Mahtot Eshetie / ማኅቶት እሸቴ
Open in Telegram
መንፈሳዊ የቤተክርስቲያን አስተምህሮና ሙሉ የግእዝ ቋንቋ ሥልጠና ትምህርት ማስተማሪያ የቴሌግራም ገጽ። በመደበኛ መርሐ ግብር የግእዝ ቋንቋ ሥልጠናን መከታተል የምትሹ በኮሜንት መስጫው ጻፉልኝ።
Show more4 635
Subscribers
+5624 hours
+1677 days
+17430 days
Posts Archive
ከነገ ጀምሮ ዓይኖቻችን ሁሉ ወደ ደብረ ታቦር ፬ቱ ጉባኤ ትርጓሜ ቤት ይሁኑ።
አንድ መጽሐፍ ለአንድ ሰው።
ግብ = 15,000 መጻሕፍት
ዓለማ = ዓለም አቀፍ የቤተክርስቲያን ቤተ መጻሕፍት እና የምርምር ማዕከል መመሥረት።
ኃላፊነት = በሁሉም የሀገራችን ከተሞች የተሰጣቸው ወንድሞች እና እኅቶች አሉ።
ለተጨማሪ መረጃ = ወንድም Ermias Melesse ን ያናግሩ
ተስፋ = በአጭር ቀናት የተፈለገውን መጻሕፍት መሳካት
በጎንደርና አካባቢው እኔን ጨምሮ ሌሎች ወንድሞቻችን አናግሩን።
ለግል ሆስፒታሎች (ጎንደር እና ባህርዳር) ያላችሁ የግል ሆስፒታሎች እኒህን ችግረኞች ባልና ሚስት የህክምና ትብብር ብታደርጉልን።
በተለይ ይቺ እናት በቶሎ ካልታከመች በሽታዋ እየተባባሰባት መጥቷል።
ወገኖቻችን ሼርና ሜንሽን በማድረግ አድሱላቸው።
✍️ አድርሻቸው
ጎንደር ከተማ ፣ ቀበሌ 18 ፣ ሕዳሴ ከቀበሌው አጠገብ ነው።
✍️✍️✍️
0962880529
አቶ ቻሌ ሀብቴ
✍️✍️✍️
የባንክ ቁጥር
ንግድ ባንክ
1000292674825
ወዳጁ አልዓዛርን ተነሥ ብሎ በቃሉ ካስነሣው ፤ ከፍጥረታት ሁሉ አብልጦ የሚወዳትን እናቱንማ በሚበልጠው ትንሣኤ እንደምን አያስነሣት?
"ኪዳነ ምሕረትን ከምክዳት ርሀብ ይግደለኝ"
ላለች እናት በእመቤታችን ስም እንድረስላት።
ካዱና እንመግባችሁ ላሉ ፕሮቴስታንቶች የሰጡት ምላሽ።
እኛ በቤታችን ያማረ የጣመ የበዓል ምግብ ልንበላ እንችላለን አንድ ሙሉ ቤተሰብ ግን ቁርሽ ዳቦ አጥቶ ገና አንደበታቸው አከናውኖ መናገር የማችሉ ሕፃናት በቤታቸው እየተራቡ ይገኛሉና።
በኪዳነ ምሕረት ስም እናግዛቸው።
✍️ አድርሻቸው
ጎንደር ከተማ ፣ ቀበሌ 18 ፣ ሕዳሴ ከቀበሌው አጠገብ ነው።
✍️✍️✍️
0962880529
አቶ ቻሌ ሀብቴ
✍️✍️✍️
የባንክ ቁጥር
ንግድ ባንክ
1000292674825
አዋሽ ባንክ
013201737987600
ቻሌ ሀብቴ ፈንታው
ከአልዓዛር የምትበልጠውን እናቱን ከአልዓዛር በሚበልጠው ትንሣኤ አስነሣት።
ሥጋውን የነሣበትን ሥጋ ከመቃብር አንሥቶ በመንግሥቱ አስቀመጠው።
አልዓዛርን በቃሉ ከመቃብር ያስነሣ አምላክ
በድንግልና የወለደችውን እናቱን ከመቃብር ማስነሣቱና በሕይወት ማኖሩ ምን ቁም ነገር ነው።
©መ/ር ማኅቶት እሸቴ
ነሐሴ /16/2018 ዓ.ም
👇👇👇
የቴሌግራም ሊንክ
https://t.me/MEBspiritualtraining21
👇👇👇
የፌስቡክ አድራሻ
https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1
ደብረ ታቦር ላይ የተሠራችዋን ቤተክርስቲያን ደብረ ታቦር ላይ እንሥራት።
ለቤተክርስቲያናችን ዓለምአቀፍ የሆነ የሕዝብ ቤተ መጻሕፍት ያስፈልጋታል ይህንን ቤተ መጻሕፍት ደብረ ታቦር ጉባኤ ቤት ላይ ተረባርበን እንሥራ።
©መ/ር ማኅቶት እሸቴ
👇👇👇
የቴሌግራም ሊንክ
https://t.me/MEBspiritualtraining21
👇👇👇
የፌስቡክ አድራሻ
https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1
"ሃይማኖቴን ከምለውጥ ከነ ልጆቼ ረሀብ ይግደለኝ"
የሱባኤውን መጨረሻ የተቸገሩትን እናግዝ
✍️ አድርሻቸው
ጎንደር ከተማ ፣ ቀበሌ 18 ፣ ሕዳሴ ከቀበሌው አጠገብ ነው።
✍️✍️✍️
0962880529
አቶ ቻሌ ሀብቴ
✍️✍️✍️
የባንክ ቁጥር
ንግድ ባንክ
1000292674825
አዋሽ ባንክ
013201737987600
ቻሌ ሀብቴ ፈንታው
በጎንደር አድርሺኝ የምትጠጡ እነዚህን ችግረኞች አስቧቸው።
✍️ አድርሻቸው
ጎንደር ከተማ ፣ ቀበሌ 18 ፣ ሕዳሴ ከቀበሌው አጠገብ ነው።
✍️✍️✍️
0962880529
አቶ ቻሌ ሀብቴ
✍️✍️✍️
የባንክ ቁጥር
ንግድ ባንክ
1000292674825
አዋሽ ባንክ
013201737987600
ቻሌ ሀብቴ ፈንታው
"አሁንም አብንና ወልድን መንፈስ ቅዱስንም እናመስግነው ለዘላለሙ አሜን።"
#ማብራሪያ :- የእመቤታችን ልመና ለጻድቃን ለንጹሓን የማያሻ ሁኖ አይደለም ለጻድቃን ለንጹሓን ያይደለ ለኃጥኣን ለተዳደፉት አሳስቢ ማለቱ።
ንጹሓን ጻድቃን ለመንግሥቱ የሚያበቃ ትንሽም ቢሆን ምግባር አላቸው ጌታም ትንሿን ምግባራቸውን አይቶ መንግሥቱን ያወርሳቸዋል።
ኃጥኣንና የተዳደፉት ግን ለምሕረት የሚያበቃ ምግባር ባለመኖራቸው የእመቤታችን ልመና ከጻድቃን ይልቅ ለኃጥኣን እጅጉን ያሻልና እንዲህ አለ እንጂ የእመቤታችን ልመና ለጻድቃንም ለኃጥኣንም አስፈላጊ ነው።
"አልቦ ጸሎት ወአልቦ ትንባሌ እንበሌኪ ማርያም ዘየዐርግ ሉዓሌ ፤ እመቤቴ ማርያም ሆይ ያለ አንኪ ያለ አንቺ ረዳትነት ቅድመ እግዚአብሔር የሚደርስ ልመናና ጸሎት የለም።" እንዳለ ደራሲ
ቅዱስ ኤጲፋንዮስም በቅዳሴው "ያን ጊዜ እኛን ኃጥኣንን ብትምረን መሐሪ ትባላለህ ጻድቃንን ግን ከሥራቸው የተነሣ ትምራቸዋለህ" ብሏል።
✍️ የቅዳሴ ማርያም የመጨረሻ ጸሎት
ካህኑ በአንብሮ እድ (እጁን ከታቦቱ ላይ አድርጎ) የሚጸልየው ጸሎት ነው።
"ለእናቱ ስለ ሰጣት ጸጋ ሁሉ በዚህችም ቅዳሴ ላይ ስላሠለጠናት እግዚአብሔርን እናመሰግነዋለን። እኛንም በቸርነቱ እንናገር ዘንድ በፈቃዱም እንፈጽም ዘንድ የተዘጋጀን አደረገን። ምስጋናም ያለው እርሱ ነው። ጥበበኛም ነው ለዘላለሙ አሜን።"
✍️ ይ.ካ "በውስጥዋ ይህን ቅዳሴ የሚቀድስ ካህን እመቤታችን ማርያምን የሚቀድስ አይደለም የሚል አገኘሁ እርሱ ይቀደሳል እንጂ የሰሙትም ሁሉ ይከብራሉ።
እመቤታችን ማርያም ግን በሰማይም በምድርም ዘወትር የተመሰገነች ናትና።
የሚቀበለው የልመናዋ ክብር ፍጹም የሆነ የረድኤትዋ ሀብት ጽንፍ እስከ ጽንፍ የሚመላ የተወደደ የልጅዋ ቸርነት በእውነት ከሁላችን ጋራ ይሁን ለዘላለሙ አሜን።"
#ተፈጸመ_ቅዳሴ_ማርያም
መ/ር ማኅቶት እሸቴ
👇👇👇
የቴሌግራም ሊንክ
https://t.me/MEBspiritualtraining21
👇👇👇
የፌስቡክ አድራሻ
https://www.facebook.com/mebrie.eshetie.1
ባለጠጋ ሲሆን ራሱን ደሀ አደረገ ማለት መለኮት በሁሉ ያለ በሁሉ የመላ ሁሉን የሚገዛ ሲሆን ፍጡር ሥጋን ደካማ ሥጋን መዋቲ ሥጋን ግዙፍ ሥጋን ገንዘቡ አደረገ ማለት ነው። #አንድም ከነገሥታት ልጆች ልወለድ በቤተ መንግሥት እንዳድግ ሳይል ምንም ከሌላት በዚህ ዓለም ገንዘብ ደሀ ከሆነች ከእመቤታችን በቤተ መንግሥት ሳይሆን በበረት ተወለደ የነገሥታት ልጆች የሚለብሱትን የክብር ልብስ ሳይሆን በጨርቅ ተጠቀለለ።
#አንድም :- በዝናም አብቅሎ በፀሐይ አብስሎ ፍጥረትን ሁሉለኸ የሚመግብ ጌታ የውቂያኖስን ስፋትና ጥልቀት የሚወስን አምላክ ከሳምራዊቷ ሴት ይጠጣው ዘንድ ውሃን ለመነ።
✍️"ኃያል ወልድን ፍቅር ከዙፋኑ ሳበው እስከ ሞትም አደረሰው"
#ማብራሪያ :- ጌታችንና መድኃኒታችን የሰው ፍቅር አገብሮት እስከሞት ድረስ የደረሰው ስለ ሰው ፍቅር ብሎ ነው።
✍️"የሚስቡትን ሰዎች በቀንዱ የማይበረታታ ለሚያርዱትም ሰዎች አንገቱን የሚያዘነብል ላም ምን ይደንቅ።"
#ማብራሪያ :- ላም ሊታረድ እየሄደ አንገቱን የሚስበውን ሰው ልዋጋ አይልም ይልቁንም አንገቱን አመቻችቶ አዘንብሎ ይሰጣል። ጌታችንም አይሁድ ያን ሁሉ መከራ ሲያደርሱበት በሥልጣኔ ላጥፋቸው አላለም እንደ ሚታረድ ላም ዝም አለ እንጂ።
