፈኞችን አምርሮ ይፀየፍ ስለነበር ከ1985 እሰከ 2008 አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ባንዲራ በማውለብለብ ከደምበጫ አስከ ሞጣ በራሪ ወረቀቶችን በመበተንና ወጣቶችን በማንቃት እንዲሁም በወጣቶች ማህበር በመደራጀት ህወሓትን በመታገሉ ከፍተኛ ድብደባና የግድያ ሙከራ ተፈፅሞበት ነበር። ምቹ ጊዜ ሲጠብቅ የነበረው ኢንጂነሩ የአማራ ፋኖ ሲደራጅ ግንባር ቀደም በመሆን የጎጃምን ፋኖ በዋናነት በማደራጀት ይታወቃል። ከዚያ በኋላ በደንበጫና አካባቢው የአገዛዙን ጦር ምርኮ እና ቁስለኛ እንዲሆን በማድረግ ብዙ ዘመቻዎችን መርቶ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ውጤታማ ነበር ። ለተከታታይ አምስት ቀን የነበረው ትንቅንቅ አይረሴ ነው። መሰከረም 5 ቀን 2016 ዓ.ም የደምበጫ ፋኖ ሙሉ የአብይን ጨፍጫፊ ሰራዊት በማፅዳት ላይ የተጠመደ ነበርና ደንበጫ ከተማን ከተቆጣጠረ በኋላ ሙላለም በሚባል ጫካ ካምፕ ያደረገው ገዳይ ሰራዊት ጋር መፋለም ተጀመረ። እንጅነሩም አብሮ ዘሎ ምሽግ ውስጥ በመግባት እልህ አሰጨራሽ ውጊያ ከተደረገ በኋላ ሙሉ የጨፍጫፊው ሰራዊት ተደ*መሰሰ። በዚህ አውደ ውጊያ የገዳዩ ካምፕ በፋኖ እጅ ከሆነ በኋላ የጠላት ጦር መሪ የነበረው የኮ/ል ሰጤ ሚስት ለፋኖዎች ደውላ " ኮሎኔሉ እጁን ይሰጥ፤ አትግደለብኝ " በማለት ተማፀነች። ኮ/ል ሰጤም "እጅ ልሰጥ፣ መውጫ መንገድ ሰጡኝ፣ አማራነኝ ወሎዬ ነኝ አትግደሉኝ " በማለት ተማፀነ። ሩህሩሁ ኢ/ር ክበር ተመስገንና የሚመራቸው ፋኖ ተኩሰ ቀነሰና ኮ/ሉን በል እጅ ስጥ ሲሉት አጃቢዎቹን ብቻ እጃቸውን አንከርፈው እንዲሄዱ ካደረገ በኋላ እሱ ለካስ ሾልኮ ወጥቶ ሂዷል። እንዲያ በአማራነት እየማለ፣ የተሰጠውን የአማራነት መሃላ የበላው ኮ/ልም ድፍር በተባለ ቦታ የተበተኑ ወታደሮችን ይዞ መሸገ። ተጨማሪ ወታደር፣ ቢኤምና ታንክ ከፍኖተ ሰላም አስልኮ ውጊያ እስኪጀምር ደምበጫ ከተማን በድሮን መደብደብ ጀመሩ። ከተማዋንም አፈራረሷት። ሙሉ ቤተሰብ፣ ካህናቶች አሰከሬናቸው ተለቅሞ ተቀበረ። ደምበጫ በንፁሀን ደም ታጠበች። ይሄን ያየው ኢንጅነሩ ውጊያውን በድል ካጠናቀቀ በኋላ የከተማዋን መውደም ሲመለከት ግን ትቶ ወደ ጫካ መሸሽ አልፈለግም። ከትግል ጓዶቹ ጋር በመሆን እየተለቃቀመ የመጣውን የአገዛዙ ጦር በመደምሰስ እስከመጨረሻው መስዕዋትነትን ተቀበለ። ብዙ ጀግኖችም