TIKVAH-ETHIOPIA
Buy Ads: https://telega.io/c/Ethiopian_ICS0 ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel TIKVAH-ETHIOPIA
Channel TIKVAH-ETHIOPIA (@ethiopian_ics0) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 13 702 subscribers, ranking 3 918 in the Politics category and 2 507 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 13 702 subscribers.
According to the latest data from 09 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -181 over the last 30 days and by -7 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 5.23%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 2.56% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 718 views. Within the first day, a publication typically gains 351 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 2.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“Buy Ads:
https://telega.io/c/Ethiopian_ICS0
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 10 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Politics category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 10 September | 0 | |||
| 09 September | +2 | |||
| 08 September | +2 | |||
| 07 September | +1 | |||
| 06 September | 0 | |||
| 05 September | 0 | |||
| 04 September | +2 | |||
| 03 September | 0 | |||
| 02 September | 0 | |||
| 01 September | 0 |
| 2 | እንኳን ለአዲሱ ዓመት አደረሳችሁ፣ አደረሰን!!
ዘመን ከፈጣሪ ለሰው የተሰጠ የመሥሪያ መጽሐፍ ነው። ይህ የመሥሪያ መጽሐፍ ለእያንዳንዱ ሰው የተሰጡ የተወሰኑ ገጾች አሉት። የመጨረሻው ገጽ ተጠናቅቆ የማጠቃለያው ሽፋን እስኪከደን ድረስ የፈለግነውን የመጻፍ መብት በእጃችን ነው። አንዳንዶች ዓለምን የቀየሩ ሐሳቦችንና ሥራዎችን፤ ሌሎች ታሪክን የቀየሩ ዕሳቤዎችንና ቴክኖሎጂዎችን ጽፈውበታል። በተቃራኒው ዓለምን ያወደሙ፤ ሕዝብ የከፋፈሉና የጨረሱ፤ ተፈጥሮን ያዛቡ፤ ክፋትንና ጭካኔን ያስተማሩ ሐሳቦችንና ተግባራትን የጻፉበትም ጥቂት አይደሉም። ስንፍናንና ድንዛዜን፣ ዕንቅልፍንና ሐኬትን የጻፉም አሉ።
ኢትዮጵያውያን በዚህ የዘመን መጽሐፍ ውስጥ ምን እየጻፍን ነበር? አሁንስ ምን እየጻፍን ነው? ወደፊትስ ምን ለመጻፍ እናስባለን? ከኋላችን ያሰናበትነው አሮጌ ዓመት እና ከፊታችን የምንቀበለው አዲስ ዓመት እነዚህን ጥያቄዎች እንድንመልስ ያስገድዱናል። ዓለምን ያስደነቁ የንግድ፣ የግብርና፣ የሥነ ሕንጻ፣ የዘመን አቆጣጠር፣ የሥነ ከዋክብት፣ ሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር፣ ሥነ ሥዕልና ሥነ ዜማ፣ ሃይማኖትና ፍልስፍና - በዘመን መጽሐፋችን ውስጥ የጻፍንባቸው የዘመን ገጾች አሉን።
በተቃራኒው ረሃብና ቸነፈር፣ ጦርነትና እልቂት፣ መከፋፈልና መለያየት፣ ማነስና መድከም፣ የጻፍንባቸው የዘመን ገጾችም አሉን።
የትናንቱ ዘመን ጠባሳውንም ዐሻራውንም፣ ዕዳውን ምንዳውንም ሰጥቶን አልፏል። አሁን ወሳኙ ነገር በቀሩን ዘመናት ምን ቁም ነገር እንሰራለን? የሚለው ነው።
