en
Feedback
Mahtot Eshetie / ማኅቶት እሸቴ

Mahtot Eshetie / ማኅቶት እሸቴ

Open in Telegram

መንፈሳዊ የቤተክርስቲያን አስተምህሮና ሙሉ የግእዝ ቋንቋ ሥልጠና ትምህርት ማስተማሪያ የቴሌግራም ገጽ። በመደበኛ መርሐ ግብር የግእዝ ቋንቋ ሥልጠናን መከታተል የምትሹ በኮሜንት መስጫው ጻፉልኝ።

Show more
4 654
Subscribers
+5624 hours
+1677 days
+17430 days
Posts Archive
የክርስቶስን የእግዚአብሔር ልጅነት ማን መሰከረ? ዕቅበተ እምነት ክፍል ሦስት ከክፍል ሁለት የቀጠለ ✍️ በክፍል ሁለት ጽሑፋችን ላይ የባሕርይ አምላክ መሆን ያለበት ማን ነው ብለን እግዚአብሔር ብቻ ብለናል። በመቀጠልም ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነውን ብለን የእግዚአብሔር ልጅነቱን የመሰከሩ የነቢያትና የሐዋርያትን ምስክርነት አይተናል። 🖋#ጥያቄ :- የክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅነት ማን መሰከረ? 🖋#መልስ :- ነቢያትና ሐዋርያት ፣ አብ ፣ እራሱ ክርስቶስ መስክረዋል። 🎤#ማብራሪያ :- ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ስለመሆኑ ሦስት ምስክሮች እንዳሉት አይተናል። የመጀመሪያ የነቢያትና የሐዋርያት ምስክርነት ነው (ይህም በክፍል ሁለት ተቀምጧል)። ሁለተኛው የአብ ምስክርነት ሲሆን የመጨረሻው የራሱ ምስክርነት ነው። 💥የአብ ምስክርነት እግዚአብሔር አብ ኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ ልጁ እንደሆነ መስክሯል። ምስክሮቹም እነዚህ ናቸው። ➣ " እነሆም፥ ድምፅ ከሰማያት መጥቶ። በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ። " (ማቴ 3:17) ➣ "እርሱም ገና ሲናገር፥ እነሆ፥ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው፥ እነሆም፥ ከደመናው። በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ።" (ማቴ 17:5) 🔹🔸🔹በቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ ከሰማይ ድምፅ መጥቶ ልጄ ብሎ የተነገረለት ለክርስቶስ ብቻ ሲሆን ይህም አብ ብቸኛ የባሕርይ ልጁ እንደሆነ ሲመሰክር ነው። 💥 የራሱ የክርስቶስ ምስክርነት ኢየሱስ ክርስቶስ በቅዱስ መጽሐፍ ከአምሳ ጊዜ በላይ አብን አባቴ በማለት የእግዚአብሔር አብ ልጅነቱን ተናግሯል። ከእነዚህም ውስጥ ጥቂቶቹን እንይ። ➣ " በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ፥ ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም።" (ማቴ 7:21) ➣" ስለዚህ በሰው ፊት ለሚመሰክርልኝ ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እመሰክርለታለሁ፤" (ማቴ 10:32) ➣ "በሰው ፊትም የሚክደኝን ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እክደዋለሁ።" (ማቴ 10:33) ➣ " ሁሉ ከአባቴ ዘንድ ተሰጥቶኛል፤ ከአብ በቀር ወልድን የሚያውቅ የለም፥ ከወልድም በቀር ወልድም ሊገለጥለት ከሚፈቅድ በቀር አብን የሚያውቅ የለም።" (ማቴ 11:27) ➣ " ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው። የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ።" (ማቴ 16:17) ➣ " እነሆም፥ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ።" (ሉቃ 24:49) ➣ " የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉት አላቸው።" (ዮሐ 2:16) ➣ " እኔንም ወይም አባቴንም አታውቁም፤ እኔንስ ብታውቁኝ አባቴን ደግሞ ባወቃችሁ ነበር አላቸው።" (ዮሐ 8:19) ➣ " ኢየሱስም። ገና ወደ አባቴ አላረግሁምና አትንኪኝ፤ ነገር ግን ወደ ወንድሞቼ ሄደሽ። እኔ ወደ አባቴና ወደ አባታችሁ ወደ አምላኬና ወደ አምላካችሁ ዓርጋለሁ ብለሽ ንገሪአቸው አላት።" (ዮሐ 20:17) ➣ " እኔ ደግሞ ድል እንደ ነሣሁ ከአባቴም ጋር በዙፋኑ ላይ እንደተቀመጥሁ፥ ድል ለነሣው ከእኔ ጋር በዙፋኔ ላይ ይቀመጥ ዘንድ እሰጠዋለሁ።" (ራእ 3:21) 🔹🔸🔹 አብ በሰማይ ልጄ ብሎ የመሰከረለትን ክርስቶስ ደግሞ በሰማይ ያለ አባቴ ብሎ የአብ የባሕርይ ልጅ መሆኑን ነገረን። 🎤#ማብራሪያ :- የሰው ልጅ ሰው ፣ የእንስሳ ልጅ እንስሳ እንደ ሆነ ሁሉ የእግዚአብሔር ልጅ ደግሞ እግዚአብሔር ነው። ስለዚህም ክርስቶስ የእግዚአብሔር የባሕርይ ልጅ መሆኑን መጻሕፍት ስለ ነገሩን ክርስቶስ እግዚአብሔር ነው ማለት ነው። ➢➢ የቀጣይ ትምህርት ከክፍል ሦስት የቀጠለ ... የክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት ማሳያዎቹ ምንድን ናቸው? ➜ ሐምሌ / 24 / 2018 ዓ.ም © ማኅቶት እሸቴ 👇👇👇 የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/MEBspiritualtraining21 👇👇👇 የፌስቡክ አድራሻ https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1

