E-LMIS -ብቁ
Open in Telegram
ብቁ ሰራተኛ•ብቁ ቀጣሪ•ብቁ.ውሳኔ ሰጭ ለመመዝገብ ፖስፖርት ፎቶ ይላኩልን https://t.me/@ELMISETHIOPIAN
Show more559
Subscribers
-224 hours
-57 days
-1030 days
Posts Archive
559
+7
ከፈጠራ ሀሳብ ወደ ገበያ፦ ለስታርታፖች የሚያስፈልግ ምቹ ምህዳር
አቤል ማስረሻ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በነበረው ቆይታ፣ የአካል ጉዳተኛ ጓደኛው ይገጥመው የነበረውን ፈታኝ ሁኔታ በመነሳት፣ የመንቀሳቀስ ችግር ላለባቸው ወገኖች መፍትሄ የሚሆን የኤሌክትሪክ ዊልቼር ፈጥሯል።
ይህ ሀሳብ ወደ ተግባር ሊሸጋገር የቻለው የአቤል ንድፈ ሀሳብ እውቀትን ከተግባራዊ ክህሎት ጋር በማጣመር ነው።
እንደ አቤል ማብራሪያ መሰል የፈጠራ ሥራዎች ወደ ዘላቂ ንግድ እንዲሸጋገሩ ፋይናንስ፣ የማምረቻ ቦታ፣ ጥሬ ዕቃ፣ የገበያ ትስስር፣ እንዲሁም ቀልጣፋ ሕግና አሠራር አይነተኛ ሚና ይጫወታሉ።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የአምስት ዓመት የልማት ጉዞ የምክክር ጉባኤ ላይ አቤልን ጨምር ውጤታማ የሆኑ ሥራ ፈጣሪዎች የተሳተፉበት የፓናል ውይይት «ከሥልጠና ወደ ሥራ፣ ከፈጠራ ሀሳብ ወደ ንግድ ልማት» በሚል ርዕስ ተካሂዷል።
ወጣቶች ፈጠራቸው ወደ ምርት፣ ምርታቸው ወደ ገበያ፣ ገበያቸውም ወደ ዘላቂ ንግድ የሚሸጋገርበትን ምቹ ምህዳር መፍጠር የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅት ይፈልጋል።
በቴክኒክና ሙያ ተቋማት የሚገኘው ተግባራዊ ክህሎት በስታርታፕ ምህዳር በተገቢው ሁኔታ ከተደገፈ፣ የወጣቶች ፈጠራ ከግል ስኬት ባሻገር ለሀገራዊ ኢኮኖሚ ዕድገትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ጉልህ አስተዋፅኦ ሊያበረክት እንደሚችል በውይይቱ ላይ በስፋት ተነስቷል፡፡
559
የጳጉሜን ቀናት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ስኬቶች በሚያሳይ መልኩ ይከበራሉ-የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
የጳጉሜን ቀናት የኢትዮጵያን ማንሰራራት እና የተገኙ ሁለንተናዊ ስኬቶችን በሚያሳይ መልኩ እንደሚከበሩ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ።
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ የ2018 የጳጉሜን ቀናት ስያሜዎችን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙሀን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።
በዚህም የጳጉሜን ቀናት "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል እንደሚከበሩ ተናግረዋል።
ጳጉሜን 1 "የእመርታ ቀን" በሚል እንደሚከበር ገልጸው፤ እለቱ ኢትዮጵያ ከአዝጋሚ የእድገት ጉዞ በመውጣት ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች የሚዘከሩበት መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም ኢትዮጵያ ያስመዘገበቻቸው እመርታዊ ለውጦች የሚዘከሩበት መሆኑን ጠቁመዋል።
ጳጉሜን 2 "የማንሰራራት ቀን" በሚል እንደሚከበር ገልጸው፤ እለቱ ኢትዮጵያ ወደ ሁለንተናዊ ልማት የተሸጋገረችበትን ጉዞ በሚያሳዩ ሁነቶች እንደሚከበር ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ከጎታች ማነቆ የወጣችበትና ማንሰራራቷም የሚገለጥበት መሆኑን አንስተዋል።
ጳጉሜን 3 "የጽናት ቀን" በሚል እንደሚከበር ገልጸው፤ ታሪካዊ ጽናትን ማስቀጠልን የምናሳይበት ነው ብለዋል። የጽናት ቀን ጀግኖች የሚወሱበትና አዳዲስ ጀግኖች የሚፈጠሩበት መሆኑን ገልጸዋል። በእለቱ ከጠዋቱ 12 ሰዓት ላይ የሰንደቅ አላማ የመስቀል መርሀ ግብር እንደሚከናወንም ገልጸዋል።
ጳጉሜን 4 "የህብር ቀን" በሚል እንደሚከበር ገልጸው፤ አንድነትን በሚያጸኑ ተግባራት እንደሚከናወን ገልጸዋል። የትብብር እና የምክክር እሴትን በሚያጎለብቱ ሁነቶች እንደሚከበር ተናግረዋል። በእለቱ ለ150 ሺህ ሰዎች ነጻ የጤና አገልግሎት እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።
559
+6
የፖሊሲና የማዕቀፍ ለውጦች ያመጡት ዋና ዋና ስኬቶች
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ላለፉት አምስት ዓመታት ያከናወናቸውን የልማት ጉዞዎች አስመልክቶ በሚያካሂደው የምክክር መድረክ 3ኛ ቀን ውሎ በፖሊሲ፣ ተቋማዊ እሳቤና ሥርዓት ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት ተደርጓል፡፡
ባለፉት አምስት ዓመታት የክህሎት ልማት ትኩረት ከአቅርቦት መር ወደ ፍላጎት መር ተቀይሯል።