✍️"በሚሸልተው ፊት የማይናገር በግ እንደምን ያለ ነው። በመከራው ጊዜ በሚወጉት ፊት አፉን ያልገለጸ ምን ትዕግሥት ነው።"
#ማብራሪያ :- በግ ጸጉሩን ሲሸልቱት (ሲላጩት) ከቀን ሐሩር (ፀሐይ) ከሌሊት ቍር (ብርድ) የምከላከልበትን ጸጉሬን ለምን ትሸልተኛለህ ብሎ እንዳይናገር ጌታችን መከራ በሚያደርሱበት በሚወጉት ሰዎች ምንም አልተናገረም።
✍️ "ዮሴፍ ከተወዳጃት ክቡር ዕንቍንም በውስጥዋ ካገኘባት ሣጥን የተገኘ ኅብስት እንደምን ያለ ነው።
በውስጥዋ ሰው ካልገባባት አዳራሽ የተገኘ ጽዋ እንደምን ያለ ነው።
ፈጽሞ የተለየ ሳይሆን ከዚህ ከኅብስት የተለየ ይህ ትእምርተ መስቀል ምን ድንቅ ነው። መልኩ ልምላሜው ጣዕሙ አንድ ነው እንጂ።
መለኮቱ ከሰውነቱ ፈጽሞ የተለየ እንዳይደለ እንደዚሁም ይህ ትእምርተ መስቀል ከዚህ ኅብስት ፈጽሞ የተለየ አይደለም።
እንዲሁም ገናንነትህ ከትሕትናችን ትሕትናችን ከገናንነትህ ጋራ አንድ ይሁን። ዓለሙን የያዝህ አንተ አምላካችን እግዚአብሔር።
ይ.ዲ :- ጸልዩ
ይ.ሕ :- አቡነ ዘበሰማያት
♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️
#ክፍል_ዐሥራ_ሦስት
💎 እናንት የክርስቲያን ወገኖች እመቤታችን ወደ አለችበት ያግባችሁ
✍️"ኦ አንትሙ ሕዝበ ክርስቲያን በከመ ተጋባእክሙ በዛቲ ዕለት ከማሁ ያስተጋብእክሙ በደብረ ጽዮን ቅድስት ወበኢየሩሳሌም አግአዚት እንተ በሰማያት ... ፤ እናንት የክርስቲያን ወገኖች ሆይ በዚህች ቀን እንደተሰበሰባችሁ እንደዚሁ ክብርት በምትሆን በደብረ ጽዮን በሰማይ ባለች ነጻ በምታወጣ በኢየሩሳሌም ይሰብስባችሁ።"
"ይህንም የማርያምን የምስጋናዋን ቃል እንደ ሰማችሁ የሕፃናትን የምስጋና ቃል ይልቁንም ከጣዕሙ ብዛት የተነሣ አጥንትን የሚያለመልም የመላእክትንም ምስጋና እንደዚሁ ያሰማችሁ።"
"የእሳት ነበልባል ድንኳኖች ወደ ተተከሉበት የካህናት አለቃ ኢየሱስ ክርስቶስ ወዳለበት ያግባችሁ የተሳለ የፊቱ መልክ ከዚያ አለ። ንጹሕ አክሊልና ብሩህ ልብስ ከዚያ አለ። እርሱም ከላይ የተገኘ ነው እንጂ የሰው እጅ ያልተጠበበት ነው።"
"የቅዱሳን ነቢያት ማኅበር ወዳሉበት ያግባችሁ። ያስተማሩ የሐዋርያት ማኅበር ድል የነሡ የሰማዕታትም ማኅበር ቡሩካን የሚሆኑ የጻድቃንም ማኅበር የተሾሙ የካህናትም ማኅበር። የፍጹማን ደናግልና የመነኰሳትም ማኅበር ወዳሉት ያግባችሁ።"
"ከሁሉ በላይ ከሆነች ከአንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን ፍጹም አንድነትዋ ጋራ። ከነርሱም ጋራ ታቦት ዘዶር ወዳለችበት ይህችውም እመቤታችን ናት።"
✍️"አንግዲህ ሞትን የምታለብስና ወደ ሲዖል የምታወርድ ትዕቢትን መታጀርንም ጌጥ አናድርግ።"
"እንግዲህ የሥጋ ንጽሕና ብቻ ያይደለ ትሕትናን ከንጽሕና ጋራ ገንዘብ እናድርግ። መንፈስን ንጹሕ በማድረግ ነቢያት እግዚአብሔርን አይተውታልና ፊት ለፊትም ተያይተዋልና።"
"እንግዲህ እንደ ሐዋርያት ፍቅርን የዋሃትንም ገንዘብ እናድርግ። ጌታቸውን ወደውታልና የዓመፃ ማሠሪያን ሁሉ ያሥሩ ይፈቱም ዘንድ እንደርሱ ያለ ሥልጣንን የሰጣቸው።"
✍️"እንግዲህ እንደ ማርያም አርምሞና ትዕግሥትን ገንዘብ እናድርግ ማርያምስ የማይቀሟትን በጎ እድልን መረጠች ብሎ ጌታችን አመስግኗታልና።"
#ማብራሪያ :- እንደ ማርያም አርምሞና ትዕግሥትን ገንዘብ እናድርግ ማርያምስ የማይቀሟትን በጎ እድልን መረጠች ብሎ ጌታችን አመስግኗታልና። ያላት ማርያም የአልዓዛር እኅትን ነው። ጌታችን በቤታቸው ተገኝቶ ሐዋርያትን ሲያስተምር እሷም ቁጭ ብላ ትማር ነበር። በወንጌል እንደ ተቀመጠ።
ሉቃ 10 ÷ 38 - 42
"ሲሄዱም እርሱ ወደ አንዲት መንደር ገባ፤ ማርታ የተባለች አንዲት ሴትም በቤትዋ ተቀበለችው። ለእርስዋም ማርያም የምትባል እኅት ነበረቻት፥ እርስዋም ደግሞ ቃሉን ልትሰማ በኢየሱስ እግር አጠገብ ተቀምጣ ነበረች። ማርታ ግን አገልግሎት ስለ በዛባት ባከነች፤ ቀርባም። ጌታ ሆይ፥ እኔ እንድሠራ እኅቴ ብቻዬን ስትተወኝ አይገድህምን? እንኪያስ እንድታግዘኝ ንገራት አለችው።
ኢየሱስም መልሶ። ማርታ፥ ማርታ፥ በብዙ ነገር ትጨነቂአለሽ ትታወኪማለሽ፥ የሚያስፈልገው ግን ጥቂት ወይም አንድ ነገር ነው፤ ማርያምም መልካም ዕድልን መርጣለች ከእርስዋም አይወሰድባትም አላት።" እንዳለ
ጌታችን ማርያምስ የማይቀሟትን በጎ እድል መረጠች ብሎ ያመሰገናት ቁጭ ብላ መማሯን ነው። አጋንንትን በውዳሴ ከንቱ የማይወስዱባት ማለት ነው። ቁጭ ብሎ የሚማር ሰው ከንቱ ውዳሴ አያገኘውምና።
✍️"ከሁንም ጸጋን የሰጠ አምላካችንን እግዚአብሔርን እንለምነው።"
ይ.ዲ :- ጸልዩ
♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️
#ክፍል_ዐሥራ_አራት
💎 አዘክሪ ድንግል
✍️ "ኦ ድንግል አዘክሪ ኀበ መዘክር ዘኢይረስዕ ኵሎ ... ፤ ድንግል ሆይ ከሚያስብ ሁሉን ከማይዘነጋ ልጅሽ ዘንድ አሳስቢ።"
➢ "ድንግል ሆይ በቤተልሔም ካንቺ የተወለደውን መወለድ በጨርቅ የተጠቀለለውንም አድግና ላህም በብርድ ወራት እስትንፋስን ያሟሟቁትንም አሳስቢ።"
➢ "ድንግል ሆይ ርጉም በሆነ በሄሮድስ ዘመን ከርሱ ጋራ ከአገር ወደ አገር ስትሸሺ ካንቺ ጋራ መሰደዱን አሳስቢ።"
➢ "ድንግል ሆይ ከዓይኖችሽ የፈሰሰውንና በተወደደ ልጅሽ ፊት የወረደውን መሪር እንባ አሳስቢ።"
➢ "ድንግል ሆይ ረኃቡንና ጥሙን ችግሩንና ኃዘኑን ከርሱ ጋራ የደረሰብሽንም ጭንቅ ሁሉ አሳስቢ።"
#ማብራሪያ :- እመቤታችን በተወደደ ልጇ ምክንያት ካገኟት ኃዘናት መካከል አምስቱ መሪር ኃዘናት ናቸው። እነዚህም
#1, አረጋዊ ስምዖን በቤተመቅደስ ጌታን ታቅፎ ለወደፊቱ በልጇ ምክንያት ብዙ መከራ እንደምትቀበል በነገራት ጊዜ።
#2, ወደ ግብፅ ሲሰደዱ የዮሴፍ ልጅ ዮሳ በመንገድ ደርሶ አስደንጋጭ ዜና በነገራት ጊዜ።
#3, ሽፍቶች የጌታን ልብስ ቀምተው ቁመው በተማከሩ ጊዜ።
#4, በቀራንዮ አደባባይ በተሰቀለ ጊዜ።
#5, ወደ መቃብር በወረደ ጊዜ።
ጌታችንም እነዚህን እመቤታችን ያዘነችባቸውን ኃዘናት እያሰበ አቡነ ዘበሰማያት እና በሰላመ ገብርኤልን የጸለየ ሰው እንደ ሚምርላት ቃል ኪዳን ሰጥቷታል።
✍️ "ጥፋትን ያይደለ ይቅርታን አሳስቢ። መዓትን ያይደለ ምሕረትን አሳስቢ። ለጻድቃን ያይደለ ለኃጥኣን አሳስቢ። ለንጹሓን ያይደለ ለተዳደፉት አሳስቢ።"
#ማብራሪያ :- ሥጋውን ደሙን ከአንቺ የተገኘ አለ ፤ የምንቀበለው ሥጋ ከእመቤታችን የነሣው ነውና።
ወይኑ ተለውጦ ደመ ወልደ እግዚአብሔር እንደሚሆን አምኖ የተቀበለውና በንስሓ እራሱን ለቍርባን ያዘጋጀ ሰው ቢቈርብ ሕይወት ይሆንለታል። ሥጋ ደሙ እውነተኛ የሕይወት መብልና መጠጥ ስለሆነ። ጌታ እንደ ተናገረ
"ሥጋዬ እውነተኛ መብል ደሜም እውነተኛ መጠጥ ነውና።" (ዮሐ 6:55)
ሳያምና ሳይበቃ ቢቀበል ግን በሕይወት ፈንታ ሞት በበረከትም ፈንታ መርገም ይሆንበታልና እንዲህ አለ።
"ሳይገባው የሚበላና የሚጠጣ የጌታን ሥጋ ስለማይለይ ለራሱ ፍርድ ይበላልና፥ ይጠጣልምና።" (1ኛ ቆሮ 11:29)
✍️ "አሁንም ላንተ ምስጋና ይገባሃል። ለመንግሥትህም ምስጋና ይገባል እያልን እናመስግነው ከንጹሕ እጣን ጋራ ምስጋናን እናቀርብልሃለን።"
♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️
#ክፍል_ዐሥራ_አንድ
💎 የዕብራውያንን ፊደል ተማረ
✍️ "ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው ... ፤ በጎ ሀብት ሁሉ ፍጹም ዕድልም ሁሉ ከእርሱ የሚገኝ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው ሆነ ከኃጢአት ብቻ በቀር የሰውን ሕግ ሁሉ ፈጸመ የዕብራውያንንም ሕግ ተማረ።"