ኢትዮጵያውያን ዛሬ ለትውልድ የሚተርፍ አስደናቂ ታሪኮችን እየሰራን ነው። አረንጓዴ ኢኮኖሚን በአረንጓዴ ዐሻራ፤ ቱሪዝምን በገበታ ፕሮጀክቶች፤ የምግብ ሉዓላዊነትን በበጋ ስንዴና በሌማት ትሩፋት፤ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪን በኢትዮጵያ ታምርት እየገነባንና እያጸናን ነው። የኢነርጂ ዐቅማችንን በተፈጥሮ ጋዝ ፕሮጀክትና ኑክሌር ቴክኖሎጂ ለማሳደግ፤ የአፈር ማዳበሪያ ግብአቶችን በሀገር ውስጥ ለመሸፈን፤ የአየር መንገድ አድማሳችንን በግዙፉ የቢሾፍቱ አየር ማረፊያ ፕሮጀክት ለማስፋት፣ ነገን አስበን ዛሬ እየተጋን ነው።
የሕዳሴ ግድብን ፍጻሜ፤ የመስኖ ግድቦችን ፍሬ፤ የሩዝ ምርትን ከፍታ፤ የፍራፍሬ ምርትን ተአምር፤ የወጪ ንግድን ጭማሬ፤ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያችንን ውጤት፤ በአፍሪካ የፈጠርነውን የኢነርጂ ትሥሥር፤ ዲጂታል 2030ን ስኬት፤ የኮሪደር ልማታችን የኢትዮጵያን ሀብትና ውበት መግለጥ፤ የዘመን መጽሐፋችን እየመዘገበ ነው። የወንዝ ዳርቻ ልማታችን አፈራችንንም፣ ከተማችንንም፣ ጤናችንንም፣ ውኃችንንም እየጠበቀ መሆኑን፤ መድኃኒት የማምረት ደረጃና ዐቅማችም እያደገ መሄዱን፤ የማዕድን ፍለጋችን፣ ምርታችንና ሽያጫችን የዘመናት ስብራትን እየጠገነ መምጣቱን፤ የባሕር በር አጀንዳችን ዓለም አቀፋዊ ተቀባይነት ማግኘቱን፤ የኢትዮጵያ የተጽዕኖ አድማስ መስፋቱን - የዚህ ዘመን የመጽሐፉ ገጾች እያሠፈሩ ናቸው።
እነሆ የዘመን መጽሐፋችንን የ2019 አዲስ ምእራፍ የምንጀምረው ሀገራዊ ምክራችንን በስኬት አጠናቅቀን ነው። ይሄንን ምክክር ለዘመናት ኢትዮጵያውያን ይጠይቁት ነበር። ችግራችንን በጦርነት ከመፍታት ይልቅ ለምን አንመካከርም ይሉ ነበር። በየብሔረሰቡ ያለውን የመነጋገርና የመመካከር ባህል ለምን ወደ ፖለቲካው አናመጣውም ይሉ ነበር። የዘመን መጽሐፍ ገጾችን ስናነባቸው ይሄን ጥያቄ ያቀረቡ ወገኖች ብዙ ዋጋ መክፈላቸውን ያስነብቡናል። እኛ ግን ሐሳቡን አመንንበት፤ አምነንም ተቀበልነው፤ ተቀብለንም ተገበርነው። ማመናችንና መተግበራችን ትክክል እንደሆነ የሚያሳዩ ውጤቶችንም ምክክሩ አስገኘልን።
የመጀመሪያው ውጤት “የጠላት ሟርት መክሸፉ” ነው። ኢትዮጵያውያን ሊመካከሩ አይችሉም፤ ቢመካከሩን ወደ ተቀራቢ ሐሳብ አይደርሱም የሚለውን ሟርት አክሽፈነዋል። ለመመካከር እንደምናቅድ፤ አቅደን እንደምንጀምር፤ ጀምረን እንደምንጨርስ በሀገራዊ ምክክር አስመስክረናል። ብዝሃ ሐሳቦቻችን በሀገር ጉዳይ የጋራ አቋም ከመያዝ እንደማያግዱን በተግባር አይተናል።
ሁለተኛው “ባህሉ” ነው። ከፀሐይ በታች ባሉ ጉዳዮች የመወያየት፣ የመነጋገርና የመግባባት ፖቲካዊ ባህልን ማዳበራችን ታላቅ ስኬት ነው። ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ የልሂቃን ጉባኤ አድርጋ ይሆናል። ለሕዝቡ “እኛ እናውቅልሃለን” የሚሉ ልሂቃን፥ የሀገርን ችግሮች በመፍታት ስም የሥልጣን ክፍፍል የሚያደርጉባቸው ጉባኤዎች ተካሂደዋል። የዘመናት ጥያቄዎቻችን ግን መፍትሄ አላገኙም። ከልሂቃን ድርድር ይልቅ ሕዝባችን ራሱ መክሮ ራሱ መፍትሔ የሚያመለክትበት ሀገራዊ ምክክር ማድረግ ያስፈለገን በዚህ ምክንያት ነው። በዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ታሪክ በደማቅ ብዕር የሚጻፍ ታላቅ ጉባኤም ተናወነ።
በተካሄደው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ሕዝባችንን ዋና ባለቤትና ዋና ተዋናይ በማድረግ ተጠናቅቋል። ሁሉንም አካባቢዎች፤ ሁሉንም ብሔረሰቦች፤ ሁሉንም እምነቶች፤ አብዛኞቹን የፖለቲካ አመለካከቶች፤ ሀገር ቤቱንና ዳያስፖራውን፤ ገበሬውን፣ አርብቶ አደሩንና ወዛደሩን፤ የሥራ ኃላፊዎችንና መደበኛ ዜጎችን፤ የተማሩትንና ያልተማሩትን፤ ወንዶችንና ሴቶችን፤ በዚህ መጠን በአንድ ጉባኤ በአንድ ቦታ ማገናኘት አዲስ ታሪካችን ነው። በዘመን መጽሐፍም በወርቅ ቀለም ተጽፏል።
ሦስተኛው “ውጤቱ” ነው። በአጀንዳዎች ላይ ተግባብተናል። እነዚህ ስምምነት የተደረሰባቸው ጉዳዮች አንድ በአንድ ወደ ተግባር የሚወሰዱ ናቸው። ባህል የሚሆኑ አሉ። ሥርዓት የሚሆኑ አሉ። አሠራር ተደርገው የሚዘረጉ አሉ። ዕሳቤ ሆነው የምንመራባቸው አሉ። ዐዋጅ ሆነው የሚወጡ አሉ። የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ሐሳቦች የሚሆኑ አሉ። የመዋቅር ማሻሻያ የሚሆኑ አሉ። የነገዎችን ትእምርቶች፣ ሐውልቶች፣ ስያሜዎችና ሀገራዊ ብራንዶች የሚወስኑ አሉ። የትናንት ጉዟችንን የሚያርሙ፣ የሚያስታርቁና በተሻለ መግባባት የሚተረጉሙ አሉ።