ሰልጣኞችን አሰልጥኖ ማውጣት ብቻ ሳይሆን በኢንተርፕራይዝ ምስረታ ላይ ያተኮረና ክህሎት ለሥራ ዕድል ፈጠራ ተመጋጋቢ የሚሆንበት የአሰራር ስርዓትም መዘርጋቱ ተገልጻል፡፡
የህግ ማዕቀፎች ማሻሻላቸው፣ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እስከ አንድ ማዕከል የተናበበ መዋቅር መዘርጋቱ፣አዳዲስ እሳቤዎችና ዘረ-መሎች መዘጋጀታቸውና ተቋማትን በቴክኖሎጂ ለማዘመን የሚደረጉ ጥረቶች ዘርፉን ከማሳደግ አንፃር ጉልህ ሚና እንደነበራቸው ተወያዮቹ አብራርተዋል።
ከአዲሶቹ እሳቤዎች አንዱ ተቋማቱን «ኢንተርፕረነሪያል» ማድረግ እንደመሆኑ ተቋማት የኢንተርፕረነርሽፕ እሳቤን በመተግበር በዜጎች ተጠቃሚነትና በሀገር እድገት ላይ የራሳቸውን አሻራ እንዲያሳርፉ እድል እንደሰጣቸው በፖናል ውይይቱ ላይ በስፋት ተነስቷል።
559
+9
የዘርፉን ምርጥ ተሞክሮዎች በማስፋት የአፈጻጸም ልዩነትን ለማጥበብ እየተሰራ ነው
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በጠንካራ የድጋፍና ክትትል ሥርዓት በዘርፉ የተገኙ ምርጥ ተሞክሮዎችን በመለየትና በማስፋት የአፈጻጸም ልዩነቶችን ለማጥበብ እየሰራ መሆኑ ተገለጸ።
ይህን የገለጹት የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ነቢሃ መሃመድ በሚኒስቴሩ የአምስት ዓመት ጉዞ የምክክር መድረክ ላይ የምርጥ ተሞክሮ ሰነድን ሲያቀርቡ ነው።
እንደ ክብርት ነቢሃ ገለጻ፣ ሚኒስቴሩ የሪፎርም አጀንዳዎችን በተግባር ለማዋል ከከፍተኛ አመራር እስከ ባለሙያ ድረስ ድጋፍና ክትትል እያደረገ ሲሆን፣ በሂደቱ የተገኙ ውጤታማ አሠራሮችን በመለየት ለሌሎች ተቋማት እንዲስፋፉ በሰነድ አደራጅቷል።
ምርጥ ተሞክሮዎቹ በተቋማት አቅም ግንባታ፣ በክህሎት ልማት፣ በሥራ ዕድል ፈጠራና በኢንዱስትሪ ሰላም የተገኙ ስኬታማ አሠራሮችን ያካተቱ ሲሆን፣ ስልጠናን ከገበያ ፍላጎት ጋር ማጣጣም፣ ዲጂታል አሠራርን ማስፋፋትና ከግሉ ዘርፍ ጋር አጋርነትን ማጠናከር የሚያስችሉ ናቸው።
ከተለዩት ተሞክሮዎች መካከል የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ተቋም ግንባታ፣ የTVET ተቋማት ዞኒንግና ዲፈረንሼሽን፣ የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ልምድና የሳታ ቴክኖሎጂና ቢዝነስ ኮሌጅ ልምድ ይገኙበታል።
ክብርት ነቢሃ እንዳሉት፣ እነዚህን ውጤታማ አሠራሮች በሌሎች የዘርፉ ተቋማት ማስፋት የሪፎርሙን ውጤት ከማጠናከር ባለፈ የተቋማትን አቅምና አፈጻጸም ለማሻሻል ያግዛል፡፡
559
+3
# አሁን
የአምስት ዓመት ጉዞ ቅኝት የፓናል ውይይት
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የአምስት ዓመት የልማት ጉዞውን አስመልክቶ እያካሄደው የሚገኘው የምክክር መድረክ በሦስተኛ ቀን ውሎውበዘርፉ ፖሊሲ፣ ተቋማዊ እሳቤና የሥርዓት እይታ ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይትን እያስተናገደ ይገኛል፡፡
የውይይት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ፣ አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ነቢሃ መሃመድ ያለፉት አምስት ዓመታት ዘላቂ አሰራሮችን በሥርዓታዊ እይታ ለመገንባት ጥረት የተደረገበት ጉልህ የመሸጋገሪያ ወቅት እንደነበር ገልፀዋል፡፡
በአምስት ዓመት ጉዞ ውስጥ በርካታ አወንታዊ ውጤቶችን ማስመዝገብ መቻሉን የገለፁት ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ወደፊት ዘርፉ የሚጠበቅበትን ግቦች ለማሳካት ደግሞ ጥልቅ ግምገማና ተከታታይ ማሻሻያ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ ውይይቱ ተዘጋጅቷል ብለዋል፡፡
የፖሊሲውን ውጤታማነት መፈተሸና ባለፉት አመታት በተጨባጭ የተሠሩ ሥራዎችን መገምገም የውይይቱ ዋንኛ ትኩረት መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
559
+1
ቶኩማ ሀርቨስቲንግ
ከኦሮሚያ ክልል ፍቼ ከተማ የመጣው ወጣት ሰለሞን ቡታ በስኪል ኢትዮጵያ ውድድር ከተገኙ ድንቅ ቴክኖሎጂ ፈጣሪዎች አንዱ ነው፡፡
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የአምስት ዓመታት የልማት ጉዞ ምክክር መድረክ በተዘጋጀው ኤግዚቢሽን ላይ ያቀረበው «ቶኩማ ሀርቨስቲንግ» የተሰኘው ማሽን ነው፡፡
ሰለሞን ይህንን ማሽን ለመስራት ያነሳሳው በአካባቢው የሚገኙ ገበሬዎች በእርሻ እና በምርት ስብሰባ ወቅት የሚገጥማቸውን እንግልት በመመልከቱ እና እንደ ሀገር ያለውን የአግሮ-ሜካናይዜሽን ችግር ለመቅረፍ በማሰብ ነው፡፡
«ቶኩማ ሀርቨስቲንግ» በውስጡ ሶስት አበይት አገልግሎቶችን የያዘ ዘመናዊ የግብርና ማሽን ነው፡፡ ማሽኑ መሬት ማረስ፣ ምርት መሰብሰብ እና ውሃ ፓምፕ ማድረግ የሚችል ሲሆን የጊር ቦክስ ስርዓቱን በመቀየር በጋዝ፣ በሶላር እንዲሁም በኤሌክትሪክ ሀይል መስራት የሚያስችል አማራጭ አለው፡፡