#ማብራሪያ :- ጌታችን በሰውነቱ ከኃጢአት በቀር የሰውን ሥራ ሁሉ ሠራ ይባላል። ይኸውም መብላት ፣ መጠጣት ፣ መድከም ፣ መተኛት ፣ መታዘዝ እንደ ሰውነቱ አላዋቂ መስሎ "አልዓዛርን ወዴት ቀበራችሁት" ብሎ መጠየቅ ፣ መጾም ፣ መጸለይ ፣ ማመስገን ፣ የሰርግ ቤት መሄድ ፣ ለንጉሥ ግብር መገበር ፣ መታመም መሞት የሰውነት ስራ ናቸው። እነዚህን ሲሠራ ግን ሰው እንደሚሠራው ኃጢአትን ወይም ጥፋትን አልሰራም።
እንደ ሰውነቱ ከሠራቸው ውስጥ አንዱ ከመምህር ዘንድ ሂዶ መማሩ ነው። እመቤታችን በሕፃንነቱ ለመምህር ወስዳ ሰጠችው መምህሩ በዕብራውያን ቋንቋ "አሌፍ" በል አለው "አሌፍ" አለ። ቀጠለና "ቤት" በል አለው ፊት የአሌፍን ትርጓሜ ንገረኝ አለው። ከዛ መምህሩ ደንግጦ ልጅ የነገሩትን ይይዛል እንጂ ይጠይቃልን ብሎ ይህንንስ ማስተማር አይቻለኝም ብሎ መለሰው።
ሁለተኛ ከሌላ መምህር ወሰደችው ፤ ያም መምህር ጸሐፊ ነበርና ከቤቱ ደጃፍ የሚጽፍበትን ቀለሙን አስቀምጦ ወደ ቤቱ ሲገባ ጌታችን ጥቁሩን ቀለም ከቀዩ ቀለም ደበለቀበት። በዚህን ጊዜ መምህሩ ተቆጥቶ ሲገርፈው ለምን ትገርፈኛለህ ይልቅ ቀለሙን ለይልኝ ለምን አትለኝም አለው ጌታ። መምህሩም ከመጀመሪያው ጥፋቱ ያሁኑ ይበልጥ ለመሆኑ ቀለም ከቀለም ከተደባለቀ በኋላ ይለያልን አይ የልጅ ነገር ብሎ ሳቀበት። ጌታ ግን የተደባለቀውን ቀለም ጥቁሩን ለብቻ ቀዩን ለብቻ አድርጎ ሰጠው። መምህሩ ደነጠ ይቅርበለኝም አለው ለእናቱም ይህ ልጅሽ ነቢያት ትንቢትን የተናገሩለት ሳይሆን አይቀርምና እሱን ማስተማር አይቻለኝም ብሎ መለሰው። ፊደለ ዕብራውያንን ወይም የዕብራውያንን ሕግ ተማረ ያሰኘው ይህንን ነው።
#አንድም :- የእጅ ጥበብ ቀለም ማግባት ልብስ መስፋት ተማረ። ከዕለታት በአንዳቸው ቀን አንዲቱ ቀለም አግባልኝ ብላ መጣች አግብቶ ሰጣት። በኋላ ዋጋ የማያወጣልኝ ሆነ አለችው። እንደ ነበረ አድርጎ ቀለሙን ለይቶ (ዘሀውን ከክሩ ለይቶ) ሰጣት።
ዳግመኛ አንዲቱ ልብስ ስፋልኝ አለችው። ሰፍቶ ሰጣት ጠበበኝ አለችው አሰፋላት ሰፋኝ ዋጋ አላወጣልኝ አለ አለችው እንደ ነበረ አድርጎ መልሶ ሰጣት። ይሄ የአምላክነቱ ግብር ነው።
✍️"ከዮሐንስ ዘንድ ተጠመቀ በገዳም ተፈተነ ተራበ ተጠማም ተአምራትን አደረገ"
#ማብራሪያ :- የጌታ ተአምራቱ ብዙ ነው ፣ ድውይ ፈውሷል ፣ ለምጽ አንጽቷል ፣ ጎባጣ አቅንቷል ፣ ኃንካሳ ረትቷል ፣ ዕውር አብርቷል ፣ ዲዳ አናግሯል ፣ ጀሮ ከፍቷል ፣ ጋኔን አውጥቷል ፣ ሙት አስነስቷል (የዕለት ሬሳ ወለተ ኢያኢሮስን ወልደ መበለትን ፣ የአራት ቀን ሬሳ አልዓዛርን አስነሥቷል)። ኅብስት አበርክቶ መግቧል።
✍️ "ሰውነቱን ለሞት በሰጠባት በዚያች ዕለት ለደቀመዛሙርቱ በብዙ ምልክት አመለከተ የሕማሙንና የስቅለቱን የሞቱን ነገር በሦስተኛው ቀን የመነሣቱን ነገር በሥጋና በነፍስ በዐጥንትና በደም ቀድሞ እንደ ነበረው ደቀመዛሙርቱ ከርሱ ጋራ በቀኙና በግራው ሳሉ። ፍጥረቱ ክርዳድ የሚሆን ከስንዴ ጋራ የተቀላቀለ ያስያዘው ይሁዳም ከነርሱ ጋራ የተቈጠረ ሆኖ ነበረ።"
#ማብራሪያ :- ክርዳድ ያለው ይሁዳን ነው ስለ ልቦናው ጥመት ስለ ሰውነቱ ክፋት ክርዳድ ሳይዘሩት ከስንዴ ጋር አብሮ ይበቅላል አብሮ ያድጋል የሚታወቀው በፍሬው ነው። እንደዚሁም ሁሉ ይሁዳ ከሐዋርያት ጋር አብሮ ደኅና መስሎ ሲማር ኑሮ በዕለተ ሐሙስ ጌታን አሳልፎ ሲሰጥ ከሀዲነቱ በፍሬው ታውቋልና።
ስንዴ ያላቸው ሐዋርያትን ነው። ስንዴ ለመሥዋዕት እንዲሆን ሐዋርያትም ሰውነታቸውን ለጌታ መሥዋዕት ለወንጌል መሥዋዕት አሳልፈው ሰጥተዋልና።
♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️
#ክፍል_ዐሥራ_ሁለት
💎 ኃያል ወልድን ከመንበሩ ፍቅር ሳበው
✍️" እግዚአብሔር ገባሬ ኵሉ ... ሁሉን የፈጠረ ሁሉን የፈጸመ ሁሉን የጀመረ ሁሉን የያዘ ሁሉንም የጨበጠ እግዚአብሔር።"
#ማብራሪያ :- እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን በውስጣቸው ያሉ ፍጥረታትን ግዙፉንና ረቂቁን የሚታየውንና የማይታየውን በአጠቃላይ ሃያ ሁለቱን ፍጥረት የፈጠረ አምላክ ነው።
ሁሉን የጀመረ ማለት ፤ ፍጥረታትን መፍጠር በዕለተ እሑድ የጀመረ ማለት ነው።
ሁሉን የጨረሰ ማለት ፤ መፍጠሩን በዕለተ ዐርብ የጨረሰ ማለት። የጀመረ ሌላ የጨረሰ እሱ ወይም የጀመረ እሱ የጨረሰ ሌላ አይባልም ፍጥረታትን መፍጠር የጀመረ የጨረሰ እሱ ብቻ ነውና።
ሁሉን የያዘ ሁሉን የጨበጠ ማለት ፤ ፍጥረታትን እንደ ጥና እንደ እንቁላል በመሀል እጁ የያዘ ማለት ነው።
#አንድም :- ሁሉን የፈጠረ አለ ፤ የቸርነቱን ሥራ በአምስት ቀን ተኩል ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ በማለት የተናገረ።
ሁሉን የጀመረ አለ ፤ የማዳኑን ሥራ በማኅፀን የጀመረ።
ሁሉን የጨረሰ አለ ፤ የማዳኑን ሥራ በዕለተ ዐርብ በመስቀል ላይ የጨረሰ።
#አንድም :- ሁሉን የፈጠረ ሁሉን የጀመረ ሁሉን የጨረሰ አለ ፤ ኦሪት የሠራ እሱ የጀመረ እሱ የፈጸመ።
#አንድም :- ሁሉን የፈጠረ ሁሉን የጀመረ ሁሉን የጨረሰ አለ ፤ ወንጌልን የሠራ እሱ የጀመረ እሱ የፈጸመ።
#አንድም :- ሁሉን የፈጠረ ሁሉን የጀመረ ሁሉን የጨረሰ አለ ፤ ጥምቀትን ንስሓን የሠራ እሱ የጀመረ እሱ የፈጸመ።
"አኃዜ ኵሉ .. ፤ ሁሉን የያዘ ሁሉን የጨበጠ" ማለት አላምንም አልጠመቅም ያለውን በፍዳ የሚይዝ።
✍️"መላእክትና የመላእክት አለቆች መናብርትና ሥልጣናት አጋዕዝትና ኃይላት ፀሐይና ጨረቃ ከዋክብትም ድርገታትም የሚሰግዱለት ተገዦቹና ግዛቱ ጕልቱም ናቸውና በሁሉ ባለጠጋ ሲሆን ራሱን ከሁሉ ድሀ አደረገ።"
#ማብራሪያ :- ድርገታት ማለት ከዋክብት መሪያቸውን ተከትለው የሚሄዱት የሚያበሩት ኅብረት ወይም የከዋክብት ክምችት አንድነት ማለት ነው።
ፀሐይ ጨረቃ ከዋክብት ይሰግዱለታል ማለቱ ሰው እነዚህን ብርሃናት የፈጠርክልን ለእኛ ነው እያለ የሚያመሰግነው በመሆኑ። #አንድም እሱ ባወቀ ይሰግዱለታል።
✍️ "አብ እሳት ነው ወልድ እሳት ነው መንፈስ ቅዱስም እሳት ነው በልዕልና ያለ አንድ የሕይወት እሳት ነው።"
#ማብራሪያ :- ለእሳት ሦስትነት አለው። ፍሕሙ ፣ ነበልባሉ ፣ ሙቀቱ።
በፍሕሙ አብ ፣ በነበልባሉ ወልድ ፣ በሙቀቱ መንፈስ ቅዱስ ይመሰላሉና። ይህ አንድ እሳት ቢባል እንጂ ሦስት እሳት እንዳይባል ሥላሴም በስም ፣ በግብር ፣ በአካል ሦስት ሲሆኑ በባሕርይ ፣ በሕልውና ፣ በአገዛዝ አንድ ይባላሉና።
✍️ "አብ ጎሕ ነው ወልድ ጎሕ ነው መንፈስ ቅዱስም ጎሕ ነው በብርሃኑ ፀዳል ጨለማ የራቀበት #አንድም ኃጢአት ድርንቁርና የጠፋችበት ፤ አንድ የጧት ጎሕ ነው።"
#ማብራሪያ :- ጎሕ ማለት የጧት ብርሃን ማለት ሲሆን ጨለማው እንደ ተወገደ ከፀሐይ መውጣት አስቀድሞ የሚመጣው እና የሌሊቱን መንጋት የሚያውጀው የተፈጥሮ ብርሃን ነው።
ለጎሕ ሦስትነት አለው አካል ፣ ብርሃን ፣ ርቀት።
አካሉ ጎሕ ቀደደ ይባላል። ብርሃኑ ከጽንፍ እስከ ጽንፍ መልቶ ይታያል። ርቀቱ በዝግ ቤት ይገባል።
በአካሉ አብ ፣ በብርሃኑ ወልድ ፣ በርቀቱ መንፈስ ቅዱስ ይመሰላሉና። ይህ አንድ ጎሕ ይባላል እንጂ ሦስት ጎሕ እንዳይባል ፤ ሥላሴም በስም ፣ በግብር ፣ በአካል ሦስት ሲሆኑ ፤ በባሕርይ ፣ በሕልውና ፣ በአገዛዝ አንድ ይባላሉና።
✍️ አብ ጕንደ ወይን ነው ወልድ ጕንደ ወይን ነው መንፈስ ቅዱስም ጕንደ ወይን ነው። ዓለሙ ሁሉ የጣፈጠበት #አንድም ሰው ሁሉ ጣዕመ ጸጋ ያገኘበት አንድ የሕይወት ወይን ነው።
