en
Feedback
Mahtot Eshetie / ማኅቶት እሸቴ

Mahtot Eshetie / ማኅቶት እሸቴ

Open in Telegram

መንፈሳዊ የቤተክርስቲያን አስተምህሮና ሙሉ የግእዝ ቋንቋ ሥልጠና ትምህርት ማስተማሪያ የቴሌግራም ገጽ። በመደበኛ መርሐ ግብር የግእዝ ቋንቋ ሥልጠናን መከታተል የምትሹ በኮሜንት መስጫው ጻፉልኝ።

Show more
4 654
Subscribers
+5624 hours
+1677 days
+17430 days
Posts Archive
"እመብርሃንን ክጄ እንጀራ ከምበላ በሃይማኖቴ ጸንቼ እስከ ልጆቼ በረሃብ ብሞት ይሻለኛል" ላለች እናት እንድረስላት የሌላ ቤተ እምነት ተከታይ የሆኑ አካላት (መ...ና#ፍ----ቃ+++ን) ሃይማኖታችሁ
+2
"እመብርሃንን ክጄ እንጀራ ከምበላ በሃይማኖቴ ጸንቼ እስከ ልጆቼ በረሃብ ብሞት ይሻለኛል" ላለች እናት እንድረስላት የሌላ ቤተ እምነት ተከታይ የሆኑ አካላት (መ...ና#ፍ----ቃ+++ን) ሃይማኖታችሁን ለውጡና እናግዛችሁ ባሏቸው ጊዜ ፤ "እመብርሃንን ክጄ እንጀራ ከምበላ በሃይማኖቴ ጸንቼ እስከ ልጆቼ በረሃብ ብሞት ይሻለኛል" ላለች እናት እንድረስላት። ✍️✍️✍️ 0962880529 አቶ ቻሌ ሀብቴ ✍️✍️✍️ የባንክ ቁጥር ንግድ ባንክ 1000292674825 አዋሽ ባንክ 013201737987600 ቻሌ ሀብቴ ፈንታው

በጋሞ አርባምንጭ የፌስቡክ ገጽ ስለ እነዚህ ምስኪን ክርስቲያኖች ተለጥፏል።
በጋሞ አርባምንጭ የፌስቡክ ገጽ ስለ እነዚህ ምስኪን ክርስቲያኖች ተለጥፏል።

ከ200 - 500 ብር ቻሌንጅ ለተራቡት እንድረስላቸው። የሚያስፈልጋቸው ነገሮች ➣ ምግብ ➣ የሕክምና ወጭ ➣ ራሳቸውን የሚመሩበትን በአቅማቸው ሥራ ማስጀመር ➣ የልጆች የትምህርት ቤት ወጭ ➣ ሲርባቸው የሸጧቸውን የቤት መገልገያ እቃዎችና ልብሶች ማሟላት። ✍️✍️✍️ የባንክ ቁጥር ንግድ ባንክ 1000292674825 አዋሽ ባንክ 013201737987600 ቻሌ ሀብቴ ፈንታው ✍️✍️✍️ 0962880529

ከሙሴ እስከ ጴጥሮስ (ደብረ ታቦርን በግጥም) ዓለምን ለማዳን የአብ ልጅ እግዚአብሔር ወልደ ማርያም ሁኖ ተገልጦ በምድር እንደ ሰውነቱ በየጥቂቱ አድጎ ተጠምቆ ጸልዮ ጹሞ ገዳም ገብቶ ወንጌልን ጀመረ ኦሪትን አስትቶ። የእርሱን አምላክነት የአባቱን ጌትነት የመንፈስ ቅዱስን የባሕርይ ሕይወት በማኅፀነ ማርያም በዮርዳኖስ ቁሞ በታቦር ተራራ በደመና አምሞ ገለጠው በምሥጢር አስረዳ ተርጉሞ። የባሕርይ ክብሩን ሊያውቁ ለወደዱ የአምላክነቱን ምሥጢር ላልተረዱ በአባቱ ሲነገር ከአብ መወለዱ ከሙሴ እስከ ጴጥሮስ በፊቱ ሰገዱ። በታቦር ተራራ ጉባኤ ተሰርቶ ሙሴ ኦሪት ሲያነብ ኤልያስ ነቢያት ያዕቆብ ዮሐንስ ጴጥሮስ ከመልእክታት ጌታ ሲተረጉም ወንበር ተዘርግቶ። ምሥጢረ ሥላሴ በስፋት ሲብራራ በመለኮት ግርማ የአምላክ ፊት ሲያበራ በብርሃን ሲጋረድ የታቦር ተራራ ትምህርቱ የገባው ጴጥሮስ ዳስ ሲሰራ ኤልያስ መነነ ሙሴ ተመለሰ ከመቃብር ስፍራ። በማኅቶት እሸቴ ነሐሴ 13 / 2017 ዓ.ም 👇 የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/MEBspiritualtraining21

"ሃይማኖቴን ከምለውጥ ከነ ልጆቼ ረሀብ ይግደለኝ" አቶ ቻሌ ኃብቴ እና ወይዘሮ በቃቢል አባተ የሚባሉ ሁለቱም እጂግ የሚዋደዱና በጉልበታቸው ሠርተው የሚተዳደሩ ኦርቶዶክሳውያን ባልና ሚስት ነበሩ። 2015 ዓ.ም የካቲት 16 ምሽት ላይ ቀን ዘንብሎባቸው የቤቱ ምሰሶ የሆነው ባልየው ባልታሰበ አደጋ ስድስት ሰዎች ተሰብስበው ጭንቅላቱን ደበደቡትና በሞትና በሕይወት መካከል ጥለውት ሄዱ በዚህም ክፉኛ ተጎድቶ ፓራላይዝድ ሁኖ እጅግሩ ተሳስሮ አንደበቱ ተዘግቶ እየተኮላተፈ ለዓመታት በሕክምና ቆየ። ከብዙ ድካም በኋላ ቀስ ብሎ መራመድ ሲጀምር ለዕለት ጉርስ የጉልበት ሥራ ሲሠራ ቤት ተደርምሶበት እግሩ ተሰበረ እንደ ድሮው ፈጽሞ መራመድ አቃተው። አቶ ቻሌ በዚህ ዓይነት ሁኔታ እያለ ሚስቱ በቃቢል በጎን እሱን እያሳከመች በጎን ጥጥ ፈትላ ለቤታቸውና ለሕፃናት ልጆቿ የዕለት ጉርስ እያመጣች ባለችበት ሁኔታ በጸና ታመመች በሽታዋም የቆዳ ካንሰርና የደም ግፊት እንደ ሆነ ተነገራት። ለባልና ሚስቱ ለሕክምና የሚሆን ገንዘብ ባለመገኘቱ ሁለታቸውም አልጋ ላይ ዋሉ። ወጥቶ መግባት ሠርቶ መብላት ቀረ። የሚበሉት ሲቸግራቸው የቤት እቃቸውን ሁሉ ሽጠው በሉ። በእኒህ ባልና ሚስት የተወለዱት ሁለቱ ሕፃናትም ገና ቦርቀው ሳይጨርሱ እናትና አባታቸውን በጽኑ ደዌ ታመው ማየቱ ሳቃቸውን ወደ እለቅሶ ቀየረው። የ10 ዓመት ልጃቸውም ትምህርቷን ልታቋርጥ ተገደደች። ይባስ ብሎ በቤታቸው ውስጥ የሚላስ የሚቀመስ አለመኖሩ ለሕፃናቱ ሌላ ሕመም ነው ለታመሙት ወላጆችም ልጅን ያክል ነገር በርኃብ ሲቀጡ ማየቱ ሌላ ስቃይ ነው። እነሆ በቤታቸው ምግብ ከቀመሱ ብዙ ወራቶች አለፉ። ሁለቱም በበሽታ ከቤት ውለው ከልጆቻቸው ጋር በርሀብ እየተቀጡ ይገኛሉ። ይህንን ችግራቸውን ያዩ በጎንደር ከተማ የሚገኙ የፕሮቴስታንት አማኞች ባልየውን ቸርቻው ድረስ በመጥራት ሃይማኖታችሁን ቀይራችሁ ወደ እኛ ኑና ሙሉ ችግራችሁን እናስወግድላችሁ ከበሽታችሁም እናሳክማችሁ አሏቸው። ከሚስቴ ጋር ልምከርና እናሳውቃችኋለን በማለት አቶ ቻሌ ወደ ቤቱ ተመልሶ የርሀቡ ዘመን እስኪያልፍ ልጆቻችን ዐይናችን እያየ በረሃብ ከሚሞቱ እሺ ብለን ወደ እነሱ ሃይማኖት እንሂድና በኋላ እንመለሳለን በማለት ለሚስቱ አማከራት። እንደ ቅዱስ ቂርቆስ በእምነቷ የጸናችው ባለቤቱ ወ/ሮ በቃቢል እመብርሃንን ክጄ እንጀራ ከምበላ እስከ ልጆቼ በሃይማኖቴ ጸንቼ በርሃብ ብሞት ይሻለኛል በማለት የእምነቷን ጽናት ገልጻለች። ለእኒህ ቤተሰቦች ብንደርስላቸው የታመኑት አምላክ የታመኗት እመብርሃን በምድር በረከትን በሰማይ መንግሥቱን ያድሉናልና ለበረከት እንሳተፍ። ጌታም በዳግም ምጽአቱ ይህንን የደስታ ቃል ያሰማናል። "ተርቤ አብልታችሁኛልና፥ ተጠምቼ አጠጥታችሁኛልና፥ እንግዳ ሆኜ ተቀብላችሁኛልና፥ ታርዤ አልብሳችሁኛልና፥" ማቴ 25:35 ✍️ አድርሻቸው ጎንደር ከተማ ፣ ቀበሌ 18 ፣ ሕዳሴ ከቀበሌው አጠገብ ነው። ✍️✍️✍️ 0962880529 አቶ ቻሌ ሀብቴ ✍️✍️✍️ የባንክ ቁጥር ንግድ ባንክ 1000292674825 አዋሽ ባንክ 013201737987600 ቻሌ ሀብቴ ፈንታው