በተጨማሪም ከመሬት ያለው ከፍታ ለየትኛውም የሀገሪቱ የመሬት አቀማመጥ ምቹ እንዲሆን ተደርጎ የተሰራ ነው፡፡
መኪና እና ትልልቅ ማሽኖች መግባት በማይችሉባቸው ገጠራማ አካባቢዎች የማሽኑን ክፍሎች በመነጠል በሰው ጉልበት ማጓጓዝ ይቻላል፡፡
አጠቃላይ ክብደቱ 150 ኪሎ ግራም ቢሆንም ሲነቃቀል እያንዳንዱ ክፍል 25 ኪሎ ግራም ብቻ ስለሚመዝን በቀላሉ ተነቃቅሎ እንዲገጣጠም አስችሎታል፡፡
ይህ ቴክኖሎጂ በሀገራችን ግብርና ውስጥ ያሉ ችግሮችን የመፍታት አቅም አለው፡፡ በአገራችን በምርት ስብሰባ ወቅት ከሚባክነው በአማካኝ 30 ፐርሰንት ምርት ውስጥ ይህ ማሽን ብክነቱን ወደ 5 ፐርሰንት ዝቅ ያደርገዋል፡፡
በስራ ቅልጥፍናውም በ4 ሰዓት ውስጥ 2 ሄክታር መሬት ማረስ፣ በ4 ሰዓት ውስጥ 1 ሄክታር ምርት ማጨድ እንዲሁም በ24 ሰዓት ውስጥ 1 ሄክታር መሬት በውሃ ፓምፕ ማጠጣት ይችላል፡፡
559
+9
የክህሎት ልማት ስኬት ባለፉት አምስት አመታት
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የአምስት ዓመታት የልማት ጉዞውን አስመልክቶ እያካሄደው በሚገኘው የምከክር መድረክ ዘርፎች አፈፃፀማቸውን በተናጥል እየገመገሙ ይገኛሉ፡፡
በዚሁ መሰረት በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ባለፉት አምስት ዓመታት የሥልጠና ጥራት እና አግባብነትን ለማሻሻል፣ እንዲሁም የሥርዓተ ትምህርት እና የሙያ ደረጃዎችን ከገበያው ሙያዊ ፍላጎት ጋር ለማጣጣም የሚያስችሉ ሰፋፊ ሥራዎች መሰራታቸው ተጠቁሟል፡፡
የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ሀገራችን ወደ ብልፅግና የምታደርገውን ጉዞ የሚያሳኩ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎች የሚፈሩባቸው ማዕከላት መሆናቸው በአዲሱ የዘርፉ እሳቤ መለየቱ ከፍተኛ መነቃቃት መፍጠሩም ተገልጿል፡፡
በአምስት ዓመታት ውስጥ የቴክኒክና ሙያ ስትራቴጂ ክለሳን ጨምሮ ዘርፉን የሚያሳድጉ የህግ ማዕቀፎችን የማሻሻል ሥራ ተሰርቷል፡፡
235 የሙያ ደረጃዎች ዝግጅትና ክለሳ የተከናወነ ሲሆን የኢንዱስትሪውን ፍላጎት ሊመጥኑ የሚችሉ የሙያ ደረጃዎችን በወቅቱ በማዘጋጀት ረገድ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከፍተኛ ርብርብ ማድረጉም ተብራርቷል፡፡
በዘርፉ በተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ሥራዎች በመደበኛ ከአንድ ነጥብ አንድ ሚሊዮን በላይ እንዲሁም ከ 20ሚሊዮን በላይ ሰልጣኞችን ደግሞ በአጫጭር ስልጠና መርሃ ግብሮች በአምስት ዓመታት እንደተቻለ በመድረኩ ተገልጿል፡፡
በቴክኒክና ሙያ ተቋማት ውስጥ የሴት ሰልጣኞችን ተሳትፎ ለማሳደግ በተደረገው ጥረት 50% ለማድረስ ታቅዶ 48% ማሳካት መቻሉም ተመላክቷል፡፡
የሥልጠና ጥራትን ከማረጋገጥ አንፃርም ከ3ሚሊዮን በላይ የሆኑ የስልጠና አጠናቃቂዎችን ብቃት በምዘና የማረጋገጥ ሥራ መሰራቱ የስልጠና ጥራትን ከማረጋገጥ አንፃር ጉልህ ሚና እንዳለውም ተብራርቷል፡፡
559
+7
ከክርክር ወደ ምክክር
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አገራዊ የምክክር መድረክ በሁለተኛ ቀኑ የዘርፎችን አፈፃፀም በመገምገም ቀጥሎ ውሏል፡፡
በዚህም የአሠሪና ሠራተኛ ዘርፍ የአምስት ዓመታት አፈጻጸም፣ ስኬቶችና ቀሪ ፈተናዎችን በመገምገም የቀጣይ ዘመን የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ መክሯል።
በመድረኩ ማህበራዊ ምክክር፣ የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት፣ የሥራ ሁኔታ ቁጥጥር፣ የሠራተኞች መብትና ደህንነት እንዲሁም የውጭ ሥራ ስምሪት ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።
559
+8
በዘርፉ በተደረገ የመዋቅር፣ የፖሊሲና የአሠራር ሪፎርሞች በአምስት ዓመታት በርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ተጠቃሚ አድርጓል
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ባለፉት አምስት ዓመታት ባከናወናቸው የመዋቅር፣ የፖሊሲና የአሠራር ሪፎርሞች ከ20.7 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን በሀገር ውስጥና በውጭ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ማድረጉ ተገለጸ።
ሚኒስቴሩ ከ2014 እስከ 2018 ዓ.ም. ያከናወነውን የአምስት ዓመት የልማትና የሪፎርም አፈጻጸም የሚገመግመው የምክክር መድረክ በዘርፍ ደረጃ ቀጥሏል።
