en
Feedback
E-LMIS -ብቁ

E-LMIS -ብቁ

Open in Telegram

ብቁ ሰራተኛ•ብቁ ቀጣሪ•ብቁ.ውሳኔ ሰጭ ለመመዝገብ ፖስፖርት ፎቶ ይላኩልን https://t.me/@ELMISETHIOPIAN

Show more
558
Subscribers
-224 hours
-57 days
-730 days
Posts Archive
የኅብር ቀን ኢትዮጵያችን በሀገር በቀል እሴቶቿ፤ የነገውን ብሩህ ተስፋዋን በገዛ እጆቿ እየቀረጸች ትገኛለች! በትውልድ ቅብብሎሽ ያገኘናቸውን ድንቅ የሀገር በቀል እሴቶቻችንን በማጎልበት እና በመደመር
የኅብር ቀን ኢትዮጵያችን በሀገር በቀል እሴቶቿ፤ የነገውን ብሩህ ተስፋዋን በገዛ እጆቿ እየቀረጸች ትገኛለች! በትውልድ ቅብብሎሽ ያገኘናቸውን ድንቅ የሀገር በቀል እሴቶቻችንን በማጎልበት እና በመደመር ፍልስፍና በመመራት፣ ለጽኑ ኅብረብሔራዊ አንድነታችን የማይናወጥ መሠረት ጥለናል። ታሪካዊውን ሀገራዊ ምክክር የመጀመር የታሪክ እጥፋት ተነስተን፣ የሁሉም ዜጎቻችንን ሕይወት ከሚለውጡ ሰው-ተኮር የኮሪደር ልማታችን፣ የበጎ ፈቃድ ስራዎቻችን እንዲሁም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃግብርን በተግባር እውን እስከማድረግ ድረስ፤ ሁላችንም በአንድነት ስንቆም የጋራ ትርክቶቻችን ወደ ጋራ ስኬት እንደሚያሻግሩን በተግባር አሳይተናል። እኛ የምንገነባው አካታች የሆነች፣ በኢኮኖሚ ራሷን የቻለች፣ የአብሮነትና መረዳዳት ባህል የጎለበተባት ጠንካራ ሀገር ብቻ ሳይሆን የሁሉንም ኢትዮጵያውያን የጋራ ታላቅነትና እምቅ አቅም በተግባር እያረጋገጥን እንገኛለን። በአንድነት ወደ ብልጽግና ጉዟችን እንቀጥላለን። አንድ ህዝብ፣ ታላቅ ሀገር ኢትዮጵያ!  #EthiopiaPrevails

🌏✈️ የውጪ ሀገር የስራ ማስታወቂያ 🚀 በህጋዊ የውጪ ሃገር ሥራ ስምሪት ፕሮግራም በተለያዩ ዘርፎች የሰው ኃይል ይፈለጋል። የዜጎችን መብት፣ ደህንነት እና ጥቅም በማስጠበቅ ህጋዊ በሆነ መንገድ ወ
🌏✈️ የውጪ ሀገር የስራ ማስታወቂያ 🚀 በህጋዊ የውጪ ሃገር ሥራ ስምሪት ፕሮግራም በተለያዩ ዘርፎች የሰው ኃይል ይፈለጋል። የዜጎችን መብት፣ ደህንነት እና ጥቅም በማስጠበቅ ህጋዊ በሆነ መንገድ ወደ ውጪ ሀገር ለመስራት የሚፈልጉ አመልካቾች እንዲያመለክቱ እናሳውቃለን። 🚧 የሞያ ዘርፎች፦ 🔹የጥበቃ ሰራተኛ 🔹ፅዳት ሰራተኛ 🔹አጠቃላይ ረዳት 🔹የሲቪል ግንባታ ረዳት 🔹የኮንስትራክሽን ዕለታዊ ሰራተኛ / ረዳት 🔹ኤሌክትሪሻን / የኤሌክትሪክ ባለሙያ 🔹ቧንቧ ሰራተኛ / የቧንቧ ባለሙያ 🔹የኤር ኮንዲሽነር ባለሙያ 🔹ብየዳ ሰራተኛ / የብየዳ ባለሙያ 🔹የእሳት አደጋ መከላከያ ባለሙያ 🔹ግንብ ሰራተኛ / የድንጋይና ጡብ ግንባታ ባለሙያ 🔹ቀለም ቀቢ 🔹ምርጋትና ልስን ሰራተኛ 🔹የጂፕሰም ባለሙያ 🔹የፎርምወርክ አናጺ / የማገር አናጺ 🔹የአሉሚኒየም ስራ ባለሙያ 🔹ላሚኔተር / የላሜራ ስራ ባለሙያ 🔹ማጠናቀቂያ ስራ ባለሙያ 🔹የብረት መዋቅር ሰራተኛ 🔹ስካፎልዲንግ ሰራተኛ 🔹ሪገር እና ምልክት ሰጪ 🔹የመጋዘን እቃ ማሸግ 🔹የፋብሪካ ሰራተኛ 🔹የጭነት አውራጅና ጫኝ ሰራተኛ 🔹የሞተር/ሳይክል አሽከርካሪ 🔹የሲቪል ፎርማን / የሳይት ተቆጣጣሪ 🔹የሲቪል ረዳት ፎርማን / የቡድን መሪ ✅ ለመመዝገብ Labor ID ካሎት ይህን https://t.me/molsgovet ማስፈንጠሪያ ተጠቅመው መመዝገብ። Labor ID ከሌሎት የሚከተሉትን ሂደቶች ይከተሉ፦ 1. በይመዝገቡ። https://t.me/molsgovet ይጫሉ 2. መታወቂያ      ፎቶግራፍ      ስልክ ቁጥር      ፖስፖርት ወይም የልደት ካርድ 3. E-LMIS OTP  ID ካገኙ በኋላ በተሰጠው የማመልከቻ ማስፈንጠሪያ ገብተው መረጃዎትን በትክክል ሞልተው ያመልክቱ ስልጠና የሚሰለጥኑ ይሆናል።