የባሕርይ አምላክ መሆን ያለበት ማን ነው? ዕቅበተ እምነት ክፍል ሁለት ከክፍል አንድ የቀጠለ ✍️ስለ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት መጽሐፍ ቅዱስ መናገሩን ከማስረዳታችን አስቀድሞ እነዚህን ነጥቦች ማየት አስፈላጊ ነው። ፩፡ አምላክ / አምላክነት ምንድን ነው? ፪፡ የባሕርይ አምላክ መሆን ያለበት ማን ነው? የመጀመሪያውን ነጥብ በክፍል አንድ በሰፊው በማየታችን እዚህ ላይ የምንመለከተው ሁለተኛውን ነጥብ ነው። ከዚህ በፊት እንዳየነው መጽሐፍ ቅዱስ የባሕርይ አምላክን አምላክ እንጂ አማልክት ብሎ አይጠራም። ምክንያቱም የባሕርይ አምላክ አንድ አምላክ ብቻ ስለሆነ ነው። የጸጋ አማልክንት እና ጣዖታትን ግን አማልክት ብሎ ይጠራቸዋል። ይህም የሚያሳየው የጸጋ አማልክት የተባሉ ቅዱሳን ብዙ ስለሆኑና ባለማወቅ ሰዎች አማልክት ያደረጓቸው ጣዖታትም ብዙ በመሆናቸው ነው። ✍️#ጥያቄ :- የባሕርይ አምላክ መሆን ያለበት ማን ነው? ✍️#መልስ :- ዓለማትን የፈጠረ እግዚአብሔር ብቻ። 📖🖋#ማብራሪያ :- ይህንንም መጻሕፍት እንደዚህ ይመሰክራሉ። ➣ " በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ።" (ዘፍ 1:1) ➣ "እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ አምላካችን እግዚአብሔር አንድ እግዚአብሔር ነው። አንተም አምላክህን እግዚአብሔርን በፍጹም ልብህ በፍጹምም ነፍስህ በፍጹምም ኃይልህ ውደድ።" (ዘዳ 6÷4-5) ➣" እግዚአብሔርም ደግሞ ሙሴን አለው። ለእስራኤል ልጆች እንዲህ ትላለህ። የአባቶቻችሁ አምላክ፥ የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ እግዚአብሔር ወደ እናንተ ላከኝ፤ ይህ ለዘላለሙ ስሜ ነው፥ እስከ ልጅ ልጅ ድረስም መታሰቢያዬ ይህ ነው። " (ዘጸ 3:15) ➣ "ስሙ ቀናተኛ የሆነ እግዚአብሔር ቅንዓት ያለው አምላክ ነውና ለሌላ አምላክ አትስገድ።" (ዘጸ 34:14) ➣ " ከእግዚአብሔር በቀር አምላክ ማን ነው? ከአምላካችንስ በቀር እግዚአብሔር ማን ነው?" (መዝ 17:31) ✍️#ጥያቄ :- የባሕርይ አምላክ ዓለማትን የፈጠረ እግዚአብሔር ከሆነ ፤ ክርስቶስ እግዚአብሔር ነውን? ✍️#መልስ :- አወ። ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እግዚአብሔር ነው። 📖🖋#ማብራሪያ :- ይህንንም የክርስቶስን እግዚአብሔርነት መጻሕፍት እንዲህ ብለው ይመሰክራሉ። የክርስቶስን የእግዚአብሔር ልጅነት እና እግዚአብሔር መሆን የመሰከሩ ምስክሮች እነዚህ ናቸው። ፩፡ የነቢያትና ፣ የሐዋርያት ምስክርነት ፪፡ የአብ ምስክርነት ፫፡ የራሱ ምስክርነት 💥 የነቢያትና ፣ የሐዋርያት ምስክርነት ➣ "እግዚአብሔር አለኝ። አንተ ልጄ ነህ፥ እኔ ዛሬ ወለድሁህ።" (መዝ 2:7) ➣ " ስምዖን ጴጥሮስም መልሶ። አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ አለ።" (ማቴ 16:16) ➣ " በታንኳይቱም የነበሩት። በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ነህ ብለው ሰገዱለት።" (ማቴ 14:33) ➣ " እርሱ ታላቅ ይሆናል የልዑል ልጅም ይባላል፥ ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል፤" (ሉቃ 1:32) ➣ " ናትናኤልም መልሶ። መምህር ሆይ፥ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ።" (ዮሐ 1:50) ➣ " ነገር ግን ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ታምኑ ዘንድ፥ አምናችሁም በስሙ ሕይወት ይሆንላችሁ ዘንድ ይህ ተጽፎአል።" (ዮሐ 20:31) ➣ " እግዚአብሔርም የዘላለምን ሕይወት እንደ ሰጠን ይህም ሕይወት በልጁ እንዳለ ምስክሩ ይህ ነው። ልጁ ያለው ሕይወት አለው፤ የእግዚአብሔር ልጅ የሌለው ሕይወት የለውም።" (1ኛ ዮሐ 5÷11-12) ➣ "እውነተኛም በሆነው በእግዚአብሔር ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን እንኖራለን።" (1ኛ ዮሐ 5÷20) ➢➢ የቀጣይ ትምህርት ከክፍል ሁለት የቀጠለ ... ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ስለመሆኑ የራሱና የአባቱ ምስክርነት? ➜ ሐምሌ / 23 / 2018 ዓ.ም © ማኅቶት እሸቴ 👇👇👇 የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/MEBspiritualtraining21 👇👇👇 የፌስቡክ አድራሻ https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1