#ማብራሪያ :- አንዱ የወይን እንጨት ሦስትነት አለው ፤ ግንድ ፣ ቅጠል ፣ ፍሬ። ይህ አንድ ወይን ወይን ይባላል እንጂ ሦስት ወይን እንዳይባል ፤ ሥላሴም በስም ፣ በግብር ፣ በአካል ሦስት ሲሆኑ በባሕርይ ፣ በሕልውና ፣ በአገዛዝ አንድ ይባላሉና።
✍️ "አብ ሐሊብ ነው ወልድ ሐሊብ ነው መንፈስ ቅዱስም ሐሊብ ነው ጭማሪ የሌለበት አንድ ሐሊብ እርሱ ነው።"
#ማብራሪያ :- ለሐሊብ (ለወተት) ሦስትነት አለው ቅቤው ፣ አጓቱ ፣ አይቡ።
#አንድም ለቅቤው ሦስትነት አለው ፤ አካል ፣ ግዘፍ ፣ ርቀት። አካሉ ልባም ሴት የያዘችው እንደ ሆነ ዝናም ያረበረበበት ቄጤማና አደይ አበባ ይመስላል። ግዘፉ ይዳሰሳል። ርቀቱ ከድንጋይ ላይ እንኳ ቢያደርጉት በውስጥ ዘልቆ ይገኛል።
በአካሉ አብ ፣ በግዘፉ ወልድ ፣ በርቀቱ መንፈስ ቅዱስ ይመሰላሉ። ይህ አንድ ቂቤ እንጂ ሦስት እንዳይባል ፤ ሥላሴም በስም ፣ በግብር ፣ በአካል ሦስት ሲሆኑ በባሕርይ ፣ በሕልውና ፣ በአገዛዝ አንድ ይባላሉና።
እንዲህ እናምናለን እንዲህም እንታመናለን የሃይማኖትንም ጸሎት እንበል። (በዚህን ጊዜ ጸሎተ ሃይማኖትን መጸለይ ይገባል)
♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️
#ክፍል_ዘጠኝ
💎 ሰባት የእሳት መጋረጃዎች በሆድሽ ውስጥ ወዴት ተዘረጉ
"ንግባእኬ ኀበ ጥንተ ነገር ወንሕትታ ለቅድስት ድንግል በእንተ ፅንሳ ዘመንክር ለኵሉ እንዘ ንብል። ... ፤ ወደ ቀደመው ነገር እንመለስ ቅድስት ድንግልንም ለሁሉ ድንቅ የሚሆን የፅንሷን ነገር እንዲህ እያልን እንመርምራት።
ድንግል ሆይ እሳተ መለኮት በሆድሽ ባደረ ጊዜ ፊቱ እሳት ልብሱ እሳት ቀሚሱ እሳት ነው እንደምን አላቃጠለሽም።"
#ማብራሪያ :- እግዚአብሔር ባሕርይው እሳት ነው ለእሳትነቱም መጠንና ልኬት የለውም እርሱ እራሱ ያውቀዋል እንጂ የመለኮትነቱን እሳትነት ፍጥረት እንዲህ ነው ብሎ ሊገልጸው አይችልም።
✍️ "ሰባት የእሳት ነበልባል መጋረጃ በሆድሽ ውስጥ ወዴት ተጋረደ ወዴትስ ተዘረጋ ከጎንሽ በቀኝ ነውን ወይስ ከጎንሽ በግራ ነውን ትንሽ አካል ስትሆኝ።
#ማብራሪያ :- ትንሽ አካል ስትሆኝ አላት እመቤታችንን እንደ ሁሉም ሰው ሦስት ክንድ ከስንዝር ናትና። አሁን አስር አስራ አምስት ክንድ ብትሆን የምትወስነው ሁና አይደለም በማዕርግ እንጂ በአካል ከሰው አትበልጥምና። እንዲህም ማለቱ የማዕርጓን ደግነት ሲናገር ነው።
✍️ "የሚያንጸባርቅ ነደ እሳት የሚከበው ኪሩቤል የተሸከሙት ዙፋን በሆድሽ ውስጥ ወዴት ተዘጋጀ ወዴትስ ተተከለ ታናሽ ሙሽራ ስትሆኝ።"
"ከገረድነት ጋር እናትነት እንደምን ያለ ነው። ከስፋት ጋራ የሆድ መጥበብ እንደምን ያለ ነው። እንደ ንብ ያለ ሩካቤ ከቃል ድምፅ የተገኘ ፅንስ ከድንግልና ጋራ አንድ የሆነ ሐሊብ።"
#ማብራሪያ :- ንብ ያለ ሩካቤ አውራው ድምፅ ሲያሰማት ትፀንሳለች። እመቤታችንም ያለ ወንድ ዘር ከመልአኩ የብስራት ድምፅ ሰምታ አካላዊ ቃልን ፀንሳለች።
ከድንግልና ጋር አንድ የሆነ ሐሊብ ማለት ሴቶች ድንግልና ካላቸው ወተት አይገኝባቸውም ከወለዱና ወተት ከፈሰሳቸው በኋላም ድንግልና አይኖራቸውም። እመቤታችን ግን ድንግል ስትሆን እናት ፤ እናትም ስትሆን ድንግል ናትና ሐሊበ ድንግልናን (የድንግልና ወተትን) ለልጇ አጥብታዋለችና።
✍️ "ይህንም ባሰብኩ ጊዜ ሕሊናዬ የልጅሽን የባሕሩን ጥልቀት ሊዋኝ ይወዳል የወዳጅሽ የመሠወሪያው ማዕበልም ያማታዋል።"
"ዳግመኛም ባሰብሁ ጊዜ ሕሊናዬ ተሠውሮ ወደ ላይ ወጥቶ የሕያው መሠወሪያ የሆነውን ሊገልጥ ይወዳል። ከነደ እሳትነቱ የተነሣ ይፈራል ከዐየራት ከሩባቸው ሩብ አይደርስም።"
"ይህንንም ባሰብኩ ጊዜ ሕሊናዬ በነፋስ ትከሻ ተጭኖ በምሥራቅና በምዕራብ በሰሜንና በደቡብ በዳርቻውም ሁሉ ሊበር ይወዳል። የፍጡራንን አኗኗር ያይ ዘንድ የአብሕርትንም ጥልቅነታቸውን ይለካ ዘንድ የሰማይን ርዝመቱን ያውቅ በሁሉ ዘንድ በሁሉም ይዞራል። አቅቶት ወደ ቀደመ አኗኗሩ ይመለሳል።"
"አሁንም ገናንነቱን እንመርምር ጥልቅነቱንም አንጠናቀቅ የገናንነቱን መጠን ለማመስገን የነቢያትና የሐዋርያት አንደበት የማይቻለው ነው።"
"የማይደፈር ግሩም ነው በእኛ ዘንድ ግን ትሑት ነው። የማይገኝ ልዑል ነው በእኛ ዘንድ ግን አርአያ ገብርን ነሣ። የማይደሰስ እሳት ነው እኛ ግን አየነው ዳሰስነውም ከርሱም ጋራ በላን ጠጣን።"
♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️
#ክፍል_ዐሥር
💎 የሚባለውን ያፈራሽልን ድንግል
✍️ "ድንግል ሆይ የሚበላውን ያፈራሽልን የሚጠጣውን ያስገኘሽልን።
ወዮ ከአንቺ የተገኘ ኅብስት በማመን ከርሱ ለሚቀበሉ ሕይወትና ድኅነትን የሚሰጥ ነው።
ወዮ ከአንቺ የተገኘ ኅብስት በማመን ከርሱ ለማይቀበሉ ሰዎች የማይላመጥ ጽኑ ነው ይኸውም ኃያል የሚሆን የአድማስ ደንጊያ ነው።"
#ማብራሪያ :- ኅብስቱ ለውጦ ሥጋ ወልደ እግዚአብሔር እንደሚሆን ያመነ እና እራሱን በንስሓ አጥቦ ተዘጋጅቶ ቢቀበል ሕይወት ይሆንለታል። "ሥጋየን የበላ ደሜን የጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው" ያለ ጌታ ለእነዚህ ነው (ማቴቀ 6÷54)።
ኅብስቱ ተለውጦ ወልደ እግዚአብሔር እንደሚሆን ሳያምን ወይም እየተጠራጠረ እና እራሱን ለቁርባን ሳያዘጋጅ በንስሓ ሳይታጠብ የሚቆርብ ቢኖር ግን መቅሰፍት በላ። ጳውሎስ እንደተናገረ
" ስለዚህ ሳይገባው ይህን እንጀራ የበላ ወይም የጌታን ጽዋ የጠጣ ሁሉ የጌታ ሥጋና ደም ዕዳ አለበት።" (1ኛ ቆሮ 11:27)
✍️ "ወዮ ከአንቺ የተገኘ ጽዋ በማመን ከእርሱ ለሚጠጡ ሰዎች ጥበብን የሚገልጽ ሕይወትንም የሚሰጥ ነው።
ወዮ ከአንቺ የተገኘ ጽዋ በማመን ከእርሱ ለማይጠጡ ሰዎች የሚያሰክር የሚያፍገመግም የሚጥልና ኃጢአትን ስለሚያስተው ፈንታ ኃጢአትን የሚጨምር ነው።"
"ለመለኮት ወርድና ቁመት ላይና ታች ቀኝና ግራ ያለው አይደለም በሁሉ የመላ ነው እንጂ።"
"ለመለኮት የሚዘረጋበትና የሚሰበሰብበት ያለው አይደለም ግዛቱ ባገር ሁሉ ነው እንጂ።"
"ለመለኮት በላይ ጠፈር በታች መሠረት ያለው አይደለም ጠፈሩም መሠረቱም እርሱ ነው እንጂ።"
"ለመለኮት ከምድር ከውስጥዋ የሆነውን ያነሣ ዘንድ ማጎንበስ ራስን ዝቅ ማድረግ ያለበት አይደለም። ለጴጥሮስ እንዳሳየው ሁሉ በእጁ የተያዘ ነው እንጂ።"
"ለመለኮት በሚታይ ገንዘብ ደረትና ፊት የኋላም ጀርባ ያለው አይደለም። በነደ እሳት የተሸፈነ ነው እንጂ። ነደ እሳት ግን እርሱ ነው። መለኮትስ ንጹሕና ጽሩይ ብሩህም ነው።"
♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️
#ክፍል_ሰባት
💎 ምሥጢረ ሥላሴ
"የላከ አብን በአናንዋሩ አባት እንደሆነ እናምናለን። የተላከ ወልድንም በአናንዋሩ ወልድ እንደሆነ እናምናለን። ማሕየዊ መንፈስ ቅዱስም በአናንዋሩ መንፈስ ቅዱስ እንደሆነ እናምናለን። ሦስቱ ስም አንድ እግዚአብሔር ነው።"
#ማብራሪያ :- የላከ አብን በአናንዋሩ አባት እንደሆነ እናምናለን ማለት ፤ አብ በተለየ አካሉ ፈናዊ (ወልድን ለኩነተ ሥጋ የላከ። "ዘተፈነወ እም አብ ፤ ከአብ የተላከ እንዳለ")። በተለየ ስሙ አብ (የወልድ የባሕርይ አባት)። በተለየ ግብሩ ወላዲ (ወልድን በባሕርይው የወለደ)። በተለየ ባሕርዩ ለባዊ አለባዊ (ልብነት ገንዘቡ ስለሆነ ለባዊ አለባዊ ወይም ማስተዋል ገንዘቡ የሆነ ማስተዋልን የሚያድል ይባላል) እንደሆነ እናምናለን።