የኢትዮጵያ የብዝኅ ዘርፍ እመርታ፡ የዜጎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት መሠረት ማኑፋክቸሪንግ፣ ከተማ ግብርና፣ ሆቴልና ቱሪዝም፣ ጨርቃ ጨርቅና ሌሎችም መስኮች ወጣቶች በስፋት ተሰማርተው ውጤታማ እየሆኑ የሚ
+5
የኢትዮጵያ የብዝኅ ዘርፍ እመርታ፡ የዜጎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት መሠረት ማኑፋክቸሪንግ፣ ከተማ ግብርና፣ ሆቴልና ቱሪዝም፣ ጨርቃ ጨርቅና ሌሎችም መስኮች ወጣቶች በስፋት ተሰማርተው ውጤታማ እየሆኑ የሚገኙበት የሥራ ዕድል ፈጠራ ትኩረት መስኮች ናቸው፡፡ ወጣቶቹ በተሰማሩበት መስክ ውጤታማ እንዲሆኑ በመንግሥት በኩል ለወጣቶቹ እየተሰጠው ያለው የክህሎት ማበልጸጊያ ስልጠና፣ የመስሪያና መሸጫ ቦታ ማመቻቸትና በማኅበር ማደራጀት እስከ ብድር ማመቻቸት ድረስ እየተወሰደ ያለው ተግባር ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ ይገኛል፡፡ በዚህም በርካታ ወጣቶች ተሰማርተው ውጤታማ ከመሆናቸውም ባለፈ ለሌሎችም የሥራ ዕድል እየፈጠሩ ይገኛሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የበጀት ዓመቱን አፈጻጸም አስመልክተው ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ፣ በተለያዩ ቦታዎች እየተካሄዱ ያሉ የገጠርና የከተማ ኮሪደር ልማቶች፣ ኢንዱስትሪ፣ ግብርና፣ ማዕድን፣ ሜጋ ፕሮጀክቶችና አዳዲስ የነፃ ንግድ ዞኖች መፈጠር ለሥራ ዕድል ፈጠራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ዜጎች ውጭ ሀገርም ሄደው መስራት እንዲችሉ ከእንግሊዝ፣ ከጀርመን፣ ከፈረንሳይ፣ ከሳዑዲ ዓረቢያና ከሌሎች ሀገራት ጋር በተፈጠሩ ስምምነቶች የውጭ ሀገር የሥራ ዕድሎች ለሀገራችን ዜጎች መስፋፋታቸውን ተናግረዋል። ሌላው አዲስ የሥራ መስክ የርቀት ሥራ (Remote Job) መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቁመው፣ በኢትዮጵያ ተቀምጠው ለውጭ ኩባንያዎች በቨርቹዋል መንገድ የሚሠሩ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል። የማዳበሪያ፣ የሪፋይነሪ፣ በክሪፕቶ ማይኒንግ የሚሠሩ ሥራዎችና የኤርፖርት ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁና ሲስፋፉ ተጨማሪ የሥራ ዕድሎች እንደሚፈጠሩም ጠቁመዋል።

የእመርታ ቀን አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል፤ ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነትን እያረጋገጥን ያለነው ከልመናና ከጥገኝነት በተላቀቀው አዲ
የእመርታ ቀን አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል፤ ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነትን እያረጋገጥን ያለነው ከልመናና ከጥገኝነት በተላቀቀው አዲሱና ታሪካዊው መንገዳችን ነው! በሚሊዮን በሚቆጠር ዶላር ስንዴ ከማስገባት ተነስተን ዛሬ የአፍሪካ ቀዳሚ ስንዴ አምራች በመሆን የሚሊዮን ዶላሮችን ወጪ ማስቀረት ችለናል። በ«ሌማት ትሩፋት» የምግብ ዋስትናን በተግባር እያረጋገጥን፣ በ«ኢትዮጵያ ታምርት» ንቅናቄም አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋትና የሥራ ዕድል በመፍጠር ሉዓላዊነታችንን እያረጋገጥን እንገኛለን። ከዚህ ቀደም የማይደፈሩና አይነኬ ይባልላቸው የነበሩ ከባድ የማክሮ-ኢኮኖሚ ሪፎርም ውሳኔዎችን በቁርጠኝነት በመተግበር፤ የሀገራችንን ኢኮኖሚ በፅኑ መሠረት ላይ እየገነባን እንገኛለን። እነዚህ ሁሉ ታላላቅ ድሎች ኢትዮጵያ በሚያጋጥሟት ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች ሸብረክ ሳትል በፅናት መጓዝ መቻሏን የሚያረጋግጡ ህያው ምስክሮች ናቸው፤ ይህ የእመርታ ጉዟችን ለመጪው ዓመት የሰነቀው ተስፋ እጅግ ግዙፍ ነው! #EthiopiaDelivers

የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት የእመርታ ቀን አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል፤ ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነት
የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት የእመርታ ቀን አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል፤ ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነትን እያረጋገጥን ያለነው ከልመናና ከጥገኝነት በተላቀቀው አዲሱና ታሪካዊው መንገዳችን ነው! በሚሊዮን በሚቆጠር ዶላር ስንዴ ከማስገባት ተነስተን ዛሬ የአፍሪካ ቀዳሚ ስንዴ አምራች በመሆን የሚሊዮን ዶላሮችን ወጪ ማስቀረት ችለናል። በ«ሌማት ትሩፋት» የምግብ ዋስትናን በተግባር እያረጋገጥን፣ በ«ኢትዮጵያ ታምርት» ንቅናቄም አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋትና የሥራ ዕድል በመፍጠር ሉዓላዊነታችንን እያረጋገጥን እንገኛለን። ከዚህ ቀደም የማይደፈሩና አይነኬ ይባልላቸው የነበሩ ከባድ የማክሮ-ኢኮኖሚ ሪፎርም ውሳኔዎችን በቁርጠኝነት በመተግበር፤ የሀገራችንን ኢኮኖሚ በፅኑ መሠረት ላይ እየገነባን እንገኛለን። እነዚህ ሁሉ ታላላቅ ድሎች ኢትዮጵያ በሚያጋጥሟት ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች ሸብረክ ሳትል በፅናት መጓዝ መቻሏን የሚያረጋግጡ ህያው ምስክሮች ናቸው፤ ይህ የእመርታ ጉዟችን ለመጪው ዓመት የሰነቀው ተስፋ እጅግ ግዙፍ ነው!"