አንድ የእምነት ተቋም ታሪክ የሚሰርቅ ከሆነ በምንም መልኩ የራሱ ታሪክ የለውም ማለት ነው። ታሪክ መስረቅ ገንዘብ ከመስረቅ ይከፋል።

የክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት በመጽሐፍ ቅዱስ ዕቅበተ እምነት ክፍል አንድ ✍️ ጥያቄ :- ክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት መሆኑ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራልን? ✍️ መልስ :- አዎ ይናገራል። 📖🖋 ማብራሪያ :- ስለ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት መጽሐፍ ቅዱስ መናገሩን ከማስረዳታችን አስቀድሞ እነዚህን ነጥቦች ማየት አስፈላጊ ነው። ፩፡ አምላክ / አምላክነት ምንድን ነው? ፪፡ የባሕርይ አምላክ መሆን ያለበት ማን ነው? 📖🖋 አምላክ / አምላክነት ምንድን ነው? አምላክ ማለት ፈጣሪ ፣ ገዥ ፣ ፈራጅ ማለት። ይኼውም ዓለምን የፈጠረ ፣ የፈጠረውን ዓለም የሚገዛ ፣ በፈጠረው ፍጥረት ላይ የመፍረድና የማስተዳደር ብቸኛ ሥልጣን ያለው ማለት ነው። 🖋 አምላክነት በሁለት መንገድ ነው። ይኼውም የጸጋና የባሕርይ። 💥 የጸጋ አምላክነት ለፍጡራን የሚሰጥ ሲሆን ይኼውም የሚቀማ የማነሣ ከራስ ያልሆነ ሰጭ ያለው ነው። "" እኔ ግን። አማልክት ናችሁ፥ ሁላችሁም የልዑል ልጆች ናችሁ አላለሁ።" መዝ 82÷6 "በፈርዖን ላይ አምላክ አድርጌሃለሁ" ዘጸ 7÷1 እንዳለ ይህ የጸጋ አምላክነትን ያስረዳናል። 💥 የባሕርይ አምላክነት። የባሕርይ አምላክ ቅድመ ዓለም የነበረ ዓለምን አሳልፎ የሚኖር እግዚአብሔር ብቻ ነው። " እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ አምላካችን እግዚአብሔር አንድ እግዚአብሔር ነው፤" እንዳለ ዘዳ 6:4 🖋 በመጽሐፍ ቅዱስ ሁለት ዓይነት አምላክ ተገልጿል። እነዚህም ⚜️ የሐሰት አማልክት (አማልክተ ሐሰት) ወይም ጣዖታት እና ⚜️ የእውነት አምላክ (አምላከ ጽድቅ) እግዚአብሔር ነው። 💥 አማልክተ ሐሰት ➺ አማልክተ ሐሰት (ሐሰተኛ አምላክ) ሁለት ናቸወ። እነዚህም #1, እግዚአብሔር የፈጠራቸው (ከፍጥረታት መካከል የሆኑ) ለምሳሌ :- ሳጥናኤል ፣ ፀሐይ ፣ ጨረቃ ፣ ከዋክብት ፣ እንስሳት ፣ አራዊት ... ወዘተ 🎤 እነዚህ ፍጥረታት ለምን ሐሰተኛ አማልክት ሊባሉ ቻሉ? #መልስ:- ሐሰተኛ አማልክት ሊባሉ የቻሉበትን በዝርዝር ስናይ ✔️ ሳጥናኤል በጥንተ ፍጥረት እኔ አምላክ ነኝ አምልኩኝ በማለቱና ዛሬም ድረስ በጣዖታት ላይ አድሮ የሚያስመልክ ስለሆነ ነው። ✔️ ፀሐይ ፣ ጨረቃ ፣ ከዋክብት ፣ እንስሳት ፣ አራዊት ወዘተ ሐሰተኛ አማልክት መባላቸው ምንም እንኳ እኛ አምላክ ነን አምልኩን ብለው ራሳቸውን ባያስመልኩም ልቡናቸው የታወረባቸው እግዚአብሔርን የማያውቁት ሰዎች እስካመለኳቸው ድረስ በእነርሱ አምላኮቻችን መባላቸው ሐሰት ነውና። እነዚህ ፍጡራን እንጂ ፈጣሪ ስለማይባሉ ነው። #2, ሰዎች እንጨት ጠርበው ፣ ደንጋይ አለዝበው ፣ ብረት አቅልጠው የሰሯቸው ጣዖታት ሲሆኑ እኒህም ሐሰተኛ አማልክት መባላቸው ፍጥረታት በመሆናቸው ነው። 🖋 ስለ እነዚህን ሐሰተኛ አማልክትም መጽሐፍ ቅዱስ እንደዚህ ይነግረናል። "ወደ ጣዖታትም ዘወር አትበሉ፥ ቀልጠው የተሠሩትንም የአማልክት ምስሎች ለእናንተ አታድርጉ፤ እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝ። " (ኦሪት ዘሌዋውያን 19:4) " የአሕዛብ ጣዖታቶች የወርቅና የብር፥ የሰው እጅ ሥራ ናቸው። አፍ አላቸው አይናገሩምም፤ ዓይን አላቸው አያዩምም፤ ጆሮ አላቸው አይሰሙምም፤ አፍንጫ አላቸው አያሸትቱምም፤ እጅ አላቸው አይዳሰሱምም፤ እግር አላቸው አይሄዱምም፤ በጕሮሮአቸውም አይናገሩም። የሚሠሩአቸውም የሚያምኑባቸውም ሁሉ እንደ እነርሱ ይሁኑ።" (መዝ 113 ÷ 12 - 16) "የኮረብታ መስገጃዎቻችሁንም አፈርሳለሁ፥ የፀሐይ ምስሎቻችሁንም አጠፋለሁ፥ ሬሳችሁንም በጣዖቶቻችሁ ሬሳዎች ላይ እጥላለሁ፤ ነፍሴም ትጸየፋችኋለች።" (ዘሌ 26:30) ➢➢ የቀጣይ ትምህርት ከክፍል አንድ የቀጠለ ... የባሕርይ አምላክ መሆን ያለበት ማን ነው? ➜ ሐምሌ / 22 / 2018 ዓ.ም © ማኅቶት እሸቴ 👇👇👇 የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/MEBspiritualtraining21 👇👇👇 የፌስቡክ አድራሻ https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1