መንግሥት ሁሉንም ሐሳቦች በተገቢው መንገድ ይጠቀምባቸዋል። የኢትዮጵያን የነገ ጉዞ በሚያቃና መልኩ ግብአት ሆነው ያገለግላሉ። በየጊዜው የሚጠቀሱ፣ የሚወሱና የሚነሡ ዕሳቤዎች ይሆናሉ። የኢትዮጵያ የዘመን መጽሐፍ ከሀገራዊ ምክክሩ በፊትና በኋላ የተለየ ነገር እንደሚጽፍ አምናለሁ። የመግባባት፣ የመስማማትና የመሰናኘት ጉዟችን እየሠመረ መሄዱን ይመዘግባል። የተግባባንባቸው ሐሳቦች መሬት ወርደው፣ ሥር ይዘው፣ ፍሬ ማፍራታቸውን ይተርካል።
ሀገራዊ ምክክራችን ገደ መልካም መሆኑን በምክክሩ ብቻ ሳይሆን በውጤቱም እያሳየ ነው። በአዲስ ዓመት ዋዜማ በመቶ የሚቆጠሩ ታራሚዎችን መንግሥት በምሕረት እንዲፈቱ አድርጓል። ይሄንን ያደረገበት ዓላማ ሁለት ነው። የመጀመሪያው የሀገራዊ ምክክሩን ውጤት በፍቅር፣ በይቅርታና በሰላም ለመጀመር ነው። ወደ ሀገራዊ ምክክር የመጡ ልዩ ልዩ ወገኖች በአንድም በሌላም ስሕተት የታሠሩ ወገኖች በይቅርታ እና በህግ አግባብ እንዲፈቱ ጠይቀው ነበር። መንግሥት ይሄንን ተቀብሎ በሂደቱ የተስማሙትን ፈትቷል። የምክክሩም ዓላማ ኢትዮጵያውያን በጉዳዮች ላይ እንዲነጋገሩ የተግባቡባቸው የመፍትሔ ሐሳቦች እንዲያቀርቡ ነው። መንግሥትም ለምክክሩ ሐሳቦች ትግበራ ያለውን ቁርጠኝነት በዚህ የይቅርታ ሂደት ማሳየት ጀምሯል። | 200 |
| 3 | No text... | 185 |
| 4 | የአሜሪካ እና ኢራን ግጭት ተባብሶ የነዳጅ ዋጋ 100 ዶላር ደረሰ።
የአሜሪካና ኢራን ግጭት መባባሱን ተከትሎ እንዲሁም ኢራን የምትደግፋቸው የየመን ሁቲ አማጽያን በሳዑዲ አረቢያና በቀይ ባሕር አካባቢ ጥቃቶችን መቀጠላቸውን ተከትሎ የነዳጅ ዓለም አቀፍ ዋጋ ከሐምሌ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በበርሜል 100 ዶላር አልፏል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) እንዳስታወቀው፣ የአሜሪካ ጦር ከኢራን አብዮታዊ ዘብ ጋር ትስስር ያላቸው አራት የነዳጅ ጫኝ መርከቦችን በኦማን ባሕረ ሰላጤ ዒላማ አድርጓል። አንድ ተጨማሪ መርከብም በኢራን ኻርግ ደሴት አቅራቢያ ጥቃት ደርሶበታል።
ማዕከላዊ ዕዙ ይህ እርምጃ ኢራን ባለፉት ሁለት ቀናት በአሜሪካ የጦር መርከቦች ላይ ሁለት ጊዜ ለፈጸመችው ጥቃት የተሰጠ የአጸፋ ምላሽ መሆኑን ገልጿል።
በተጨማሪም፣ ኢራን ለደረሰባት ጥቃት ምላሽ በዮርዳኖስ የሚገኝ የአሜሪካ የጦር ሰፈርን ዒላማ ማድረጓ ተገልጿል።
በሌላ በኩል፣ ኢራን የምትደግፋቸው የየመን ሁቲ አማጽያን በሳዑዲ አረቢያ የነዳጅ ማምረቻ ተቋማት ላይ ጥቃቶችን መቀጠላቸው ተዘግቧል።
ማክሰኞ በቀይ ባሕር ላይ የነዳጅ ጫኝ መርከቦችን ዒላማ ማድረጋቸው ተገልጿል።
በሐምሌ መጨረሻ የኢራንና አሜሪካ የተኩስ አቁም ስምምነት መክሸፉን ተከትሎ ብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ከፍተኛ ዋጋ መመዝገቡ ይታወሳል። አሁን ደግሞ ግጭቱ በድጋሚ መባባሱ በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ ላይ አዲስ የዋጋ ጭማሪ እያስከተለ ነው።
መረጃው የቢቢሲ ነው።
ጳጉሜን 4 ቀን 2018 ዓ/ም
@Ethiopian_ICS0💌 | 504 |
| 5 | No text... | 462 |
| 6 | "ወጣቶቻችን እና የሚቀጥለው ትውልድ በኢትዮጵያ ትልቁ ሀብት ውሃ ስለሆነ፣ የውሃ ልማቱን ይቀጥልበታል፣ ይገፋበታል ብለን እናስባለን " - ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ፕሮፌሰር እና የቀድሞ የህዳሴ ግድብ ተደራዳሪ ቡድን አባል ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ ኢትዮጵያ ውሃዋን ማኔጅ እያደረገች ለራሷ እና ለጎረቤቶቿ ልታበቃ የምትችልበትን ትልቅ አቅም እያሳየች መሆኑን ገልጸዋል።
ከትላንት በስቲያ የኮይሻ የኃይል ማመንጫ ግድብ ለመጎብኘት በተገኙበት ወቅት ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር አጭር ቆይታ አድርገዋል።
ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ ምን አሉ ?