በዚህም ከ19 ሚሊዮን በላይ ዜጎች በሀገር ውስጥ የሥራ ዕድል ሲያገኙ፣ ከ1.6 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ደግሞ በሕጋዊ መንገድ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት አግኝተዋል።
የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማስፋፋት ለኢንተርፕራይዞች የፋይናንስ፣ የመሬት፣ የመሠረተ ልማትና የገበያ ትስስር ድጋፎች መደረጋቸውም ተጠቁሟል።
በአምስቱ ዓመታት 166 ቢሊዮን ብር ያህል ብድር ለኢንተርፕራይዞች ቀርቦ፣ 900ሺህ በላይ ኢንተርፕራይዞች ተጠቃሚ ሆነዋል።
በተጨማሪም ለኢንተርፕራይዞች 295 ቢሊዮን ብር የገበያ ትስስር በመፍጠር፣ 1.2 ሚሊየን በላይ ኢንተርፕራይዞች ከድጋፉ ተጠቃሚ መሆናቸው ተገልጿል።
በአጠቃላይ የተከናወኑት ሪፎርሞችና የተለያዩ የድጋፍ ሥራዎች የሥራ ዕድል ፈጠራንና የኢንተርፕራይዞችን ዕድገት ለማስፋፋት ጉልህ ሚና ማበርከታቸው በመድረኩ ተገልጿል።
559
+4
በጀሞ አካባቢ እየተገነባ የሚገኘው ግዙፍ የገበያ ማዕከል በጉባኤው ተሳታፊዎች ተጎበኘ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ላለፉት አምስት ዓመታት ያከናወነውን የልማትና የሪፎርም ጉዞ አስመልክቶ ያዘጋጀው የምክክር መድረክ ተሳታፊዎች፣ በጀሞ አካባቢ እየተገነባ የሚገኘውን ግዙፍ የገበያ ማዕከል(የኢምፖርየም) ሕንፃ ጎብኝተዋል።
በአሁኑ ወቅት የማጠናቀቂያ ሥራዎች እየተከናወኑለት የሚገኘው ይህ ባለ 11 ወለል ሕንፃ፣ በቅርቡ ተጠናቆ ሙሉ ለሙሉ ለአገልግሎት እንደሚበቃ በጉብኝቱ ወቅት ተገልጿል።
ኢምፖርየሙ ተጠናቆ ወደ ሥራ ሲገባ፣ በሀገሪቱ የሚገኙ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ያመረቷቸውን ምርቶች የሚያስተዋውቁበትና ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ ገበያ የሚያቀርቡባቸው ዘመናዊ የሽያጭ ሱቆች ይኖሩታል።
በተመሳሳይም የኢትዮጵያን ብዝሃነት የሚያንፀባርቁ ልዩ ልዩ ባህላዊ ምግቦችና መጠጦች የሚያስተዋወቁበትና የሚሸጡበት በርካታ ሬስቶራንቶችም በሕንፃው ውስጥ ተካተዋል።
በተጨማሪም ሕፃናት የሀገራቸውን ባህላዊ ጨዋታዎች የሚያውቁበት፣ የሚጫወቱበትና ልምድ የሚያካብቱበት ልዩ የመዝናኛ ስፍራ፣ ለተለያዩ ሁነቶች የሚያገለግል ዘመናዊ የስብሰባ አዳራሽ እንዲሁም ሰፊ የመኪና ማቆሚያ ስፍራ እንደሚኖሩት ተጠቁሟል።
ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት የኢንተርፕራይዞችን የገበያ ትስስር ችግር ከመቅረፍ ባለፈ፣ የሀገር ውስጥ ምርቶችንና የኢትዮጵያን ባህል በማስተዋወቅ፣ እንዲሁም ለአምራቾች የገበያ ዕድል በመፍጠር ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ተገልጿል።
559
+9
መሠረቱን አጠናክረን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ …
የዘርፋችንን የአምስት ዓመታት የልማት ጉዞ ከአስፈጻሚና ባለድርሻዎች ጋር መገምገም ጀምረናል። ይህ መድረክ ያስመዘገብነውን ውጤት ለመዘከር ብቻ ሳይሆን፣ ችግሮቻችንን ለቅሞ ለማረም፣ ስኬቶቻችንን ለማላቅና ቀጣዩን የልማት አቅጣጫችንን በጋራ መቅረጽን ታሳቢ ያደረገ ነው።
ባለፉት አምስት የለውጥ ዓመታት በክህሎት ልማት፣ በሥራ ዕድል ፈጠራና በኢንዱስትሪ ሰላም ጠንካራ ተቋማዊ መሠረት ጥለናል። የሥልጠና ሥርዓቱን ከኢንዱስትሪ ፍላጎት ጋር ለማጣጣም፣ የሥራ ገበያ መረጃን ለማዘመን፣ የሥራ ዕድልን ለማስፋፋት እና የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነትን ለማጠናከር የሚያስችሉ ሥርዓቶችን ገንብተናል።
የቀጣዩ ምዕራፍ ትኩረት ይህንን መሠረት ማስፋትና ወደ ላቀ የዜጎች ተጠቃሚነት ማሸጋገር ነው። ክህሎትን ከሥራ፣ ሥራን ከምርታማነት፣ ምርታማነትንም ከሀገራዊ ልማት ጋር ማስተሳሰር የትኩረታችን ዋና ማጠንጠኛ ይሆናል።
የሪፎርማችን የመጨረሻ መለኪያ የገነባነው ተቋም ሳይሆን፣ በዜጎች ሕይወት የሚታየው ዘላቂ ለውጥ ነው። ስለሆነም በሚቀጥሉት ሦስት ቀናት ያለፈውን እንገመግማለን፣ የአሁኑን ትግበራችንን ምን ላይ እንዳለ እናያለን፣ የመጪው ጊዜ ትኩረቶቻችን ላይ የጋራ መግባባት እንፈጥራለን።
በዛሬው መድረክ የታደማችሁ የህዝብ ተወካዮች፣ የፌደራልና የክልል መንግስታት አመራሮች፣ የዘርፋችን አስፈፃሚዎች፣ አለም ዓቀፍ የዕድገት አጋሮች ፣ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና ተጠሪ ተቋማቱ አመራሮችና ሰራተኞች እንዲሁም በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ ለአምስቱ አመታት ስኬታማ ጉዞ አስተዋጽዖ የነበራችሁ ሁሉ ስኬቱ የጋራችን ነውና ለነበራችሁ በጎ ድርሻ በራሴና በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ስም ላቅ ያለ ምስጋና አቀርባለሁ::
የሥራ ባለቤት እርስዎ ነዎት!