Digital_Ethipian_Bible_(pdf).pdf15.57 MB

ይህንን ጥንታዊ መጽሐፍ የምትሹ ከዚህ በታች አስቀምጫለሁ።
ይህንን ጥንታዊ መጽሐፍ የምትሹ ከዚህ በታች አስቀምጫለሁ።

የሌላን ቤተ እምነት ታሪክ በሐሰት የራስ ለማድረግ መጣር በሃይማኖታቸው አለመተማመንንና የሃይማኖታቸውን ሐሰተኛነት ያጋልጣል።

የቀጣይ ተከታታይ ትምህርቶቻችን ፩ ፡ በዕቅበተ እምነት ዙሪያ በጥያቄና መልስ መልኩ ሁሉንም የቤተክርስቲያናችን ትምህርቶች መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት በማድረግ በተከታታይ እንማማራለን። ፪ : የውዳሴ ማር
+1
የቀጣይ ተከታታይ ትምህርቶቻችን ፩ ፡ በዕቅበተ እምነት ዙሪያ በጥያቄና መልስ መልኩ ሁሉንም የቤተክርስቲያናችን ትምህርቶች መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት በማድረግ በተከታታይ እንማማራለን። ፪ : የውዳሴ ማርያም ትርጉም እና ማብራሪያ #የማስተማሪያ_ሚዲያዎች 👇👇👇 የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/MEBspiritualtraining21 👇👇👇 የፌስቡክ አድራሻ https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1 🔷🔶🔷 ትምህርቱ ለሁሉም እንዲዳረስ #ሼር እና #ሜንሽን በማድረግ ለሌሎች እናጋራቸው። መምህር ማኅቶት እሸቴ

በኢትዮጵያ የነገሥታት ታሪክ ነጃሺ የሚባል እስላማዊ ንጉሥ አልነበረም። ንጉሥ አርማህ እስልምናን ተቀብሏል ማለት የእስልምና አስተምህሮ በውሸት ላይ መመሥረቱን ያሳያል።

