en
Feedback
4-3-3 World News

4-3-3 World News

Open in Telegram

ይህ የእርሶ፣ የአንተ፣ የአንቺ፣ የእናንተ፣ የኛ የሁላችንም ድምጽ ነው! ለሃሳብ አስተያየት ለመስጠት @atsbaha12 ይጠቀሙ ለማስታወቂያ ስራ @Marketing_team433

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel 4-3-3 World News

Channel 4-3-3 World News (@ethionews433) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 50 316 subscribers, ranking 5 228 in the News & Media category and 666 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 50 316 subscribers.

According to the latest data from 08 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -275 over the last 30 days and by -28 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 38.10%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 29.30% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 19 174 views. Within the first day, a publication typically gains 14 746 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 235.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ይህ የእርሶ፣ የአንተ፣ የአንቺ፣ የእናንተ፣ የኛ የሁላችንም ድምጽ ነው! ለሃሳብ አስተያየት ለመስጠት @atsbaha12 ይጠቀሙ ለማስታወቂያ ስራ @Marketing_team433

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 09 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

50 316
Subscribers
-2824 hours
-1327 days
-27530 days
Posts Archive
"የህንድ አየር መንገድን እንደገና ታላቅ እናደርገዋለን" ሲሉ አቶ ተወልደ ገብረማርያም ቃል ገቡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቀድሞ ዋና ስራ አስፈፃሚ የነበሩት አቶ ተወልደ ገብረማርያም የህንድ
"የህንድ አየር መንገድን እንደገና ታላቅ እናደርገዋለን" ሲሉ አቶ ተወልደ ገብረማርያም  ቃል ገቡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቀድሞ ዋና ስራ አስፈፃሚ የነበሩት አቶ ተወልደ ገብረማርያም የህንድ አየር መንገድ አዲስ ዋና ስራ አስፈፃሚ እና ማኔጂንግ ዳይሬክተር በመሆን በታታ ግሩፕ ስር የሚተዳደረውን አየር መንገድ መምራት መጀመራቸው ተዘግቧል። በዋና መ/ቤቱ ከተደረገ የመጀመሪያ ስብሰባ በኋላ ባሰሙት ንግግር፣ ለአየር መንገዱ የደህንነት ስርዓት ልዩ ትኩረት እንደሚሰጡ አስታውቀዋል። የአየር መንገዱ ስራዎች በፍጥነት እያደጉ ባለበት በዚህ ወቅት የደህንነት ባህልን ማጠናከር ቀዳሚ ስራቸው መሆኑን የገለጹት አዲሱ ስራ አስፈፃሚ፣ "ኤር ኢንዲያን እንደገና ታላቅ እናደርገዋለን" በሚል መሪ ቃል አየር መንገዱን ተአማኒነት ወደሚጠበቅበት ከፍታ ለማድረስ እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል ሲል ካፒታል አስነብቧል። አቶ ተወልደ ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ አየር መንገድን ከአነስተኛ አህጉራዊ ተሸካሚ ወደ ዓለም አቀፍ ግዙፍ ኦፕሬተር ያሳደጉበትን ልምድ በመጠቀም፣ አሁን ላይ አየር መንገዱ ካለው ሰፊ የዕድገት ሂደት ጋር የተጣጣመ ጠንካራ የኢንጂነሪንግ፣ የጥገና እና የሰራተኞች ስልጠና ማዕቀፍ እንዲኖር ለማስቻል ርብርብ እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።   @Ethionews433 @Ethionews433

ካናዳ በአሜሪካ ምርቶች ላይ አዲስ ቀረጥ ጣለች ካናዳ ከአሜሪካ ጋር ያላት የንግድ ውዝግብ እየተባባሰ ባለበት ሁኔታ በአሜሪካ ምርቶች ላይ አዲስ ቀረጥ መጣል ጀምራለች። ከማክሰኞ ጀምሮ ተግባራዊ የሆነ
ካናዳ በአሜሪካ ምርቶች ላይ አዲስ ቀረጥ ጣለች ካናዳ ከአሜሪካ ጋር ያላት የንግድ ውዝግብ እየተባባሰ ባለበት ሁኔታ በአሜሪካ ምርቶች ላይ አዲስ ቀረጥ መጣል ጀምራለች። ከማክሰኞ ጀምሮ ተግባራዊ የሆነው እና በአሜሪካ ምርቶች ላይ የተጣለው ቀረጥ ወደ 28 ቢሊዮን የካናዳ ዶላር፣ ወይም ወደ 20 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር እንደሚደርስ ቢቢሲ አስነብቧል። በቀረጡ ከሚካተቱት ምርቶች መካከል ብረት፣ የቤት ዕቃዎች፣ ልብሶች፣ ኤሌክትሮኒክስና የተለያዩ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች ይገኙበታል። ይህ እርምጃ የመጣው በቅርቡ አሜሪካ በካናዳ ምርቶች ላይ እስከ 50 በመቶ የሚደርስ ቀረጥ መጣሏ ተከትሎ ነው። አሜሪካ በካናዳ መኪናዎችና የጭነት መኪናዎች ላይ 25 በመቶ ቀረጥ እንዲሁም በብረትና አልሙኒየም ላይ ተጨማሪ ቀረጥ አስቀምጣለች። የንግድ ግጭቱ በአሜሪካና ካናዳ ንግዶች ላይ ብቻ ሳይሆን በሸማቾችም ላይ ተጽዕኖ ሊያሳድር እንደሚችል ተገልጿል። ሁለቱ አገራት የንግድ ግጭቱን በድርድር ለመፍታት ፍላጎት እንዳላቸው ቢገልጹም፣ በነሐሴ መጨረሻ ያቋረጡትን የንግድ ድርድር እስካሁን እንደገና አልጀመሩም።   ሰላማዊት ዲታ   @Ethionews433 @Ethionews433