559
+6
ጉባኤው የተገኙ ውጤቶችና ተሞክሮዎችን መነሻ በማድረግ ለቀጣዩ የልማት ዘመን የሥራ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ ያለመ ነው
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ባለፉት አምስት ዓመታት ያስመዘገባቸውን የልማትና የሪፎርም ውጤቶች በመገምገም፣ የተገኙ ተሞክሮዎችንና የታዩ ክፍተቶችን መነሻ በማድረግ ለቀጣዩ የልማት ዘመን የሥራ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ ያለመ ሀገር አቀፍ ጉባኤ ዛሬ በአዲስ አበባ ተጀምሯል።
በአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል በተጀመረው በዚህ ሀገር አቀፍ መድረክ፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ እና የቋሚ ኮሚቴው አባላት፣ የፌዴራልና የክልል ባለድርሻና አጋር አካላት በተገኙበት ነው የተጀመረው።
ከዛሬ ጀምሮ ለአራት ተከታታይ ቀናት በሚካሄደው ጉባኤ በዘርፉ ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ዋና ዋና የልማትና የሪፎርም ሥራዎች በጥልቀት ይገመገማሉ፤ በዘርፉ አንኳር ጉዳዮች ዙሪያም የፓናል ውይይቶች ይካሄዳሉ።
ጉባኤው ያለፉትን አምስት ዓመታት የሚዘክር ብቻ ሳይሆን፣ የተገኙ ውጤቶችንና ተሞክሮዎችን በመገምገም፣ የታዩ ክፍተቶችን በመለየትና የተሻሉ አሠራሮችን በማስፋፋት ለቀጣዩ የልማት ዘመን የሥራ አቅጣጫ ለማስቀመጥ መሆኑን በመክፈቻ መርሃ ግብሩ ላይ ተመላክቷል፡፡
ከጉባኤው ጎን ለጎን የክህሎት ኢትዮጵያ 2.0 ሁለተኛ ዙር ማጠቃለያና የቀጣዩ ዙር ይፋዊ ማብሰሪያ መርሃ ግብር እንዲሁም የቴክኖሎጂ ኤክስፖ እየተካሄደ ይገኛል።
በቴክኖሎጂ ኤክስፖው በክህሎት ኢትዮጵያ 2.0 መርሃ ግብር የታቀፉ ወጣቶች ያበለጿቸው፣ ተጨባጭ ችግሮችን የሚፈቱ እና ከሀሳብ ወደ ምርትና አገልግሎት የተሸጋገሩ የፈጠራና የቴክኖሎጂ ውጤቶች ለእይታ ቀርበዋል።
559
የዘርፉ የአምስት ዓመታት የልማት ጉዞ ሀገር አቀፍ ጉባኤ ነገ ይጀምራል
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የዘርፉን የአምስት ዓመታት የልማትና የሪፎርም ጉዞ በመገምገም፣ የቀጣይ የልማት ዘመን አቅጣጫዎችን የሚያስቀምጥበት ሀገር አቀፍ ጉባኤ ነገ በአዲስ አበባ መካሄድ ይጀምራል።
ለአራት ተከታታይ ቀናት በሚቆየው በዚህ ሀገር አቀፍ መድረክ፣ ባለፉት አምስት ዓመታት በዘርፉ የተከናወኑ ዋና ዋና የልማት ሥራዎች በጥልቀት ይገመገማሉ፤ በዘርፉ አንኳር ጉዳዮች ዙሪያም የፓናል ውይይቶች ይካሄዳሉ።
ከዚሁ ጎን ለጎን የክህሎት ኢትዮጵያ የሁለተኛው ዙር (2.0)ማጠቃለያ እና የቀጣዩ ዙር ይፋዊ ማብሰሪያ መርሃ ግብር እንዲሁም የቴክኖሎጂ ኤክስፖ ይካሄዳል።
በኤክስፖው ሁለተኛው ዙር የክህሎት ኢትዮጵያ መርሃ ግብር ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ በመርሃ ግብሩ በታቀፉ ወጣቶች የተሰሩ፣ ችግር ፈቺ የሆኑና ወደ ምርትና አገልግሎት የተሸጋገሩ ውጤታማ ቴክኖሎጂዎች ለእይታ ይቀርባሉ።
እንዲሁም ባለፉት አምስት ዓመታት በተተገበረው የክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ አቅጣጫ ውጤት ያመጡና ማሳያ የሆኑ ኢንተርፕራይዞችና ሥራ ፈጣሪዎች፣ እንዲሁም የተመረጡ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ምርትና አገልግሎቶቻቸውን ያስተዋውቃሉ።
ጉባኤው ያለፉትን አምስት ዓመታት የሚዘክር ብቻ ሳይሆን፣ የተገኙ ውጤቶችን መነሻ በማድረግ የቀጣይ ዘመን የሥራ አቅጣጫዎችን የሚያስቀምጥ፣ ክህሎትን ከሥራ፣ ከፈጠራ፣ ከቴክኖሎጂ እና ከባለድርሻና አጋር አካላት ጋር የሚያስተሳስር ሀገር አቀፍ መድረክ ነው።
በጉባኤው የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የዘርፉ ባለድርሻና አጋር አካላት ተወካዮች፣ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይሳተፋሉ።
559
+9
ሥራ ፈጣሪ እና ብቁ ዜጎችን ለማፍራት ያለመ የፋዌ (FAWE) የሁለተኛ ዙር ተማሪዎች ዓመታዊ ጉባኤ ተካሄደ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አጋር የሆነው Forum for African women educationalist (FAWE) ከማስተርካርድ ፋውንዴሽን ጋር በመሆን የሁለተኛ ዙር የትምህርትና ስልጠና ፕሮግራም ተጠቃሚዎችን ዓመታዊ ጉባኤ አካሄደ፡፡
ጉባኤው ትምህርት ፈልገው አቅም ላጡ ወጣቶች፣ ለሴቶች፣ ለአካል ጉዳተኞች፣ ለተፈናቃዮች እና ለስደተኞች በቴክኒክና ሙያ ተቋማት ገብተው ስልጠና እንዲያገኙ ማስቻልን ዓላማ ያደረገ ነው፡፡