አዲሱን ዓመት በአዲስ ተስፋና በአዲስ ራዕይ! ጳጉሜን 1 — የእመርታ ቀን ጳጉሜን፤ የአሮጌው ዓመት መደምደሚያ፣ የአዲሱ ዓመት መነሻ ነው። አዲሱን ዓመት በአዲስ ተስፋና በአዲስ ራዕይ እንቀበላለን።
+1
አዲሱን ዓመት በአዲስ ተስፋና በአዲስ ራዕይ! ጳጉሜን 1 — የእመርታ ቀን ጳጉሜን፤ የአሮጌው ዓመት መደምደሚያ፣ የአዲሱ ዓመት መነሻ ነው። አዲሱን ዓመት በአዲስ ተስፋና በአዲስ ራዕይ እንቀበላለን። በፈጠራና በፍጥነት በታጀበው ሀገራዊ ሪፎርም፣ ኢትዮጵያ ከአዝጋሚ ዕድገት ወደ እመርታዊ ለውጥ እየተሸጋገረች ትገኛለች። ይህ እመርታም በተጨባጭ ውጤቶች ተገልጧል፡፡ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተጠናቆ ወደ ሥራ በመግባቱ በተፈጠረው መነቃቃት፣ የኮሪደር ልማቶች፣ በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ እውን የሆኑ ፕሮጀክቶችና የፈጠሯቸው አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎች የዚህ እመርታ መገለጫዎች ናቸው። በስንዴ አብዮትና በሌማት ትሩፋት በግብርናው፣ በትምህርትና ሥልጠና እና በጤና ዘርፎች የተመዘገቡ ውጤቶችም የዚህ እመርታ ተጨባጭ ማሳያዎች ናቸው። በሰው ሰራሽ አስተውሎትና በዲጂታላይዜሽን አዳዲስ አቅሞችን እየገነባን፣ በኢንዱስትሪ ምርትና ምርተማነትን እያሳደግን፣ በቱሪዝም ያለንን ሀብት ወደ ዕድል እየቀየርን፣ በቴክኖሎጂና ፈጠራ አዳዲስ የዕድገት አድማሶችን መክፈት ችለናል፡፡ ይህን እምራተዊ ለውጥ ቀጣይነት ማረጋገጥ የሚችለው የሰው ሀይላችን ነው፡፡ ስለሆነም ገበያ መር በሆነው የክህሎት ልማት እና ክህሎት መር የሆነውን የሥራ ዕድል ፈጠራ አጠናክሮ በማስቀጠል እንዲሁም ሰላማዊ ኢንዱስትሪ ግንኙነቱን በማጠናከር በመስኩ የተመዘጉቡ ውጤቶችን በማላቅና የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ርብርቡ በአዲሱ ዓመትም ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ መልካም የእመርታ ቀን!

የሲዳማ ክልል የሥራና ክህሎት ቢሮ የISO 9001:2015 ዓለም አቀፍ የጥራት ሰርተፊኬት አገኘ የሲዳማ ክልል የሥራና ክህሎት ቢሮ የISO 9001:2015 ዓለም አቀፍ የጥራት ማኔጅመንት ሥርዓት ሰር
+5
የሲዳማ ክልል የሥራና ክህሎት ቢሮ የISO 9001:2015 ዓለም አቀፍ የጥራት ሰርተፊኬት አገኘ የሲዳማ ክልል የሥራና ክህሎት ቢሮ የISO 9001:2015 ዓለም አቀፍ የጥራት ማኔጅመንት ሥርዓት ሰርተፊኬትን ከኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት በይፋ ተረክቧል። ሰርተፊኬቱ እንደ ሀገር ለአንድ የክልል የሥራና ክህሎት ቢሮ የተሰጠ የመጀመሪያው መሆኑ ተገልጿል። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ፣ ስኬቱ በክልሉ የመንግሥት ተቋማት ዘመናዊና ጥራት ያለው አገልግሎት የማስፈን ጥረትን የሚያፋጥን እና ለሌሎች ተቋማትም አርአያ የሚሆን መሆኑን ገልጸዋል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ነቢሃ መሀመድ በበኩላቸው፣ ሰርተፊኬቱ ቢሮው የጥራት አሠራሩን ለማጠናከር ያደረገውን ተነሳሽነት የሚያሳይ በመሆኑ፣ የተገኘውን ደረጃ በማስጠበቅ ለተገልጋዮች የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጥ አሳስበዋል። የኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ማዓዛ አበራ፣ ቢሮው የISO 9001:2015 መስፈርቶችን በአግባቡ በማሟላቱ ሰርተፊኬቱን ማግኘት መቻሉን ገልጸው፣ የተገኘውን የጥራት ደረጃ ለማስቀጠል ጥረቱ እንዲጠናከር አሳስበዋል። የቢሮው ኃላፊ ወ/ሮ ሀገረጽዮን አበበ ደግሞ ስኬቱ የተጠናከረ ቡድናዊ ሥራና ቀጣይነት ያለው ተቋማዊ ሪፎርም ውጤት መሆኑን ጠቅሰው፣ ሰርተፊኬቱ የተገልጋዮችን እርካታና የዜጎችን የሥራ ዕድልና የክህሎት ልማት ፍላጎት በተሻለ ደረጃ ለማሟላት ተጨማሪ ብርታት እንደሚሆን ገልጸዋል።

የአላጌ ኮሌጅ የአምስት ዓመታት ፍሬዎች ‎ ‎ስልጠናን ከምርትና ከፈጠራ ጋር ያጣመረው የአላጌ ግብርና ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጅ በአምስት ዓመታት አበይት አገራዊ ውጤቶችን ማስመዝገቡን ገለጸ ‎የአላ
+5
የአላጌ ኮሌጅ የአምስት ዓመታት ፍሬዎች ‎ ‎ስልጠናን ከምርትና ከፈጠራ ጋር ያጣመረው የአላጌ ግብርና ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጅ በአምስት ዓመታት አበይት አገራዊ ውጤቶችን ማስመዝገቡን ገለጸ ‎የአላጌ ግብርና ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጅ ባለፉት አምስት ዓመታት ስልጠናን ከምርት፣ ምርትን ከቴክኖሎጂ፣ ቴክኖሎጂን ከፈጠራና ሥራ ፈጠራ፣ እንዲሁም ምርትን ከገቢ ማመንጨት ጋር በማስተሳሰር የሚታይ ተቋማዊና ተግባራዊ ለውጥ ማስመዝገቡን አታወቀ። ‎ ‎የኮሌጁ ዲን ረዳት ፕሮፌሰር መርክነህ  መሰኔ እንደገለጹት፤ ተቋሙ የትምህርትና ስልጠና ሚናውን በማስፋት ሰልጣኞች የሚማሩትን እውቀት በቀጥታ በምርትና በቴክኖሎጂ ሥራ ላይ እንዲተገብሩ አድርጓል። ‎ ‎ በዚህም ኮሌጁ የሚያፈራው የሰው ኃይል የሙያ ብቃት ያለው ብቻ ሳይሆን ምርታማ፣ ፈጣሪና ሥራ የመፍጠር አቅም ያለው እንዲሆን የሚያስችል አዲስ የስልጠና ሥርዓት በተግባር መተርጎሙን አብራርተዋል። ‎ ‎ኮሌጁ በአትክልትና ፍራፍሬ፣ በሰብልና በእንስሳት ምርት ዘርፎች ሰፊ የምርት ማሳዎችን ማልማቱን የጠቆሙት ረዳት ፕሮፌሰር መርክነህ፤ እንደ ቺያ ሲድ ያሉ ከፍተኛ የገበያ እሴት ያላቸውን ሰብሎች ማልማት መቻሉን ተናግረዋል። በተጨማሪም የወተት፣ የዶሮ፣ የንብ ማነብና የሀር ትል እርባታን በማስፋፋት ጥሬ ምርቶችን ወደ ተጨማሪ እሴት የመቀየር አሠራር መጠናከሩን ጠቁመዋል። ‎ ‎በተለይም ከሀር ጥሬ ምርት ኮምፎርት፣ ካራቫት፣ ስካርቭና ነጠላ በማዘጋጀት የኮሌጁን ልዩ የማቀነባበርና የፈጠራ አቅም ማሳየት መቻሉን አብራርተዋል። ‎ ‎በቴክኖሎጂ ሽግግርና ፈጠራ በኩልም የሽንኩርትና የመኖ መፍጫዎችን፣ ዘመናዊ የዶሮ ቤቶችንና የቨርሚኮምፖስት (ኦርጋኒክ ማዳበሪያ) ምርትን በመጠቀም የምርት ውጤታማነትን ከስልጠና ጋር ማጣመር ተችሏል። ‎