በእሳተ ገሞራ ፍንዳታ ምክኒያት በኢንዶኔዥያ የ270ሺ መንገደኞች ጉዞ ተስተጓጎለ የኢንዶኔዥያ ባለስልጣናት በእሳተ ገሞራ ፍንዳታ ምክኒያት በስምንት አውሮፕላን ማረፊያዎች የሚሰጠውን አገልግሎት በጊዜያ
በእሳተ ገሞራ ፍንዳታ ምክኒያት በኢንዶኔዥያ የ270ሺ መንገደኞች ጉዞ ተስተጓጎለ የኢንዶኔዥያ ባለስልጣናት በእሳተ ገሞራ ፍንዳታ ምክኒያት በስምንት አውሮፕላን ማረፊያዎች የሚሰጠውን አገልግሎት በጊዜያዊነት ለማቋረጥ መገደዳቸውን ተከትሎ፣ የ270ሺ መንገደኞች ጉዞ ተስተጓጉሏል። የአናክ ክራካታው እሳተ ገሞራ አመድ በአውሮፕላን ማረፊያው አቅራቢያ በሚገኝ የአየር ክልል ውስጥ መታየቱን ተከትሎ፣ እሁድ ጠዋት መጀመሪያ የተዘጋው በጃካርታ የሚገኘው የሶካርኖ-ሀታ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ነው።የትራንስፖርት ሚኒስቴሩ አውሮፕላን ማረፊያዎቹ እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ ዝግ ሆነው እንደሚቆዩና ከ 2ሺ በላይ በረራዎች መዘግየታቸውን አስታውቋል። እሳተ ገሞራው አርብ ምሽት ላይ መፈንዳት የጀመረ ሲሆን፣ ተከታታይነት ያለው የመሬት ንዝረት እና ከፍተኛ የፍንዳታ ድምፆችን አስከትሏል። እሁድ ማለዳ ላይ ተጨማሪ ሁለት ፍንዳታዎች መከሰታቸውን ባለስልጣናት ገልጸዋል።የበረራ አገልግሎቶች መቋረጥ በዋናነት ከሲንጋፖር እና ወደ ሲንጋፖር የሚደረጉ በረራዎችን ያስተጓጎለ ሲሆን፣ ዶሃን፣ ሲድኒን እና ኩዋላልምፑርን ጨምሮ ሌሎች ዓለም አቀፍ የበረራ መስመሮችም ተጎድተዋል ሲል የትራንስፖርት ሚኒስቴሩ አስገንዝቧል። የትራንስፖርት ሚኒስትሩ ዱዲ ፑርዋጋንዲ ተጨማሪ አውሮፕላን ማረፊያዎችን በጊዜያዊነት ለመዝጋት ውሳኔ ላይ የተደረሰው፣ የእሳተ ገሞራው አመድ ወደ ምዕራብ ጃቫ አቅጣጫ መሰራጨቱን ምርመራዎች ማረጋገጣቸውን ተከትሎ ነው ብለዋል።በረራ በመሰረዙ ምክኒያት ለተስተጓጎሉ መንገደኞች የቲኬት ገንዘብ ተመላሽ የማድረግ ሂደትን አየር መንገዶች እንዲያፋጥኑ ያሳሰቡት ሚኒስትሩ፣ በአውሮፕላን ማረፊያዎች የሰዎች መጨናነቅን ለማስቀረት አየር መንገዶች ቀጣይ በረራ ላላቸው መንገደኞች ወቅታዊ መረጃ እንዲያቀርቡም ጠይቀዋል። የኢንዶኔዥያ የሚቲዎሮሎጂ ኤጀንሲ መረጃ እንደሚያመለክተው፣ የእሳተ ገሞራው አመድ ከእሳተ ገሞራው በስተምስራቅ በኩል በጃቫ እስከ 20ሺ ጫማ ከፍታ ላይ የደረሰ ሲሆን፣ ከእሳተ ገሞራው በስተምዕራብ በሱማትራ በኩል ደግሞ 50ሺ ጫማ ከፍታ ላይ ደርሷል። በሚኪያስ ጸሀዬ @Ethionews433 @Ethionews433

Repost from 4-3-3 Tech
ቻይና ዓለም አቀፍ ቀዳሚ የሆነውን አእምሮን ከኮምፒውተር ጋር የሚያገናኝ ቴክኖሎጂ ለገበያ እንዲቀርብ ፈቀደች የቻይና ብሔራዊ የመድኃኒትና የሕክምና ምርቶች አስተዳደር NEO የተሰኘውን የሳንቲም ያህል
ቻይና ዓለም አቀፍ ቀዳሚ የሆነውን አእምሮን ከኮምፒውተር ጋር የሚያገናኝ ቴክኖሎጂ ለገበያ እንዲቀርብ ፈቀደች የቻይና ብሔራዊ የመድኃኒትና የሕክምና ምርቶች አስተዳደር NEO የተሰኘውን የሳንቲም ያህል መጠን ያለው አእምሮን ከኮምፒውተር ጋር የሚያገናኝ (BCI) ቴክኖሎጂ ለገበያ እንዲቀርብ ፈቃድ ሰጥቷል። በጽንግሁዋ ዩኒቨርሲቲ እና በኒውራክል ቴክኖሎጂ የተገነባው ይህ መሳሪያ፣ ከምርምር ማዕከላት ውጭ የሰዎችን የእንቅስቃሴ አቅም ለመመለስ ለገበያ እንዲቀርብ ፈቃድ ያገኘ በዓለማችን የመጀመሪያው በአእምሮ ውስጥ የሚተከል ቴክኖሎጂ ሆኗል። የኢሎን መስክ ኒውራሊንክ (Neuralink) አሁንም በሰው ልጅ ላይ በሚደረግ የሙከራ ደረጃ ላይ ብቻ የሚገኝ ሲሆን፣ NEO ግን ደህንነቱን ባስቀደመው ልዩ ዲዛይኑ ምክንያት በፍጥነት የንግድ ፈቃድ ማግኘት ችሏል። መሳሪያው የአእምሮ ክፍሎችን ጥሶ ከመግባት ይልቅ ስምንት ሴንሰሮቹ ከአእምሮ ውጫዊ ሽፋን (dura mater) ላይ በደህና ሁኔታ የሚያርፉ በመሆናቸው የህብረህዋሳት ጉዳትንና ደም መፈሰስን በእጅጉ ይቀንሳል። ይህ ፈቃድ በፅኑ የአንገት አጥንትና የሕብረ-ሰstandard አደጋ ምክንያት ሙሉ በሙሉ የእጅና የእግር ሽባነት ለገጠማቸው ነገር ግን የተወሰነ የእጅ እንቅስቃሴ ላላቸው ከ18 እስከ 60 ዕድሜ ክልል ውስጥ ላሉ አዋቂዎች ብቻ የሚያገለግል ነው። በ11 ሆስፒታሎች ውስጥ በተደረጉ የሕክምና ሙከራዎች፣ ስርዓቱ በቤት ውስጥ በአእምሮ እዘዛ ዕቃዎችን የመጨበጥ ድጋፍ በመስጠት 100 በመቶ ስኬት አስመዝግቧል። ይህ ቴክኖሎጂ የሰዎችን የሃሳብ ፍላጎት በመተርጎም ከሮቦቲክ የእጅ ጓንት ጋር በማያያዝ፣ ታካሚዎች እንደ መብላትና መጠጣት ያሉ የዘወትር ተግባራቸውን በራሳቸው እንዲያከናውኑ አስችሏቸዋል።(የኔታ) https://t.me/+5sCQf3Z1UUAxZDAy