በዚሁ መሠረት በፕሮግራሙ ከታቀፉ 396 ተማሪዎች መካከል 326ቱ ሴቶች፣ 60ቹ በተለያዩ ምክንያቶች የተፈናቀሉ እና 40 የሚሆኑት ደግሞ የተለያዩ የአካል ጉዳት ያለባቸው ተማሪዎች መሆናቸው ተገልጿል፡፡
በመክፈቻ መርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥልጠናና የተቋማት አቅም ግንባታ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሙሁዲን አባሞጋ እንደገለጹት፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከአለም አቀፍ አጋር አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ከእነዚህም መካከል FAWE አንዱ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ተማሪዎቹ በቴክኒክና ሙያ ተቋማት ስልጠና አግኝተው የተሻለ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማስቻል ከፌዴራል እስከ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮዎች የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመው በትብብር እየሰሩ እንደሚገኙም አስረድተዋል፡፡
ተማሪዎቹ በመጪው ጊዜ ሥራ ፈጣሪ፣ ብቁ ተወዳዳሪ፣ ትጋት የተሞላባቸው እና ለሀገር የሚጠቅሙ ዜጎች እንዲሆኑ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አስፈላጊውን ትብብር እንደሚያደርግም ጠቁመዋል፡፡
በጉባኤው ቆይታ ተማሪዎች እርስ በእርስ ልምድ የሚለዋወጡበት፣ መሪነትን የሚያዳብሩበት፣ ዲጂታል ብቃታቸውን የሚያሳድጉበት እና ምክረ-ሀሳቦችን የሚወስዱበት ሰፊ ዕድል ተፈጥሯል።
559
+3
የምሥራቅ አፍሪካ ገበያ ላይ ተፎካካሪ ለመሆን እየሠራ ያለው ተቋም
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር ሰሎሞን ሶካ በደብረ ብርሀን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በመገኘት የማኑፋክቸሪንግ፣ ኦቶሞቲቭ፣ ኮንስትራክሽንና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ላቦራቶሪዎችን ጎብኝተዋል።
ኮሌጁ ከመንግሥት ድጋፍ ብቻ ተጠቃሚ ከመሆን በመውጣት ያለውን አቅም ወደ ምርት አገልግሎትና ገቢ መቀየር እንዳለበት በጉብኝታቸው ወቅት አሳስበዋል።
ክቡር አቶ ሰሎሞን እንደገለጹት፣ ኮሌጁ የዓለም አቀፍ ISO የጥራት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ማግኘቱ ለቀጣናዊና ዓለም አቀፍ ትስስር ትልቅ ዕድል የሚፈጥር በመሆኑ፣ ተቋሙ ይህንን አቅም በመጠቀም የምሥራቅ አፍሪካ ገበያን በድፍረት እንዲፎካከር ጠይቀዋል።
በተለይም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ የተማሪዎችና የአሰልጣኞችን አቅም በመጠቀም ከሀገር ውጭ የሚሰሩ የርቀት ሥራዎችን ማምጣት፣ የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኙ የቴክኖሎጂ ፕሮጀክቶችን ማበልጸግና በኮዲንግ ዘርፍ የተሰጠውን የአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን የኮደሮች ዕድል መጠቀም እንደሚገባ አመልክተዋል።
በኦቶሞቲቭና ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የሰለጠኑ ተማሪዎች በቀጥታ ወደ ኢንዱስትሪው መግባታቸውን ያደነቁት ሚኒስትር ዲኤታው፣ ኮሌጁ ከአካባቢው ጋራጆችና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ጋር ያለውን ትስስር አጠናክሮ የመለዋወጫ እቃዎችን በማምረት ገቢ የመፍጠር አቅሙን እንዲያሳድግ ጠቁመዋል።
በኮንስትራክሽን ዘርፍም ወጪ ቆጣቢና በሳይንሳዊ መንገድ የሚመረቱ የኢንተርሎኪንግ ጡቦችን፣ የኮብልስቶን ድንጋይ ዝግጅትንና የግንባታ ፈጠራ ቴክኖሎጂዎችን ከከተማና ገጠር ኮሪደር ልማት ጋር በማስተሳሰር የሚጨበጥ ውጤት እንዲያመጣ አቅጣጫ ሰጥተዋል።
559
የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ባለፉት አምስት ዓመታት ያስመዘገባቸው ለውጦች
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከተቋቋመ አምስት ዓመታትን አስቆጥሯል፡፡
በዚህ ጊዜ ውስጥ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የነበሩ ማነቆዎችን ለመፍታት አጠቃላይ የህግና የማዕቀፍ ለውጦችን አድርጓል፡፡
የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ተሻለ በሬቻ እንዳብራሩት፤ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ከዚህ በፊት ሲመራበት የነበረው የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በአዲስ መልክ ተከለሶ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡
በተጨማሪም አዲስ የቴክኒክና ሙያ ስትራቴጂ እንዲሁም የቴክኒክና ሙያ፣ ከፍተኛ ትምህርት፣ የምርምር እና የኢንዱስትሪ ትስስር አዋጅ መሻሻላቸው በዚህ የአምስት ዓመት ጉዞ ውስጥ የሚጠቀሱ ዋና ዋና ማሻሻያዎች ናቸው፡፡
ይህንን የፖሊሲ ክለሳ ተከትሎ አዲስ ሀገራዊ የብቃት ማዕቀፍ የተዘጋጀ ሲሆን ከዚህ ቀደም ተቋማቱ እስከ ደረጃ 5 ብቻ ያሰለጥኑ የነበረውን አሰራር በመቀየር አሁን እስከ ደረጃ 8 (ፒ.ኤች.ዲ) ድረስ ማሰልጠን እንዲችሉ ወደ ትግበራ ተገብቷል፡፡
እነዚህ ለውጦች የተደረጉት የዘርፉንና የኢንዱስትሪውን ፍላጎት በማጣጣም ነው፡፡ የአዲሱ ቴክኒክና ሙያ እሳቤ አሰልጥኖ ሰርተፍኬት ከመስጠት ባለፈ ክህሎትን፣ ዕውቀትን የሚያስጨብጥ እና ጥሩ አመለካከትን በዜጎች ላይ የሚቀርጽ እንዲሆን ታስቦ የተሰራበት ነው፡፡
ከዚህ ቀደም ሁሉም የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ተመሳሳይ ስልጠናዎች የሚሰጡበት አሰራር ቀርቶ አሁን የገበያውን ፍላጎትና የአካባቢን ጸጋ መሰረት ያደረገ ስልጠና እንዲሰጡ ተቋማቱ ዘመኑ በሚዋጀው ሁኔታ እንዲደራጁ ተደርገዋል፡፡
ከዚህም ባሻገር ተቋማት ማሰልጠን ብቻ ሳይሆን አምራችና አገልግሎት የሚሰጡ ኢንተርፕሩኒያል መሆን እንዳለባቸው በማድረግ ስልጠናው ይበልጥ ተግባር ተኮር ለማድረግ ተችሏል፡፡
559
+4
የኮሪያ ልዑካን ቡድን በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የክህሎት ፓርክን ጎበኙ
የኮሪያ ሪፐብሊክ ልዑካን በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘውን የክህሎት ፓርክን ጎብኝተዋል፡፡
ከጉብኝቱ በተጨማሪ ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ ጋር በክህሎት ልማትና በቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ትብብር ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።
በውይይቱ የኢትዮጵያና የኮሪያን የክህሎት ልማት ትብብር ይበልጥ ማጠናከር፣ የኢንዱስትሪና የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን ትስስር ማሳደግ እና ወጣቶችን ለዘመናዊ የሥራ ዓለም የሚያዘጋጁ የክህሎት ሥልጠናዎችን ማጠናከር ላይ ትኩረት ተደርጓል።
ልዑኩ በተጨማሪም በሚኒስቴሩ እየተገነባ ያለውን የክህሎት ፓርክ (Skills Park) በመጎብኘት የግንባታ ሂደቱንና ፕሮጀክቱ ለኢትዮጵያ የክህሎት ልማት ያለውን ሚና ተመልክቷል።
የኮሪያ ልዑኩ ከLG Electronics፣ KOICA Ethiopia Office፣ World Together፣ LGE East Africa፣ LGEME እና Dragon Electronics የተውጣጡ ከፍተኛ ኃላፊዎችን አካቷል።
ጉብኝቱ ኢትዮጵያና ኮሪያ በክህሎት ልማት፣ በቴክኖሎጂ እና በኢንዱስትሪ ተኮር ሥልጠና ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ወደ ተጨማሪ የጋራ ዕድሎች ለማስፋት ያለውን አቅም ያመላከተ ነው።
559
የካናዳ የሥራ ዕድል ምዝገባ ጥሪ
0931158358 ይደውሉልን ከ70 በላይ የሙያ ስራዎች አሉ።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በኢትዮጵያ የካናዳ አምባሳደር ጆሿ ታባህ ጋር ውይይት አካሄደ። በውይይቱ ኢትዮጵያ በክህሎት ልማት፣ ሥራ ዕድል ፈጠራ እና ሰላማዊ የኢንዱስትሪ ግንኙነት ላይ ያከናወነችውን ሪፎርም ተመልክተዋል።
ካናዳ በክህሎት ልማትና ሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፎች ከኢትዮጵያ ጋር ለመተባበር ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል።
የሚፈለጉ የሙያ ዘርፎች:-
. ሹፌር
.ዴሊቨሪ
.ጥበቃ
· የጥበቃ ሰራተኛ
· ፅዳት ሰራተኛ
· አጠቃላይ ረዳት
· የሲቪል ግንባታ ረዳት
· የኮንስትራክሽን ሰራተኛ
· ኤሌክትሪሻን
· ቧንቧ ባለሙያ
· የHVAC ባለሙያ
· ብየዳ ባለሙያ
· የእሳት አደጋ መከላከያ ባለሙያ
· ግንብ ሰራተኛ
· ቀለም ቀቢ
· ምርጋትና ልስን ሰራተኛ
· የጂፕሰም ባለሙያ
· የፎርምወርክ አናጺ
· ላሚኔተር
· የብረት መዋቅር ሰራተኛ
· ስካፎልዲንግ ሰራተኛ
· የመጋዘን እቃ ማሸጊያ
· የፋብሪካ ሰራተኛ
· የጭነት ጫኝ
· የሞተር ሳይክል አሽከርካሪ
· የሳይት ተቆጣጣሪ
ከ70 በላይ ስራ አለ
ለመመዝገብ የሚያስፈልጉ ነገሮች
· ብሔራዊ መታወቂያ ወይም መንጃ ፈቃድ
· የሚሰራ የስልክ ቁጥር
· የቅርብ ጊዜ ፓስፖርት መጠን ፎቶ
· ፓስፖርት ወይም የልደት ካርድ
የምዝገባ ሂደት
Labor ID ካለዎት፦ በቴሌግራም አድራሻችን በቀጥታ ይመዝገቡ።
Labor ID ከሌለዎት፦
1. በቴሌግራም ይመዝገቡ።