‎በአምስት ዓመቱ የተመዘገቡ የኢንተርፕራይዝ፣ የቅመማ ቅመም እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ውጤቶች የሚዛን ግብርና ኮሌጅ በአምስት ዓመቱ የተመዘገቡ የኢንተርፕራይዝ፣ የቅመማ ቅመም እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ው
+3
‎በአምስት ዓመቱ የተመዘገቡ የኢንተርፕራይዝ፣ የቅመማ ቅመም እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ውጤቶች የሚዛን ግብርና ኮሌጅ በአምስት ዓመቱ የተመዘገቡ የኢንተርፕራይዝ፣ የቅመማ ቅመም እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ውጤቶቹን በሚኒስቴሩ አገራዊ የምክክር ጉባኤ ላይ እያቀረበ ይገኛል፡፡ ‎ ‎ከጉባኤው ጎን ለጎን በተዘጋጀው አገራዊ ኢግዚቢሽን ላይ ኮሌጁ በዞኒንግና ዲፈረንሴሽን ከተሰጠው የትኩረት አቅጣጫ አንጻር ያመረታቸውን የቡና፣ ቁንዶ በርበሬ፣ የሻይ ቅጠል፣ ሙዝ እና የማር ምርቶችን በአካል በማቅረብ ለጎብኚዎች  እያስጎበኘ ነው። ‎ የኮሌጁ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንተርፕራይዝ ልማት ምክትል ሃላፊ አቶ ጥላሁን አለማየሁ እንደገለጹት፤ ሚዛን ግብርና ኮሌጅ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ተጠሪ ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ በአዲስ እሳቤ ከተዋቀረ ወዲህ ስልጠናን ከኢንተርፕራይዝ ልማት፣ ከቴክኖሎጂ ሽግግርና ከሥራ ዕድል ፈጠራ ጋር አስተሳስሮ በርካታ ውጤቶችን አስመዝግቧል። ‎ተቋሙ በዶሮ እርባታ፣ በወተት ከብት፣ በንብ ማነብና በሰብል ልማት ዘርፎች ባቋቋማቸው ኢንተርፕራይዞች ባለፉት ዓመታት 33,952 ሊትር ወተት፣ 1,559,738 እንቁላል፣ እና 334 ኪሎ ግራም ማር ማምረት ችሏል። ‎በሰብል ልማት በኩል ከተረከበው 200 ሄክታር የማስፋፊያ መሬት ውስጥ በ45 ሄክታሩ ላይ ብቻ በተሰራ ስራ በአንድ ዓመት በ3 ዙር 845 ኩንታል ምርት የሰበሰበ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅትም የሩዝ ልማት ማሳ እንክብካቤ እያደረገ ይገኛል። ‎ ‎አቶ ጥላሁን አክለው እንደገለጹት፤ እነዚህ የተገኙ የኢንተርፕራይዝ ውጤቶች ስልጠናውን ተግባር ተኮር ከማድረጋቸው ባለፈ፣ ከሥራ እድል ፈጠራ ጋር በመስተሳሰራቸው ለአካባቢው ሥራ አጥ ወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጥረዋል።

የዘርፉ የመካከለኛ ዘመን ዕቅድ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ባካሄደው የ5ዓመታት ልማት የምክክር መድረክ ላይ የሚኒስቴሩ መካከለኛ ዘመን የ2019–2021 የልማት ዕቅድና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ
+9
የዘርፉ የመካከለኛ ዘመን ዕቅድ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ባካሄደው የ5ዓመታት ልማት የምክክር መድረክ ላይ የሚኒስቴሩ  መካከለኛ ዘመን የ2019–2021 የልማት ዕቅድና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሂዷል። በመድረኩ የሥራ ዕድል ፈጠራን ማስፋፋት፣ የዜጎችን ክህሎት ከሥራ ገበያው ፍላጎት ጋር ማጣጣምና የተረጋጋ የኢንዱስትሪ ሰላም መፍጠር የዕቅዱ ዋና ትኩረቶች መሆናቸው ተገልጿል። በተለይም ወጣቶችና ሴቶችን ተጠቃሚ ያደረገ የሀገር ውስጥ የሥራ ዕድል ፈጠራን ማስፋፋትና የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪትን ማጠናከር በዕቅዱ ቀዳሚ ትኩረት ተሰጥቷል። የዕድገት አቅም ያላቸውን ኢንተርፕራይዞች መደገፍ፣ ኢ-መደበኛ የሥራ እንቅስቃሴዎችን ወደ መደበኛ ሥርዓት ማሸጋገርና የፋይናንስና የገበያ ትስስርን ማጠናከርም የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማስፋፋት ከሚከናወኑ ዋና ተግባራት መካከል ተጠቅሰዋል። በክህሎት ልማት ዘርፍ ደግሞ የሥራ ገበያውን ፍላጎት ያማከሉ የሙያ ክህሎቶችን በመደበኛና በአጫጭር ሥልጠናዎች ማሳደግ፣ የፋብሪኬሽን ኢንጂነሪንግና የቴክኖሎጂ አቅምን ማጠናከር እንዲሁም የፈጠራ ሀሳቦችን ወደ ምርትና ኢንተርፕራይዝ መቀየር ትኩረት ተሰጥቷቸዋል። የኢንዱስትሪ ሰላምን ለማጠናከርም በሠራተኛና በአሠሪ መካከል የተሻለ ግንኙነት መፍጠር፣ የሠራተኞችን መብትና የሥራ ደህንነት ማስጠበቅ እንዲሁም የሥራ ክርክሮችን በሰላማዊ የውይይትና የመፍትሔ ሥርዓት ማስተናገድ በቀጣይ ትኩረት የሚሰጣቸው መሆኑ ተጠቁሟል። በአጠቃላይ ዕቅዱ የሥራ ዕድል ፈጠራን ከክህሎት ልማት፣ ከኢንተርፕራይዝ እድገትና ከኢንዱስትሪ ሰላም ጋር በማስተሳሰር የሥራ ገበያውን ለማጠናከርና የዜጎችን የሥራ ተሳትፎ ለማሳደግ ያተኮረ መሆኑ ተመላክቷል።