ኤኮን በመካከለኛው ምስራቅ ለሚገኙ ሶስት ባለፀጋ ሰዎች ብቻ “Lonely” የተሰኘውን አንድ ዘፈን ብቻ ለአንድ ሰዓት ያህል ደጋግሞ እንዲዘፍን 1 ሚሊዮን ዶላር እንደተከፈለው ገለፀ ታዋቂው የዓለም አ
ኤኮን በመካከለኛው ምስራቅ ለሚገኙ ሶስት ባለፀጋ ሰዎች ብቻ “Lonely” የተሰኘውን አንድ ዘፈን ብቻ  ለአንድ ሰዓት ያህል ደጋግሞ እንዲዘፍን 1 ሚሊዮን ዶላር እንደተከፈለው ገለፀ ታዋቂው የዓለም አቀፍ የሙዚቃ ኮከብ ኤኮን (Akon) በቅርቡ በነበረው የFlagrant ፖድካስት ቆይታው፥ በአንድ ወቅት በመካከለኛው ምስራቅ በሚገኝ አንድ ባለጸጋ ቤተሰብ የሙዚቃ ኮንሰርት እንዲዘፍንተቀጥሮ ያስተናገደውን እጅግ አስገራሚ እና እንግዳ የሆነ የኮንሰርት ታሪክ ይፋ አድርጓል። ድምፃዊው ለግል የሙዚቃ ዝግጅቱ የ1 ሚሊዮን ዶላር ክፍያ ተፈፅሞለት በቅንጦት ቦይንግ 747 የግል አውሮፕላን ተሳፍሮ ወደ ስፍራው ቢያቀናም፤ ታላቅ መድረክ እና የሌዘር መብራቶች በተዘጋጁበት ግዙፍ አዳራሽ ውስጥ የጠበቁት ግን ሶስት ተመልካቾች ብቻ ነበሩ። በወቅቱ በአዳራሹ መሃል በተቀመጡ ሶስት ወንበሮች ላይ የነበሩት ባለጸጋዋ እናት ከሁለት ልጆቻቸው ጋር ብቻ የነበሩ ሲሆን፤ ዝግጅቱ እንደተጀመረ የባለጸጋው ቤተሰብ ሴት ልጅ ኤኮን በ2005 ዓ.ም ያወጣውንና ዝነኛ ያደረገውን “Lonely” የተሰኘውን ዘፈን እንዲጫወት ጠየቀችው። ዘፈኑ ባለቀ ቁጥር እየሳቀች “ድገመው” በማለት ለአንድ ሰዓት ያህል ያንንኑ አንድ ዘፈን ብቻ ደጋግሞ እንዲዘፍን እንዳደረገችው ያስታወሰው ኤኮን፥ ሌላ ዘፈን ለመዝፈን ሲዘጋጅ ፣ እጅግ ተዝናንተናል እናመሰግናለን ይበቃናል ብለዉ ዝግጅቱ እንደተጠናቀቀ ገልጿል። ኤኮን ክስተቱን ሲያስታውስ፦ “እጅግ ከፍተኛ ሀብት ሰውን እንደ ‘ግል ሲዲ ማጫወቻ’ (Personal CD Player) ሊያደርግ እንደሚችል የተረዳሁበት ነበር፤ ግን ክፍያዬን በደስታ ይዤ ወጥቻለሁ” ብሏል። via መዝናኛ ሚዲያ @Ethionews433 @Ethionews433

በቦንጋ ከተማ የተሰረቁ ሞባይሎችን የገዙ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ . በቦንጋ ከተማ የተሰረቁ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን በተለይም ሞባይሎችን የገዙና የተቀበሉ ግለሰቦች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው ም
በቦንጋ ከተማ የተሰረቁ ሞባይሎችን የገዙ ግለሰቦች  በቁጥጥር ስር ዋሉ . በቦንጋ ከተማ የተሰረቁ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን  በተለይም ሞባይሎችን የገዙና የተቀበሉ ግለሰቦች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን የቦንጋ ከተማ ፖሊስ አስታውቋል። የቦንጋ ከተማ ወጣቶች ያለአግባብ እየታሰሩ ነው በሚል በማህበራዊ ትስስር ገጾች የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑንና ዓላማውም ወንጀል የፈጸሙ ግለሰቦች በህግ እንዳይጠየቁ ለማድረግ እንደሆነ ፖሊስ ገልጿል። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለፁት በከተማው የስርቆት ወንጀል ተፈጽሞ የተሰረቁ ሞባይሎችን የሚገዙ፣ የሞባይል ይለፍ ቃል የሚጠልፉ እና ከህገወጥ የስርቆት ተግባር ፈጻሚዎች ጋር ግንኙነት ያላቸው አምስት ግለሰቦች በመረጃ እንዲለዮ ተደርጓል። በሞባይል ጥገና ስራ የተሰማሩ አራት ግለሰቦችም በቁጥጥር ስር ውለዋል።አንደኛው ተጠርጣሪ መሰወሩ የተገለፀ ሲሆን በቁጥጥር ስር ለማዋል ፖሊስ በክትትል ላይ ይገኛል ሲሉ ኢንስፔክተሩ ጨምረው ገልፀዋል።ተጠርጣሪዎቹ የተሰረቁ ሞባይሎችን የይለፍ ቃል በመክፈትና በውስጣቸው ያሉ መረጃዎችን በማጥፋት ገንዘብ ሲቀበሉ እንደነበር ተነግሯል። ፖሊስ በተጨማሪም የተሰረቁ ዕቃዎችን የሚገዙ፣ የሚረከቡና የሚያጓጉዙ ግለሰቦች እንዲሁም ባለሦስት እግር ባጃጅ ተሽከርካሪዎች በመኖራቸው ህብረተሰቡ እነዚህን ሕገወጥ ተግባራት ለመከላከልና ወንጀለኞችን ለሕግ ለማቅረብ ከፖሊስ ጋር እንዲተባበር ጥሪ አቅርቧል። በሳምራዊት ስዮም @Ethionews433 @Ethionews433