የተላከ ወልድንም በአናንዋሩ ወልድ እንደሆነ እናምናለን ማለት ፤ ወልድም በተለየ አካሉ ተፈናዊ (ሥጋን ለመልበስ የተላከ)። በተለየ ስሙ ወልድ(የአብ የባሕርይ ልጅ)። በተለየ ግብሩ ወይም ሥራው ተወላዲ (ከአብ ባሕርይ ዘእም ባሕርይ አካል ዘእም አካል የተወለደ)። በተለየ ባሕርዩ ነባቢ አንባቢ (ቃልነት ገንዘቡ ስለሆነ ተናጋሪ አናጋሪ ይባላል)።
ማሕየዊ መንፈስ ቅዱስም በአናንዋሩ መንፈስ ቅዱስ እንደሆነ እናምናለን ማለት ፤ መንፈስ ቅዱስም በተለየ አካሉ ተፈናዊ (የተላከ ማለት ሲሆን ፤ "ወአነ እፌኑ ለክሙ ጰራቅሊጦስሃ መንፈሰ ጽድቅ ፡ እኔ እውነተኛ መንፈስ መንፈስ ቅዱስን እልክላችኋለሁ" እንዳለ ጌታ በሐዋርያት ላይ ተልኮ የወረደው መንፈስ ቅዱስ ነውና)። በተለየ ስሙ መንፈስ ቅዱስ። በተለየ ግብሩ ሠራፂ (ከአብ የተገኘ)። በተለየ ባሕርዩ ማኅየዊ (ሕይወትነት ገንዘቡ ስለሆነ አዳኝ ይባላል) እንደሆነ እናምናለን ማለት ነው።
✍️ "አኮ ከመ አብርሃም ዘይልሕቅ እም ይስሐቅ ... ፤ አብርሃም ከይስሐቅ ይስሐቅም ከያዕቆብ እንደሚበልጥ አይደለም። አብ ከልጁ አይበልጥም። ወልድም ከመንፈስ ቅዱስ አይበልጥም። መንፈስ ቅዱስም ከወልድ አያንስም። ወልድም ከአባቱ አያንስም።
#ማብራሪያ :- በፍጥረታት ባሕርይ አባት ከልጁ ቀድሞ ይገኛል ይበልጣል ልጁ ከአባቱ በዘመን ወደ ኋላ ይሆናል ያንሳል። አብርሃም ከልጁ ከይስሐቅ በዘመን ተቀድሟል በልጧል ይስሐቅም ከአባቱ በዘመን ወደኋላ ሁኗል አንሷል ያዕቆብም እንዲሁ። በሥላሴ ዘንድ ግን አብ ወልድን ስለ ወለደ መንፈስ ቅዱስን ስላስገኘ በዘመን አይቀድምም አይበልጥም። ወልድም ከአብ ስለ ተወለደ በዘመን ከአባቱ አያንስም ወደ ኋላ አይሆንም። መንፈስ ቅዱስም ከአብ ስለተገኘ በዘመን አያንስም ወደ ኋላ አይሆንም።
የሦስቱ ዘመን መቀዳደም መበላለጥ የሌለበት አንድ ነው እንጂ።
"አሐቲ ቅድምናሆሙ ለሥላሴ ፤ የሥላሴ ቅድምናቸው አንዲት ናት" እንዳለ ሃይ.አ ኪራ 91÷5
✍️ "አኮ ከመ አብርሃም ዘይኤዝዞ ለይስሐቅ በሕገ ፍጥረት ... ፤ አብርሃም በፍጥረት ሥርዓት ይስሐቅን እንዲያዘው ይስሐቅም ያዕቆብን እንዲያዘው አይደለም። መለኮት እንዲህ አይደለም። አባት በመሆን አብ ልጁን አያዘውም ወልድም ልጅ በመሆን አይበልጥም መንፈስ ቅዱስም ትክክል ነው።"
#ማብራሪያ :- በዚህ ዓለም ያለ አባት ልጁን ይህን አድርግ ይህን ሥራ ብሎ እንደሚያዘው በሥላሴ ዘንድ የለም። ምክንያቱም ፈቃዳቸው አንድ ስለሆነ። አብ ሊሠራ ያወቀውን ወልድ መንፈስ ቅዱስም አውቀው ይሰሩታልና።
✍️ "መለኮት ግን አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ነው። አንድ አምላክ አንዲት መንግሥት አንዲት ሥልጣን አንዲት አገዛዝ ነው።"
"አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ያስባሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ይናገራሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ይወዳሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ይመክራሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ይናገራሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ይፈጽማሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ይሠራሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ያስማማሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ያከናውናሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ይልካሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ያሠለጥናሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ምስክር ይሆናሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ይስባሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ያለምዳሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ይመክራሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ያነጻሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ያጋራሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ያከብራሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ያጸናሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ያስጨክናሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ያስተምራሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ይጋርዳሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ያለብሳሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ባለሟል ያደርጋሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ በአደባባይ ይቀመጣሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ይፈርዳሉ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ይመረምራሉ።
#ማብራሪያ :- በሥላሴ ዘንድ መቆም መቀመጥ መሄድ መምጣት ኑሮ አይደለም። በአደባባይ ይቀመጣሉ ይፈርዳሉ ይመረምራሉ ሲል። በነገሥታት በመኳንንት በመሳፍንት አድረው የሚመረምሩ ሥጋዊ ፍርድን የሚፈርዱ ስለሆነ ነው እንጂ። በካህናት በጳጳሳት አድረው መንፈሳዊ ፍርድን የሚፈርዱ ስለሆነ እንጂ። ሌላውንም በዚሁ አረዳድ ይገንዘቡት።
♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️
#ክፍል_ስምንት
💎 የምሥጢረ ሥላሴ ምሳሌዎች
" ከመዝ ነአምን ወከመዝ ንትአመን ድማሬ ወኍባሬ እንዘ ኢንፈልጥ ወኢንሌሊ ከመ ኢይኩን ብዑደ ... ፤ እንዲህ እናምናለን እንዲህም እንታመናለን አንድነትን ሳንለይ። የተለየ እንዳይሆን የተቀላቀለ እንዳይሆን እንለይ።"
እንደ አብርሃምና እንደ ይስሐቅ እንደ ያዕቆብም ሦስት የምን አይደለንም በአካል ሦስት ሲሆን በባሕርይ አንድ ነው እንጂ።
ከፍጥረት ሁሉ እንደሚቀድም እንደ አዳም አንድ የምንል አይደለንም በባሕርይ አንድ ሲሆን በአካል ሥስት እንላለን እንጂ።
ክፉዎች አይሁድን ባለማወቃቸው የእግዚአብሔር ገጽና አካል አንድ ነው ኢያሉ የሚናገሩ በደለኞቹን የይስማኤል ወገኖችንም እነሆ እንሰማቸዋለን ልቡናቸውን ያሳወሩ ናቸው።
አምላኮቻቸው ብዙ አጋንቶቻቸውም ብዙ የሆኑ በጣዖት የሚያመልኩ አረማውያንን እነሆ እናያቸዋለን።
እኛ ግን በጎ ጎዳና የሚያስተምሩትን እንከተላለን። ሐዋርያት እንዲህ እያሉ እንዳስተማሩን።
✍️ "አብ ፀሐይ ነው ወልድም ፀሐይ ነው መንፈስ ቅዱስም ፀሐይ ነው ከሁሉ በላይ የሚሆን አንድ የእውነት ፀሐይ ነው።"
#ማብራሪያ :- ለፀሐይ ሦስትነት አለው ክበቡ ፣ ጸዳሉ (ብርሃኑ) ፣ ሙቀቱ። በክበቡ አብ ፣ በጸዳሉ ወልድ ፣ በሙቀቱ መንፈስ ቅዱስ ይመሰላሉና።
ይህ አንድ ፀሐይ ቢባል እንጅ ሦስት ፀሐይ እንዳይባል ሥላሴም በስም ፣ በግብር ፣ በአካል ሦስት ሲሆኑ በባሕርይ ፣ በሕልውና ፣ በአገዛዝ አንድ ይባላሉና።
የያዕቆብ መሰላል አንቺ ነሽ አለ ያዕቆብ ወደ ሶርያ ሲሄድ ሎዛ ላይ ደርሶ በተኛ ጊዜ በራዕይ ያያት የወርቅ መሰላል ነበረች። በመሰላሏ ጫፍ ዙፋን ተዘርግቶ ንጉሥ ተቀምጦ መላእክት ሲወጡባት ሲወርዱባት አይቷል። ይኼውም ምሳሌ ነው።