በአምስት ዓመታት የልማት ጉዞ የተገኙ ውጤቶችን የበለጠ ማላቅ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከሰኞ ነሐሴ 25 ጀምሮ ለተከታታይ አራት ቀናት ሲያካሄድ የቆየውን የአምስት ዓመታት የልማት ጉዞ የምክክር መድረ
+8
በአምስት ዓመታት የልማት ጉዞ የተገኙ ውጤቶችን የበለጠ ማላቅ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከሰኞ ነሐሴ 25 ጀምሮ ለተከታታይ አራት ቀናት  ሲያካሄድ የቆየውን የአምስት ዓመታት የልማት ጉዞ የምክክር መድረክ ለዘርፉ ዕድገት አስተዋፅኦ ላበረከቱ ተጠሪ ተቋማት ፣ የክልል አስፈፃሚ አካላት፣ የስኪል ኢትዮጵያና ኢንተርፕራይዞች ዕውቅና በመስጠት ተጠናቋል፡፡ አማራ ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ ድሬዳዋ አስተዳደር፣ ኦሮሚያና ሲዳማ ክልሎች፣ ድሬዳዋ አስተዳደርና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በዘርፉ ባስመዘገቡት ውጤት የዋንጫ ተሸላሚ ሆነዋል፡፡ በዕውቅና እና ማጠቃለያ መድረኩ  ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ፣ አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ፣ ክብርት ነቢሃ መሃመድ በአምስት ዓመታት በዘርፉ የተገኙ ውጤቶችን በላቀ መልኩ ለማስቀጠል የሚያስችል ስንቅ ከመድረኩ መገኘቱን ጠቁመዋል፡፡ በክህሎት ልማት ዘርፍ የስልጠና ደረጃና  ጥራትን ለማሳደግ ፣ የተጀመሩ የዲጂታላይዜሽን ሥራዎችን  ለማጠናከርና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆኑ የክህሎት ባለቤቶችን በስፋት ለማፍራት  የሚያስችሉ ጉልህ ተግባራት በትኩረት እንደሚከናወኑ ተናግረዋል፡፡ ከሥራ ዕድል ፈጠራ አንፃር እንደ ሀገር ያለውን የሥራ ፍላጎት ምላሽ ለመስጠት በሚያስችል መልኩ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር  የሚያስችሉ ሥራዎች በቀጣይ እንደሚሰሩም ጠቁመዋል፡፡ በኢንዱስትሪ ሰላምና ጤንነት ላይ የሚታዩ ችግሮችን በመሰረታዊነት ለመፍታት ፣የምክክር ሥርዓትን በአግባቡ ማሳለጥ እንደሚገባም አሳስበዋል ። በተቋም ግንባታ አስቀድመው  የተጀመሩ የሰው  ኃይል ልማት፣   የፒ ኤ ስ አይ ላብ ፣ የISO የጥራት ሥራ አመራርና የዲጂታለይዜሽን ሥራዎችን የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ እንደሚሠራም ተናግረዋል።

በሀገራችን የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለውን ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (I
+2
በሀገራችን የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለውን ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) መካከል ስምምነት ዛሬ አከናውነናል። ‎በ100 ቢሊዮን የኢትዮጵያ ብር ካፒታል የተቋቋመው እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን ደግሞ 200 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ አስተዋፅኦ የሚያደርግበት ይህ ተቋም፤ በባንክ ዘርፋችን ውስጥ የጥሬ ገንዘብ ፍሰት አለመመጣጠንን የሚቀርፍ እና በመላው ኢትዮጵያ ተደራሽ የሚሆን የቤት መግዣ ብድር ፋይናንስን የሚያስገኝ ይሆናል። ‎ ‎ይህ አጋርነት በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገነቡና የኢትዮጵያውያንን ክብር የጠበቁ 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ለማቅረብ እንዲሁም በፋይናንስ ሥርዓታችን ውስጥ የግል ዘርፉን ተሳትፎ ለማስፋት ያስቀመጥነውን ግብ የሚያሳካ ወሳኝ እርምጃ ነው። ‎ኢትዮጵያ ፈጣን፣ ጠንካራ እና ሁሉንም ያካተተ ኢኮኖሚ መገንባቷን ትቀጥላለች።

የልማት ዘርፎችን ከአለም አቀፍ አዝማሚያዎች ጋር መጣጣም በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የአምስት ዓመት የልማት ጉዞ የምክክር መድረክ ላይ የልማት ዘርፎችን የሚቀርፁባቸው ዓለም አቀፍ አዝማሚያዎች(Megat
+4
የልማት ዘርፎችን ከአለም አቀፍ  አዝማሚያዎች ጋር መጣጣም በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የአምስት ዓመት የልማት ጉዞ የምክክር መድረክ ላይ የልማት ዘርፎችን የሚቀርፁባቸው ዓለም አቀፍ አዝማሚያዎች(Megatrends)  የተመለከተ ጥናት ቀርቧል፡፡ በመድረኩ ላይ የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የጥናትና ምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሀብታሙ ሙሉጌታ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ቅድሚያ የሰጠቻቸውን የልማት ዘርፎች ከዓለም አቀፍ አዝማሚያዎች ጋር እንዴት ማጣጣም እንደሚገባ ቀድሞ መስራትና መዘጋጀት ያስፈልጋል፡፡ ተቋማትም ለቀጣይ ሀገራዊ ህልም እና ለዓለም አዝማሚያ መዘጋጀት እንዳለባቸው ገልጸው፤ መረጃዎችን ዲጂታል በማድረግ የሚቀርቡ ጥያቄዎችን ፈጣንና ውጤታማ በሆነ መንገድ ምላሽ መስጠት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ የቀረበው ጥናት እንደሚያመለክተው  ዓለም በአሁኑ ወቅት በቴክኖሎጂ፣ በአየር ንብረት፣ በስነ-ሕዝብ ለውጥ እና በዓለም አቀፍ ኢኮኖሚ ለውጦች እያለፈች እንደመሆኑ ይህንን ያገናዘበ ቅድመ ዝግጅት ማድረግ  ለልማት ግቦቻችን ስኬት ወሳኝ መሆኑ ተገልጿል፡፡ ዓለም አቀፉ ገበያ በሚፈልገው መስፈርትና ደረጃ  የሰው ኃይል ልማትን መቅረፅና መተግበርም  የልማት ግቦቻችንን ለማሳካት የሚያስችል ዋንኛ ስልት መሆኑም በጥናቱ ተጠቁሟል፡፡