➢➢➢እሳትን ያቃጠሉት እሳቶች... ✍️ እሳታዊው ባሕርይ ክርስቶስ ተጠምቆ ጥምቀትን ለሰው ልጆች ሰጥቷል። ክርስቶስን እንዲያጠምቅ የታደለው ቅዱስ ዮሐንስ ስለ ክርስቶስ ሲናገር " እኔስ ለንስሐ በውኃ አጠምቃችኋለሁ፤ ጫማውን እሸከም ዘንድ የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይልቅ ይበረታል፤ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ በእሳትም ያጠምቃችኋል።" ማቴ 3:11 ብሏል። ይህም ክርስቶስ በእሳታዊዉ ባሕርይዉ በጥምቀት እንደ ሚወልደን ሲናገር ነው። ✍️ በጥምቀት ዳግም መወለድን ለኒቆዲሞስ ሲያስምተረው "ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም።" ዮሐ 3:5 አለው። ይህ መንፈስ የተባለ በጥምቀት ልጅነት የሚገኝ እሳታዊ ባሕርይ ነው። ✍️ ስለዚህም በጥምቀት የተወለዱ ሁሉ እሳታዊ ባሕርይ ልክ ለሐዋርያት መንፈስን ቅዱስ በወረደላቸው ጊዜ በእሳት አምሳል እንደ ተሰጣቸው ለምእመናን ይሰጣቸዋል። ✍️ ከዚህ እሳታዊ ባሕርይ ተወልደው በመንፈስ ቅዱስ እሳትነት የመንፈስን ቅዱስን ሥራ ከሠሩት መካከል ሰማዕታት ቀዳሚዎቹ ናቸው። ✍️ በዛሬው ዕለት የምናከብራቸው ሕፃኑ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ በዘመኑ የነበረው ንጉሥ እግዚአብሔርን ካዱ ሐጣዖት ስገዱ ባላቸው ጊዜ ለጣዖት አንሰግድም እግዚአብሔርን አንክድም በማለት ነበልባል ወደ ሆነው ጋን ለመግባት ተስማሙ። ✍️ የእሳቱ ነበልባል ድምፅ ከሩቅ ወደ ሚያስተጋባው ጋን በገቡ ጊዜ በእነርሱ እሳትነት የጋኑን እሳት አቃጥለው የእሳትነት ባሕርይውን ወደ ውኃ ቀይረው አቀዘቀዙት። ✍️ ሰማዕታቱ ይህንን ያደረጉበት በጥምቀት ልጅነት በተወለዱበት እሳታዊ ባሕርይ ነው። ይህ የልጅነት እሳትነት በእንጨት ብዛት የተወሰነውን ዘመን የሚገድበውን ምድራዊ ውኃ የሚያጠፋውን ምድራዊ እሳትን ብቻ ሳይሆን በውኃ የማይጠፋውን የእሳትነት ባሕርይው ከምድራዊው እሳት በፍጹም የሚለየውን ዘመን የማይወስነውን እሳትነቱ በዚህ ጊዜ ያበቃል ነበልባሉ በዚህ ጊዜ ያልቃል የማይባለውንና ለኃጢአተኞች መቅጫ በሲዖል በገሀነም የተዘጋጀውን እሳትም ማጣፋት የሚቻለው ረቂቅ የልደት እሳት ነው። ✍️ ስለዚህም በዳግም ልደት በእሳታዊ ባሕርይ የተወለዱት ሁሉ እሳትነታቸው ምድራዊዩንም ሰማያዊዩንም እሳት ማጥፋት ይቻለዋል። ሐምሌ 19 / 2018 ዓ.ም © መ/ር ማኅቶት እሸቴ 👇👇👇 የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/MEBspiritualtraining21 👇👇👇 የፌስቡክ አድራሻ https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1

ሆን ተብሎ በድሮን ስለ ተጨፈጨፉት ገዳማውያን ቅዱስ ፖትርያሪኩ መግለጫ ሰጡ የተፈጸመውንም ግፍ አወገዙ። ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ መልእክት #Ethiopia | ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ወቅታዊ ጉዳዮች በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ መልእክት እንደሚከተለው ነው፦ መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! "ገባሬ ሣህል እግዚአብሔር፥ ወይፈትህ ለኩሉ ግፉዓን፦ እግዚአብሔር ይቅርታ አድራጊ ነው፤ ለተበደሉ ሁሉ ይፈርዳል።" (መዝሙር ፻፪፥፮) ከሁሉ በማስቀደም በሀገር ውስጥ እና በመላው ዓለም የምትኖሩ ኦርቶዶክሳውያን የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንን ሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓመተ ምሕረት በከፍተኛ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ለሚከበረው፤ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተልኮ በእምነታቸው የጸኑትን ቅዱስ ቂርቆስንና ቅድስት ኢየሉጣን በመከራቸው መካከል እየተራዳ የእሳቱን ነበልባል እንደክረምት ውኃ ላቀዘቀዘበት፤ በእግዚአብሔር ቃል ኪዳን የታመኑትንም እስከ ሰማዕትነት ፍጻሜ ድረስ የሚያጸና መሆኑን ለምንዘክርበት ታላቅ በዓል እንኳን አደረሳችሁ ለማለት እንወዳለን። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከዘመነ ሐዋርያት ጀምሮ የወንጌልን ብርሃን በማብራት፣ የሰላምን መንገድ በማስተማር፣ ፍትሕን በማጽናት፣ የተጨነቁትንም በማጽናናት፣ ሕዝብንና ሀገርን እየደገፈች የኖረች ናት። በዚህ ቅዱስ ተልእኮ ውስጥም መናንያን መነኮሳት እና መነኮሳይያት ዓለምንና ከዓለም የሚገኘውን ጊዜያዊ ክብር፣ ጥቅም፣ ምቾትና የመሳሰሉትን በፈቃዳቸው ትተው፤ በየገዳማቱ በበአታቸው በጾም፣ በጸሎት ተወስነው፤ ሕይወታቸውን በትሕትና ለእግዚአብሔር በመስጠት፤ ስለ ራሳቸው ብቻ ሳይሆን ስለ ሀገር፣ ስለ ሕዝብ፣ ስለ ሰላምና ስለ ዓለም ደኅንነት በመዓልትና በሌሊት የሚጸልዩ የምድራችን በረከቶች ናቸው። መስቀልን በተሸከሙ፣ ጸሎትን መከታ ባደረጉ፣ ለፍጥረት ሁሉ ምሕረትን በሚለምኑ፣ ራሳቸውን ለመከላከልም ምንም ዓይነት ቁሳዊ ዝግጅት በሌላቸው በእነዚህ መናንያን ላይ እጅን ማንሣት በእግዚአብሔር ዘንድ የተከለከለ፣ በታሪክ ፊትም የሚያሳፍር ድርጊት ነው። የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን! በደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት በቦረና ወረዳ በግዮን አባይ ገዳመ አስቄጥስ ቅድስት አርሴማ፣ አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶችና የእናቶች አንድነት ገዳም ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓመተ ምሕረት በተፈጸመው ጥቃት የመናንያን መነኮሳይያት ሕይወት በግፍ መጥፋቱን፤ በርካቶች መቁሰላቸውን፤ በገዳሙና በንዋየ ቅድሳቱ ውድመት መድረሱን ከሀገረ ስብከቱ መግለጫ በከፍተኛ ሐዘን የሰማን ሲሆን፤ በተመሳሳይም በዚሁ ዕለት በሀድያና ስልጤ ሀገረ ስብከት የአምልኮ ሥፍራ በኃይል መፍረሱና በምእመናን ላይ ጥቃት መድረሱ የሚያሳዝንና በፍጹም ተቀባይነት የሌለው የተወገዘ ተግባር ነው። በመሆኑም የጸሎት፣ የትምህርት፣ የሰላምና የመንፈሳዊ እሴት ማዕከል የሆኑትን ገዳማት መጠበቅ የአንድ ሃይማኖት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፣ የሰው ልጅ ክብርን፣ የሕግ የበላይነትንና የሀገር ሰላምን የማስጠበቅ ሓላፊነት ያላቸው በየደረጃው የሚገኙ ባለሥልጣናትና የሕግ አስከባሪ አካላት ጭምር እንደመሆኑ አሰቃቂ ጥቃት የፈጸሙት ተጠያቂዎች ለፍትሕ እንዲቀርቡ፤ ሌሎች ገዳማትና አድባራት ደኅንነታቸው እንዲጠበቅልን፤ ለተጎዱትም ተገቢው ድጋፍ እንዲደረግልን ዛሬም አበክረን እንጠይቃለን ። በመጨረሻም ሕዝበ ክርስቲያንና መላው ኢትዮጵያውያን የጥቃት ሰለባ ከሆኑት ወገኖች ጋር በመንፈሳዊም ሆነ በሰብአዊ ድጋፍ አብራችሁ እንድትቆሙ ከአደራ ጭምር እያሳሰብን፤ በጽድቅ የሚፈርደው እግዚአብሔር አምላካችን ለተበደሉት ፍትሕን፣ ለቆሰሉት ፈውስን፣ በግፍ ሕይወታቸውን ለተነጠቁት ዕረፍተ ነፍስን፣ ለቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን ፍጹም ሰላምን ይስጥልን እያልን አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን። እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!! ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!! አሜን። አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም. አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ © የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት

ከኃይስኩል highschool ጀምሮ በአንድ ዩኒቨርስቲ አብሮኝ የተማረው ጠንካራው ወንድማችን የፋሲል ጋቢ ጉባኤው ፍሬ ዲያቆን ኢንጂነር ደርሶ እሸቴ ለታላቁ ክብር በመብቃትህ ደስ ብሎናል። በነገራችን
ከኃይስኩል highschool ጀምሮ በአንድ ዩኒቨርስቲ አብሮኝ የተማረው ጠንካራው ወንድማችን የፋሲል ጋቢ ጉባኤው ፍሬ ዲያቆን ኢንጂነር ደርሶ እሸቴ ለታላቁ ክብር በመብቃትህ ደስ ብሎናል። በነገራችን ላይ ዲቁናውን ዩኒቨርሲቲ ከገባ በኋላ ነው ከፋሲል ግቢ ጉባኤ የተማረ። ግቢ ጉባኤ ማለት የብዙዎችን ሕይወት የለወጠ ነው የዚህም ትልቁ ድርሻ ማኅበረ ቅዱሳን ነው። 👇👇👇 የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/MEBspiritualtraining21 👇👇👇 የፌስቡክ አድራሻ https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1

ማስታወሻ (notebook) የሚሰጡኝን መጽሐፍ ገዝተው ከሚሰጡኝ ለይቼ አላያቸውም። እነዚህን የመሰሉ ማስታዎሻዎችን በጣም ነው የምወዳቸው ለጽሑፍ እጂጉን ይመቹኛል ሱቅ ላይ የሚሸጡት ማስታወሻዎች (no
+2
ማስታወሻ (notebook) የሚሰጡኝን መጽሐፍ ገዝተው ከሚሰጡኝ ለይቼ አላያቸውም። እነዚህን የመሰሉ ማስታዎሻዎችን በጣም ነው የምወዳቸው ለጽሑፍ እጂጉን ይመቹኛል ሱቅ ላይ የሚሸጡት ማስታወሻዎች (notebooks) መሥመራቸው ሰፋፊ (wide) በመሆኑ ለጽሑፍ አይመቹኝም የተለያዩ ተቋማት የሚያሳትሟቸው ግን እጂጉን ለጽሑፌ የተመቹ ናቸው። ምክንያቱም የእጅ ጽሑፌ ደቃቅ በመሆኑ ነው። 👇👇👇 የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/MEBspiritualtraining21 👇👇👇 የፌስቡክ አድራሻ https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1 © መ/ር ማኅቶት እሸቴ