"የኮይሻ ግድብ ማለት ኢትዮጵያ ውስጥ እየተሰሩ ካሉት ትልልቅ ግድቦች አንዱ ነው። ጊቤ ላይ አራተኛው ነው። እንግዲህ በኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ ግድቦች ለወደፊት ይሰራሉ።
እስካሁን ለተሰሩት ግድቦች፣ ይሄ አንዱ ማጎልበቻ ስለሆነ የኢትዮጵያን የመስራት አቅም፣ ሁለተኛ ኃይል የማመንጨት አቅም፣ ኢትዮጵያ ውሃዋን ማኔጅ እያደረገች ለራሷ እና ለጎረቤቶቿ ልታበቃ የምትችልበት ትልቅ አቅም ማሳያ ስለሆነ ዛሬ እዚህ በመገኘቴ በጣም ደስ ብሎኛል።
አሁን በጀመርነው፣ በያዝነው አጠቃቀም በጣም ጥሩ አጠቃቀም ነው። ህዳሴ ግድብ አሁን አልቆ ከተመረቀ ዓመት መሆኑ ነው፤ ከፍተኛ ኃይል እናመነጭበታለን። የኢትዮጵያን የኤሌክትሪክ ኃይል በ100 ፐርሰንት ጨምሮልናል።
ይሄ ደግሞ ሲጨመር፣ ምን ያህል እንደምጨምር እንገምታለን። ይሄ 1,800 ሜጋዋት ስለሆነ፣ ተጨማሪ ነው። እንግዲህ ይህንን የውሃ፣ በተለይም የግድብ ግንባታ በሌሎችም ጅረቶቻችን ላይ መቀጠል ያለብን ይመስለኛል።
ለኢትዮጵያ የግድብ ስራ እና የውሃ ልማት እነዚህ መጀመሪያዎች እና መነሻዎች፣ መማሪያዎች፣ አቅም መገንቢያዎች ናቸው። እንግዲህ ወጣቶቻችን እና የሚቀጥለው ትውልድ በኢትዮጵያ ትልቁ ሀብት ውሃ ስለሆነ፣ የውሃ ልማቱን ይቀጥልበታል፣ ይገፋበታል ብለን እናስባለን።
ይህ ለራሳችን ልማት ብቻ ሳይሆን፣ ጎረቤቶቻችንንም የምናስተሳስርበት ትልቁ አቅማችን ስለሆነ አሁን እስካሁን የተሰራው ስራ ብዙ አሳይቶናል፤ ኤሌክትሪክ እንሸጣለን ለሱዳን፣ ለጂቡቲ፣ ለኬንያ፣ ለታንዛኒያ፣ ለወደፊቱ ደግሞ ለሱማሊያ፣ ለሌሎችም የመሸጥ አቅማችን ከፍ እያለ ይሄዳል። በዚያው መጠን እነሱንም በጉርብትና እናስተሳስራቸዋለን ማለት ነው።
በዚያው መጠን የእኛ ከፍታ፣ የእኛ ተፅዕኖ በአካባቢያችን ከፍ ይላል፣ ዲፕሎማሲያችን ከፍ ይላል። እንግዲህ የውሃ ሀብታችን የሁሉም ነገር መሰረት ስለሆነ፣ አሁን ይሄ ትልቅ ማሳያ ነው፤ ለወደፊቱ እንቀጥልበታለን ብዬ ትልቅ እምነት አለኝ " ሲሉ ነው የገለጹት።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ኮይሻ
ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ/ም
@Ethiopian_ICS0💌 | 815 |
| 7 | የጓሮ " ሌብነቶች " እና ማስፈራራቶች
የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ በግብር ተቆጣጣሪዎቹና በግብር ከፋዮች መካከል የሚደረጉ ሕገወጥ አሠራሮችን፣ ምዝበራንና የሙስና ቅሬታዎችን ለመግታት በሚል በቅርቡ አዲስ የቴክኖሎጂ ሥርዓት መዘርጋቱ ይታወሳል፡፡
በተቆጣጣሪዎች ደረት ላይ የሚገጠመውና ድምፅ እንዲሁም ምሥል በቀጥታ (Live Stream) ወደ ማዕከል የሚያስተላልፈው " የሰወነት ላይ ካሜራ " (Body-Worn Camera) ከተተገበረ ወዲህ የግብር ሰብሳቢነት አቅም ማደጉና ቅሬታዎች መቀነሳቸው ተነግሯል፡፡
ነገር ግን በተዘረጋው የቴክኖሎጂ መረብ ውስጥ ሳይያያዙ የሚያመልጡና ነጋዴውን ምሬት ውስጥ የከተቱ አዳዲስ " የጓሮ " ሌብነቶችና የማስፈራራት ሥልቶች መበራከታቸውን የሚጠቁሙ ቅሬታዎች መኖራቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።
ከካሜራ ጀርባ የሚደረግ የማስፈራራት እና የደላላ ሴራ
በቦሌ መድኃኔዓለም አካባቢ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች የሚሸጡ አንድ ነጋዴ የደረሰባቸውን በደል ሲናገሩ " ተቆጣጣሪዎቹ ካሜራ ያለው ዩኒፎርም ለብሰው መጥተው 'ያለደረሰኝ ሸጠሃል" አሉኝ፡፡ አልሸጥኩም ብዬ ስሞግታቸው ፈጽሞ የማላውቀውን ሰው እንደ ምስክር ይዘው መጡ፡፡ ነገሩ ወደ ሕግ እንዲሄድ ሱቅ ዘግቼ ስወጣ፣ መስካሪ የተባለው ሰው ነጠል አድርጎ ወስዶኝ 'ገንዘብ ሰጥተህ ብትገላገል ይሻላል፣ እኔ ምስክርነቴን ከተናገርኩ ደግሞ እስር ቤት ነው የምትገባው" ሲል አስፈራራኝ " ብለዋል፡፡