2. በአቅራቢያዎ ባለ ወረዳ/ቀበሌ በመሄድ ባዮሜትሪክስ ያድርጉና Labor ID ይውሰዱ።
📲 ለምዝገባ :- https://t.me/molsgovet
ማሳሰቢያ:-
· ምዝገባና ስምሪት የሚከናወነው በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ አማካኝነት ነው።
· የክፍያ ውል ዋስትና በተቋሙና በኤጀንሲው በኩል ይጠናቀቃል።
559
የካናዳ የሥራ ዕድል ምዝገባ ጥሪ
0931158358 ይደውሉልን ከ70 በላይ የሙያ ስራዎች አሉ።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በኢትዮጵያ የካናዳ አምባሳደር ጆሿ ታባህ ጋር ውይይት አካሄደ። በውይይቱ ኢትዮጵያ በክህሎት ልማት፣ ሥራ ዕድል ፈጠራ እና ሰላማዊ የኢንዱስትሪ ግንኙነት ላይ ያከናወነችውን ሪፎርም ተመልክተዋል።
ካናዳ በክህሎት ልማትና ሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፎች ከኢትዮጵያ ጋር ለመተባበር ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል።
የሚፈለጉ የሙያ ዘርፎች:-
. ሹፌር
.ዴሊቨሪ
.ጥበቃ
· የጥበቃ ሰራተኛ
· ፅዳት ሰራተኛ
· አጠቃላይ ረዳት
· የሲቪል ግንባታ ረዳት
· የኮንስትራክሽን ሰራተኛ
· ኤሌክትሪሻን
· ቧንቧ ባለሙያ
· የHVAC ባለሙያ
· ብየዳ ባለሙያ
· የእሳት አደጋ መከላከያ ባለሙያ
· ግንብ ሰራተኛ
· ቀለም ቀቢ
· ምርጋትና ልስን ሰራተኛ
· የጂፕሰም ባለሙያ
· የፎርምወርክ አናጺ
· ላሚኔተር
· የብረት መዋቅር ሰራተኛ
· ስካፎልዲንግ ሰራተኛ
· የመጋዘን እቃ ማሸጊያ
· የፋብሪካ ሰራተኛ
· የጭነት ጫኝ
· የሞተር ሳይክል አሽከርካሪ
· የሳይት ተቆጣጣሪ
ከ70 በላይ ስራ አለ
ለመመዝገብ የሚያስፈልጉ ነገሮች
· ብሔራዊ መታወቂያ ወይም መንጃ ፈቃድ
· የሚሰራ የስልክ ቁጥር
· የቅርብ ጊዜ ፓስፖርት መጠን ፎቶ
· ፓስፖርት ወይም የልደት ካርድ
የምዝገባ ሂደት በዚህ በኩል ይላኩልን 📲 ለምዝገባ :- https://t.me/molsgovet
Labor ID ካለዎት፦ በቴሌግራም አድራሻችን በቀጥታ ይመዝገቡ።
1. በቴሌግራም ይመዝገቡ።
2. በአቅራቢያዎ ባለ ወረዳ/ቀበሌ በመሄድ ባዮሜትሪክስ ያድርጉና Labor ID ይውሰዱ።
ማሳሰቢያ:-
· ምዝገባና ስምሪት የሚከናወነው በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ አማካኝነት ነው።
· የክፍያ ውል ዋስትና በተቋሙና በኤጀንሲው በኩል ይጠናቀቃል።
559
+3
በኦሮሚያ ክልል ስራ አጥነትን ለመቀነስና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑ ተገለጸ
በኦሮሚያ ክልል ስራ አጥነትን ለመቀነስና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ በክህሎት ልማት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን የክልሉ የስራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ።
ቢሮው የስራ እድል ፈጠራን ለማበረታታት የሙያና ክህሎት ስልጠናዎችን በመስጠት፣ ከመንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ባለድርሻ አካላት ጋር የተቀናጀ አሰራር በመዘርጋት ላይ ይገኛል።
ዛሬ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው የምክክር መድረክም፣ ቢሮው ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ወጣቶችን በሙያና ክህሎት ለማብቃት የሚያደርገው የዚሁ ጥረት አካል ነው።
የቢሮው ሃላፊ ኢንጂነር ኤባ ገርባ በወቅቱ፤ ስራ አጥነትን ከመሰረቱ ለመቀነስ፣ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና ተኪ ምርት ለማምረት በሙያ የበቃ የሰው ሃይል በጥራትና በብዛት ማፍራት ወሳኝ ነው ብለዋል።
የክልሉ ወጣቶች በሙያ ራሳቸውን ችለው ከመደበኛ ስራ በተጨማሪ በክህሎትና ኢንተርፕሩነርሽፕ ራሳቸውን ማጎልበት አለባቸው ብለዋል።
ገበያው የሚፈልገውን የሰው ሃይልና የሙያ ልማት ላይ መስራት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከግብርና፣ ትምህርት ፣ ማዕድን፣ ከተለያዩ ሴክተሮች ጋር በጋራ እየሰራን ነው ብለዋል።
የቢሮው የክህሎት ልማት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ነርሰዲን ቃድ በበኩላቸው በየአካባቢው ያሉ ፀጋዎችንና አቅሞችን በመለየት የልማት ፕሮጄክቶች፣ ሆቴሎችና የቱሪዝም መስቦች እንዲሁም የኢንቨስትመንት መስኮች ላይ ትኩረት አድርገን የሙያ ስልጠና እንሰጣለን ነው ያሉት
በአዲሱ በጀት ዓመት ሰፊ የስራ ዕድል ለመፍጠር የሚያስችሉ ገበያ ተኮር አጫጭር የሙያና ክህሎት ልማት ስልጠናዎችን 3 ሚሊዮን ለሚሆኑ ሰጣቶች በመስጠት ወደ ስራ ለማስገባት መታቀዱን ለአብነት አንስተዋል