የዛክሰን አንሀልት ምርጫ ውጤት በሜርስ ላይ የሚያሳድረው ተጽእኖ በምስራቅ ጀርመንዋ የዛክሰን አንሀልት ግዛት ትናንት እሁድ የተካሄደው ምርጫ ውጤት በጀርመን ፌዴራል መንግሥት ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ሊያ
የዛክሰን አንሀልት ምርጫ ውጤት በሜርስ ላይ የሚያሳድረው ተጽእኖ በምስራቅ ጀርመንዋ የዛክሰን አንሀልት ግዛት ትናንት እሁድ የተካሄደው ምርጫ ውጤት በጀርመን ፌዴራል መንግሥት ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ሊያሳድር እንደሚችል እየተነገረ ነው። AfD 43.8 በመቶ ድምጽ በማግኘት እጅግ በገዘፈበት በእሁዱ ምርጫ ወግ አጥባቂው የክርስቲያን ዴሞክራት ኅብረት ፓርቲ ኮስሷል። ፓርቲው ከዚህ ቀደሙ ምርጫ ያነሰ 17.2 በመቶ ድምጽ ብቻ ነው ያገኘው። ውጤቱ AfD ካስመዘገበው ጋር ሲነፃጸር ከ26 በመቶ በታች ነው። የዚህም ምክንያቱ የዶቼቬለው የንስ ቱራው እንደዘገበው መራጩ ህዝብ በክርስቲያን ዴሞክራቱ ፖለቲከኛ የጀርመን መራኄ መንግሥት ፍሪድሪሽ ሜርስ አለመርካቱ መሆኑ ነው የሚነገረው። በዛክሰን አንሀልት የAfD ድል የጀርመን መራኄ መንግሥት የፍሪድሪሽ ሜርስ ሽንፈት ተደርጎ ተወስዷል። ውጤቱ በተመሳሳይ ሁኔታ ውስጥ ለሚገኙ ለሌሎች የአውሮጳ ሀገራት መሪዎች የማስጠንቀቂያ መልዕክት ያስተላልፋል ተብሏል። እጅግ የተራራቀ ጽንፍ በያዘው የጀርመን የፖለቲካ ስርዓት ውስጥ ሜርስ በህዝብ ዘንድ ያላቸው ተቀባይነት አሽቆልቁሏል። መራጩ ህዝብ ከሚያማርራቸው ጉዳዮች ውስጥ የኑሮ ውድነት እና የጡረታ ጉዳይ እዲሁም የኤኮኖሚ ዋስትና ማጣት ዋነኛዎቹ ናቸው። ኢንፍራሴት ዲማፕ የተባለው ተቋም ARD ለተባለው የጀርመን ቴሌቪዥን ጣቢያ ባካሄደው የዳሰሳ ጥናት ከተሳተፉት 87 በመቶው በአሁኑ የጀርመን መንግሥት ደስተኛ አይደሉም። ZDF ለተባለው ለሌላ የቴሌቪዥን ጣቢያ የተካሄደ የዳሰሳ ጥናት ላይ የCDUን ደጋፊዎች ጨምሮ ከተካፈሉት ሦስት አራተኛው ደግሞ የፓርቲውን ውጤት የጎዱት ሜርስ ናቸው ብለው ያምናሉ።ሜርስ ዛሬ ስለ ምርጫው ውጤት ለፓርቲያቸው ስራ አስፈጻሚ ቦርድ እንዳሉት ውጤቱ ፓርቲያቸውን መሠረቱ ድረስ አናግቶታል። ያም ሆኖ ከAfD ጋር እንደማይተባበሩ ነው ያሳወቁት። AfD የዛሬ ሦስት በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄደውን አጠቃላይ ምርጫ ለማሸነፍ የትናንትናውን ውጤት አንድ እርምጃ ብሎታል። ቀኝ ጽንፈኛው ፓርቲ ናሽዮናል ራሊ በፈረንሳይ በሚቀጥለው ዓመት በሚካሄደው ምርጫ እንደሚያሸንፍ የህዝብ አስተያየት መመዘኛዎች ያመለክታሉ። የፈረንሳይ የገንዘብ ሚኒስትር የዛክሰን አንሀልቱን ምርጫ ውጤት በጣም በጣም አሳሳቢ ምልክት በማለት አስጠንቅቀዋል። ምንም እንኳን በዛክሰን አንሀልት ልዩ ልዩ ለውጦችና እደገቶች እየመጡ ቢሆንም የህዝቡ ልብ በAfD ተሰርቋል። በአሁኑ ጀርመን የምትከተለውን የፍልሰት አቋም የሚጻረረው AfDን መምረጥ በግዛቲቱ በተለይ የውጭ መዋዕለ ነዋይን ሊያሽሽ እንደሚችል ሜርስን ጨምሮ ሌሎች ፖለቲከኞች ቢያስጠነቅቁም ሰሚ ያገኙ አይመስልም። የ35 ዓመቱ የፓርቲው እጩ ኡልሪሽ ዚግመንድ «የጥንቷን ጀርመን እንመልሳለን» በማለት በምርጫ ዘመቻዎቻቸው በገቡት ቃል ህዝቡን ለመሳብ መብቃታቸው በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎችም በርካታ ህዝብ መድረስ መቻላቸው ስኬታማ ሆነዋል። ሜርስ አሁን ከተጋፈጧቸው ጉዳዮች ውስጥ ቀውስ ውስጥ ያለው የጀርመን ኢንዱስትሪ ፣የጡረታ ማሻሻያ ይገኙበታል። ይሁንና እነዚህ ጥረቶቻቸው በምስራቅ ጀርመን ያን ያህል የህዝቡን ትኩረት አልሳቡም። ታዋቂው የጀርመን የመኪና አምራች ኩባንያ ፎክስቫገን ጀርመንን ጨምሮ በውጭ ሀገራት 50 ሺህ የስራ መደቦችን ሊቀነስ እንደሚችል ፣ጀርመን የሚገኙ ዋና ዋና ፋብሪካዎቹንም እንደሚዘጋ ማሳወቁ ትልቁ የአውሮጳ ኤኮኖሚ ምን ያህል ችግር ውስጥ እንደወደቀ አመልካች ሆኗል። በዩክሬን ጦርነት እና በኢራኑ ግጭት የተሰቀለው የነዳጅ ዋጋም ለAfD ድል ጠቅሟል። @Ethionews433 @Ethionews433

የአሜሪካ ከፍተኛ ባለሥልጣን ከኢራን ጋር «የኑክሌር ስምምነት ላይደረስ ይችላል» አሉ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው የሃይል እርምጃ በተባባሰበት በዚህ ወቅት፣ የአሜሪካ የኢነርጂ ሚኒስትር
የአሜሪካ ከፍተኛ ባለሥልጣን ከኢራን ጋር «የኑክሌር ስምምነት ላይደረስ ይችላል» አሉ   በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው የሃይል እርምጃ በተባባሰበት በዚህ ወቅት፣ የአሜሪካ የኢነርጂ ሚኒስትር ክሪስ ራይት ከኢራን ጋር የኑክሌር ስምምነት የመፈራረም እድሉ አነስተኛ መሆኑን ገልጸዋል።   ሚኒስትሩ እሁድ ዕለት ከኤቢሲ ኒውስ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ አሜሪካ ስምምነት ከማድረግ ይልቅ የኢራንን የኑክሌር መሰረተ ልማት እና አቅም በወታደራዊ ድብደባ ወደ ማፍረስ ልታደላ እንደምትችል ጠቁመዋል።   ኢራን የኑክሌር ፕሮግራሟ ለሰላማዊ መንገድ ብቻ እንደሆነ ትገልጻለች፣ አሜሪካ ግን የኢራንን የኑክሌር እና የሜሳይል ማምረት አቅም እያዳከመች እንደሆነ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።   አክለውም ከኢራን ጋር ስምምነት ላይ መድረስ የሚቻለው ወደፊት በሚመጣው አዲስ የኢራን አስተዳደር ወቅት ሊሆን እንደሚችል ገልጸዋል። ይህም የትራምፕ አስተዳደር በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ስምምነት ለማድረግ ያለው ተስፋ እየመነመነ መምጣቱን ያሳያል።   @Ethionews433 @Ethionews433