ነጋዴው አያይዘውም " ካሜራው በምሥልና በድምፅ ይቀርፃል መባሉ እወነት አይመስለኝም፡፡ አልያም ደግሞ ካሜራው አጠገብ ሆነው በድፍረት የኮንትሮ ባንድ ወንጀለኛ አድርገው ሲያሸማቅቁኝ ካሜራው አይሠራም ማለት ነው " ሲሉ ምሬታቸውን ገልጸዋል፡፡
በገርጂ መብራት ኃይል አካባቢ የመለስተኛ ሬስቶራንት ባለቤት የሆኑ አንዲት ነጋዴ ደግሞ ተቆጣጣሪዎች ቴክኖሎጂውን እንዴት እንደሚያታልሉት ያስረዳሉ፡፡
" ካሜራው የተገጠመበትን ዩኒፎርም ለብሰው መጥተው ቁጥጥር ያደርጋሉ። ከዚያም 'ምሳ አዘጋጂልን እንመለሳለን' ብለው ይወጣሉ፡፡ ሲመለሱ ግን ዩኒፎርማቸውን አውልቀውና ካሜራውን አጥፍተው ነው፡፡ የፈለጉትን ያህል በልተውና ጠጥተው፣ ሌሎችንም ጋብዘው ሳይከፍሉ ይሄዳሉ፡፡ ይህ በተደጋጋሚ የሚደረግ በመሆኑ ሠርተን የምንከፍለው ለእነሱ ሆኗል " ሲሉ ተናግረዋል።
በካራሎ አካባቢ በሚገኙ የሥጋ ቤቶችና ምግብ ቤቶች መረጃ መሠረት ደግሞ ተቆጣጣሪዎች አስቀድመው ያለ ዩኒፎርም እንደ ተራ ደንበኛ በመሆን ይመጣሉ፡፡ የፈለጉትን ከተመገቡ በኋላ ክፍያ ፈጽመው ይወጣሉ፣ ወይም ደረሰኝ ሳይቀበሉ ይሄዳሉ፡፡
ከዚያም ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ዩኒፎርማቸውን ለብሰውና ካሜራቸውን አብረው በመመለስ " ቅድም ያለደረሰኝ አስተናግዳችሁናል፣ እጅ ከፍንጅ ይዘናችኋል " በሚል ከፍተኛ ቅጣት እንደሚያስፈራሩና ድራማዊ በሆነ መንገድ ጉቦ እንደሚጠይቁ ነጋዴዎች ገልጸዋል፡፡
በተመሳሳይ ሁኔታ በካራሎ የሚገኙ የሥጋ ቤት ባለቤቶች የግብር ከፋዮች ተቆጣጣሪዎች ያለ ክፍያ እንደሚመገቡና የታወቁ ነጋዴዎችን ስም እየጠሩ " እገሌንም ቢሆን ማንም አላዳነውም፣ ብትስማሙ ይሻላችኋል " በሚል ማስፈራሪያ፣ ገንዘብና ነፃ አገልግሎት እንደሚጠይቁ ተናግረዋል።
ወደ ማዕከል የማይደርሱት ቅሬታዎች
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ኃላፊ አቶ ሰውነት አየለ፣ የካሜራ ቴክኖሎጂው በኅዳር ወር 2018 ዓ.ም. በይፋ ሥራ ከጀመረ ወዲህ በይፋ የሚቀርቡ ቅሬታዎች በከፍተኛ መጠን ቀንሰዋል፣ የግብር ገቢም አድጓል፡፡
" ቴክኖሎጂው በተቆጣጣሪውና በግብር ከፋዩ መካከል የሚደረገውን የቃላት ልውውጥ በምሥልና በድምፅ በቅፅበት ወደ ማዕከል የሚያስተላልፍ ከመሆኑም በላይ፣ ጂፒኤስ (GPS) የተገጠመለት በመሆኑ ተቆጣጣሪው የት እንደሚገኝ በግልጽ ያሳያል " ሲሉ አቶ ሰወነት ያስረዳሉ።
አክለውም " ቀደም ሲል ይቀርቡ የነበሩት 'ያላግባብ ተቀጣን' ወይም 'ጉቦ ተጠየቅን' የሚሉ አቤቱታዎች አሁን ላይእምብዛም አሉ ማለት አይቻልም " ብለዋል፡፡
" ካሜራው 24 ሰዓት ሙሉ የሚቀርፅ በመሆኑ ቅሬታ የቀረበበት አጋጣሚ ሲኖር ማዕከል ላይ ተቀምጠው የሚከታተሉ ባለሙያዎች ቪዲዮውን በመመልከት ውሳኔ ይሰጣሉ " ውጤታማነቱን አብራርተዋል፡፡
ኃላፊው ቴክኖሎጂው ስኬታማ መሆኑን ቢገልጹም፣ ሪፖርተር ጋዜጣ በተለያዩ የከተማዋ የንግድ አካባቢዎችና ማዕከላት አደረኩት ባለው ቅኝት ግን የካሜራውን መኖር ተገንዝበው አሠራራቸውን የለወጡ፣ ነገር ግን ሕገወጥ ድርጊታቸውን ያላቆሙ ተቆጣጣሪዎች መኖራቸውን ያሳያል፡፡
አቶ ሰውነት ቅሬታ ያላቸው ግብር ከፋዮች በተቆጣጣሪዎቹ ዩኒፎርም ላይ ያለውን መለያ ኮድ (ID Code) በመያዝ በነፃ ስልክ መስመር 7075 ደውለው ማመልከት እንደሚችሉና ቪዲዮው ተፈትሾ ዕርምጃ እንደሚወሰድ ገልጻዋል።
ነጋዴዎች ግን አቤቱታ ለማቅረብ ወደኋላ የሚሉባቸው የራሳቸው ምክንያቶች እንዳሏቸው ይናገራሉ፡፡
ነጋዴዎች " ቅሬታ ብናቀርብ አቤቱታችን ተሰሚነት አያገኝም፣ ይልቁንም ተቆጣጣሪዎቹ በግላቸው ተናደውብን የባሰ ተደጋጋሚ ቅጣትና እንግልት ያመጡብናል " የሚል ሥጋት አለባቸው፡፡
በርካታ ነጋዴዎች ቅሬታቸውን የትና እንዴት ማቅረብ እንዳለባቸው፣ ወይም የ'7075' ነፃ ስልክ መስመር መኖሩን እንደማያውቁ ተናግረዋል።
ለጉቦና ላልተገባ አሠራር እጅ መስጠት በሕግ ፊት ተጠያቂ እንደሚያደርጋቸው የሚያውቁት ነጋዴዎች፣ ጉዳዩን ወደ ሕግ ከመውሰድ ይልቅ የንግድ ጊዜያቸውን ላለማጥፋት ሲሉ አላስፈለጊውን እንግልት በዝምታ ለማለፍ ይገደዳሉ፡፡