#ማብራሪያ :- 🔹🔸🔹 እመቤታችንን ከሰማይ የወረደ የሕይወት እንጀራ ያለበት መሶበ ወርቅ እናላታለን። መሶበ ወርቅን እግዚአብሔር ለሙሴ ከማይነቅዝ እንጨት እንዲሠራ በውስጥና በውጭ በወርቅ ለብጠው። መስፈሪያ ሙሉ መና ጊዜ ሳትወስን አኑርበት አለው። ይህ መና ለእስራኤል የወረደላቸው መና ሲሆን ሙሴ ካስቀመጠው ጀምሮ ከመሶበ ወርቁ ሳይጎድል ሳይጠፋ እስከ ክርስቶስ ልደት ቆይቷል አማናዊ የሕይወት መና ጌታ በተወለደ ጊዜ ግን እንደ ሰም ቀልጦ ጠፍቷል። ይኸውም ምሳሌ ነው። ➣ መሶበ የእመቤታችን : ወርቅ የንጽሕናዋ የቅድስናዋ ምሳሌ። ➣ መና የጌታ ምሳሌ ➣ መናው ብዙ ዘመን ሲኖር እንዳልተለወጠ ጌታም ሰው ሲሆን አምላክነቱ ላለመለወጡ ምሳሌ። 🔹🔸🔹ሰአሊ ለነ ቅድስት። ኅብስተ ሕይወት ከሚባል ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን አእምሮውን ማስተዋሉን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን። ◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊ ♦️🔹♦️አንቲ ውእቱ ተቅዋም ዘወርቅ "አንቲ ውእቱ ተቅዋም ዘወርቅ እንተ ጾርኪ ማኅቶተ ፀዳል ... ፤ ሁል ጊዜ ብርሃንነት ያለውን ፋና የተሸከምሽ የወርቅ መቅረዝ አንቺ ነሽ። ይኸውም ፋና የዓለም ብርሃን ነው። ጥንት ከሌለው ብርሃንም የተገኘ ብርሃን ነው። ከእውነተኛ አምላክ የተገኘ እውነተኛ አምላክ ነው። ያለ መለወጥም ከአንቺ ሰው የሆነው ነው። በመምጣቱም (ሰው በመሆኑም) በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለምንኖር ለእኛ አበራልን በልዩ የጥበቡ ምሥጢር በሥጋዌ የልቦናችንን እግር ወደ ሰላም መንገድ አቀናልን። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።" #ማብራሪያ :- 🔹🔸🔹 እመቤታችን ፋና ባለው መቅረዝ ትመሰላለች። እግዚአብሔር ሙሴን መቅረዝን እንዲሠራ ሰባት የመብራት ማብሪያ ቅርጫፍ እንዲያበጅለትና በመካከለኛው ባለው ዘይቱ ሲገባ በሁሉ እንዲ ሞላ አድርጎ እንዲሠራ አዘዘው። ይኸውም ምሳሌ ነው። ➣ ተቅዋም የእመቤታችን ምሳሌ ፤ ተቅዋም ፋናን ወይም ብርሃንን እንዲያስገኝ እመቤታችንም ከብርሃን የተገኘ ብርሃን የተባለ ጌታን አስገኝታለችና። ➣ ሰባት አዕፁቅ (ሰባት የፋና ቅርንጫፎች) ፡ ሰባት ቁጥር በዕብራውያን ፍጹም እንደሆነ እመቤታችንም በክብር ፍጽምት ናትና። #አንድም ➣ተቅዋም የጌታ ምሳሌ ፤ ያ እንዲያበራ ጨለማውን እንዲያርቅ እርሱም የዓለም ጨለማ በብርሃኑ አስወግዷልና። ➣ሰባቱ አዕፁቅ (ቅርንጫፎች) የምእመናን ምሳሌ። " እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ።" (ዮሐ 15:5) እንዳለ። ➣ በመካከለኛው አዕፁቅ የተቀዳው ዘይት በሁሉ እንዲሞላ ጌታም መንፈስ ቅዱስን ለሁሉም የሚያድል ሁኗልና። 🔹🔸🔹ሰአሊ ለነ ቅድስት። እግረ ልቡናችንን ወደ ወንጌል ካቀናልን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን አእምሮውን ማስተዋሉን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን። ◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊ ➢➢ የቀጣይ ትምህርት #ክፍል_ዐሥራ_ሁለት የእሑድ ውዳሴ ማርያም ከማዕጠንት - ለኪ ይደሉ ➜ ነሐሴ / 11 / 2018 ዓ.ም ©መ/ር ማኅቶት እሸቴ 👇👇👇 የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/MEBspiritualtraining21 👇👇👇 የፌስቡክ አድራሻ https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1