የገበያ ክፍተት የወለደው ፈጠራ አንድ የተጣለ የፕላስቲክ ቆሻሻ ወደ ጥሬ ዕቃ፣ አንድ ሀሳብ ደግሞ ወደ ምርት ሊቀየር ይችላል። የጀማል አብደላ ፈጠራ ይህንን በተግባር ያሳያል። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴ
+1
የገበያ ክፍተት የወለደው ፈጠራ አንድ የተጣለ የፕላስቲክ ቆሻሻ ወደ ጥሬ ዕቃ፣ አንድ ሀሳብ ደግሞ ወደ ምርት ሊቀየር ይችላል። የጀማል አብደላ ፈጠራ ይህንን በተግባር ያሳያል። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የ5ዓመት የልማት ጉዞ ምክክር መድረክ ጎን ለጎን በአዲስ ኮንቬንሽን ማዕከል በተዘጋጀው «ስኪል ኢትዮጵያ» የፈጠራ ውጤቶች አውደ-ርዕይ ላይ የቀረበው «ሃይብሪድ 3D ፕሪንቲንግ እና ሌዘር ማሽን» በአንድ ጊዜ 3D ማተምና የሌዘር ቅርጽ ሥራ ማከናወን የሚችል ሁለገብ ማሽን ነው። ጀማል በቴክስታይል ኢንጂነሪንግ ያገኘውን እውቀት ተጠቅሞ በጨርቃጨርቅና ማተሚያ ዘርፍ ያለውን የመሳሪያና የጥሬ ዕቃ እጥረት ለመፍታት ተነሳ። በተለይም ለ3D ማተሚያ የሚያስፈልገውን Filament ከውጭ ከመግዛት ይልቅ፣ እንደ ሃይላንድና ማይካ ያሉ የፕላስቲክ ቆሻሻዎችን በመልሶ ጥቅም ወደ ጥሬ ዕቃነት በመቀየር ይጠቀማል። ይህም በአንድ በኩል የምርት ወጪን ለመቀነስ፣ በሌላ በኩል የፕላስቲክ ቆሻሻን ለመቀነስ ያግዛል። ማሽኑ 3D አካላትን ከማተም ባሻገር በእንጨት፣ በቆዳ፣ በቦርሳና በማይካ ላይ ጽሑፍና ዲዛይን በሌዘር መቅረጽ ይችላል። ከውጭ የሚገቡ ውድ ማሽኖችን በሀገር ውስጥ እውቀትና ጥሬ ዕቃ ለመተካት የተደረገው ይህ ጥረት፣ ማሽኑን እስከ 80 ሺህ ብር ወጪ ለተጠቃሚዎች ለማቅረብ አስችሏል። በኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት እየተሰጠ በሚገኘው የ«ስኪል ኢትዮጵያ» ተግባራዊ ስልጠናዎችና የባለሙያዎች ድጋፍ ጀማል የማሽኑን የኤሌክትሪካል ገጠማ ሥራ ለማሻሻል እንደረዱት ይገልጻል። አሁን ፈጠራው ከአውደ-ርዕይ አልፎ ወደ ገበያ መግባት ጀምሯል። ማሽኑን ለማዘዝ የመጡ የመጀመሪያዎቹ ሦስት ደንበኞች ትዕዛዝ በመቀበል ወደ ማምረት ተሸጋግሯል።

ተሰጥኦ መነሻ፤ ክህሎት መሣሪያ፤ ትጋት ደግሞ ወደ ውጤት የሚወስድ መንገድ ነው! ተሰጥኦ በክህሎት ሲታጀብ፣ ሃሳብ ወደ ምርት፣ ፈጠራም ወደ ሥራና ዕድል ይቀየራል። የገነት ደበበ ታሪክም ይህንኑ እውነ
+7
ተሰጥኦ መነሻ፤ ክህሎት መሣሪያ፤ ትጋት ደግሞ ወደ ውጤት የሚወስድ መንገድ ነው! ተሰጥኦ በክህሎት ሲታጀብ፣ ሃሳብ ወደ ምርት፣ ፈጠራም ወደ ሥራና ዕድል ይቀየራል። የገነት ደበበ ታሪክም ይህንኑ እውነታ የሚያሳይ የትጋት፣ የፈጠራና የሥራ ፍቅር ታሪክ ነው። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ባዘጋጀው የአምስት ዓመት የልማት ጉዞ የምክክር መድረክ ተሳታፊ የሆነችው ገነት ደበበ፣ ከልጅነቷ ጀምሮ ያላትን የፈጠራ ችሎታ በማሳደግ ዛሬ ወደ ሥራ የቀየረች ሥራ ፈጣሪ ናት። ገነት ማንኛውንም ያየችውን ነገር በተለየ የፈጠራ እይታ ትመለከታለች። ከተለመዱ ግብዓቶች የተለዩ ነገሮችን በመጠቀም ፣ ሃሳቧን ወደ ተጨባጭ ምርት ትቀይራለች። ለመኖሪያ ቤቶች፣ ለእንግዳ ማረፊያዎችና ለሬስቶራንቶች የሚያገለግሉ የተለያዩ ጌጣጌጦችን፣ ፎቶዎችን፣ ቅርጻቅርጾችንና ሌሎች ለቤት ውበት የሚጨምሩ ምርቶችን በራሷ ሃሳብና ፈጠራ ታዘጋጃለች። የፈጠራ ሃሳቦቿም በድንገት የሚመጡ አይደሉም። ሃሳብ በመጣላት ጊዜ በወረቀት ትመዘግባለች ወይም ድምጿን በመቅረጽ ታስቀምጣለች። በኋላም ወደ ሥራ ትለውጠዋለች። በትዕዛዝ የሚመጡላትን ሥራዎችም እንደተቀበለች ብቻ አትሠራቸውም፤ የራሷን ግብዓት፣ እይታና ፈጠራ ጨምራ የተለየ ምርት ለማቅረብ ትጥራለች። የገነት የፈጠራ ጉዞ ዛሬ ከምታከናውነው የሥራ ዓለም ብቻ የሚጀምር አይደለም። ከልጅነቷ ጀምሮ የሰዎችን ምስሎች ትቀርጽ፣ ቁርጥራጭ ጨርቆችን በመስፋት ቦርሳዎችን ትሠራ ነበር። ለተማሪዎች የመማሪያ እገዛ የሚሆኑ ትምህርታዊ ቅርጾችንም ታዘጋጅ ነበር። ይህ የልጅነት ፍላጎት ከጊዜ ወደ ጊዜ ወደ ክህሎት፣ ከክህሎቷም ወደ ምርታማ ሥራ ተለውጧል። ገነት በሥራዋ የምትጠቀመው ግብዓት ብዙውን ጊዜ ለሌሎች ተራ ወይም የማይጠቅም የሚመስሉ ነገሮችን ነው።