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የሰወነት ላይ ካሜራ (Body Camera) ቴክኖሎጂን መተግበሩ በግብር አሰባሰብ ሒደት ላይ ግልጽነትን ለመፍጠርና ቀጥተኛ ሌብነትን ለመቀነስ ትልቅ ዕርምጃ መሆኑ አይካድም፡፡
ነገር ግን የቴክኖሎጂው መኖር ብቻውን ሙስናን ሙሉ በሙሉ ሊያጠፋው አልቻለም። ተቆጣጣሪዎች ካሜራው የማይደርስባቸውን ዘዴዎች (ዩኒፎርም ማውለቅና ምስክር በማስፈራራት መጠቀም) በመጠቀም አዳዲስ የሕገወጥነት መንገዶችን መቀየሳቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ አመልክቷል።
ቢሮው የቴክኖሎጂ ቁጥጥሩን ብቻ ሳይሆን፣ ከካሜራ ውጪ የሚደረጉ የቅድመ ስለላና ድኅረ ቁጥጥር እንቅስቃሴዎችን የሚያጠኑ ድብቅ የክትትል ቡድኖችን ማሰማራት፣ ለነጋዴው የጥቆማ መስመሮች አስተማማኝ የደኅንነት ዋስትና መስጠትና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን አጠናክሮ መቀጠል ይጠበቅበታል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።
ጳጉሜን 1 ቀን 2018 ዓ/ም
@Ethiopian_ICS0💌 | 586 |
| 8 | No text... | 392 |
| 9 | "ወጣቶቻችን እና የሚቀጥለው ትውልድ በኢትዮጵያ ትልቁ ሀብት ውሃ ስለሆነ፣ የውሃ ልማቱን ይቀጥልበታል፣ ይገፋበታል ብለን እናስባለን " - ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ፕሮፌሰር እና የቀድሞ የህዳሴ ግድብ ተደራዳሪ ቡድን አባል ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ ኢትዮጵያ ውሃዋን ማኔጅ እያደረገች ለራሷ እና ለጎረቤቶቿ ልታበቃ የምትችልበትን ትልቅ አቅም እያሳየች መሆኑን ገልጸዋል።
ከትላንት በስቲያ የኮይሻ የኃይል ማመንጫ ግድብ ለመጎብኘት በተገኙበት ወቅት ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር አጭር ቆይታ አድርገዋል።
ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ ምን አሉ ?
"የኮይሻ ግድብ ማለት ኢትዮጵያ ውስጥ እየተሰሩ ካሉት ትልልቅ ግድቦች አንዱ ነው። ጊቤ ላይ አራተኛው ነው። እንግዲህ በኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ ግድቦች ለወደፊት ይሰራሉ።
እስካሁን ለተሰሩት ግድቦች፣ ይሄ አንዱ ማጎልበቻ ስለሆነ የኢትዮጵያን የመስራት አቅም፣ ሁለተኛ ኃይል የማመንጨት አቅም፣ ኢትዮጵያ ውሃዋን ማኔጅ እያደረገች ለራሷ እና ለጎረቤቶቿ ልታበቃ የምትችልበት ትልቅ አቅም ማሳያ ስለሆነ ዛሬ እዚህ በመገኘቴ በጣም ደስ ብሎኛል።
አሁን በጀመርነው፣ በያዝነው አጠቃቀም በጣም ጥሩ አጠቃቀም ነው። ህዳሴ ግድብ አሁን አልቆ ከተመረቀ ዓመት መሆኑ ነው፤ ከፍተኛ ኃይል እናመነጭበታለን። የኢትዮጵያን የኤሌክትሪክ ኃይል በ100 ፐርሰንት ጨምሮልናል።
ይሄ ደግሞ ሲጨመር፣ ምን ያህል እንደምጨምር እንገምታለን። ይሄ 1,800 ሜጋዋት ስለሆነ፣ ተጨማሪ ነው። እንግዲህ ይህንን የውሃ፣ በተለይም የግድብ ግንባታ በሌሎችም ጅረቶቻችን ላይ መቀጠል ያለብን ይመስለኛል።
ለኢትዮጵያ የግድብ ስራ እና የውሃ ልማት እነዚህ መጀመሪያዎች እና መነሻዎች፣ መማሪያዎች፣ አቅም መገንቢያዎች ናቸው። እንግዲህ ወጣቶቻችን እና የሚቀጥለው ትውልድ በኢትዮጵያ ትልቁ ሀብት ውሃ ስለሆነ፣ የውሃ ልማቱን ይቀጥልበታል፣ ይገፋበታል ብለን እናስባለን።
ይህ ለራሳችን ልማት ብቻ ሳይሆን፣ ጎረቤቶቻችንንም የምናስተሳስርበት ትልቁ አቅማችን ስለሆነ አሁን እስካሁን የተሰራው ስራ ብዙ አሳይቶናል፤ ኤሌክትሪክ እንሸጣለን ለሱዳን፣ ለጂቡቲ፣ ለኬንያ፣ ለታንዛኒያ፣ ለወደፊቱ ደግሞ ለሱማሊያ፣ ለሌሎችም የመሸጥ አቅማችን ከፍ እያለ ይሄዳል። በዚያው መጠን እነሱንም በጉርብትና እናስተሳስራቸዋለን ማለት ነው።
በዚያው መጠን የእኛ ከፍታ፣ የእኛ ተፅዕኖ በአካባቢያችን ከፍ ይላል፣ ዲፕሎማሲያችን ከፍ ይላል። እንግዲህ የውሃ ሀብታችን የሁሉም ነገር መሰረት ስለሆነ፣ አሁን ይሄ ትልቅ ማሳያ ነው፤ ለወደፊቱ እንቀጥልበታለን ብዬ ትልቅ እምነት አለኝ " ሲሉ ነው የገለጹት።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ኮይሻ
ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ/ም
@Ethiopian_ICS0💌 | 447 |
| 10 | No text... | 431 |
| 11 | አንጋፋዋ አርቲስት እልፍነሽ ቀኖ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች
አዲስ አበባ፣ጳጉሜን 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአፋን ኦሮሞ ሙዚቃዎቿ የምትታወቀው አንጋፋዋ አርቲስት እልፍነሽ ቀኖ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች።
ተወዳጇ አርቲስት እልፍነሽ ቀኖ ለበርካታ ዓመታት በተለይም በትግል ዘፈኖቿና በግጥሞቿ ለኦሮሞ ሕዝብ መብት ስትታገል ቆይታለች።
አርቲስቷ የጥበብን ኃይል በመጠቀም በሕዝባዊ ትግል ውስጥ ከፍተኛ ሚና በመጫወት በቀዳሚነት ከሚጠቀሱ ድምጻውያን መካከል ትጠቀሳለች።
የኦሮሞ ሴት የጀግንነትና ጽናት ምልክት የነበረችው እልፍነሽ ቀኖ የተወለደችው በምሥራቅ ወለጋ ዞን ነቀምቴ ከተማ አቅራቢያ በምትገኘው ሲቡ ጉቶ በተባለች ስፍራ ነው።
በ1969 ወደ ትግል በመቀላቀል ከዚያ ጊዜ ጀምሮ በሥነ-ጥበብ ሥራዎቿ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ስታበረክት ቆይታለች፡፡
ለበርካታ ዓመታት ከኖረችበት ኖርዌይ በቅርቡ ወደ ሀገሯ የተመለሰች ሲሆን፤ ባደረባት ሕመም በህክምና ስትረዳ ቆይታ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች፡፡
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በአንጋፋዋ አርቲስት ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ሀዘን ገልጿል፡፡
@Ethiopian_ICS0💌 | 532 |
| 12 | No text... | 444 |
| 13 | " አንዳንድ አስመጪዎች ቢሮው እየወሰደ ያለው እርምጃ ጊዜያዊ ነው፣ ከሆነ ጊዜ በኋላ ይቀራል የሚል እሳቤ አላቸው። ግን እርምጃው ይቀጥላል " - አቶ መሐመድ አብዱራህማን
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ፣ በክልል የመኪና አስመጪነት የንግድ ፈቃድ ያለው አካል አዲስ ያመጣውን መኪና መሸጥ ያለበት ፈቃድ ባወጣበት ክልል ላይ መሆኑን እና በመዲናዋ ውስጥ መነገድ ከፈለገ ደግሞ የክልል ንግድ ፈቃዱን በመጥቀስ የሽያጭ ደረሰኙንና የሽያጭ መመዝገቢያ ማሽኑን ከገቢዎች ቢሮ ጋር አያይዞ ወርሃዊ ተጨማሪ እሴት ታክሱንም ሆነ ዓመታዊ ግብሩን መክፈል እንዳለበት በቢሮው የሕግ ተገዢነት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ መሐመድ አብዱራህማን አስታወቀዋል።
ኃላፊው፤ " ያገለገሉ መኪናዎችን የሚሸጡ ኤጀንቶች በምንም ዓይነት ተአምር አዲስ መኪና ከአስመጪው ተቀብለው መሸጥ የለባቸውም " ብለዋል።
" እያንዳንዱ የኮሚሽን ኤጀንት መሸጫ ቦታው ውስጥ የተቀመጡትን መኪኖች የመኪና የባለቤትነት ማረጋገጫ ደብተር (ሊብሬ)፣ የታርጋ ቁጥር እና የተለያዩ ዝርዝር መረጃዎችን በአቅራቢያው ለሚገኝ የታክስ ባለስልጣኑ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ማሳወቅ አለበት " ሲሉ ገልጸዋል።
በተጨማሪም " ያገለገሉ መኪናዎች ወደ መሸጫ ቦታቸው ሲያስገቡ 24 ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ የማስመዝገብ ግዴታ የሚጥል ውልና ቃለ መሃላ ፈርመው ኤጀንቶች ወደ ስራ እንዲገቡ ተደርጓል " ብለዋል።
ከዚህ በፊት ያገለገሉ መኪናዎች ሲሸጡ ምንም ዓይነት ትራንዛክሽን አይመዘገብም ያሉት ኃላፊው አመታዊ ግብር ብቻ ሲከፍሉ መቆየታቸውን አስታውሰዋል።
" አሁን ላይ ቢሮ ከዚህ እያጣ ያለው ታክስ አሳሳቢ በመሆኑ የኮሚሽን ኤጀንቶች ያገለገሉ መኪኖችን ሲሸጡ በየጊዜው የመኪናዎች ትራንዛክሽን ግብር በሚከፍሉበት ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ማሳወቅ አለባቸው " ሲሉ ተናግረዋል።