የመጨረሻው ትምህርት ... የእሑድ ውዳሴ ማርያም ማብራሪያ #ክፍል_ዐሥራ_አንድ ከ ተሰመይኪ - ተቅዋም ♦️🔹♦️ መግቢያ ከአይሁድ ሰንበት (ከቀዳሚት ሰንበት) ሲለያት ሰንበተ ክርስቲያን (የክርስቲያኖች ሰንበት) አለ። በዚህም ቀን እመቤታችንን በቤተ መቅደስ ባሉ መገልገያ ንዋያት በመሶበ ወርቅ ፣ በተቅዋመ ወርቅ ፣ በማዕጠንተ ወርቅ ፣ በበትረ አሮን እየመሰለ ያመሰግናታል። ♦️🔹♦️ተሰመይኪ ፍቅርተ "ተሰመይኪ ፍቅርተ ኦ ቡርክት እም አንስት ... ፤ ከሴቶች ይልቅ ተለይተሽ የተባረክሽ ሆይ የተወደድሽ ተባልሽ። ከተለዩ የተለየሽ በውስጧም የኪዳን ጽላት ያለባት የምትባይ ሁለተኛ ክፍል አንቺ ነሽ። ኪዳንም በእግዚአብሔር ጣቶች የተጣፉ ዐሥሩ ቃላት ናቸው። ያለመለወጥ ካንቺ ሰው የሆነ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደገኛ ስሙን መጀመሪያ ስሙን አስቀድሞ በየውጣ ነገረን ለአዲስ ኪዳንም አስታራቂ ሆነ። በከበረ ደሙ ፈሳሽነት ወይም መፍሰስ ያመኑትንና ንጹሓን የሆኑትን ወገኖች አነጻቸው። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።" #ማብራሪያ :- 🔹🔸🔹በኦሪቱ ቤተ መቅደስ ሊቀ ካህናቱ በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ገብቶ መሥዋዕት ሠውቶ የሚወጣበት ቅድስተ ቅዱሳን አለ። በዚያም ኪሩቤል የተሣሉበት ታቦት በታቦቱ ውጥስ ጽላት በጽላቱ ላይ ሕጉ ተጽፎ ይገኛል። መሠዊያውም በዚያ አለ። ይኽም የእመቤታችን ምሳሌ ነው። ➣ ቅድስተ ቅዱሳኑ የእመቤታችን ምሳሌ ➣ ሊቀ ካህናቱ ብቻ በዓመት የሕዝቡን ኃጢአት ለማስተሠርይ እንዲገባ : ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስ የዓለምን ኃጢአት ለማስተሠርይ ከእርሷ ሰው ሆኗልና። ➣ በቅድስተ ቅዱሳኑ ታቦቱ ጽላቱ እንዲገኝ በእርሷ የመለኮትና የትስብእት ተዋሕዶ ተፈጽሟልና። 🔹🔸🔹ነቢየ እግዚአብሔር ሙሴ ከእግዚአብሔር ጋር ቃል ለቃል ተነጋግሮ በእግዚአብሔር እጅ የተሠራውንና ሕጉ የተቀረፀበትን ጽላቱን ተቀብሎ ከደብረ ሲና ሲወርድ ሕዝቡ ጣዖት አቁመው ሲሰግዱ አየ ቢደነግጥ ጽላቱ ከእጁ ወድቆ ተሰበረ። ጣዖት ያመለኩትንና ፍቅረ ጣዖት ያለባቸውን ሰዎች ወንዝ አስወርዶ አስፈጃቸው። ጽላቱ ስለተሠበረበት ወደ እግዚአብሔር ቢያመለክት እንደመጀመሪያው አድርገህ ሥራ አለው። እርሱም እንደመጀመሪያው አድርጎ ሠራው እና ወደ እግዚአብሔር አቀረበው። ሕጉ በአምላካዊ ግብር ተጽፎለታል። ይኸውም ምሳሌ ነው። ➣ የመጀመሪያው የተሰበረው ጽላት የአዳም። ያ ከእግዚአብሔር በአምላዊ ሥራ እንደተገኘ አዳም ያለ ዘር ለመገኘቱ ምሳሌ። ➣ ሁለተኛው ሙሴ የሠራው የእመቤታችን ምሳሌ። በሙሴ እጅ መሠራቱ እመቤታችን በዘር ለመወለዷ ምሳሌ። ቃሉ የጌታ ምሳሌ ሲሆን በግብር አምላካዊ (በአምላካዊ ሥራ) እንደተፃፈ እመቤታችን ጌታን ያለ ዘር ለመፅነሷ ምሳሌ ነው። 🔹🔸🔹በከበረ ደሙ ፈሳሽነት አዳነን። የክርስቶስ ደም ክቡር ደም ነው። ምክንያቱም ኃጢያትን ያነፃ ሞትን ያስወገደ ነውና። ለዚህም ነው በዕለተ ዐርብ በመስቀል ላይ ደሙ ሲፈስ መላእክት በብርሃን ፅዋ ተቀብለው ወደ ዓለም የረጩት። ዛሬ ቤተክርስቲያን የምትሠራው ደሙ በተንጠበጠበበትም ቦታ እንደሆነ አቀው በትውፊት ይናገራሉ። "እንተ ተሐንፀት በስሙ ወተቀደሰት በደሙ ቤተክርስቲያን ፤ ቤተክርስቲያን በስሙ ታንፃ በደሙ ተቀደሰች" "ወምድርኒ ትገብር ፋሲካ ተሐፂባ በደመ ክርስቶስ ፤ ምድር በክርስቶስ ደም ታጥባ ፋሲካን አደረገች" እንዳለ ቅዱስ ያሬድ። 🔹🔸🔹ሰአሊ ለነ ቅድስት። በከበረ ደሙ ፈሳሽነት ካዳነን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን አእምሮውን ማስተዋሉን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን። ◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊ ♦️🔹♦️ ወበእንተዝ ናዐብየኪ ኵልነ "ወበእንተዝ ናዐብየኪ ኵልነ ኦ እግዝእትነ ወላዲተ አምላክ ... ፤ ሁል ጊዜ ንጽሕት የሆንሽ አምላክን የወለድሽ እመቤታችን ሆይ ሁላችን ስለዚህ እናገንሻለን። ሰውን በሚወድ በጌታ ዘንድ ይቅርታን እናገኝ ዘንድ እንለምንሻለን። ወዳንቺም እናንጋጥጣለን። ከማይነቅዝ እንጨት የተቀረፀ በውስጥና በውጭ በወርቅ የተለበጠ ታቦት ያለመለየትና ያለመለወጥ ሰው የሆነ የእግዚአብሔርን ቃል ይመስልልናል። ይኸውም መለወጥ የሌለበት ንጹሕ መለኮት ነው። ከአብ ጋር የተካከለ ነው። ለንጽሕት በራሱ አበሠራት። በልዩ ጥበቡ ያለ ወንድ ዘር እንደ እኛ ሆነ። መለኮቱን አዋሕዶ ያለ ርኩሰት ባንቺ ሰው ሆነ። ቅድስት ሆይ ለምኝልን። #ማብራሪያ :- 🔹🔸🔹 እግዚአብሔር ሙሴን ሸምሸር ሸጢን ከሚባል ከማይነቅዝ ዕንጨት አቆልቋዩን ሁለት ክንድ ከስንዝር ፣ ቁመቱን ክንድ ከስንዝር ፣ ስፋቱን ክንድ ከስንዝር አድርገህ ታቦት ቅረጽ። በውስጥና በውጭ በወርቅ ለብጠው። አራት ቀለበት ሁለት መሎጊያ አብጅለት ብሎታል። ሁለቱን ኪሩብም ሣልበት ብሎታል። ይኸውም ምሳሌ ነው። ➣ ታቦት የእመቤታችን ምሳሌ። ➣ የታቦቱ ታች የንጹሐን አበው ምሳሌ። ➣ ሁለቱ መሎጊያ የፍቅረ ቢጽ እና የፍቅረ እግዚአብሔር (እግዚአብሔርን መውደድና ባልንጀራን መውደድ) ምሳሌ። ➣ አራቱ ቀለበት ፤ እመቤታችን ኃጢአት በሚሠራባቸው በአራቱ ነገሮች በማየት ፣ በመስማት ፣ በመዳሰስ ፣ በማሽተት ንጽሕት የመሆኗ ምሳሌ። ➣ ሁለቱ ኪሩቤል እመቤታችንን የሚጠብቃት መልአክ እና ያበሠራት መልአክ ምሳሌ። ሊቀ ካህናቱ በዓመት አንድ ጊዜ ወደ ቅድስተ ቅዱሳኑ ገብቶ በተሣሉት በሁለቱ ኪሩቤል መካከል ድምፅ ሰምቶ እንዲወጣ እመቤታችንም በጠባቂ መልአኳ ስትጠበቅ ቆይታ ከመልአከ መበሥሯ ድምፅ ሰምታ ጌታን ፀንሳ የመገኘቷ ምሳሌ ነው። 🔸🔹ሰአሊ ለነ ቅድስት። መለኮቱን ከሥጋሽ ከአዋሐደ ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን አእምሮውን ማስተዋሉን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን። ◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊ ♦️🔹♦️መቅደስ ዘይኬልልዋ ኪሩቤል "መቅደስ ዘይኬልልዋ ኪሩቤል እለ ሥዑላን በሥዕለ እግዚአብሔር ... ፤ በእግዚአብሔር ሥዕል የተሣሉ ኪሩቤል የሚጋርዱሽ መቅደስ አንቺ ነሽ። ንጽሕት ሆይ ያለመለወጥ ካንቺ ሰው የሆነው ቃል ኃጢአታችንን የሚያስተሠርይልንና አበሳችንን የሚደመስስልን ሆነ። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።" #ማብራሪያ :- 🔹🔸🔹 እመቤታችን መቅደስ ትባላለች በመቅደሱ እግዚአብሔር እንደሚገለጽበትና እንደሚያድርበት አካላዊ ቃል በማኅፀኗ አድሯልና። ሊቁ ኤራቅሊስም "ኦ መቅደስ ዘኮነ ለሊሁ እግዚአብሔር ሊቀ ካህናት ፤ እግዚአብሔር ያገለገለባት መቅደስ ወዮ እንዴት ያለች ናት።" በማለት ይናገራል። ሃይ.አበ 48÷17 🔸🔹ሰአሊ ለነ ቅድስት። ኃጢአታችንን ከሚያስተሠርይልን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን አእምሮውን ማስተዋሉን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን። ◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊ ♦️🔹♦️አንቲ ውእቱ መሶበ ወርቅ "አንቲ ውእቱ መሶበ ወርቅ ንጹሕ እንተ ውስቴታ መና ኅቡዕ ... ፤ የተሠወረ መና ያለብሽ ንጹሕ የወርቅ መሶብ አንቺ ነሽ። መናም ከሰማይ የወረደውና ለዓለም ሁሉ ሕይወትን የሚያድለው ኅብስት ነው። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።"