➢ መሰላል የእመቤታችን የወርቅ መሆኑ የንጽሕናዋ የቅድስናዋ ምሳሌ
➢ ዙፋን የማኅፀኗ ምሳሌ
➢ ንጉሥ በማኅፀኗ ያደረ የጌታ ምሳሌ ነው።
✍️"የሙሴ ጽላት ጳጦስ የተባለች የሲና ዕፅ በካህን አሮን ልብስ የነበረች ጸናጽል ዳግመኛም የበቀለችና ያፈራች በትር አንቺ ነሽ።"
ሙሴ ጽላቱን ከእግዚአብሔር በተቀበለ ጊዜ በእግዚአብሔር ጣት የተጻፉ ዐሥሩ ቃላት ነበሩበት። በፊትም ከመጠራቱ በፊት ቅጠልና እሳት ተዋህደው አይቷል። ይኼውም ምሳሌ ነው
➢ ጽላት የእመቤታችን የማኅፀኗ ምሳሌ
➢ ዐሥሩ ቃላት በማኅፀኗ ያደረው የእግዚአብሔር ቃል ምሳሌ
➢ እሳት የመለኮት
➢ ቅጠል የትስብእት (ከእመቤታችን የነሣው ሥጋ) ምሳሌ። እሳቱ ቅጠሉን አለማቃጠሉ መለኮት ትስብእትን ያለማጥፋቱ። ቅጠሉም እሳቱን አለማጥፋቱ ትስብእት መለኮትን ያለ መዋጡ። ቅጠሉና እሳቱ ተዋሕደው ማየቱ የመለኮትና የትስብእት ተዋሕዶ ምሳሌ ነው።
#አንድም :- ቅጠል (ሐመልማል) የእመቤታችን እሳዠቸተ (ነበልባል) የጌታ ምሳሌ።
እመቤታችን በአሮን በትር ትመሰላለች የአሮን በትር በቤተ መቅደስ ውስጥ ገብታ 12 ገውዝ ለውዝ አፍርታለች እመቤታችንም 12 ዓመት በቤተ መቅደስ ኑራ ጌታን ጸንሳለችና።
✍️ "የኢያሱ የምስክሩ ሐውልት የጌዴዎን ፀምር የሳሙኤል የሽቱ ሙዳይ የዘይት ቀንድ አንቺ ነሽ።
ጌዴዎን የእግዚአብሔር ተራዳኢነቱን ለማወቅ ፀምር ዘረጋ
መጀመሪያ ጠል በፀምሩ ላይ ሲወርድ ዙሪያው ደረቅ ሆነ። ይኼውም ምሳሌ ነው
➢ ፀምር የእመቤታችን ጠል የጌታ
➢ ጠል በዙሪያው ሳይወርድ ከፀምሩ ላይ ብቻ መውረዱ ጌታ ከሌሎች እሴቶች ሳይወለድ ከእመቤታችን ብቻ ለመወለዱ ምሳሌ።
በሁለተኛው ጠል ከፀምሩ ሳይወርድ በዙሪያው ወረደ። ይኼውም ምሳሌ ነው
➢ ፀምሩ ደረቅ መሆኑ እመቤታችን እንበለ ዘር ለመውለዷ ምሳሌ።
➢ በዙሪያው ጠል መውረዱ ሌሎች ሴቶች በር በሩካቤ የመውለዳቸው ምሳሌ።
#አስተውሉ:- ጠል ማለት ጤዛ ወይም የዝናብ ነጠብጣብ ማለት ነው።
ዳግመኛም እመቤታችን በነቢዩ በሳሙኤል የሽቱ ሙዳይ ትመሰላለች።
ነቢየ እግዚአብሔር ሳሙኤል አራቱን ሽቱ አምተኛ ዘይት አድርጎና አጣፍጦ በሽቱ ሙዳይ አስቀምጦ ካህናትን ነገሥታትን እየቀባ ይሾም ያነግሥ ነበር። እንደዚሁም ሁሉ ጌታችን ከእመቤታችን አራቱን ባሕርያተ ሥጋ አምተኛ ባሕርየ ነፍስን ነሥቶ ክህነትን መንግሥትን ገንዘብ አድርጓልና።
✍️ "የተመካባት የዕሤይ ስሥር የአሚናዳብም ሠረገላ የዳዊት መሰንቆ የሰሎሞን አክሊል አንቺ ነሽ። የታጠረች ተክል የተዘጋጅ የውሃ ጉድጓድ አንቺ ነሽ።"
እነዚህ ሁሉ የእመቤታችን ምሳሌዎቿ ናቸው።
#ማብራሪያ :- ከዘመነ አበው ጀምሮ እሥራኤላውያን የውሃ ጉድጓዳቸውን ጠላት መርዝ እንዳይነሰንስበት ለ50 ለ60 የማይነሣ ታላቅ ድንጋይ ይገጥሙት ነበር። እንደዚሁም ሁሉ በእመቤታችንም የሴቶች ልማድ በዘር መውለድ የለባትምና።
ተክላቸውንም ሌላ እንዳይደርስበት አውሬ እንዳይተነፍስበት በውስጥ በአፍኣ ያጥሩታል።
እንደዚሁም ሁሉ ከእመቤታችን የሐልዮ (የማሰብ) ኃጢአት የለባትም አጋንንት ድል አይነሷትምና።
➢ ነገት (ጓሮ) የእመቤታችን ምሳሌ።
➢ ተክል የጌታ ምሳሌ።
➢ ቅጽር የረድኤተ እግዚአብሔር ምሳሌ።
♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️
#ክፍል_አምስት
💎 ምድራዊ መጠጥን አልጠጣሽም
"ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተፀነስኪ አላ በሩካቤ ዘበሕግ እም ሐና ወኢያቄም ተወለድኪ ... ፤ ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ።
ድንግል ሆይ አንገታቸውን እንደ ሚያገዝፉ እንደ ዕብራውያን ሴቶች ልጆች በዋዛ ያደግሽ አይደለም
በንጽሕና በቅድስና በቤተ መቅደስ ኖርሽ እንጂ።
(አሥራ ሁለት ዓመት በቤተ መቅደስ ውስጥ ኑራለች በኋላም ከቤተ መቅደስ አልተለየችም።)
ድንግል ሆይ ምድራዊን ኅብስትን የበላሽ አይደለሽም ከሰማየ ሰማያት የበሰለ ሰማያዊ ኅብስትን ነው እንጂ።
#ማብራሪያ :- አሁን በሰማይ ስንዴ ምጣድ ነሮ የሚጋገር ሁኖ አይደለም። በሰማያዊ መልአኩ እጅ ስለመጣ ከወደላይ መምጣቱን ሲያይ በአምላካዊ ሥራ (በግብር አምላካዊ) ከወደላይ መገኘቱን ሲያይ እንዲህ አለ እንጂ።
ድንግል ሆይ ምድራዊ መጠጥን የጠጣሽ አይደለሽም ከሰማየ ሰማያት የተቀዳ ሰማያዊ መጠጥን ነው እንጂ።
#ማብራሪያ :- አሁን በሰማይ ወይን ማድጋ አሳላፊ ነሮ አይደለም። በሰማያዊ መልአኩ እጅ ስለመጣ ከወደላይ መምጣቱን ሲያይ በአምላካዊ ሥራ (በግብር አምላካዊ) ከወደላይ መገኘቱን ሲያይ እንዲህ አለ እንጂ።
#አንድም :- ምድራዊ ኅብስትን አልበላሽም ምድራዊ መጠጥን አልጠጣሽም ማለት የወለድሽው በዘር በሩካቤ የተፈጠረ ዕሩቅ ብእሲ አይደለም።
ከሰማይ የበሰለ ኅብስት ከሰማይ የተቀዳ ወይን ነው እንጂ ማለት ደግሞ ፤ ከዓለም አስቀድሞ ከአብ አካል ዘእምአካል ባሕርይ ዘእምባሕርይ የተወለደ የባሕርይ አምላክ ነው እንጂ።
በነገረ ማርያም ታሪክ እንደ ተቀመጠው እመቤታችን ወደ ቤተ መቅደስ በሦስት አመቷ በስለት የሰጧት ወላጆቿ ይዘዋት ሲሄዱ ካህናቱ ምን እናበላታለን ብለው ተጨንቀው ሳለ መልአኩ ፋኑኤል ከእግዚአብሔር ታዞ ኅብስት ሰማያዊ ፣ ጽዋዓ ሰማያዊ መግቧት አርጓል። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሰማያዊ መብልና መጠጥ ነበር ምግቧ።
"ድንግል ሆይ ከአንቺ አስቀድሞ ከአንቺም በኋላ እንዳሉ ሴቶች እድፍ የምታውቂ አይደለሽም በንጽሕና በቅድስና ያጌጥሽ ነሽ እንጂ።"
#ማብራሪያ :- የሴቶች ልማድ (ልማደ አንስት ዘርዓ ወራዙት) የለባትምና።
"ድንግል ሆይ የሚያታልሉ ጎልማሶች ያረጋጉሽ አይደለሽም የሰማይ መላእክት ጎበኙሽ እንጂ። እንደ ተነገረ ካህናትና የካህናት አለቆች አመሰገኑሽ እንጂ።"
"ድንግል ሆይ ለዮሴፍ የታጨሽ ለመገናኘት አይደለም ንጹሕ ሁኖ ሊጠብቅሽ ነው እንጂ እንዲሁ ስለሆነ።"
"እርሱ ቅሉ እግዚአብሔር አብ ንጽሕናሽን ባየ ጊዜ ስሙ ገብርኤል የሚባል ብርሃናዊ መልአኩን ወደ አንቺ ላከ። መንፈስ ቅዱስ በላይሽ ይመጣል የልዑል ኃይልም ይጋርድሻል አለሽ።"
♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️
#ክፍል_ስድስት
💎 ምሥጢረ መለኮት
"መጽአ ኀቤኪ ቃል እንዘ ኢይትፈለጥ እምሕፅነ አቡሁ ... ፤ ከአባቱ አጠገብ ሳይለይ ቃል ወደ አንቺ መጣ ሳይወሰን ፀነሽው በላይ ሳይጎድል በታችም ሳይጨምር በማኅፀንሽ ተወሰነ።"
#ማብራሪያ :- ቃል ወደ አንቺ መጣ ማለት አምላክ ሰው ሆነ ሰው አምላክ ሆነ ማለት ነው። በላይ ሳይጎድል ማለት በጥንት አነዋዋሩ እንዳለ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ አንድነት ሳይለይ በታችም ሳይጨምር ማለት ሰው እንደሚፀነሰው ተፀነሰ።
#አንድም :- በላይ ሳይጎድል በታች ሳይጨምር ማለት በአንድነቱ ሕፀፅ ሳይኖርበት በታች ሳይጨምር ማለት ሥጋ ሁለተኛ ሳይሆነው። #አንድም :- በሦስትነቱ ሕፀፅ ሳይኖርበት ሥጋ አራተኛ ሳይሆነው።
"መጠንና መመርመር የሌለበት እሳተ መለኮት በሆድሽ አደረ። በምድራዊ እሳት እንመስለው ዘንድ አይገባም ለእሳትስ መጠን አለው ልክም አለው። መለኮት ግን ይህን ያህላል ይህንም ይመስላል ሊባል አይችልም።"
"ለመለኮት እንደ ፀሐይና ጨረቃ ክበብ እንደ ሰውም መጠን ያለው አይደለም ድንቅ ነው እንጂ የሰው ሕሊና የመላእክትም አእምሮ በማይደርስበት በአርያሙ የሚኖር ነው እንጂ። "