ከማረሚያ ቤት ከተፈታ በሦስተኛ ቀኑ የአምቡላንስ ተሽከርካሪ ቁልፍ የሰረቀው ግለሰብ በጽኑ እሥራት ተቀጣ። ከዚህ ቀደም በተጣለበት የፍርድ ውሳኔ መሠረት በማረሚያ ቤት ቆይታ የእስር ጊዜውን አጠናቆ በ
ከማረሚያ ቤት ከተፈታ በሦስተኛ ቀኑ የአምቡላንስ ተሽከርካሪ ቁልፍ የሰረቀው ግለሰብ በጽኑ እሥራት ተቀጣ። ከዚህ ቀደም በተጣለበት የፍርድ ውሳኔ መሠረት በማረሚያ ቤት ቆይታ የእስር ጊዜውን አጠናቆ በወጣ በሦስተኛው ቀን በድጋሚ በስርቆት ወንጀል የተከሰሰው አቶ ያሬድ ገብረሚካኤል የተባለው ግለሰብ መሆኑ የአክሱም ከተማ ፖሊስ  አስታውቋል። የማዕከላዊ ዞን ዓቃቤ ሕግ ቢሮ እንዳስታወቀው ተከሳሹ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀመው፣ ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ.ም በዓድዋ ከተማ በሚገኝ አንድ ሆስፒታል ያለችን እህቱን ለመጠየቅ የመጓጓዣ ገንዘብ እንደሌለው በመግለጽ በዓድዋ ከተማ ቀይ መስቀል ማህበር አምቡላንስ ተሳፍሮ በመጓዝ ላይ በነበረበት ወቅት ነው። ግለሰቡ በተሳፈረበት አምቡላንስ ውስጥ ተቀምጦ የነበረውን የተሽከርካሪውን ቁልፍ ሰርቆ ከተሰወረ በኋላ በጸጥታ አካላት በተደረገ ክትትል በአክሱም ከተማ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተሰምቷል።የአክሱም ከተማ ፖሊስ ወንጀል ፈፃሚዉን እጅ ከፍንጅ ይዞ በቁጥጥር ስር በማዋሉ አስፈላጊውን ማጣራት በማጠናቀቅ መዝገቡን ለዓቃቤ ሕግ አቅርቧል። ጉዳዩን ሲከታተል የቆየው የአክሱም ከተማ ፍርድ ቤትም ነሐሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት የቀረበበትን የሰነድ እና የሰው ማስረጃ መርምሮ ግለሰቡ በተከሰሰበት የስርቆት ወንጀል ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ በ6 ዓመት ከ6 ወር ጽኑ እሥራት እንዲቀጣ ወስኖበታል። በሰብል አበበ @Ethionews433 @Ethionews433

ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌው የሙዚቃ አልበም ሊለቁ ነው! ላለፉት ሶስት አስርት አመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ እንቅስቃሴ በማድረግ የሚታወቁት አቶ ልደቱ፤ ሀሳብን በዜማ በሚል ለአዲስ አመት የሙዚ
ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌው የሙዚቃ አልበም ሊለቁ ነው! ላለፉት ሶስት አስርት አመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ እንቅስቃሴ በማድረግ የሚታወቁት አቶ ልደቱ፤ ሀሳብን በዜማ በሚል ለአዲስ አመት የሙዚቃ አልበም ሊያሰራጩ መሆኑን ገልጸዋል። ፖለቲከኛው አዲስ የከፈቱትን የዩቲዩብ ገጽ ይፋ ባደረጉበት ወቅት እንዳሳወቁት የሙዚቃ አልበሙን ያዘጋጁት አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን በመጠቀም ነው። እንደሚታወሰው ቴዲ አፍሮ ኢቶሪካ አልበሙን ካሰራጨ በኋላ የፈጠረውን ተጽእኖ ተከትሎ አቶ ልደቱ በወቅቱ፣ "የመንፈስ ቅናት አደረብኝ" ሲሉ ገልጸው ነበር። (አንዳፍታ ) @Ethionews433 @Ethionews433

ሩሲያ እና አሜሪካ በዩክሬን ጦርነት እልባትና በሁለተናዊ ግንኙነት ዙሪያ መክረዋል። የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን፤ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ልዩ መልእክተኞች ስቲቭ ዊትኮፍ እና ጃ
ሩሲያ እና አሜሪካ በዩክሬን ጦርነት እልባትና በሁለተናዊ ግንኙነት ዙሪያ መክረዋል። የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን፤ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ልዩ መልእክተኞች ስቲቭ ዊትኮፍ እና ጃሬድ ኩሽነር ጋር ውይይት አደረጉ። ከሦስት ሰዓታት በላይ የፈጀውና በሞስኮ የተካሄደው ይኸው ስብሰባ “ፍሬአማ፣ ገንቢ እና እጅግ ግልጽ” እንደነበር የክሬምሊን ረዳት ዩሪ ኡሻኮቭ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል። ፕሬዝዳንት ፑቲን በሰላም ሂደቱ ውስጥ በአሜሪካን ልዑካን ላይ ከፍተኛ እምነት እንዳላቸው ገልጸው፤ ለፖለቲካዊና ዲፕሎማሲያዊ መፍትሔዎች ከአሜሪካ ጋር አብሮ ለመሥራት ሩሲያ ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል። አሜሪካውያኑ ልዑካን በጥሩ ሁኔታ ተዘጋጅተው መቅረባቸውንና ወደ መፍትሔ ሊወስዱ የሚችሉ ሃሳቦችን ማቅረባቸው የተገለጸ ሲሆን፤ በኪዬቭ በሚያደርጓቸው ቀጣይ ግንኙነቶችም የፑቲንን ግምገማዎች እንደሚጠቀሙባቸው ታውቋል። የዕለቱ ውይይት ከዩክሬን ቀውስ ባለፈ በሁለቱ አገሮች መካከል ያለውን ኢኮኖሚያዊ ትብብር እና ሊሠሩ የሚችሉ ግዙፍ የጋራ ፕሮጀክቶችን መቃኘቱ ተገልጿል። ልዑካኑ በሞስኮ ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ውይይት ካደረጉ በኋላ ወደ ኪዬቭ በማቅናት ከዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዜሌንስኪ ጋር ዛሬ እሁድ ዕለት እንደሚገናኙ ተረጋግጧል። ስለ ልዑካኑ ጉብኝት የተጠየቁት ትራምፕ “ጦርነቱን ለማቆም የቀረበ ሀሳብ ይዘው ሄደዋል” ማለታቸውን ቢቢሲ አስታውሷል። የአሜሪካ ፕሬዝዳንት መልዕክተኞች ስቲቭ ዊትኮፍ እና ጃሬድ ኩሽነር፣ ከዚህ ቀደም ሩሲያን ብዙ ጊዜ ጎብኝተዋል። በዩክሬን የሚያደርጉት ውይይት ግን የመጀመሪያው ይሆናል። ዜሌንስኪ በልዑካኑ ጉብኝት ወቅት በዩክሬን አየር ክልል ደኅንነታቸው እንደሚጠበቅ ዋስትና ሰጥተው፣ ሩሲያም በተመሳሳይ መንገድ ለልዑካኑ ደኅንነት ዋስትና እንድትሰጥ ጠይቀዋል። @Ethionews433 @Ethionews433