መራሕያን / ተውላጠ ስም / Pronouns መራሕያን ማለት መሪዎች ፊት አውራሪዎች ማለት ነው። መራሕያን በአማርኛ ቋንቋ ስምን የሚተኩ ተውላጠ ስሞች ሲባሉ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ደግሞ Pronouns ይባላሉ። መራሕያን በአስር ይከፈላሉ ፩፡ ውእቱ = ያነ (እርሱ) ፪፡ አንተ = አንተ ፫፡ ውእቶሙ = እነዚያ / እነርሱ (ለወንዶች) ፬፡ አንትሙ = እናንተ (ለወንዶች) ፭፡ ይእቲ = ያቺ (እርሷ) ፮፡ አንቲ = አንቺ ፯፡ ውእቶን = እነዚያ / እነርሱ (ለሴቶች) ፰፡ አንትን = እናንተ (ለሴቶች) ፱፡ አነ = እኔ ፲፡ ንሕነ = እኛ መራሕያን ሩቅና ቅርብ ፣ አንድ እና ብዙ ፣ ሴትና ወንድ ብለን እንመድባቸዋለን። 🔷ሩቅ ወንድ ውእቱ = ያነ ውእቶሙ = እነዚያ 🔷ቅርብ ወንድ አንተ = አንተ አንትሙ = እናንተ 🔷ሩቅ ሴት ይእቲ = ያቺ ውእቶሙ = እነዚያ 🔷ቅርብ ሴት አንቲ = አንቺ አንትን = እናንተ 🔷ለቅርብ ለወንድም ለቅርብ ለሴትም የሚሆኑ አነ = እኔ ንሕነ = እኛ በአማርኛና በእንግሊዝኛ ቋንቋም በሦስት መደብ ይመደባሉ። 🔷አንደኛ መደብ (First person) ➣አነ = I ➛ ነጠላ (Singular) ➣ንሕነ = We ➛ ብዙ (Plural) 🔷ሁለተኛ መደብ (Second person) ➣አንተ = You ➛ ነጠላ (Singular) ➣አንቲ = You➛ነጠላ (Singular ➣አንትሙ= You ➛ ብዙ (Plural) ➣አንትን = You➛ብዙ (Plural) 🔷ሦስተኛ መደብ (Third person) ➣ውእቱ = He ➛ ነጠላ (Singular) ➣ይእቲ = She➛ነጠላ (Singular ➣ውእቶሙ = They ➛ ብዙ (Plural) ➣ውእቶን = They ➛ብዙ (Plural) 👇👇👇 የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/MEBspiritualtraining21 👇👇👇 የፌስቡክ አድራሻ https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1 © መ/ር ማኅቶት እሸቴ

ቤተክርስቲያንን ከሚወጓት የማይተናነስ እየወጓት ያሉ እና የአጥፊዎች ተባባሪ በመሆን የልጆቿን የገዳማውያንን እና የምእመናንን ሞት እያፋጠኑት ያሉት በቤተክህነት ስር ያሉና በመሪነት ደረጃ የተቀመጡት
ቤተክርስቲያንን ከሚወጓት የማይተናነስ እየወጓት ያሉ እና የአጥፊዎች ተባባሪ በመሆን የልጆቿን የገዳማውያንን እና የምእመናንን ሞት እያፋጠኑት ያሉት በቤተክህነት ስር ያሉና በመሪነት ደረጃ የተቀመጡት ናቸው።