✍️ እንዳንቺ ያለ አላገኘም
ይ.ዲ :- ወደ ምሥራቅ ተመልከቱ
ይ.ካ :- በአማን ነጸረ እግዚአብሔር አብ እምሰማይ ... ፤ እግዚአብሔር አብ በሰማይ ሆኖ ምሥራቅንና ምዕራብን ሰሜንና ደቡብን ዳርቻወችን ሁሉ ተመለከተ። ተነፈሰ አሻተተ እንዳንቺ ያለ አላገኘም (በንጽሕና በቅድስና እንዳንቺ ያጌጠች)። የአንቺን መዓዛ ደም ግባትሽንም (መዓዛ ንጽሕናሽን መዓዛ ቅድስናሽን) ወደደ። የሚወደውን ልጁንም ወዳንቺ ሰደደ።
ይ.ዲ :- እናስተውል
ይ.ካ :- አንቺን የወደደ (ለልጁ ተዋሕዶ የመረጠሽ) እግዚአብሔር አብ ቅዱስ ነው። በማኅፀንሽ ያደረ ወልድ ዋሕድም ቅዱስ ነው። ያጸናሽ የጽድቅ መንፈስ ጰራቅሊጦስም ቅዱስ ነው።
♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️
#ክፍል_ሦስት
💎 በማን እንመስልሻለን
ይ.ካ :- "ኦ ድንግል ምልእተ ውዳሴ በመኑ በአምሳለ መኑ ናስተማስለኪ ... ፤ ምስጋናን የተመላሽ ድንግል ሆይ በማንና በማንስ ምሳሌ እንመስልሻለን።
#ማብራሪያ:- አሁን ለእመቤታችን ምሳሌ የሚታጣላት ሁኖ አይደለም። ነቢያት በብዙ ምሳሌ መስለዋት የለ። በመሶበ ወርቅ ፣ በተቋም ፣ በበትረ አሮን ፣ በማዕጠንተ ወርቅ ወዘተ።
በሰማይ በምድር ያሉ ፍጥረታት ለእመቤታችን ምሳሌዎቿ ሲሆኑ ለምን በምን እንመስልሻለን አለ ቢሉ ምሳሌው ዘየሐጽጽ (የማይተካከላት) ስለሆነ ነው።
#አንድም ምንም ያክል ብንመስልሽ ክብርሽን ገናንነትሽን ቅድስናሽን ልንገልጸው አንችልም።
#አንድም እንደ ክብርሽ እንደ ቅድስናሽ እንደ ድንግልናሽ የአምላክ እናት እንደ መሆንሽ ምሳሌ አይገኝልሽም ሲል ነው።
✍️ "አማኑኤል የማይተረጎም የሥጋን ልብስነት ከአንቺ የለበሳት መሥሪያ (የሸማኔ ጉድጓድ) አንቺ ነሽ። ዝሐውን ከአዳም ጥንተ ሥጋ አደረ። ማጉም ያንቺ ሥጋ ነው መወርወሪያውም ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። መሕኑም ከልዕልና የወረደ የልዑል እግዚአብሔር አምሳል ነው። ሠሪውም መንፈስ ቅዱስ ነው።"
#ማብራሪያ :- እመቤታችንን በሸማኔ ጉድጓድ ይመስላታል። በሸማኔ ጉድጓድ ድርና ማግ አንድ እንዲሆኑ በእርሷም መለኮትና ትስብእት አንድ ሁነውባታልና።
ዝሐውን ከአዳም ጥንተ ሥጋ አደረገ ማለቱ ጌታ ከእመቤታችን የነሣው ሥጋ ጥንተ አብሶ የሌለበት አዳም እንደ ተፈጠረ በገነት ሳለ ከመበደሉ አስቀድሞ እንዳለው ያለ ሥጋ መሆኑን ለማስረዳት ነው።
✍️ "ኦ ዝ መንክር ወዕፁብ ዝንቱ ነገር ... ፤ ወዮ ይህ ነገር ዕፁብ ድንቅ ነው የቀደሙ አባቶች ከሞት ወደ ሕይወት የተሸጋገሩብሽ ድልድይ ሆይ ከምድር እስከ ሰማይ የምትደርሽ መሰላል ሆይ የፍጥረት ሁሉ መጀመሪያ በአንቺ ታደሰ።"
#ማብራሪያ :- የቀደሙ አባቶች ከሞት ወደ ሕይወት የተሸጋገሩብሽ ድልድይ አንቺ ነሽ አለ ነቢያት አበው ከሞት ወደ ሕይወት ከሲዖል ወደ ገነት ከገሃነም ወደ መንግሥተ ሰማያት የተሸጋገሩ በእመቤታችን ነው። የመዳናቸው የመዳናችን ምክንያት እሷ ናትና።
ከምድር እስከ ሰማይ ደርሳ ያለች መሰላል አላት ፤ በሰላል የላዩ ወደ ታች እንዲ ወርድበት የታቹ ወደላይ እንዲ ወጣበት እርሷም ለቃል መውረድ ለሥጋ ማረግ ምክንያት ናትና።
የፍጥረት ሁሉ መጀመሪያ በአንቺ ታደሰ አለ ፤ አዳም ዕፀ በለስን በልቶ ብልየት (በኃጢአት ማርጀት) አግኝቶት ነበርና በእመቤታችን ምክንያት ስለ ታደሰ ወይም ልጅነቱ ክብሩ ስለተመለሰለት ነው።
#አንድም :- ቀውስጦስ የተባለ መልአክ የታደሰብሽ አንቺ ነሽ። ቀውስጦስ የተባለውን መልአክ በገምኑዲ ከደብረ ቀልሞን አማልዳለችና።
♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️
#ክፍል_አራት
💎 የአዳም ተስፋው አንቺ ነሽ
✍️ "አንቲ ውእቱ ተስፋሁ ለአዳም አመ ይሰደድ እም ገነት ፤ ከገነት በተሰደደ ጊዜ ነአዳም ተስፋው አንቺ ነሽ።"
#ማብራሪያ :- አዳም አትብላ የተባለውን ፅበ በለስን ከበላ በኋላ ከክብሩ ተዋረደ ከገነት ተሰደደ። በዚህን ጊዜ ንስሓ ቢገባ እግዚአብሔር ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅኽ ተወልጄ አድንኃለሁ አለው። አምስት ቀን ተኩሉም አምስት ሽህ አምስት መቶ ዘመን ነበር። ከገነት ከወጣ ጀምሮ በሲዖልም ሳለ በእርሷ ምክንያት ያድነኛል እያለ ለአምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን በተስፋ የጠበቃት እመቤታችን ናት። የአዳም የመዳኑ ተስፋም እውን የሆነው በእመቤታችን ነው። ስለዚህም ነው የአዳም የመዳኛ ተስፋው አንቺ ነሽ ያለ ሊቁ አባ ሕርያቆስ።
✍️" በግፍ የተገደለ የአቤል የውሃቱ አንቺ ነሽ።"
#ማብራሪያ :- አቤል በወንድሙ በቃኤል የተገደለ የመጀመሪያው ሟች ነው። ወንድሙ እንደሚገድለው እያወቀ ተከትሎት ሂዷልና የዋህ ይባላል። የአቤል የውሃቱ ማለቱ እመቤታችንን አቤል በየዋህነቱ ቢገደልም ወደ ሲዖል ነው የወረደ ከሲዖል የሚወጣው የየዋህነቱንም ዋጋ የሚያገኘው በእመቤታችን ምክንያት ስለሆነ የዋሃቱ ለአቤል አላት እመቤታችንን።
✍️ "ኂሩቱ ለሴት ... ፤ የሴት ቸርነት አንቺ ነሽ። የሄኖክም ሥራዎቹ አንቺ ነሽ። ከክፉ ጥፋት የዳነባት የኖኅ መርከብ የሴም ቡራኬው ዕድል ፈንታውም አንቺ ነሽ።"
#ማብራሪያ :- ኖኅ የጥፋት ውሃ በሆነ ጊዜ አስቀድሞ እንዲሰራት በታዘዘው መርከብ ድኗል። ይችም መርከብ ዓለሙ ሁሉ ከሲዖል ጥፋት የዳነባት ከሞት ወደ ሕይወት የተሸጋገረባት የእመቤታችን ምሳሌ ናት።
➢ኖኅ የጌታ ምሳሌ።
➢መርከቧ ባለ ሦስት ክፍል መሆኗ እመቤታችን የሥላሴ ማደሪያ ለመሆኗ ምሳሌ።
#አንድም እመቤታችን በንጽሐ ሥጋ በንጽሐ ነፍስ በንጽሐ ልቡና ንጽሕት ናትና።
➢ ከመርከቡ ውጭ ያሉትና በጥፋት ውሃ የጠፉት በእመቤታችን ቃልኪዳን ያላመኑና በኋላ በነፍሳቸው የሚፈረድባቸው።
➢ ከመርከቡ ውስጥ ያሉትና ከኖኅ ጋር ከጥፋት ውሃ የዳኑት በእመቤታችን ቃልኪዳን በማመን በነፍሳቸው ክብር ያገኙ የሚያገኙ የቅዱሳን የምእመናን ምሳሌ።
✍️ "የአብርሃም እንግድነት የይስሐቅም መዓዛ የያዕቆብም መሰላል አንቺ ነሽ። ዮሴፍንም የምታረጋጊው አንቺ ነሽ።"
#ማብራሪያ :- የአብርሃም እንግድነት አንቺ ነሽ አለ ፤ አባታችን አብርሃም በተመሳቀለ ጎዳና ቤቱን ሠርቶ ያለፈ ያገደመውን የወጣ የወረደውን በቤቱ በእንግድነት እየተቀበ ይመግብ ነበር። በዚህ ደግነቱም ሥላሴን በእንግድነት ለመቀበል በቃ እግዚአብሔር ወዳጄ ብሎ ጠርቶታል። እመቤታችን የአብርሃም ዋጋው አንቺ ነሽ መባሏ አብርሃም ከሲዖል የወጣው የደግነቱን ዋጋም የተቀበለው ጌታችን ከእመቤታችን ሰው ሁኖ ዓለምን ካዳነ ወዲህ ነውና። ለዚህም እመቤታችን ምክንያተ ድኂን ናት።
የይስሐቅ መዓዛው አንቺ ነሽ አለ ፤ እግዚአብሔር አብርሃምን ልጁን እንዲሠዋለት ባዘዘው ጊዜ ደጉ አብርሃምም ሦስት ቀን ተጉዞ ልጁን ለመሠዋት ተዘጋጅቶ ሲጨርስ በዕፀ ሳቤቅ የታሰረ በግ ከወደላይ ወረደለት። እርሱም ይህን ሠዋ ሲለኝ ነው ብሎ ልጁን ትቶ በጉን ሠውቷል።
ይኼውም ምሳሌ ነው
➢ አብርሃም የእግዚአብሔር አብ ምሳሌ (አንድያ ልጁን ለመሥዋዕትነት ወደ ዓለም በፈቃዱ የሰደደ አብ ነውና)።
➢ ይስሐቅ የምእመናን ምሳሌ።
➢ በግዕ የክርስቶስ ምሳሌ (በጉ ይስሐቅን ከሞት ከመሠዋት ታድጎ እንደ ተሠዋ ክርስቶስም ይህንን ዓለም ከሞት ታድጎ ስለ ዓለሙ ተሠውቷልና)።
➢ ዕፀ ሳቤቅ የእመቤታችን ምሳሌ (በጉ በዕፀ ሳቤቅ ወይም ሀረግ ታስሮ እንደ ወረደ ጌታም መሥዋዕት የሆነው ከእመቤታችን በነሣው ሥጋ ነውና)።
ሊቁ የይስሐቅ መዓዛው አንቺ ነሽ ማለቱ ለይስሐቅ ከሲዖል መውጣት ከሞት ወደ ሕይወት የመሸጋገር ምክንያት እመቤታችን በመሆኗ ነው።