#ማብራሪያ :- 🔹🔸🔹 እመቤታችንን ከሰማይ የወረደ የሕይወት እንጀራ ያለበት መሶበ ወርቅ እናላታለን። መሶበ ወርቅን እግዚአብሔር ለሙሴ ከማይነቅዝ እንጨት እንዲሠራ በውስጥና በውጭ በወርቅ ለብጠው። መስፈሪያ ሙሉ መና ጊዜ ሳትወስን አኑርበት አለው። ይህ መና ለእስራኤል የወረደላቸው መና ሲሆን ሙሴ ካስቀመጠው ጀምሮ ከመሶበ ወርቁ ሳይጎድል ሳይጠፋ እስከ ክርስቶስ ልደት ቆይቷል አማናዊ የሕይወት መና ጌታ በተወለደ ጊዜ ግን እንደ ሰም ቀልጦ ጠፍቷል። ይኸውም ምሳሌ ነው። ➣ መሶበ የእመቤታችን : ወርቅ የንጽሕናዋ የቅድስናዋ ምሳሌ። ➣ መና የጌታ ምሳሌ ➣ መናው ብዙ ዘመን ሲኖር እንዳልተለወጠ ጌታም ሰው ሲሆን አምላክነቱ ላለመለወጡ ምሳሌ። 🔹🔸🔹ሰአሊ ለነ ቅድስት። ኅብስተ ሕይወት ከሚባል ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን አእምሮውን ማስተዋሉን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን። ◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊ ♦️🔹♦️አንቲ ውእቱ ተቅዋም ዘወርቅ "አንቲ ውእቱ ተቅዋም ዘወርቅ እንተ ጾርኪ ማኅቶተ ፀዳል ... ፤ ሁል ጊዜ ብርሃንነት ያለውን ፋና የተሸከምሽ የወርቅ መቅረዝ አንቺ ነሽ። ይኸውም ፋና የዓለም ብርሃን ነው። ጥንት ከሌለው ብርሃንም የተገኘ ብርሃን ነው። ከእውነተኛ አምላክ የተገኘ እውነተኛ አምላክ ነው። ያለ መለወጥም ከአንቺ ሰው የሆነው ነው። በመምጣቱም (ሰው በመሆኑም) በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለምንኖር ለእኛ አበራልን በልዩ የጥበቡ ምሥጢር በሥጋዌ የልቦናችንን እግር ወደ ሰላም መንገድ አቀናልን። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።" #ማብራሪያ :- 🔹🔸🔹 እመቤታችን ፋና ባለው መቅረዝ ትመሰላለች። እግዚአብሔር ሙሴን መቅረዝን እንዲሠራ ሰባት የመብራት ማብሪያ ቅርጫፍ እንዲያበጅለትና በመካከለኛው ባለው ዘይቱ ሲገባ በሁሉ እንዲ ሞላ አድርጎ እንዲሠራ አዘዘው። ይኸውም ምሳሌ ነው። ➣ ተቅዋም የእመቤታችን ምሳሌ ፤ ተቅዋም ፋናን ወይም ብርሃንን እንዲያስገኝ እመቤታችንም ከብርሃን የተገኘ ብርሃን የተባለ ጌታን አስገኝታለችና። ➣ ሰባት አዕፁቅ (ሰባት የፋና ቅርንጫፎች) ፡ ሰባት ቁጥር በዕብራውያን ፍጹም እንደሆነ እመቤታችንም በክብር ፍጽምት ናትና። #አንድም ➣ተቅዋም የጌታ ምሳሌ ፤ ያ እንዲያበራ ጨለማውን እንዲያርቅ እርሱም የዓለም ጨለማ በብርሃኑ አስወግዷልና። ➣ሰባቱ አዕፁቅ (ቅርንጫፎች) የምእመናን ምሳሌ። " እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ።" (ዮሐ 15:5) እንዳለ። ➣ በመካከለኛው አዕፁቅ የተቀዳው ዘይት በሁሉ እንዲሞላ ጌታም መንፈስ ቅዱስን ለሁሉም የሚያድል ሁኗልና። 🔹🔸🔹ሰአሊ ለነ ቅድስት። እግረ ልቡናችንን ወደ ወንጌል ካቀናልን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን አእምሮውን ማስተዋሉን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን። ◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊ ➢➢ የቀጣይ ትምህርት #ክፍል_ዐሥራ_ሁለት የእሑድ ውዳሴ ማርያም ከማዕጠንት - ለኪ ይደሉ ➜ ነሐሴ / 11 / 2018 ዓ.ም ©መ/ር ማኅቶት እሸቴ 👇👇👇 የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/MEBspiritualtraining21 👇👇👇 የፌስቡክ አድራሻ https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1

የእሑድ ውዳሴ ማርያም ማብራሪያ #ክፍል_ዐሥራ_አንድ ከ ተሰመይኪ - ተቅዋም ♦️🔹♦️ መግቢያ ከአይሁድ ሰንበት (ከቀዳሚት ሰንበት) ሲለያት ሰንበተ ክርስቲያን (የክርስቲያኖች ሰንበት) አለ። በዚህም ቀን እመቤታችንን በቤተ መቅደስ ባሉ መገልገያ ንዋያት በመሶበ ወርቅ ፣ በተቅዋመ ወርቅ ፣ በማዕጠንተ ወርቅ ፣ በበትረ አሮን እየመሰለ ያመሰግናታል። ♦️🔹♦️ተሰመይኪ ፍቅርተ "ተሰመይኪ ፍቅርተ ኦ ቡርክት እም አንስት ... ፤ ከሴቶች ይልቅ ተለይተሽ የተባረክሽ ሆይ የተወደድሽ ተባልሽ። ከተለዩ የተለየሽ በውስጧም የኪዳን ጽላት ያለባት የምትባይ ሁለተኛ ክፍል አንቺ ነሽ። ኪዳንም በእግዚአብሔር ጣቶች የተጣፉ ዐሥሩ ቃላት ናቸው። ያለመለወጥ ካንቺ ሰው የሆነ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደገኛ ስሙን መጀመሪያ ስሙን አስቀድሞ በየውጣ ነገረን ለአዲስ ኪዳንም አስታራቂ ሆነ። በከበረ ደሙ ፈሳሽነት ወይም መፍሰስ ያመኑትንና ንጹሓን የሆኑትን ወገኖች አነጻቸው። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።" #ማብራሪያ :- 🔹🔸🔹በኦሪቱ ቤተ መቅደስ ሊቀ ካህናቱ በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ገብቶ መሥዋዕት ሠውቶ የሚወጣበት ቅድስተ ቅዱሳን አለ። በዚያም ኪሩቤል የተሣሉበት ታቦት በታቦቱ ውጥስ ጽላት በጽላቱ ላይ ሕጉ ተጽፎ ይገኛል። መሠዊያውም በዚያ አለ። ይኽም የእመቤታችን ምሳሌ ነው። ➣ ቅድስተ ቅዱሳኑ የእመቤታችን ምሳሌ ➣ ሊቀ ካህናቱ ብቻ በዓመት የሕዝቡን ኃጢአት ለማስተሠርይ እንዲገባ : ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስ የዓለምን ኃጢአት ለማስተሠርይ ከእርሷ ሰው ሆኗልና። ➣ በቅድስተ ቅዱሳኑ ታቦቱ ጽላቱ እንዲገኝ በእርሷ የመለኮትና የትስብእት ተዋሕዶ ተፈጽሟልና። 🔹🔸🔹ነቢየ እግዚአብሔር ሙሴ ከእግዚአብሔር ጋር ቃል ለቃል ተነጋግሮ በእግዚአብሔር እጅ የተሠራውንና ሕጉ የተቀረፀበትን ጽላቱን ተቀብሎ ከደብረ ሲና ሲወርድ ሕዝቡ ጣዖት አቁመው ሲሰግዱ አየ ቢደነግጥ ጽላቱ ከእጁ ወድቆ ተሰበረ። ጣዖት ያመለኩትንና ፍቅረ ጣዖት ያለባቸውን ሰዎች ወንዝ አስወርዶ አስፈጃቸው። ጽላቱ ስለተሠበረበት ወደ እግዚአብሔር ቢያመለክት እንደመጀመሪያው አድርገህ ሥራ አለው። እርሱም እንደመጀመሪያው አድርጎ ሠራው እና ወደ እግዚአብሔር አቀረበው። ሕጉ በአምላካዊ ግብር ተጽፎለታል። ይኸውም ምሳሌ ነው። ➣ የመጀመሪያው የተሰበረው ጽላት የአዳም። ያ ከእግዚአብሔር በአምላዊ ሥራ እንደተገኘ አዳም ያለ ዘር ለመገኘቱ ምሳሌ። ➣ ሁለተኛው ሙሴ የሠራው የእመቤታችን ምሳሌ። በሙሴ እጅ መሠራቱ እመቤታችን በዘር ለመወለዷ ምሳሌ። ቃሉ የጌታ ምሳሌ ሲሆን በግብር አምላካዊ (በአምላካዊ ሥራ) እንደተፃፈ እመቤታችን ጌታን ያለ ዘር ለመፅነሷ ምሳሌ ነው። 🔹🔸🔹በከበረ ደሙ ፈሳሽነት አዳነን። የክርስቶስ ደም ክቡር ደም ነው። ምክንያቱም ኃጢያትን ያነፃ ሞትን ያስወገደ ነውና። ለዚህም ነው በዕለተ ዐርብ በመስቀል ላይ ደሙ ሲፈስ መላእክት በብርሃን ፅዋ ተቀብለው ወደ ዓለም የረጩት። ዛሬ ቤተክርስቲያን የምትሠራው ደሙ በተንጠበጠበበትም ቦታ እንደሆነ አቀው በትውፊት ይናገራሉ። "እንተ ተሐንፀት በስሙ ወተቀደሰት በደሙ ቤተክርስቲያን ፤ ቤተክርስቲያን በስሙ ታንፃ በደሙ ተቀደሰች" "ወምድርኒ ትገብር ፋሲካ ተሐፂባ በደመ ክርስቶስ ፤ ምድር በክርስቶስ ደም ታጥባ ፋሲካን አደረገች" እንዳለ ቅዱስ ያሬድ። 🔹🔸🔹ሰአሊ ለነ ቅድስት። በከበረ ደሙ ፈሳሽነት ካዳነን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን አእምሮውን ማስተዋሉን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን። ◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊ ♦️🔹♦️ ወበእንተዝ ናዐብየኪ ኵልነ "ወበእንተዝ ናዐብየኪ ኵልነ ኦ እግዝእትነ ወላዲተ አምላክ ... ፤ ሁል ጊዜ ንጽሕት የሆንሽ አምላክን የወለድሽ እመቤታችን ሆይ ሁላችን ስለዚህ እናገንሻለን። ሰውን በሚወድ በጌታ ዘንድ ይቅርታን እናገኝ ዘንድ እንለምንሻለን። ወዳንቺም እናንጋጥጣለን። ከማይነቅዝ እንጨት የተቀረፀ በውስጥና በውጭ በወርቅ የተለበጠ ታቦት ያለመለየትና ያለመለወጥ ሰው የሆነ የእግዚአብሔርን ቃል ይመስልልናል። ይኸውም መለወጥ የሌለበት ንጹሕ መለኮት ነው። ከአብ ጋር የተካከለ ነው። ለንጽሕት በራሱ አበሠራት። በልዩ ጥበቡ ያለ ወንድ ዘር እንደ እኛ ሆነ። መለኮቱን አዋሕዶ ያለ ርኩሰት ባንቺ ሰው ሆነ። ቅድስት ሆይ ለምኝልን። #ማብራሪያ :- 🔹🔸🔹 እግዚአብሔር ሙሴን ሸምሸር ሸጢን ከሚባል ከማይነቅዝ ዕንጨት አቆልቋዩን ሁለት ክንድ ከስንዝር ፣ ቁመቱን ክንድ ከስንዝር ፣ ስፋቱን ክንድ ከስንዝር አድርገህ ታቦት ቅረጽ። በውስጥና በውጭ በወርቅ ለብጠው። አራት ቀለበት ሁለት መሎጊያ አብጅለት ብሎታል። ሁለቱን ኪሩብም ሣልበት ብሎታል። ይኸውም ምሳሌ ነው። ➣ ታቦት የእመቤታችን ምሳሌ። ➣ የታቦቱ ታች የንጹሐን አበው ምሳሌ። ➣ ሁለቱ መሎጊያ የፍቅረ ቢጽ እና የፍቅረ እግዚአብሔር (እግዚአብሔርን መውደድና ባልንጀራን መውደድ) ምሳሌ። ➣ አራቱ ቀለበት ፤ እመቤታችን ኃጢአት በሚሠራባቸው በአራቱ ነገሮች በማየት ፣ በመስማት ፣ በመዳሰስ ፣ በማሽተት ንጽሕት የመሆኗ ምሳሌ። ➣ ሁለቱ ኪሩቤል እመቤታችንን የሚጠብቃት መልአክ እና ያበሠራት መልአክ ምሳሌ። ሊቀ ካህናቱ በዓመት አንድ ጊዜ ወደ ቅድስተ ቅዱሳኑ ገብቶ በተሣሉት በሁለቱ ኪሩቤል መካከል ድምፅ ሰምቶ እንዲወጣ እመቤታችንም በጠባቂ መልአኳ ስትጠበቅ ቆይታ ከመልአከ መበሥሯ ድምፅ ሰምታ ጌታን ፀንሳ የመገኘቷ ምሳሌ ነው። 🔸🔹ሰአሊ ለነ ቅድስት። መለኮቱን ከሥጋሽ ከአዋሐደ ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን አእምሮውን ማስተዋሉን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን። ◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊ ♦️🔹♦️መቅደስ ዘይኬልልዋ ኪሩቤል "መቅደስ ዘይኬልልዋ ኪሩቤል እለ ሥዑላን በሥዕለ እግዚአብሔር ... ፤ በእግዚአብሔር ሥዕል የተሣሉ ኪሩቤል የሚጋርዱሽ መቅደስ አንቺ ነሽ። ንጽሕት ሆይ ያለመለወጥ ካንቺ ሰው የሆነው ቃል ኃጢአታችንን የሚያስተሠርይልንና አበሳችንን የሚደመስስልን ሆነ። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።" #ማብራሪያ :- 🔹🔸🔹 እመቤታችን መቅደስ ትባላለች በመቅደሱ እግዚአብሔር እንደሚገለጽበትና እንደሚያድርበት አካላዊ ቃል በማኅፀኗ አድሯልና። ሊቁ ኤራቅሊስም "ኦ መቅደስ ዘኮነ ለሊሁ እግዚአብሔር ሊቀ ካህናት ፤ እግዚአብሔር ያገለገለባት መቅደስ ወዮ እንዴት ያለች ናት።" በማለት ይናገራል። ሃይ.አበ 48÷17 🔸🔹ሰአሊ ለነ ቅድስት። ኃጢአታችንን ከሚያስተሠርይልን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን አእምሮውን ማስተዋሉን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን። ◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊ ♦️🔹♦️አንቲ ውእቱ መሶበ ወርቅ "አንቲ ውእቱ መሶበ ወርቅ ንጹሕ እንተ ውስቴታ መና ኅቡዕ ... ፤ የተሠወረ መና ያለብሽ ንጹሕ የወርቅ መሶብ አንቺ ነሽ። መናም ከሰማይ የወረደውና ለዓለም ሁሉ ሕይወትን የሚያድለው ኅብስት ነው። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።"