መርካቶ ዛሬም ነደደች ..... በተለምዶ ጣሳ ተራ በመባል የሚታወቀው ስፍራ አከባቢ በሚገኙ የልብስ እና መሰል መሸጫ ሱቆች ላይ ከፍተኛ የሆነ የእስት ቃጠሎ መድረሱ ተገልጿል።
መርካቶ ዛሬም ነደደች ..... በተለምዶ ጣሳ ተራ በመባል የሚታወቀው ስፍራ አከባቢ በሚገኙ የልብስ እና መሰል መሸጫ ሱቆች ላይ ከፍተኛ የሆነ የእስት ቃጠሎ መድረሱ ተገልጿል።

በጃፓን ያኩሺማ ከተማ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከፍተኛው የመሬት መንሸራተት ማስጠንቀቂያ ተሰጠ። የጃፓን የአየር ሁኔታ ኤጀንሲ በካጎሺማ ግዛት ስር በምትገኘው ያኩሺማ ከተማ ከፍተኛውን የመሬት መንሸራተ
በጃፓን ያኩሺማ ከተማ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከፍተኛው የመሬት መንሸራተት ማስጠንቀቂያ ተሰጠ። የጃፓን የአየር ሁኔታ ኤጀንሲ በካጎሺማ ግዛት ስር በምትገኘው ያኩሺማ ከተማ ከፍተኛውን የመሬት መንሸራተት ወይም የናዳ አደጋ ማስጠንቀቂያ አውጥቷል። ኤጀንሲው ይህንን ከፍተኛ ደረጃ ያለው ማስጠንቀቂያ ያወጣው፣ በአካባቢው ታሪክ የማይረሳውና ክብረ ወሰን የሰበረ የዝናብ መጠን መመዝገቡን ተከትሎ ነው። በከባድ ዝናቡ ምክንያት ሊከሰት የሚችለውን የመሬት መንሸራተት አደጋ ለመከላከል ነዋሪዎች አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉና የደህንነት መመሪያዎችን እንዲከተሉ ጥሪ ቀርቧል። ይህ ከፍተኛው ደረጃ ላይ የሚገኝ ማስጠንቀቂያ ነዋሪዎች ሕይወታቸውን ለመታደግ አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስዱ የሚያሳስብ መሆኑም ተገልጿል። በአካባቢው ያለው የዝናብ ሁኔታ አሁንም አሳሳቢ በመሆኑ፣ የሚመለከታቸው አካላት ሁኔታውን በቅርበት እየተከታተሉ ይገኛሉ ሲል አናዶሉ ዘግቧል። ልዑል ወልዴ @Ethionews433 @Ethionews433

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶችን በመጠቅለያዎቹ ላይ የሚያሰፍረው የአሜሪካው በርገር ቤት ኢን-ኤንድ-አውት ተቃውሞ ቢገጥመውም መቼም ታሪካዊ ልምዱን እንደማይተው አስታወቀ በአሜሪካ አገር 424 ቅርንጫፎች ያሉ
+2
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶችን በመጠቅለያዎቹ ላይ የሚያሰፍረው የአሜሪካው በርገር ቤት ኢን-ኤንድ-አውት ተቃውሞ ቢገጥመውም መቼም ታሪካዊ ልምዱን እንደማይተው አስታወቀ በአሜሪካ አገር 424 ቅርንጫፎች ያሉት እና ከ28,000 በላይ ሰራተኞችን የሚያስተዳድረው ዝነኛው የፈጣን ምግብ ሰንሰለት ኢን-ኤንድ-አውት በሚሸጣቸው የበርገር ማሸጊያዎች ላይ የሚያትማቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች በደንበኞች እና በሲቪል መብት ተሟጋቾች መካከል ሰፊ የሃሳብ መከፋፈል ፈጥረዋል። ተቋሙ በለስላሳ መጠጥ መያዣ እቃዎች የታችኛው ክፍል እና በበርገር መጠቅለያ ወረቀቶች ላይ እንደ “ዮሐንስ 3:16”፣ “ምሳሌ 3:5”፣ “ምሳሌ 24:16”፣ “ናሆም 1:7”፣ “ሉቃስ 6:35” እና “ራዕይ 3:20” የመሳሰሉ ጥቅሶችን የሚያትምባቸው ሲሆን፣ ይህም አሰራር የተጀመረው ከ46 ዓመት በፊት በድርጅቱ መስራች  በነበሩት ሐሪ ስናይደር አማካኝነት የቤተሰቡን የክርስትና እምነት ለማንጸባረቅ ታስቦ ነበር። የድርጅቱ ደጋፊዎች ማናቸውም የግል ኩባንያ በራሱ ምርት ላይ የፈለገውን ነገር የማድረግ ሙሉ መብት እንዳለውና ጥቅሶቹም ማንንም ደንበኛ እምነት እንዲቀይር እንደማያስገድዱ ይከራከራሉ። በአንጻሩ ነቃፊዎች ደግሞ ተቋሙ የተለያየ እምነት ያላቸውንና ምንም እምነት የሌላቸውን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ደንበኞችን የሚያስተናግድ አገር አቀፍ የንግድ ሰንሰለት በመሆኑ፣ የበርገር መጠቅለያ ወይም የፈሳሽ መያዣ የወረቀት ብርጭቆዎች ላይ የሃይማኖት መልዕክቶች ፈጽሞ መኖር የለባቸውም ሲሉ ይተቻሉ። የአሁኗ የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ እና የመስራቹ የልጅ ልጅ የሆኑት ሊንሲ ስናይደር ይህንን ተግባር እንደ ቤተሰብ መዘከሪያ ቅርስ በመቁጠር ከአቋማቸው ፍንክች እንደማይሉ በተደጋጋሚ የገለጹ ሲሆን፣ በጥቅሶቹ ምክንያት ነቀፌታ እና የተሟጋቾች ግፊት ቢኖርም የኩባንያው ቅርንጫፎች መስፋፋታቸውን እና የድርጅቱ ተወዳጅነት ከመጨመር ወደ ኋላ አላለም። Via መዝናኛ ሚዲያ @Ethionews433 @Ethionews433