🔹ጢ ብሂል ➣ መያጢሆሙ ለኃጥኣን ፤ ኃጢአተኞችን በንስሓ የሚመልሳቸው ማለት ነው። 🔹ጣ ብሂል ➣ የውጣ እንተ አሐቲ ሕርመታ ፤ የአምላክ ስም ማለት ነው። 🔹ጤ ብሂል ➣ ጤት ጠቢብ እግዚአብሔር ፤ እግዚአብሔር ጠቢብ ነው ማለት ነው። 🔹ጥ ብሂል ➣ ስሉጥ ወርኡስ እግዚአብሔር ፤ እግዚአብሔር የሰለጠ ነው ማለት ነው። 🔹ጦ ብሂል ➣ ሦጦ ለመንፈስ ቅዱስ ላዕሌነ ፤ መንፈስ ቅዱስን በላያችን ላይ ጨመረ ማለት። ➖ ➖ ➖ ➖ 🔹ጰ ብሂል ➣ ጰራቅሊጦስ መንፈሰ ጽድቅ ፤ ጰራቅሊጦስ የእውነት መንፈስ ነው። 🔹ጱ ብሂል ➣ ኮጱ መዓዛ ሰብእ ፤ የሰዎች የንጽሕና ፣ የቅድስና መዓዛ ማለት ነው። 🔹ጲ ብሂል ➢ ሠራጲሁ ለዓለም ፤ ዓለምን የሚቀድስ እግዚአብሔር ማለት ነው ። 🔹ጳ ብሂል ➣ ጳጳሰ ወንጌል ፤ የወንጌል ጳጳስ ማለት ነው። 🔹ጴ ብሂል ➢ አክራጴ ኃጢኣት ፤ ከኃጢኣት የሚያነጻ እግዚአብሔር ማለት ነው። 🔹ጵ ብሂል ➣ ጵርስፎራ ፤ ሥጋ ወደሙ ማለት ነው። 🔹ጶ ብሂል ➣ ጶሊስ ፤ ጳጳስ ፣ ሊቀ ጳጳስ ማለት ነው። ➖ ➖ ➖ ➖ 🔹ጸ ብሂል ➣ ጸጋ ወጽድቅ ተውኅበ ለነ ፤ እውነትና ጸጋ ተሠጠን ማለት ነው። 🔹ጹ ብሂል ➣ ገጹ ለአብ ፤ የአብ ፊቱ ማለት ነው። 🔹ጺ ብሂል ➣ ሐዋጺ ነፍሰ ትሑታን ፤ የትሑታንን ሰውነት የሚጎበኝ እግዚአብሔር ማለት ነው ። 🔹ጻ ብሂል ➣ ጻዴ ጻድቅ እግዚአብሔር ፤ እግዚአብሔር እውነተኛ ነው ማለት ነው። 🔹ጼ ብሂል ➣ አእቃጼ ሰኮና ፤ ሰኮናን የሚያሰናክል ማለት ነው። 🔹ጽ ብሂል ➣ ጽንሑ ተስፋሁ ለአብ ፤ የአብን ተስፋ ጠብቁ ፣ ጽኑ ማለት ነው። 🔹ጾ ብሂል ➣ ጾም ትፌውስ ቁስለ ነፍስ ፤ ጾም የነፍስን ቁስል ታድናለች። ➖ ➖ ➖ ➖ 🔹ፀ ብሂል ➣ ፀሐየ ጽድቅ እግዚአብሔር ፤ የእውነት ፀሐይ እግዚአብሔር ነው ማለት ነው። 🔹ፁ ብሂል ➣ ዮም ሠረፁ ጽጌ በረከት ፤ የበረከት አበቦች ዛሬ በቀሉ ማለት ነው። 🔹ፂ ብሂል ➣ መላፂ ዘክልኤ አፉሁ ፤ ሁለት አፍ ያለው ምላጭ ማለት ነው። 🔹ፃ ብሂል➣ ፋፃ መንፈስ ቅዱስ ፤ መንፈስ ቅዱስ ማለት ነው። 🔹ፄ ብሂል ➣ ሕፄሁ ለዳዊት ፤ የዳዊት ትል ማለት ነው። (ዳዊት እኔ ትል ነኝ ያለውን አነጋገር ነው። የዳዊት ትል ማለትም የዳዊት ትህትና ማለት ነው) 🔹ፅ ብሂል ➣ ዕፅ ዘአብርሃም ዘሠፀረ ለምሥዋዕ ፤ ለመሥዋዕት የበቀለ የአብርሃም እንጨት ማለት ነው። 🔹ፆ ብሂል ➣ ማዕፆ አፉሆሙ ለጻድቃን ፤ የጻድቃን የአንደበታቸው መዝጊያ ማለት ነው። ➖ ➖ ➖ ➖ 🔹ፈ ብሂል ➣ ፈጠረ ዓለመ በጥበቡ ፤ ዓለምን በጥበቡ ፈጠረ ማለት ነው። 🔹ፉ ብሂል ➣ ምዕራፉ ለዓለም ፤ የዓለም (የሰው) ዕረፍት ወይም ማረፊያ ማለት ነው። 🔹ፊ ብሂል ➣ ፊደለ ወንጌል ፤ የወንጌል ፊደል ማለት ነው። 🔹ፋ ብሂል ➣ አልፋ ወኦ ፤ ያለና የሚኖር ማለት ነው። 🔹ፌ ብሂል ➣ ኀዳፌ ነፍሳት ፤ ነፍሣትን የምታሻግር ማለት ነው። 🔹ፍ ብሂል ➣ ፍኖት ለኀበ አቡሁ ፤ ወልድ ለባሕርይ አባቱ ለአብ መንገድ ነው ማለት ነው። 🔹ፎ ብሂል ➣ ፎራ ኅብስተ ቁርባን ፤ የቁርባን መሥዋዕት ማለት ነው። ➖ ➖ ➖ ➖ 🔹ፐ ብሂል ➣ ፓፓኤል ስሙ ለእግዚአብሔር ፤ ፓፓኤል ማለት የእግዚአብሔር ስም ማለት ነው። 🔹ፑ ብሂል ➣ ኖፑ አስካለ ወንጌል ፤ የወንጌል ፍሬ ማለት ነው። 🔹ፒ ብሂል ➣ ፒላሳሁ ፤ አምላክ ማለት ነው። 🔹ፓ ብሂል ➣ ፓንዋማንጦን ፤ መንፈስ ቅዱስ ማለት ነው። 🔹ፔ ብሂል ➣ ፔ እግዚአብሔር ፤ እግዚአብሔር ማለት ነው። 🔹ፕ ብሂል ➣ ሮፕ ጽኑዕ እግዚአብሔር ፤ እግዚአብሔር ጽኑዕ ነው ማለት ነው። 🔹ፖ ብሂል ➣ በቀዳሚ ገብረ እግዚአብሔር ሰማየ ወምድረ ወበደኃሪ የኀልፎ ለዓለም ፤ በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን ፈጠሪ በመጨረሻም ዘመን ዓለምን ከመኖር ወደ አለመኖር ያሳልፈዋል። ተፈጸመ ትርጓሜ ፊደላት (የፊደላት ትርጉም ከዚህ ላይ አበቃ)። ✍️✍️✍️የማስተማሪያ ገጾች 👇👇👇 የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/MEBspiritualtraining21 👇👇👇 የፌስቡክ አድራሻ https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1 © መ/ር ማኅቶት እሸቴ