♦️🔹♦️ ተሰመይኪ እመ ለክርስቶስ "ተሰመይኩ እመ ለክርስቶስ ... ፤ የንጉሥ ክርስቶስ እናቱ ተባልሽ እርሱንም ከወለድሽው በኋላ በድንግልና ኖርሽ። ድንቅ በሆነ ምሥጢር (ተዋሕዶ) አማኑኤልን ወለድሽው ስለዚህም ባለመለወጥ አጸናሽ። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።" #ማብራሪያ 🔹🔸🔹 እመቤታችን የክርስቶስ እናቱ ትባላለች እርሱን ከወለደችው በኋላም በድንግልና ኑራለች። 🔹🔸🔹 ሰአሊ ለነ ቅድስት። አማኑኤል ከሚባል ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን አእምሮውን ማስተዋሉን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን። ◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊ ♦️🔹♦️አንቲ ውእቱ ሰዋስው "አንቲ ውእቱ ሰዋስው ዘርእየ ያዕቆብ እግዚአብሔር ላዕሌሁ ... ፤ እግዚአብሔር በላይዋ ተቀምጦባት ያዕቆብ ያያት መሰላል አንቺ ነሽ። በሁሉ በኩል የማይመረምር እርሱን ተፈትሖ በሌለበት ማኅፀንሽ ተሸክመሽዋልና። እኛን ስለማዳን ካንቺ ሰው በሆነ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ አማላጅ ሆንሽን። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።" #ማብራሪያ 🔹🔸🔹 ያዕቆብ ያያትን መሰላል በማክሰኞው እና በዚህኛው ምስጋናው አመጣ። ያዕቆብ ራዕዩን ያየበት ዕለት ቅዳሜ ቀን ነበር። ራዕዩ የተፈጸመት ማለትም በመሰላል ከተመሰለች እመቤታችን በዙፋኑ የተቀመጠው ክርስቶስ የተወለደ ማክሰኞ ቀን ነውና። ከዛም ከዚህም አነሣ። 🔹🔸🔹በሁሉ በኩል የማይመረምር እርሱን ተፈትሖ በሌለበት ማኅፀንሽ ተሸክመሽዋልና ማለት ፤ እርሱን ከመፅነስሽ አስቀድሞ ፣ እርሱን በፀነሽ ጊዜ ፣ እርሱንም ከፀነስሽ በኋላ ፣ እርሱን ከመውለድሽ አስቀድሞ ፣ እርሱን በወለድሽ ጊዜ ፣ እርሱንም ከወለድሽ በኋላ በተፈትሖ በማይታወቅ ማኅፀንሽ ችለሽዋልና። #አንድም :- ሰው ከመሆኑ አስቀድሞ ፣ ሰው በሆነ ጊዜ ፣ ሰውም ከሆነ በኋላ የማይመረመር እርሱን በተፈትሖ በማይታወቅ ማኅፀንሽ ችለሽዋልና። 🔹🔸🔹 ሰአሊ ለነ ቅድስት። እኛን ስለማዳን ሰው ከሆነ ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን አእምሮውን ማስተዋሉን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን። ◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊ ♦️🔹♦️ናሁ እግዚእ "ናሁ እግዚእ ወጽአ እምኔኪ ኦ ቡርክት ጽርሕ ንጽሕት ... ፤ የተባረክሽና ንጽሕት የሆንሽ አዳራሽ ሆይ እነሆ ጌታ የፈጠረውን ዓለም ሁሉ በይቅርታው ብዛት ያድን ዘንድ ካንቺ ወጣ (ተወለደ)። ፈጽመን እናመስግነው። ቸርና ሰውን ወዳጅ ነውና። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።" #ማብራሪያ :- 🔹🔸🔹 እመቤታችንን በእልፍኝ በአዳራሽ ሲመስላት ጌታን ደግሞ በእልፍኙ በአዳራሹ እንዳለ ሙሽራ ይመስለዋል። ዳግመኛም የእመቤታችንን በነቢዩ ሚልክያስ ንጽሕት አዳራሽ ይመስላታል። 🔸🔹 ሰአሊ ለነ ቅድስት። ቸር ሰው ወዳጅ ከሆነ ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን አእምሮውን ማስተዋሉን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን። ◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊ ♦️🔹♦️ተፈሥሒ ኦ ምልእተ ጸጋ "ተፈሥሒ ኦ ምልእተ ጸጋ ድንግል ዘእንበለ ርኵስ ... ፤ ያለ ርኵሰት ድንግል የሆንሽ ጸጋን የተመላሽ ሆይ ደስ ይበልሽ። የዓለም ሁሉ መክበሪያ ንጽሕት ጽዋ ነሽ። የማትጠፊ ፋና ነሽ። የማትፈርሽ መቅደስ ነሽ። የቅዱሳን መደገፊያቸው (መጠጊያቸው) የማትለወጭ የሃይማኖት በትር ነሽ። ቸር አዳኛችን ወደ ሆነ ልጅሽ ለምኝልን ፈጽሞ ይቅር ይለን ዘንድ ኃጢአታችንንም ያስተሠረይልን ዘንድ። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።" #ማብራሪያ :- 🔹🔸🔹 እመቤታችን በኤልሳዕ ማሠሮ ትመሰላለች። ነቢዩ ኤልሳዕ በ1ኛ ነገ 2÷20 እንደተቀመጠው የተበከለውን ውኃ በአዲስ የሸክላ ማሠሮ ውስጥ ጨም ጨምሮ ውኃውን ፈውሶታል። ይኸውም ምሳሌ ነው። ➣ የሸክላ ማሠሮ የእመቤታችን አዲስ መሆኑ እመቤታችን ንጽሕት የመሆኗ። ➣ ጨው የጌታ ➣ የውኃው ምረት የፍዳ የመርገም ➣ ምረቱ ከውኃው እንጂ ከመሬት እንዳልተገኘ ፍዳ መርገም ከዲያብሎስ እንጂ ከአዳም ላለመገኘቱ ምሳሌ። ➣የውኃው ምረት በሸክላው ውስጥ ባለው ጨው እንደጣፈጠ ፍዳ መርገም ከእመቤታችን በተወለደ በጌታ ጠፍቶልናልና። 🔹🔸🔹 እመቤታችንን የማትጠፋ ፋና አላት ፤ በደብተራ ኦሪት ሙሴና አሮን በቀዳማይ ሰዓተ ሌሊት (ማታ አንድ ሰዓት) አብርተዋት በቀዳማይ ሰዓተ መዓልት (ጧት አንድ ሰዓት) የሚያጠፏት ፋና ነበረችና ከዚያ ሲለያት የማትጠፋ ፋና አላት። የማትፈርስ መቅደስ ማለቱም ሰሎሞን ከሠራው ቤተ መቅደስ ሲለያት ነው። ያ ፈርሶ ጠፍቶ ቀርቷልና። 🔹🔸🔹 ሰአሊ ለነ ቅድስት። ኃጢአታችንን ከሚያስተሠረይልን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን አእምሮውን ማስተዋሉን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን። ◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊ ➢➢ የቀጣይ ትምህርት #ክፍል_ዐሥራ_አንድ የእሑድ ውዳሴ ማርያም ➜ ነሐሴ / 10 / 2018 ዓ.ም ©መ/ር ማኅቶት እሸቴ 👇👇👇 የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/MEBspiritualtraining21 👇👇👇 የፌስቡክ አድራሻ https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1