አብረው ተሰው። ኢንጅነሩ ዛሬ ከመካከላችን አብሮን ባይኖርም እሱ ከአርበኞች ባልተናነሰ ሁኔታ አሰባስቦ የጀመረው ትግል ግን በአሸናፊነት ግስጋሴ ላይ ነው፤ የሰበሰባቸው አሰልጥኖ ከጎኑ አሰልፎ ይመራቸው የነበሩ ጓዶቹ ሁሌም እሳት ፍም በእጃቸው እንደጨበጡ በጀግንነትና በቆራጥነት በስሙም ብርጌድ ተሰይሞለት የሚያቆማቸው ምድራዊ ሀይል ቀርቶ በድሮንና በመድፍ ቢዋጉም የደምበጫን ፋኖ አንገት ማሰደፋት አልተቻለም፤ አይቻልምም። ኢንጅነር ክበር ተመስገን ብርጌድ ዛሬም ብርጌዱ ጀግናውን እያሰበ ስራን የሚከውን ኩራት የሆነ ብርጌድ ነው። ኢ/ር ክበር ተመስገን ብር ግድ ሲባል ጠላት መውጫ መግቢያ የሚጠፋው እኮ ያለአንዳች ነገር አይደለም። የብርጌዱ ሀይልና አሸናፊነት ያለው ከስሙ ላይ ስለሆነ ነው። ይሄ እንዲሆን ጥዋት ማታ ለምትለፉ የብርጌዱ አባላትም ክብር ይገባችኋልና ክብር ያድላችሁ። መስከረም 5/2016 ዓ.ም ሲቪል ኢንጅነር ፋኖ ክበር ተመስገን ለአማራ ሲል ውድ ህይወቱን አሳልፎ የሰጠባት ክፉ ቀን !! አንረሳህም !

የኦህዴድ አገዛዝ በባህር ዳር ወቅታዊ አቋም ! እነ ሆድ አምላኩ ህዝባቸውን የካዱና የኦህዴድ ከፍተኛ እንደራሴዎች የጭፍጨፋው አሳላጮች በባህር ዳር ከ2017 ዓ.ም ጥር ወር ጀምሮ ከስልጣናቸው ተባረው ነገር ግን ካለው የፋኖ የህልውና ትግል አጣብቂኝ ውስጥ የገባው ብአዴን ልክ እንደ ጅ*ብ አመች ሁኔታን ሲጠብቅ ከርሟል። አዳሜ ተባራሪዎችም ሲጠጡ እያደሩ አረፋፍደው ከሃንጎቨር ሲነቁ የሽኝት ዜናውን ፌስቡክ ላይ ሲፈልጉ ውለው ያድሩ ነበር አሉ 😜 ጭንቀት !! " ከሰሞኑ ግን አለቃቸው ቀስበቀስ ሊነገራቸው ይገባል የሚል ትዕዛዝ አውርዷልና ሊነገራቸው ነው ያኔ የሚሆነውን እናያለን፤ አሁን ባለው ሁኔታ ሁሉ እርስ በራሱ በጥርጣሬና በጎሪጥ እየተያየ ነው በመሀከላቸው መተማመን የሚባል ነገር ጠፍቷል፣ ከሁሉም ተላላኪ ፊት ላይ ተስፋን ሳይሆን ጣዕረ ሞት ያሸነፈው የሚመስል ተስፋ ማጣትን ትመለከታለህ " ሲል ቀኜ የውስጥ አርበኞች አባል ሹክ ብሎኛል። በእርግጥ አይገርምም የበሻሻው ፋራ ባንዳዎችን ተጠቅሞ የመወርወር ጥሩ ልምድ ስላለው 😂 ለማንኛውም አሁን ሰራዊታቸው ብቻ ሳይሆን ካድሪያቸውም መፈራረሱን ይጀምራል፤ ለአቀባበሉ በደንብ ተዘጋጁ ! እንደ አሮጌ ቁና እንዳገለገለው ፣ ሰው መሆን አቅቶህ ነው የትም ምትጣለው። ቁናስ ክብር አለው በክብር ይቀመጣል ፣ የአንተ ግን መውደቂያ አ*ህያን ያስንቃል ።