ሙሉ የቅዳሴ ማርያም ማብራሪያ
#ክፍል_አንድ
✍️ ልቦናየ በጎ ነገርን አወጣ (ጎሥዐ ልብየ)
#መግቢያ
የእመቤታችን ቅዳሴ (ቅዳሴ ማርያም) በቤተክርስቲያናችን ካሉ 14ቱ ቅዳሴያት አንዱ ሲሆን የተጻፈው ግን ከሁሉም መጨረሻ ወይም 14ኛ ሁኖ ነው።
የቅዳሴ ማርያም ደራሲ የብህንሳው ኤጲስ ቆጶስ አባ ሕርያቆስ ሲሆን ለእርሱም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በቅዳሴ ጊዜ ገልጻለት ሰተት አድርጎ ደርሶታል።
አባ ሕርያቆስ በብሕንሳ በሺዎች መነኮሳት በአባትነት ቢሾምም ብዙም ያልተማረ ነገር ግን ግብረ ገብና የምግባር አባት ነበር። ባለመማሩም ሌሎቹ ይነቅፉት ነበር። የሚነቅፉት እሱን ያዋረዱ መስሏቸው በእመቤታችን ዓመታዊ በዓል ቅዳሴ በግድ አስገብተው ከሊቃውንት ቅዳሴ አስቸጋሪውን አውጥተው ሰጡት።
እርሱ ግን ምኞቱ እንደ ቅዱስ ኤፍሬም (የውዳሴ ማርያም ደራሲ) ስለነበረ እመቤታችን ገልጻለት ይህንን ቅዳሴዋን በዕለቱ ቀድሷል። በኋላም ይህንን እንግዳ ድርሰት ቅዳሴ ማርያም ጽፈው ደጉሰው
✔️ ከባህር ጣሉት ቀለሙ ሳይጠፋ ወረቀቱ ሳይበሰብስ ወጣ
✔️ ከእሳት ከተቱት ሳይቃጠል በደኅና ወጣ
✔️ ከድውይ ላይ አስቀመጡት ድውይ ፈወሰ የሞተም አስነሳ።
ከዚህም በኋላ ከ14ቱ ቅዳሴ አብሮ ተቆጠረ።
ይህንን ቅዳሴ ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ በዜማ ደርሶታል ከሌሎቹ ቅዳሴዎችም ይልቅ ዜማ በቅዳሴ ማርያም ይበዛል።
በኋላ ዘመንም አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባም በቃሉ ሲግመው ከምድር ስንዝር ከፍ ይል ነበር። ዛሬም በዋልድባ ቅዳሴ ማርያም ሳይጸልይ የሚውል አባት የለም።
እመቤታችን ለአንድ ባሕታዊ እንደ ነገረችው ልጇ ዳዊትን አቡነ ዘበሰማያትን ሲደግሙለት እንዲወድ እሷም ቅዳሴዋንና ውዳሴዋን ሲጸልዩላት ትወዳለች። ለሚጸልዩትም የቅዱስ ኤፍሬምንና የአባ ሕርያቆስን በረከት እንደምታሳድርባቸውና እነርሱ ከገቡበት እንደምታስገባቸው ቃል ኪዳን ሰጥታቸዋለችና።
ካህኑ ቅዳሴ ማርያምን ሲጀምር እንዲህ ይላል
"አኰቴተ ቍርባን ዘእግዝእትነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ ዘደረሰ ላቲ በመንፈስ ቅዱስ አባ ሕርያቆስ ኤጲስ ቆጶስ ዘሀገረ ብሕንሳ ... ፤ የብሕንሳ ኤጲስቆጶስ አባ ሕርያቆስ አምላክን ስለ ወለደች ስለ እመቤታችን ድንግል ማርያም በመንፈስ ቅዱስ የደረሰው የቍርባን ምስጋና ይህ ነው። ልመናዋና በረከትዋ ከኛ ጋራ ይኑር ለዘላለሙ አሜን።
ይ.ካ :- #ጐሥዐ_ልብየ_ቃለ_ሠናየ (3 ጊዜ)
አባቷ ዳዊት ለንጉሠ ሰማይ ወምድር ምስጋና ላቅርብ ባለ ጊዜ ፡ "ጐሥዐ ልብየ" ብሎ አምስግኖ ነበርና እርሱም ለንግሥተ ሰማይ ወምድር ለእመቤታችን ምስጋና ላቅርብ ባለ ጊዜ "ጐሥዐ ልብየ" አለ።
#አንድም ለዳዊት የገለጸ መንፈስ ቅዱስ ገልጾለት "ጐሥዐ ልብየ" አለ።
➢ 3 ጊዜ "ጐሥዐ" አለ
✔️ በንጽሐ ሥጋ ፣ በንጽሐ ነፍስ ፣ በንጽሐ ልቡና አምሳል። #አንድም
✔️ እመቤታችን ወጣንያን ፣ ማዕከላውያን ፣ ፍጹማን የሚያመሰግኗት ስለሆነ። #አንድም
✔️ በዚህ ዓለም ፣ በገነት ፣ በመንግሥተ ሰማያ ያሉ ጻድቃን የሚያመሰግኗት ስለሆነ። #አንድም
✔️ ሊቃውንት በምሥጢረ ሥላሴ መጀመር ልማዳቸው ነው። ሦስት መሆኑ የሦስትነት ቃሉ አለመለወጡ የአንድነት ምሳሌ ነው።
✍️" ... እኔም የማርያምን ቅዳሴ እናገራለሁ በማብዛት አይደለም በማሳነስ ነው እንጂ።"
#ማብራሪያ :- አሁን የእመቤታችን ቅዳሴ ቢበዛ እንጂ አያንስም። በማሳነስ ነው ማለቱ እመቤታችን ከፍጡራን ሁሉ በላይ ከፈጣሪ በታች ስትሆን ይህ ምስጋና እንደ ቅድስናዋ እንደ ንጽሕናዋ እንደ ክብሯ ብዛትና መጠን አይደለም። የእርሷ ምስጋና ሰማይና ምድር ብራና (ወረቀት) ፣ አብሕርት (ባህሮች) ቀለም ፣ ዕጽዋት ብዕር ፣ አዕባን መዳመጫ ፣ መላእክትና ደቂቀ አዳም ቀለም ቢሆኑ ባልተፈጸመ ነበር ማለት ነው።
"ጽሒፈ ውዳሴኪ እም ኢሐልቀ ፡ ሶበ ኮነ ጥቀ ፡ ዝናመ ክረምት ቀለመ ፡ ወሰማይ ረቀ። ድንግል ማርያም ሆይ ሰማይ ብራና የክረምት ዝናምም ቀለም ቢሆን የምስጋናሽን ውዳሴ በመጻፍ ባልተፈጸመ ነበር።" እንዳለ የመልክዓ ማርያም ደራሲ።
#አንድም የቅዳሴዋን ምስጋና ንባቡን በማብዛት ምሥጢሩን በማሳነስ አይደለም። ምሥጢሩን በማብዛት ንባቡን በማሳነስ ነው እንጂ።
✍️ " እኔም የድንግልን ውዳሴ እናገራለሁ። መዘንጋት ባለበት ቃል በማስረዘም አይደለም በማሳጠር ነው እንጂ። እኔም የድንግልን ገናንነቷት እናገራለሁ።"
#ማብራሪያ:- ንባቡን በማስረዘም ምሥጢሩን በማሳጠር አይደለም። ንባቡን በማሳጠር ምሥጢሩን በማስረዘም ነው እንጂ።
✍️"ወእቀውም ዮም በትሕትና ወበፍቅር ... ፤ ዛሬ በዚህች ቀን በፍቅርና በትሕትና ግሩም በሚሆን በዚህ ምሥጢር ፊት እቆማለሁ። በዚህም ማዕድና ቍርባን ፊት።
መንፈሳቸውን ያረከሱ ሰዎች (በኃጢአት በክህደት ያሉ ሰዎች) ሊቀምሱ የማይቻላቸው በእውነት ቍርባን ነው።
"አሁንም ሳይገባው ይህን ኅብስት የበላ ይህንንም ጽዋ የጠጣ ሁሉ የጌታችን ሥጋውና ደሙ ስለሆነ ዕዳ አለበት። አሁንም ሰው ራሱን መርምሮና አንጽቶ ከዚህ ኅብስት ይብላ ከዚህም ጽዋ ይጠጣ። ሳይገባው የጌታችን ሥጋም እንደሆነ ሳያውቅ ሰውነቱንም ሳያነጻ የሚበላና የሚጠጣ ለራሱ ፍርዱንና መቅሠፍቱን ይበላል ይጠጣልም።" እንዳለ 1ቆሮ 11÷27-29
በበግ በጊደርና በላን ደም እንደ ነበረው እንደ ቀደሙት አባቶች መሥዋዕት (የኦሪቱ) አይደለም እሳት ነው እንጂ።
ፈቃዱን ለሚሰሩ ልቦናቸውን ላቀኑ ሰዎች የሚያድን እሳት ነው ስሙን ለሚክዱ ለአመጸኞች ሰዎች የሚባላ እሳት ነው።
ማርያም ሆይ ስለዚህ እንደወድሻለን ከፍ ከፍም እናደርግሻለን እውነተኛ የጽድቅ መብልንና እውነተኛ የጽድቅ መጠጥን ወልደሽልናልና። ..."
♦️🔹♦️🔹♦️🔹♦️
#ክፍል_ሁለት
💎 እንዳንቺ ያለ አላገኘም
ይ.ዲ :- በእንተ ብፅዕት
ይ.ካ :- ጸሎተ ቡራኬ (በክፍል ሃያ ሁለት ተገልጿል)
ይ.ዲ :- መሐሮሙ እግዚኦ
ይ.ካ :- "ለእሉኒ ወለኵሎሙ ... ፤ አማላጅቱ ሆይ እሉህንም ሁሉ ከልጅሽ ዘንድ አማልጅ። በዚህ እነዚህን ይጠራል
✔️ የጳጳሳት የሊቃነ ጳጳሳት የኢጲስ ቆጶሳትንም ሁሉ ነፍስ ረፍተ ነፍስ ሰጥተሽ አሳርፊ
✔️ የቀሳውስት የዲያቆናትን ነፍስ
✔️ የነገሥታቱን የመኳንንቱን የመሳፍንቱን
✔️ የወራዙትን የደናግልን የመነኮሳትን
✔️ ባለጠጋውንና ደሃውን ታላቁንና ታናሹን
✔️ ባልቴቱንና አባት እናት የሞቱበትን መጻተኛውንና ችግረኛውን
✔️ ከቤተክርስቲያን ማኅበር ተለይተው ያረፉትን የክርስቲያንንም ወገኖች
✔️ ይልቁንም በዚች ቦታ ስለሞቱ አንቺ ስለነርሱ አብዝተሽ አማልጂ ነፍሳቸውን ረፍተ ነፍስ ሰጥቶ ያሳርፍ ዘንድ።
✔️ የሰማዕታት የጻድቃን የመላእክት ስማቸው በተጠራበት ቤተክርስቲያናቸው በታነጸበት ታቦታቸው በተቀረጸበት ሥዕላቸው በተሣለበት በዚህ ሁሉ ያረፉት ረፍተ ነፍስ ሰጥተሽ አሳርፊ።
በቦታው ሁሉ አንቺ ርስት ነሽ ስምሽም በእግዚአብሔር ዘንድ የሠለጠነ ነው።
ይ.ዲ :- የተቀመጣችሁ ተነሡ
ይ.ካ :- እግዚአብሔርን በመፍራት እንነሣ። ምስጋናን የተመላች እርስዋን ከፍ ከፍ እናደርጋት ዘንድ እንዲህም እያልን እናመሰግናት ዘንድ ጸጋን የተመላሽ ሆይ የደስታ መፍሰሻ ሆይ ዓይኖቻቸው ብዙዎች ከሚሆኑ ከኪሩቤል ክንፎቻቸው ስድስት ከሚሆኑ ከሱራፌልም ይልቅ የሚበልጥ የመልክ ግርማ አለሽ። (በሥላሴ ዘንድ የባለመዋልነት ግርማ ፣ በምእመናን የመወደድ ግርማ ፣ በአይሁድ በአሕዛብ በአጋንንት ዘንድ የመፈራት ግርማ አለሽ)።