የቅዳሜ ውዳሴ ማርያም ማብራሪያ #ክፍል_ዐሥር ከንጽሕት - ተፈሥሒ ኦ ምልዕተ ጸጋ ♦️🔹♦️ ንጽሕት ወብርህት "ንጽሕት ወብርህት ወቅድትስት በኵሉ ... ፤ ንጽሕት ነሽ ብርህት ነሽ። ጌታን በመኻል እጅሽ የያዝሽው ሆይ በሁሉ የተቀደስሽ ነሽ። ፍጥረት ሁሉ ቅድስት ሆይ ለምኝልን ብለው እየጮኹ ካንቺ ጋር ደስ ይላቸዋል።" #ማብራሪያ 🔹🔸🔹ቅዱስ ኤፍሬም ምስጋናውን የጀመረ ሰኞ ዕለት ሲሆን ቅዳሜ ላይ ሲደርስ ንጽሕት ነሽ ብርህት ነሽ ቅድስት ነሽ ማለቱ እመቤታችን የምትለወጥ ሁና ሳይሆን እሱ እየቀደመ እየቆየ መብቃቱን መናገር ነው። ሕፃናትን አናት እንዳይወርዷቸው ብለው እናቶቻቸው በመሐል እጃቸው አቅፈው እንዲይዟቸው እመቤታችንም በክንዷ ታቅፋ በመሐል እጇ ይዛዋለችና። ♦️🔹♦️ ተፈሥሒ ኦ ምልእተ ጸጋ "ተፈሥሒ ኦ ምልእተ ጸጋ ... ፤ ጸጋን የተመላሽ ሆይ ደስ ይበልሽ። ባለሟልነትን አግኝተሻልና ደስ ይበልሽ። እግዚአብሔር ካንቺ ጋር ነውና ደስ ይበልሽ። ግርማ ያለሽ ድንግል ሆይ ገናንነትሽን እናመሰግናለን እናደንቃለን። እንደ መልአኩ ገብርኤልም ምስጋና እናቀርብልሻለን የባሕርያችን መዳን ከማኅፀንሽ ፍሬ ተገኝቷልና። ወደ አባቱ ወደ እግዚአብሔርም አቀረበን። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።" #ማብራሪያ :- 🔹🔸🔹እመቤታችን ጸጋን የተመላሽ ትባላለች ይህም ማለት እግዚአብሔር ለቅዱሳን የሰጠውን ሁሉ ጸጋ ለእመቤታችን ሰጥቷታል ከዛም በላይ የአምላክ እናት የመሆን ጸጋ ለእሷ ብቻ የተሰጠ ነው። እግዚአብሔር ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ከእርሷ ጋር አንድ ባሕርይ በመሆኑ ባለሟልነትን አግኝታለች። ግርማ ያለሽ ድንግል ማለት መፈራት ያለሽ ድንግል ማለት ነው። መፈራቷም በአይሁድ በመናፍቃን በአጋንንት ዘንድ ነው። 🔹🔸🔹 ሰአሊ ለነ ቅድስት። ወደ ባሕርይ አባቱ ካቀረበን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን አእምሮውን ማስተዋሉን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን። ◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊ ♦️🔹♦️ ከመ ከብካብ "ከመ ከብካብ ዘአልቦ ጥልቀት ... ፤ እንደ ሠርግ ቤት ጉድፍ የሌለብሽ ነሽ መንፈስ ቅዱስ አድሮብሻልና የልዑል ኃይልም ጸልሎሻልና። ማርያም ሆይ ለዘለዓለም የሚኖር መጥቶ ከኃጢአት ያዳነን የአብ ልጅ ቃልን በእውነት ወለድሽ። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።" #ማብራሪያ :- 🔹🔸🔹መንፈስ ቅዱስ አድሮብሻልና የልዑል ኃይልም ጸልሎሻልና ማለት ፤ መንፈስ ቅዱስ ከሦስቱ ግብራት እነዚህም በዘር በሩካቤ ከመፅነስ ከመውለድ ከተፈትሖ ድንግልና ከልክሎሻልና። የአብ ኃይሉ የተባለ ወልድም ከሦስቱ ግብራት ከልክሎሻልና ማለት ነው። 🔹🔸🔹 ሰአሊ ለነ ቅድስት። ሰው ሆኖ ከኃጢአታችን ፍዳ ካዳነን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን አእምሮውን ማስተዋሉን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን። ◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊ ♦️🔹♦️አንቲ ውእቱ ዘመድ "አንቲ ውእቱ ዘመድ ዘእምሥርወ ዳዊት ... ፤ ከዳዊት ሥር የተገኘች ባሕርይ ዘር አንቺ ነሽ። መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በሥጋ ወልደልሽልናልና። ከአብ የተወለደ ከዓለም በፊት የነበረ አንዱ ቃል ራሱን (ባሕርዩን) ሠወረ። ከአንቺም የተገዥን (የሰውን) አርአያ ነሣ። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።" 🔹🔸🔹 ከዳዊት ሥር የተገኘሽ ባሕርይ ማለቱ እመቤታችን የዳዊት ልጅ መሆኗን መናገሩ ነው። ➣ከአብ የተወለደ ከዓለም በፊት የነበረ አንዱ ቃል ራሱን (ባሕርዩን) ሠወረ። ከአንቺም የተገዥን (የሰውን) አርአያ ነሣ ማለቱ ፤ እግዚአብሔር ወልድ በተዋሕዶ ሰው በሆነ ጊዜ እንደ ሰው በምድር ላይ በመመላለሱ በመብላት በመጠጣቱ በትሕትና ነውና መለኮታዊ ባሕርዩን ገልጾ አምላክ ነኝና ዕለቱን ልደግ ሳይል በየጥቁቱ አድጎ አልታዘዝም አላገለግልም አላለም። ዲያብሎስንም ድል ያደረገው መለኮታዊ ባሕርይውን በሥጋ ሰውሮ ነው። በነሣው ሥጋም ከበረ ፣ ከፍ ከፍ አለ ፣ ነገሠ ፣ የአባቱን መንግሥት ወረሰ (ምእመናንን ገንዘቦቹ አደረገ) ተባለ። 🔹🔸🔹 ሰአሊ ለነ ቅድስት። ከበረ ፣ ነገሠ ፣ ወረሰ ፣ ከፍ ከፍ አለ ከሚባል ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን አእምሮውን ማስተዋሉን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን። ◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊ ♦️🔹♦️ኮንኪ ዳግሚት ሰማይ "ኮንኪ ዳግሚት ሰማይ ዲበ ምድር ... ፤ አምላክን ያለርኩሰት የወለድሽው ሆይ የምድር ሁለተኛ ሰማይን ሆንሽ እውነተኛ ፀሐይ ካንቺ ወጥቶልናልና። እንደነቢያት ትንቢትም ያለዘርና ያለመለወጥ ወለድሽው። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።" #ማብራሪያ :- 🔹🔸🔹 ክርስቶስ የእውነት ፀሐይ ይባላል እመቤታችንም የፀሐይ መውጫ ምሥራቅ እንላታለን። ያለዘርና ያለመለወጥ ወለድሽው ማለት እመቤታችን ጌታችን ያለወንድ ዘር በድንግልና ፀነሰችው ከወለደችው በኋላም ድንግልናዋ አልተለወጠም ወይም አልጠፋም። ጌታም እንበለ ዘር በድንግልና ተፀንሶ ሲወለድ መለኮቱ አልተለወጠምና። 🔹🔸🔹 ሰአሊ ለነ ቅድስት። ዘር ምክንያት ሳይሆንሽ ከወለድሽው ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን አእምሮውን ማስተዋሉን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን። ◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊ ♦️🔹♦️አንቲ ውእቱ ደብተራ "አንቲ ውእቱ ደብተራ እንተ ተሰመይኪ ቅድስተ ቅዱሳን ... ፤ ከተለዩ የተለየሽ የተባልሽ የኪዳን ጽላት ያለብሽ የተሠወረ መና ያለበት የወርቅ መሶብ ያለብሽ ደብተራ ድንኳን አንቺ ነሽ። ይኸውም መና የተባለው መጥቶ በድንግል ማርያም ማኅፀን ያደረው የእግዚአብሔር ልጅ ነው። የአብ ቃል በርስዋ ሰው ሆነ መጥቶ ያዳነን የባሕርይ ንጉሥን በዓለም ውስጥ ወለደችው የሚናገር በግ የክርስቶስ እናቱ ገነት ደስ ይላታል ለዘለዓለም የሚኖር የአብ ልጅ እርሱ መጥቶ ከኃጢአት አድኖናልና። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።" #ማብራሪያ :- 🔹🔸🔹 እመቤታችን ደብራተ (ድንኳን) ትባላላች። የመጀመሪያዋ ድንኳን በእግዚአብሔር ትእዛዝ ሰጭነት በሙሴ አስተዳዳሪነት ጥበበኞቹ ኤልያብ እና ባስልኤል ሰፍተው ሠርተው ለሙሴ ሰጡት። በዛች ድንኳንም ሕጉ የተጻፈበት ጽላት በውስጡ ያለበት ታቦት ተቀመጦበት ነበር። (ዘጸ : 26) ይኸውም ምሳሌ ነው : ➣ ደብተራ የእመቤታችን ምሳሌ። ➣ ቅድስት የነፍሷ ምሳሌ። ➣ ቅዱሳን የአራቱ ባሕርያት ምሳሌ። ➣ ታቦት የመንፈስ ቅዱስ። ➣ ጽላት የልቡናዋ። ➣ ቃሉ በመንፈስ ቅዱስ የተገለጸላት ምሥጢር። #አንድም ➣ ቅዱሳን ደሥጋውና የነፍሷ ➣ ቅድስት የልቡናዋ ➣ ታቦት የማኅፀኗ ➣ ጽላት የትስብእት ➣ በጽላቱ ላይ የተጻፈው ቃል የመለኮት ምሳሌ። 🔹🔸🔹የነባቢ በግ እናቱ አለ ክርስቶስን የሚናገር በግ ይለዋል የማይናገሩ በጎች አሉና። #አንድም : ሰባቱን ንግግሮች በመስቀል ላይ የተናገረ። እሊህም ➣ አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው። ➣ ኤሎሄ ኤሎሄ ➣ ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር ትሆናለህ ➣ እነኋት እናትህ እነሆ ልጅሽ ➣ ተጠማሁ ➣ አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ ➣ እነሆ ሁሉ ተፈጸመ። 🔹🔸🔹 ሰአሊ ለነ ቅድስት። ሰው ሆኖ ከኃጢአታችን ፍዳ ካዳነን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን አእምሮውን ማስተዋሉን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን። ◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊

አድርሺኝ ብለን እኛ ከምንመገበው ይልቅ አድርሺኝ ብለን ነዳያንን በስሟ ብንመግባቸው የእመቤታችን ፍቅር ይበዛልናል።

10፤ ይህም ሦስት ጊዜ ሆነ እንደ ገናም ሁሉ ወደ ሰማይ ተሳበ። ✍️የመጋረጃው ምሳሌዎች 💥የወንጌል ምሳሌ : መጋረጃዋ በአራት ማዕዘን መያዟ ወንጌል በአራቱ ማዕዘን የመሰበኩ ምሳሌ። 🔈የእንስሳት ሥዕል አይሁድ ኑረው ያመኑ ምእመናን ምሳሌ። 🔈የአራዊት ሥዕል ከአሕዛብ ወገን ያመኑ ምእመናን ምሳሌ። 🔈የአዕዋፍ ሥዕል የነቢያት የካህናት ምሳሌ። 🔈አርደህ ብላ ማለቱ ከአሕዛብ ወገን የሆነውን ቆርነሌዎስን አስጥምቀው ሲለው ነው። 🔈ቃሉ ሦስት ጊዜ መሆኑ የሦስትነት አለመለወጡ የአንድነት ምሳሌ። 🔈ተጠቅልሎ ሲያርግ ማየቱ እኒህ ሁሉ አምነው ገነት መንግሥተ ሰማያት ለመግባታቸው ምሳሌ። #አንድም 💥 መጋረጃ የእመቤታችን ምሳሌ ፤ መጋረጃዋ በአራት ማዕዘን መያዟ እመቤታችንን በአራቱም ማዕዘን ሰአሊ ለነ ቅድስት ሳይላት የሚውል የለምና። 🔹🔸🔹 እመቤታችንን ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል ሆንሽ አላት። በመሰላል የላዩ ወደታች ይወርድበታል የታቹ ወደላይ ይወጣበታል። የላዩ ወደ ታች እንዲወርድበት መለኮት ከትስብእት (ሥጋ) ለመዋሐዱ። የታቹ ወደ ላይ እንዲወጣበት ትስብእት ከመለኮት ጋር ለመዋሐዱ ምክንያት እርሷ ናትና። #አንድም : የላዩ ወደ ታች እንዲወርድበት ፤ ሥላሴ በእኛ ለማደራቸው። የታቹ ወደ ላይ እንዲወጣበት እኛ ከሥላሴ ለመወለዳችን ምክንያቲቱ እመቤታችን ናትና። 🔹🔸🔹 ሰአሊ ለነ ቅድስት። እንዲህ ካለ ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን አእምሮውን ማስተዋሉን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን። ◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊ ➢➢ የቀጣይ ትምህርት #ክፍል_ዐሥር የቅሜ ውዳሴ ማርያም ➜ ነሐሴ / 9 / 2018 ዓ.ም ©መ/ር ማኅቶት እሸቴ 👇👇👇 የቴሌግራም ሊንክ https://t.me/MEBspiritualtraining21 👇👇👇 የፌስቡክ አድራሻ https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1