ሀገር አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ሴት አመራሮችና አሰልጣኞች ፎረም የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እያካሄደ የሚገኘው የአምስት ዓመት የልማት ጉዞ የምክክር መድረክ አካል የሆነው ‹‹ ሀገር አቀፍ የቴክኒክና ሙያ
+4
ሀገር አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ሴት አመራሮችና አሰልጣኞች ፎረም የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እያካሄደ የሚገኘው የአምስት ዓመት የልማት ጉዞ የምክክር መድረክ አካል የሆነው ‹‹ ሀገር አቀፍ የቴክኒክና ሙያ አመራሮችና አሰልጣኞች ፎረም›› ተመሰረተ፡፡ በፎረሙ ምስረታ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ነቢሃ መሃመድ የቴክኒክና ሙያ ሴት አመራሮችና አሰልጣኞች የቴክኒክና ሙያ ስልጠና  ውስጥ  ሴቶች ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ የማድረግ ጉልህ ኃላፊነት እንዳለባቸው ተናረዋል፡፡ ይህን ኃላፊነታቸውን በሚጠበቀው ደረጃ  እንዲወጡ ለማስቻል ቀደም ሲል በክልል ደረጃ  ፎረሙ መመስረቱን የገለፁት ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ አደረጃጀቱን የበለጠ ለማጠናከር የክልል ፎረሞችን በአንድ ጥላ የሚሰባስብ  ሀገር አቀፍ ፎረም መመስረት አስፈላጊ ሆኖ እንደተገኘም ገልፀዋል፡፡ የሴት አመራርና አሰልጣኞችን አቅም ማጎልበት፣ ልምድና ተሞክሮዎችን መለዋወጥ እንዲሁም የኢንዱስትሪውን ፍላጎት ከሥርዓተ ፆታ እኩልነት አጀንዳዎች ጋር ያላቸውን ቁርኝነት ማጠናከር ፎረሙ ለማቋቋም መነሻ የሆኑ ዋንኛ ዓላማዎች መሆናቸውም በመድረኩ ተገልጿል፡፡

ጳጉሜን 2018 — የኢትዮጵያ ማንሰራራት! የ2018 ዓ.ም. የጳጉሜን ቀናት “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል መሪ ሀሳብ ይከበራሉ። ✅ ጳጉሜን 1 — የምርታማነት ቀን ኢትዮጵያ ከአዝጋሚ የዕድገት ጉዞ
ጳጉሜን 2018 — የኢትዮጵያ ማንሰራራት! የ2018 ዓ.ም. የጳጉሜን ቀናት “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል መሪ ሀሳብ ይከበራሉ። ✅ ጳጉሜን 1 — የምርታማነት ቀን ኢትዮጵያ ከአዝጋሚ የዕድገት ጉዞ ተላቃ ወደ ፈጣንና ምርታማ ዕድገት መግባቷን በማሰብ ይከበራል። በእለቱ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በገቢ አሰባሰብ፣ በዕዳ ቅነሳ፣ በቱሪዝም እና በውጭ ምንዛሬ ዘርፎች የተመዘገቡት አስደማሚና ዘርፈ ብዙ ስኬቶች ይነሳሉ። ✅ ጳጉሜን 2 — የማንሰራራት ቀን ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ፣ በታዳሽ ኃይል፣ በከተሞች ገጽታ እና በገጠር ኮሪደር ልማት በጣለችው ጠንካራ መሠረት ላይ በመቆም ወደ ተሻለ ከፍታ የተሻገረችበት ድንቅ ሥራ ይወሳል። ✅ ጳጉሜን 3 — የፅናት ቀን የዛሬውን ትውልድ ሀገራዊ ተሳትፎ የሚያበረታቱ እና የነገውን ጀግኖች የሚቀርጹ ልዩ ልዩ ክንውኖችም ይኖራሉ። በእለቱ ከማለዳው 12 ሰዓት ላይ በሁሉም የመንግሥትና የግል ተቋማት እንዲሁም በኤምባሲዎች የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ የመስቀልና ብሔራዊ መዝሙር የመዘመር ሥነ-ሥርዓት በታላቅ ሥነ-ሥርዓት ይካሄዳል። ✅ ጳጉሜን 4 — የህብር ቀን የኢትዮጵያ ጌጥ የሆነው ብዝሃነት ጎልቶ የሚወጣበትና የሚከበርበት ቀን ነው። በመካከላችን የሚፈጠሩ ልዩነቶችን ሁልጊዜም በውይይትና በምክክር ለመፍታት ትኩረት ተሰጥቶ ሲሠራ ቆይቷልና፣ ዕለቱ የምክክርና የትብብር እሴቶችን በሚያጎለብቱ ተግባራት ይከበራል። ✅ ጳጉሜን 5 — የነገ ቀን ነገን ዛሬ ላይ የመገንባት እሳቤ የሚጎላበት ቀን ነው። በዲጂታል ኢኮኖሚ፣ በመረጃ ሉዓላዊነት፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ በወጣቶች የክህሎት ልማት እና በዲጂታላይዜሽን ላይ ትኩረት በማድረግ ይከበራል። ይህም የሀገራችንን የወደፊት ብሩህ ተስፋ ያሳያል።