በክልል ንግድ ፈቃድ አዲስ አበባ ውስጥ መስራት አይቻልም ሲል ቢሮው አሳወቀ‼️ በክልል ፈቃድ አዲስ አበባ ውስጥ የሚሰሩ አስመጪዎች ንግድ ፈቃዳቸውን ወደ አዲስ አበባ ማዛዋወር አለባቸው ብሏል። የአዲ
በክልል ንግድ ፈቃድ አዲስ አበባ ውስጥ መስራት አይቻልም ሲል ቢሮው አሳወቀ‼️ በክልል ፈቃድ አዲስ አበባ ውስጥ የሚሰሩ አስመጪዎች ንግድ ፈቃዳቸውን ወደ አዲስ አበባ ማዛዋወር አለባቸው ብሏል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በመኪና ሽያጭ ዘርፍ በሚደረጉ ህገወጥ አሰራሮች እና የታክስ ስወራዎች ላይ ጥብቅ እርምጃና ቁጥጥር እንደሚያደርግ አስታወቀ። በክልል ፈቃድ አዲስ አበባ ውስጥ የሚሰሩ አስመጪዎች ንግድ ፈቃዳቸውን ወደ አዲስ አበባ ማዛወር አለባቸው ተብሏል። ደረሰኝ መለየት የሽያጭ ማሽን ማስተካከል እና ወርሃዊና ዓመታዊ ግብር መክፈል አለባቸው ነው የተባለው። ህገወጥ ደረሰኝ መጠቀም ወይም የውጭ ሀገር ፈቃድ ብቻ ይዞ መንቀሳቀስ በህግ ያስጠይቃል። አስመጪዎችና የመኪና ማሳያ ባለቤቶች ፈቃድ ከሌላቸው ደላሎች ጋር በመተባበር ህገወጥ የሽያጭ ሰነድ ከመፈራረም እንዲቆጠቡ ተሳስቧል። ቢሮው ከዚህ አሰራር ውጭ በሚንቀሳቀሱ አስመጪዎች ፈቃድ የሌላቸው ደላሎች በኦንላይን ህገወጥ ንግድ የሚያካሂዱ ግለሰቦች እና ከተዋናዮቹ ጋር በሚተባበሩ አካላት ላይ ቢሮው ክትትልና ምርመራ በማድረግ ህጋዊ እርምጃ ይወስዳል ሲል አሳስቧል። @Ethionews433 @Ethionews433

የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ለህፃን ፊዮና ሰለሞን አቀባበል አደረገ፡፡ ህፃን ፊዮና ሰለሞን ነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 12፡30 ሠዓት አካባቢ ከቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ልዩ
+4
የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ለህፃን ፊዮና ሰለሞን አቀባበል አደረገ፡፡ ህፃን ፊዮና ሰለሞን ነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 12፡30 ሠዓት አካባቢ ከቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ቦታው ቦሌ ቡልቡላ በቤት ሠራተኛቸው የእገታ ወንጀል ተፈጽሞባት 3 ሚሊዮን ብር ተጠይቆባታል፡፡ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ከሌሎች የፀጥታ ተቋማት ጋር በመተባበር ባደረገው የተቀናጀ ኦፕሬሽን ተጠርጣሪዋን ከጎንደር ከተማ ማራኪ ክ/ከተማ በቁጥጥር ስር መዋሏን መግለፃችን ይታወቃል፡፡ ታጋችዋ ህፃን ፊዮና ሰለሞን ከባህዳር አዲስ አበባ ስትገባም የአዲስ አበባ ፖሊስ የታክቲክ ወንጀሎች ምርመራ ዋና መምሪያ ኃላፊ ረዳት ኮሚሽነር አድማሱ ኢፋን ጨምሮ ሌሎች በምርመራው ዘርፍ የሚገኙ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም የህጻኗ ቤተሰቦችና ወዳጅ ዘመድ አቀባበል አቀባበል አድርገውላታል፡፡ ህፃናት ልዩ ትኩረት ከሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎች ቀዳሚ በመሆናቸው መጠበቅ፣ መንከባከብና ተገቢውን ትኩረት መስጠት እንደሚገባ የተናገሩት ረዳት ኮሚሽነር አድማሱ ኢፋ ወላጆች ልጆቻቸው የሚውሉበትንና የሚጫወቱበትን ቦታ ማወቅና መከታተል የሚገባ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ የህፃን ፊዮና እናት ወ/ሮ ሄለን ኃ/ሚካኤል በበኩላቸው ተጠርጣሪዋ መቅደስ ሞገስ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ ስትሰራ የቆየች በመሆኑ ህጻኗ ስለምታውቃት ይህን አጋጣሚ ተጠቅማ የእገታ ወንጀሉን በመፈፀሟ ማዘናቸውን በመግለፅ በወቅቱ የልጃችንን መጥፋት ለአዲስ አበባ ፖሊስ ካመለከትን ጀምሮ ፖሊስ ቀን ከሌሊት ፍለጋውን በማድረግ ልጃችንን በእጃችን በማስገባቱ ወደር የሌለው ደስታ ተሰምቶናል ብለው በዚህ ስራ ለተሳተፉ በሙሉ ክብር ይገባቸዋል ብለዋል፡፡ የወ/ሮ ሄለን ጎረቤት የሆኑት ወ/ሮ ሂሩት ለዓለም በበኩላቸው ፖሊስ የሰራው ስራ እጅግ የሚያስመሰግን መሆኑን በመግለፅ በማንኛውም ጉዳይ ህብረተሰቡ የፖሊስን ስራ ሊያግዝ ይገባልም ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ በከተማችን አዲስ አበባ በሚፈፀሙ ማንኛውም ዓይነት ወንጀሎች፤ ፈፃሚዎች ለጊዜውም ቢሆን ከሰው ዓይንና ጆሮ ቢሰወሩም ከህግ ማምለጥ አይችሉም ያለው የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ በዚህ ስራ ውስጥ ተሳታፊ ለነበሩ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ እና የጎንደር ከተማ ፖሊስ እንዲሁም ሌሎች የፀጥታ ተቋማት ላደረጉት ቀና ትብብር ምስጋናውን አቅርቧል፡፡ ህብረተሰቡ በአካባቢው ላይ የሚያያቸውን ማንኛውም አጠራጣሪ ጉዳዮች ለአቅራቢያ ፖሊስ መረጃ በመስጠት የህግ የበላይነትን ሊያረጋግጥ እንደሚገባም መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡ @Ethionews433 @Ethionews433

በኔፓል በደረሰው የጎርፍ አደጋ ከዘጠኝ ቀን ፍለጋ ቡሀላ ሁለት ሰዎች በህይወት ተገኙ፡፡ በኔፓል በድንገተኛ ጎርፍ ምክንያት በዋሻ ውስጥ ለዘጠኝ ቀናት ተይዘው የነበሩ ሁለት የውሃ ኃይል ማመንጫ ሠራተ
በኔፓል በደረሰው የጎርፍ አደጋ ከዘጠኝ ቀን ፍለጋ ቡሀላ ሁለት ሰዎች በህይወት ተገኙ፡፡   በኔፓል በድንገተኛ ጎርፍ ምክንያት በዋሻ ውስጥ ለዘጠኝ ቀናት ተይዘው የነበሩ ሁለት የውሃ ኃይል ማመንጫ ሠራተኞች በሕይወት መገኘታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ በኔፓል በደረሰው አስከፊ የጎርፍ አደጋ ከ አንድ ሺህ ሁለት መቶ በላይ ሰዎች ህይወታቸው ማለፉና ወደ አምስት ሺህ የሚጠጉ ሰዎች እስካሁን አለመገኘታቸው የሚታወስ ነው። ሳንጃያ ሻህ እና ካቢር ማሃርጃን ከትሪሹሊ 3A የኃይል ማመንጫ ዋሻ ውስጥ በአዳኝ ቡድኖች የተገኙ ሲሆን፣ በእጅና በእግራቸው ጉዳት ቢደርስባቸውም አምቡላንስ ወደ ካትማንዱ ሆስፒታል ተወስደዋል። በዚያው ዋሻ ውስጥ ወደ 40 የሚጠጉ ሰዎች አሁንም ተይዘው እንዳሉ ሲገመት፣ የነፍስ አድን ሰራተኞች የፍለጋ ሥራቸውን አሁንም ቀጥለዋል። ቤዛዊት አራጌ @Ethionews433 @Ethionews433