አብ አስነሣው መንፈስ ቅዱስ አስነሣው ቢል አንድ ነው ዕሪናቸውን (መተካከላቸውን) መናገር ነውና። #አንድም : ➣ የእነአልዓዛር ትንሣኤ በብሉይ ሥጋ ነው። ይህም ማለት ከተነሡ በኋላ በሚደክም በሚራብ በሚጠማ በሚታመም ሥጋ ነው የነሡ ማለት ነው። የእርሱ ግን በሐዲስ ሥጋ ነውና። ይኽም ማለት ክርስቶስ ከተነሣ በኋላ በሥጋው መራብ መጠማት መድከም መታመም መሞት የለበትምና። ሁላችንም በትንሣኤ ዘጉባኤ ስንነሣ እንደ ክርስቶስ በሐዲስ ሥጋ ነው። ክርስቶስ የትንሣኤያችን በኵር ነው የምንለውም ለዚህ ነው። 🔹🔸🔹 ሰአሊ ለነ ቅድስት። አዳምን ዳግመኛ ወደ ገነት ከመለሰው ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን አእምሮውን ማስተዋሉን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን። ◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊ ♦️🔹♦️ማርያም ንጽሕት "ማርያም ንጽሕት ድንግል ወላዲተ አምላክ ማእምንት ... ፤ ንጽሕት ድንግል ማርያም የታመነች አምላክን የወለደች ናት። ለሰዎች ልጆችም የምሕረት አማላጅ ናት። ኃጢአታችንን ያስተሠርይልን ዘንድ ወደ ልጅሽ ወደ ክርስቶስ ለምኝልን። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።" #ማብራሪያ :- 🔹🔸🔹 ማርያም ንጽሕት ድንግል ወላዲተ አምላክ ማእምንት ... ፤ ንጽሕት ድንግል ማርያም የታመነች አምላክን የወለደች ናት። የሚለው የምስጋና ክፍል ከአባቶቻችን እንዳየነው ዘወትር በየጊዜያቱና በየሰዓቱ ጸሎተ ማርያም አቡነ ዘበሰማያት በደገምነ ቁጥር አብረን የምንጸልየው የተወደደ የምልጃ ጸሎት ነው። 🔹🔸🔹 እመቤታችን የታመነች ወላዲተ አምላክ ናት። ከሐዲው ንስጥሮስ የአምላክ እናት አትባልም የወለደች ሰውን እንጂ አምላክን አልወለደችም ብሏት ነበር ፤ የታመነች አምላክን የወለደች ናት አለ ቅዱስ ኤፍሬም። ዳግመኛም የታመነች የምሕረት አማላጅ ትባላለች። ከዚህ ዓለም ሰው ሲለያት ነው። የዚህ ዓለም ሰው አማልደኝ አስታርቀኝ ብሎ ቢልኩት ፤ የተበደለው ሰው እንደዚህ አድስጎኝ እንደዚህ በድሎኝ ባለው ጊዜ እንኪያስ ፍርድህ ነው ብሎ እንኳን ሊያስታርቀው ይባስ ነገር አጽንቶ ይመጣልና ከዚህ ሲለያት ነው። 🔹🔸🔹 ሰአሊ ለነ ቅድስት። ኃጢአታችንን ከሚያስተሠርይልን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን አእምሮውን ማስተዋሉን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን። ◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊◈◊ ♦️🔹♦️ማርያም ድንግል ትጸርሕ በቤተ መቅደስ "ማርያም ድንግል ትጸርሕ በቤተ መቅደስ ወትብል የአምር እግዚአብሔር ... ፤ ድንግል ማርያም በቤተ መቅደስ አሰምታ ትናገር ነበር። መልአኩ ቅድስት ድንግል ሆይ ሰላምታ ይገባሻል ብሎ አክብሮ ከነገረኝ በቀር ምንም ምን የማውቀው እንደሌለኝ እግዚአብሔር ያውቃል አለች። የማይቻለውን ቻልሽ የማይወሰነውንና ምንም ምን የሚወስነው የሌለውን ወሰንሽ። በክብር ሁሉ ላይ ጸጋን የተመላሽ ሆይ ምስጋናሽ ይበዛል ክብርሽ ፍጹም ነው። የአብ ቃል ማደሪያ ሆነሻልና የክርስቲያን ወገኖች ምእመናንን የምትሰበስቢያቸውና ማሕየዊ የሚያድኑን ለሆኑ ሥላሴ ሰጊድን (መስገድን) የምታስተምሪላቸው ሰፊ መጋረጃ ሙሴ ያየውን የእሳት ዓምድ የተሸከምሽ አንቺ ነሽ። ይኸውም መጥቶ በማኅፀንሽ ያደረው የእግዚአብሔር ልጅ ነው። ሰማይና ምድርን ለፈጠረ ጌታ ማደሪያ ሆንሽ። ዘጠኝ ወር በማኅፀንሽ ተሸከምሽው። ሰማይና ምድር ለማይወስኑት የታመንሽ አንቺ ነሽ። ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል ሆንሽ። ብርሃንሽ ከፀሐይ ብርሃን ይበልጣል። ቅዱሳን በፍጹም ደስታ ያዩት ኮከብ ካንቺ የተወለደ ምሥራቅ አንቺ ነሽ። ይኸውም በጻርና በምጥ ትወልድ ዘንድ በሔዋን የፈረደባት ነው። አንቺ ማርያም ግን ጸጋን የተመላሽ ሆይ ደስ ይበልሽ የሚል ቃልን ሰማሽና መጥቶ ያዳነን የፍጥረት ሁሉ ገዥ የሆነ ንጉሥን ወለድሽልን። መሐሪ ነው ፤ ሰውንም ወዳጅ ነው። ስለዚህ ማርያም ሆይ የተባረክሽ ነሽ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው። ጸጋን የተመላሽ ሆይ እግዚአብሔር ካንቺ ጋር ነውና ደስ ይበልሽ እያልን መልአኩ ገብርኤል እንዳመሰገነሽ እናመሰግንሻለን። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።" #ማብራሪያ :- 🔹🔸🔹 ድንግል ማርያም በቤተ መቅደስ አሰምታ ትናገር ነበር። ሲል ምን ማለቱ ነው ፤ እመቤታችን በሦስት ዓመቷ ወደ ቤተመቅደስ ገባች። ዐሥራ ሁለት ዓመት በቤተ መቅደስ ኑራ በዐሥራ አምስት ዓመቷ ለዮሴፍ እንዲጠብቃት ተሰጠችና ወደ ቤቱ ወሰዳት። ዮሴፍ ለሥራ ወደሌላ ሀገር በሄደ ጊዜ መልአኩ ገብርኤል አበሠራትና ፀነሰች። ዮሴፍ ከንግድ ሲመለስ እመቤታችንን ፀንሷ አገኛት። በዚህ ጊዜ የእስራኤል ልጅ ሆይ ማን አታለለሽ ብሎ ጠየቃት። እሷም እኔስ መልአኩ አክብሮ ከነገረኝ በቀር ሌላ አላውቅም ብላ ተናግራ ነበርና አሰምታ ተናገረች አለ። በዚያውስ ላይ ንቦችን በባሕርያቸው እንዲራቡ የሚያደርግ እኔንስ በኅቱም ድንግልና ፀንሼ በኅቱም ድንግልና እንድወልድ ቢያደርግ የሚሳነው አለን አለችው። ዳግመኛም ከደጃቸው የወደቀ ግንድ ነበር ያንን አለምልማ አሳይታው በዚህ ነገሯን ተቀብሏታል። ከዚህ በኋላ ለበዓል ወደ ኢየሩሳሌም የሚወጡበት ጊዜ ደረሰ ፤ ዮሴፍም ይዣት ብሄድ ሰሰነች ብለው በእሳት አቃጥለው በድንጋይ ወግረው ይገሉብኛል ፤ ትቻትም ብሄድ ያደረገው አውቆ ትቷት መጣ ይሉኛል ብሎ በሀሳብ ሲናውዝና ሲጨናነቅ የእግዚአብሔር መልአክ " እርሱ ግን ይህን ሲያስብ፥ እነሆ የጌታ መልአክ በሕልም ታየው፥ እንዲህም አለ። የዳዊት ልጅ ዮሴፍ ሆይ፥ ከእርስዋ የተፀነሰው ከመንፈስ ቅዱስ ነውና እጮኛህን ማርያምን ለመውሰድ አትፍራ።" (ማቴ 1:20) አለው። እርሱም ይዟት ሄደ። አይሁድም ባይዋት ጊዜ ከማን ፀነሰች በማለት ማየ ዘለፋ ትጠጣልን ብለው አጠጧት። ባጠጧት ጊዜ ከፀሐይ ሰባት እጅ አበራች። ይህንን ሲያዩም ይቺን ብላቴና በከንቱ አምተናታል ብለው አሰምተው ተናግረው ነበርና የእነርሱን ጩኸት ለእርሷ ሰጥቶ አሰምታ ተናገረች አለ። #አንድም : ዛሬ ካህናት በቤተ መቅደስ ዕለት ዕለት ድንግል ለዮሴፍ የታጨሽ ለመገናኘት አይደለም ንጹሕ ሆኖ ሊጠብቅ ነው እንጂ እያሉ የሚያመሰግኗት ስለሆነ እንዲህ አለ። 🔹🔸🔹 እመቤታችንን ለሥላሴ ሰጊድን (መስገድን) የምታስተምሪላቸው ሰፊ መጋረጃ አንቺ ነሽ አላት። አንድነት ሦስትነት የታወቀ ጌታ ከእመቤታችን ሰው ከሆነ ወዲህ ነውና። ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ አንዲት ስግደት እንሰግዳለን ማለት የቻልነው በሐዲስ ኪዳን ነውና ሰጊድን የምታስተምሪላቸው አላት። "ሥሉስ ቅዱስን እግዚአብሔር ወልድ ከእመቤታችን ሰው ከመሆኑ አስቀድሞ በአንድነት በሦስትነት ያወቃቸው የለም ከእመቤታችን ሰው ከሆነ ወዲህ ነው እንጂ።" ጎር ሃይ.አበ 9÷13 ሰፊ መጋረጃ ያላት ጴጥሮስ በኢዮጴ ባያት መጋረጃ ሲመስላት ነው። ይህም በሐዋርያት ሥራ ያለው ታሪክ ነው። (የሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 11) ---------- 5፤ እኔ በኢዮጴ ከተማ ስጸልይ ሳለሁ ተመስጬ ራእይን አየሁ፤ ታላቅ ሸማ የመሰለ ዕቃ በአራት ማዕዘን ተይዞ ከሰማይ ወረደና ወደ እኔ መጣ፤ 6፤ ይህንም ትኵር ብዬ ስመለከት አራት እግር ያላቸውን የምድር እንስሶች አራዊትንም ተንቀሳቃሾችንም የሰማይ ወፎችንም አየሁ። 7፤ ጴጥሮስ ሆይ፥ ተነሣና አርደህ ብላ የሚለኝንም ድምፅ ሰማሁ። 8፤ እኔም። ጌታ ሆይ፥ አይሆንም፤ ርኵስ ወይም የሚያስጸይፍ ከቶ ወደ አፌ ገብቶ አያውቅምና አልሁ። 9፤ ሁለተኛም። እግዚአብሔር ያነጻውን አንተ አታርክሰው የሚል ድምፅ ከሰማይ መለሰልኝ።