ከፈጠራ ሀሳብ ወደ ገበያ፦ ለስታርታፖች የሚያስፈልግ ምቹ ምህዳር አቤል ማስረሻ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በነበረው ቆይታ፣ የአካል ጉዳተኛ ጓደኛው ይገጥመው የነበረውን ፈታኝ ሁኔታ በመነሳት፣ የመንቀሳ
+7
ከፈጠራ ሀሳብ ወደ ገበያ፦ ለስታርታፖች የሚያስፈልግ ምቹ ምህዳር አቤል ማስረሻ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በነበረው ቆይታ፣ የአካል ጉዳተኛ ጓደኛው ይገጥመው የነበረውን ፈታኝ ሁኔታ በመነሳት፣ የመንቀሳቀስ ችግር ላለባቸው ወገኖች መፍትሄ የሚሆን የኤሌክትሪክ ዊልቼር  ፈጥሯል። ይህ ሀሳብ ወደ ተግባር ሊሸጋገር የቻለው የአቤል ንድፈ ሀሳብ እውቀትን ከተግባራዊ ክህሎት ጋር በማጣመር ነው። እንደ አቤል ማብራሪያ መሰል የፈጠራ ሥራዎች ወደ ዘላቂ ንግድ እንዲሸጋገሩ ፋይናንስ፣ የማምረቻ ቦታ፣ ጥሬ ዕቃ፣ የገበያ ትስስር፣ እንዲሁም ቀልጣፋ ሕግና አሠራር አይነተኛ ሚና ይጫወታሉ። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የአምስት ዓመት የልማት ጉዞ የምክክር ጉባኤ ላይ አቤልን ጨምር ውጤታማ የሆኑ ሥራ ፈጣሪዎች የተሳተፉበት የፓናል ውይይት «ከሥልጠና ወደ ሥራ፣ ከፈጠራ ሀሳብ ወደ ንግድ ልማት» በሚል ርዕስ ተካሂዷል። ወጣቶች  ፈጠራቸው ወደ ምርት፣ ምርታቸው ወደ ገበያ፣ ገበያቸውም ወደ ዘላቂ ንግድ የሚሸጋገርበትን ምቹ ምህዳር መፍጠር  የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅት ይፈልጋል። በቴክኒክና ሙያ ተቋማት የሚገኘው ተግባራዊ ክህሎት በስታርታፕ ምህዳር በተገቢው ሁኔታ ከተደገፈ፣ የወጣቶች ፈጠራ ከግል ስኬት ባሻገር ለሀገራዊ ኢኮኖሚ ዕድገትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ጉልህ አስተዋፅኦ ሊያበረክት እንደሚችል በውይይቱ ላይ በስፋት ተነስቷል፡፡

የጳጉሜን ቀናት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ስኬቶች በሚያሳይ መልኩ ይከበራሉ-የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የጳጉሜን ቀናት የኢትዮጵያን ማንሰራራት እና የተገኙ ሁለንተናዊ ስኬቶችን በሚያሳይ መልኩ እን
የጳጉሜን ቀናት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ስኬቶች በሚያሳይ መልኩ ይከበራሉ-የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የጳጉሜን ቀናት የኢትዮጵያን ማንሰራራት እና የተገኙ ሁለንተናዊ ስኬቶችን በሚያሳይ መልኩ እንደሚከበሩ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ የ2018 የጳጉሜን ቀናት ስያሜዎችን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙሀን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በዚህም የጳጉሜን ቀናት "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል እንደሚከበሩ ተናግረዋል። ጳጉሜን 1 "የእመርታ ቀን" በሚል እንደሚከበር ገልጸው፤ እለቱ ኢትዮጵያ ከአዝጋሚ የእድገት ጉዞ በመውጣት ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች የሚዘከሩበት መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም ኢትዮጵያ ያስመዘገበቻቸው እመርታዊ ለውጦች የሚዘከሩበት መሆኑን ጠቁመዋል። ጳጉሜን 2 "የማንሰራራት ቀን" በሚል እንደሚከበር ገልጸው፤ እለቱ ኢትዮጵያ ወደ ሁለንተናዊ ልማት የተሸጋገረችበትን ጉዞ በሚያሳዩ ሁነቶች እንደሚከበር ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ከጎታች ማነቆ የወጣችበትና ማንሰራራቷም የሚገለጥበት መሆኑን አንስተዋል። ጳጉሜን 3 "የጽናት ቀን" በሚል እንደሚከበር ገልጸው፤ ታሪካዊ ጽናትን ማስቀጠልን የምናሳይበት ነው ብለዋል። የጽናት ቀን ጀግኖች የሚወሱበትና አዳዲስ ጀግኖች የሚፈጠሩበት መሆኑን ገልጸዋል። በእለቱ ከጠዋቱ 12 ሰዓት ላይ የሰንደቅ አላማ የመስቀል መርሀ ግብር እንደሚከናወንም ገልጸዋል። ጳጉሜን 4 "የህብር ቀን" በሚል እንደሚከበር ገልጸው፤ አንድነትን በሚያጸኑ ተግባራት እንደሚከናወን ገልጸዋል። የትብብር እና የምክክር እሴትን በሚያጎለብቱ ሁነቶች እንደሚከበር ተናግረዋል። በእለቱ ለ150 ሺህ ሰዎች ነጻ የጤና አገልግሎት እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።

የፖሊሲና የማዕቀፍ ለውጦች ያመጡት ዋና ዋና ስኬቶች የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ላለፉት አምስት ዓመታት ያከናወናቸውን የልማት ጉዞዎች አስመልክቶ በሚያካሂደው የምክክር መድረክ 3ኛ ቀን ውሎ በፖሊሲ፣ ተ
+6
የፖሊሲና የማዕቀፍ ለውጦች ያመጡት ዋና ዋና ስኬቶች የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ላለፉት አምስት ዓመታት ያከናወናቸውን የልማት ጉዞዎች አስመልክቶ በሚያካሂደው የምክክር መድረክ 3ኛ ቀን ውሎ በፖሊሲ፣ ተቋማዊ እሳቤና ሥርዓት ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት ተደርጓል፡፡ ባለፉት አምስት ዓመታት  የክህሎት ልማት ትኩረት  ከአቅርቦት መር ወደ ፍላጎት መር ተቀይሯል። ሰልጣኞችን አሰልጥኖ ማውጣት ብቻ ሳይሆን በኢንተርፕራይዝ ምስረታ ላይ ያተኮረና ክህሎት ለሥራ ዕድል ፈጠራ ተመጋጋቢ የሚሆንበት የአሰራር ስርዓትም  መዘርጋቱ ተገልጻል፡፡ የህግ ማዕቀፎች ማሻሻላቸው፣  ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ  እስከ አንድ ማዕከል የተናበበ መዋቅር  መዘርጋቱ፣አዳዲስ እሳቤዎችና ዘረ-መሎች መዘጋጀታቸውና  ተቋማትን  በቴክኖሎጂ ለማዘመን የሚደረጉ ጥረቶች  ዘርፉን ከማሳደግ አንፃር ጉልህ ሚና እንደነበራቸው ተወያዮቹ አብራርተዋል። ከአዲሶቹ እሳቤዎች አንዱ ተቋማቱን «ኢንተርፕረነሪያል» ማድረግ  እንደመሆኑ ተቋማት የኢንተርፕረነርሽፕ እሳቤን በመተግበር በዜጎች ተጠቃሚነትና  በሀገር እድገት ላይ የራሳቸውን አሻራ እንዲያሳርፉ እድል እንደሰጣቸው በፖናል ውይይቱ ላይ በስፋት ተነስቷል።