ማስታወቂያ የ2018 ዓ.ም. የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው የትምህርት መርሃ ግብር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ውጤት ላስመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ
ማስታወቂያ የ2018 ዓ.ም. የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው የትምህርት መርሃ ግብር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ውጤት ላስመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፡-  የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን ከነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ከታች የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ (Link) በመጠቀም ምርጫችሁን ት/ቤት መሄድ ሳይጠበቅባችሁ ባላችሁበት ቦታ እራሳችሁ በመሙላት እንድታሳውቁ እንገልጻለን።  ማስፈንጠሪያ (Link) https://student.ethernet.edu.et/ ማሳሰቢያ፡-  የህክምና፣ የአካል ጉዳተኝነት፣ ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትያዎች እና ከ6 ወር በታች ህፃን የሚያጠቡ እናቶች አስፈላጊውን ሕጋዊ ማስረጃ ማያያዝ ይኖርባችኋል። የትምህርት ሚኒስቴር

ህፃን ልጅ አግታ 4 ሚሊዮን ብር የጠየቀች የቤት ሰራተኛ በቁጥጥር ስር ዋለች፡፡ መቅደስ ሞገስ የተባለች ግለሰብ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ቦታው ቦሌ ቡልቡላ አቶ ሰለሞን ፋንታሁንና ወ/ሮ ሄ
ህፃን ልጅ አግታ 4 ሚሊዮን ብር የጠየቀች የቤት ሰራተኛ በቁጥጥር ስር ዋለች፡፡ መቅደስ ሞገስ የተባለች ግለሰብ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ቦታው ቦሌ ቡልቡላ አቶ ሰለሞን ፋንታሁንና ወ/ሮ ሄለን ኃይለሚካል መኖሪያ ቤት በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ ለሶስት ወራት ስትሰራ ቆይታ ቤተሰብ ለመጠየቅ ፈቃድ ጠይቃ ሳትመለስ ትቀራለች፡፡ ወንጀል ፈፃሚዋ ከአንድ ግብረ አበሯ ጋር በመሆን ከሁለት ወር ቆይታ በኋላ ወደ አሰሪዎቿ ሰፈር በመምጣት የሰባት ዓመቷን ህፃን ፊዮና ሰለሞንን ከምትጫወትበት ስፍራ ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ/ም ይዛ ትሰወራለች፡፡ የግለሰቧ ግብር አበር ለህፃኗ ወላጅ 3 ሚሊዮን ብር እንዲከፍሉት በስልክ ይገልፅላቸዋል፡፡ ቤተሰቧ የግለሰቡን ዛቻ በመፍራት 370ሺ ብር በባንክ ገቢ ያደርጉለታል፡፡ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ከሌሎች የፀጥታ ተቋማት ጋር በቴክኖሎሎጂ በመታገዝ ባደረገው ክትትል ግለሰቧ ህፃኗን አግታ ወደ አማራ ክልል ይዛ መሰወሯን ይደርስበታል፡፡ ወንጀል ፈፃሚዋን በጎንደር ከተማዋ ማራኪ ክፍለ ከተማ ዩኒቨርሲቲ ጫካ ውስጥ በተደረገ ክትትል እና ጥቆማ እንደተያዘች ዋና ጠቅላይ መምሪያው አስታውቋል፡፡ ህፃኗ በጥሩ ደህንነት ላይ እንደምትገኝ የገለፀው ፖሊስ ወንጀል ፈፃሚዋን በቁጥጥር ለማዋል በተደረው ጥረት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ እና የጎንደር ከተማ ፖሊስ እንዲሁም ሌሎች የፀጥታ ተቋማት ላደረጉት ቀና ትብብር የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ምስጋናውን አቅርቧል፡፡ @Ethionews433 @Ethionews433

Repost from 4-3-3 Tech
Open Ai እጅግ በጣም ኃይለኛ የሆነውን የ Ai ሞዴል 'GPT-6 Astra' ግልጋሎትን መስጠት ጀምሯል።🥶🥶 GPT-6 Astra ምንድን ነው? በምሳሌ እንካቹ... የዱሮ Ai 👉 “ኢሜይል ጻፍል
Open Ai እጅግ በጣም ኃይለኛ የሆነውን የ Ai ሞዴል 'GPT-6 Astra' ግልጋሎትን መስጠት ጀምሯል።🥶🥶 GPT-6 Astra ምንድን ነው? በምሳሌ እንካቹ... የዱሮ Ai 👉 “ኢሜይል ጻፍልኝ” ብለን ስንጠይቅ ኢሜሉን ይፅፋል... አዲሱ ​GPT-6 Astra ግን ፦ 👉 “ይህን የደንበኛ ቅሬታ አስተካክልልኝ” ስትሉት እሱም ችግሩን ተረድቶ → ምላሽ አዘጋጅቶ → መረጃዎችን አጣርቶ → አስፈላጊ መሣሪያዎችን ተጠቅሞ → ለውጦችን አድርጎ → ስራውን ሰርቶ ይጨርሳል። ​ስለዚህ ትልቁ ለውጥ፦ AI ከማስረዳት ወይም ከመመለስ አልፎ “ሙሉ ስራን ለኛ ወደ መሥራት” ተሸጋግሯል። ​🧠 ቀላል ምሳሌ ​የቀድሞውን Ai ፦ “ለንግድ ድርጅቴ የሚሆን ዌብሳይት ሠራልኝ።” ብለን ስንጠይቅ ​የቀድሞ AI የተወሰነ የኮድ ጽሁፍ ይልካል። ​ይህ አዲሱ Ai ግን፦ ​የዌብሳይቱን እቅድ ያወጣል፤ ​ኮዱን ይጽፋል፤ ​ገጾቹን ይፈጥራል፤ ​ይፈትሻቸዋል (Test ያደርጋል)፤ ​ስህተቶችን ፈልጎ ያርማል፤ ​ዲዛይኑን ያሻሽላል፤ ​በመጨረሻም የተጠናቀቀውን ዌብሳይት በእጅዎ ያስገባል። Share https://t.me/+5sCQf3Z1UUAxZDAy https://t.me/+5sCQf3Z1UUAxZDAy