" የኮሚሽን ኤጀንት ንግድ ፈቃድ ባላቸው ግለሰቦች መሸጫ ቦታ የሚሸጡት አዳዲስ መኪኖችን የሚያመጡ አስመጪዎች እነማን እንደሆኑ አይታወቁም፣ ግን አዳዲስ መኪኖቹ በከተማዋ ባሉ መሸጫ ቦታዎች ላይ ተደርድረው ይሸጣሉ። መኪኖቹ ባሉበት መሸጫ ያለው ፈቃድ ሲታይ የግለሰብ ወይም የኮሚሽን ኤጀንት ፈቃድ ነው " ብለዋል።
" መኪና አስመጪዎቹ መኪኖቻቸውን ሲሸጡ የመኪናውን ትክክለኛ የመሸጫ ዋጋ በደረሰኙ ላይ ሳይጽፉ አነስተኛ አድርገው በመጻፍ (Under-invoice) በሁለት እና በሦስት የባንክ ሂሳቦች ገቢ በማድረግ ሰፊ የግብር ስወራ ሲፈጽሙ እንደነበር ደርሰንበታል " ብለዋል።
" አንዳንዶቹ ደግሞ የመኪና አስመጪነት ንግድ ፈቃድ ይለጥፋሉ፣ ግን ከውጪ የሚያስመጡት ሁለት ወይም ሦስት አዲስ መኪና ነው። በመሸጫ ቦታው ግን ከ40 እስከ 60 አዳዲስ መኪኖች ይገኛሉ። እነዚህ መኪኖች ከየት መጡ ? ብለን ስናጣራ በተለያዩ ማንነታቸው በማይታወቁ የመኪና አስመጪዎች የመጡ ናቸው " ሲሉ ገልጸዋል።
" ያገለገሉ መኪኖች የሚሸጡ የኮሚሽን ኤጀንት ፈቃድ ያላቸው ግለሰቦችንም አግኝተናል። ማንነታቸው የማይታወቁ አስመጪዎችም በኮሚሽን ኤጀንት ፈቃድ ሲሰሩ ተገኝተዋል " ብለዋል።
" በየቀኑ ትልቅ የመኪና ትራንዛክሽኖች በመዲናዋ ይደረጋሉ፣ ግን አስመጪው በውል አይታወቅም። በዚህም በኮሚሽን ፈቃድ የስራ ዘርፍ የተሰማሩ ግለሰቦችን ፈቃዳቸውን ለጊዜው አግደናል " ሲሉ አሳውቀዋል።
" በኮሚሽን ኤጀንት ፈቃድ አላግባብ ተደርድረው ሲሸጡ የተገኙ አዳዲስ መኪኖች በቀጥታ ለአስመጪዎች እንዲመለሱ ተደርጓል " ሲሉም ገልጸዋል።
" አንዳንድ አስመጪዎች ቢሮው እየወሰደ ያለው እርምጃ ጊዜያዊ ነው፣ ከሆነ ጊዜ በኋላ ይቀራል የሚል እሳቤ አላቸው። በዚህም መኪኖቻቸውን በተለያዩ የግለሰብ ቦታዎች፣ መጋዘኖች አስቀምጠው እየሰሩ ነው። በእነዚህም ላይ እርምጃ እንወስዳለን " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
" ቢሮው የቁጥጥር ሰራተኞች አሉት፣ እነዚህ ሰራተኞች የበር ለበር ቁጥጥር፣ የመጋዘን ክትትል፣ የመኪና ላይ ቁጥጥር ያደርጋሉ፣ በዚህም በመኪኖች ተጭነው ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ሲጓጓዙ እየተገኙ ነው፣ በር ለበር ቁጥጥር ወቅትም የተደበቁ መኪኖች ተገኝተዋል " ብለዋል።
" አዲስ አበባ ውስጥ ምን ያህል የመኪና መጋዘኖች አሉ የሚለውን በቢሮ ደረጃ ለይተን ጨርሰናል " ያሉት ኃላፊው በመጋዘኖች ውስጥ ከሕግ አግባብ ውጪ የተቀመጡ መኪናዎች ካሉ ቢሮ አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቀዋል።
አክለውም " ማንኛውም የመኪና አስመጪ ያስመጣቸውን መኪኖች መሸጥ ያለበት በራሱ የመሸጫ ቦታ ላይ ብቻ በመሆኑ፣ በመንገዶች ላይም ሆነ በተለያየ የግለሰቦች ቤት ውስጥ ሲሸጥ የተገኘ አስመጪ ላይ ቢሮው ቀጣይነት ያለው ህጋዊ እርምጃ ይወስዳል " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ/ም
@Ethiopian_ICS0💌 | 514 |
| 14 | No text... | 383 |
| 15 | የአከራይና ተከራይ ውል እድሳት ጊዜ ተራዘመ።
የአከራይና ተከራይ ውል ምዝገባና እድሳት የመጨረሻ ጊዜ እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. መራዘሙን የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታውቋል።
ቢሮው የጊዜ ገደቡን ያራዘመው በተለያዩ ምክንያቶች ውላቸውን ማደስ ያልቻሉ አከራዮችና ተከራዮች በመኖራቸውና ከህብረተሰቡ በቀረቡ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች መሆኑን ገልጿል።
በመሆኑም ውላቸውን ያላደሱ ሁሉም አከራዮች እና ተከራዮች እስከ ጳጉሜ 5 ድረስ በክፍለ ከተሞች፣ በመሶብ አንድ ማዕከላትና ለአገልግሎቱ በተዘጋጁ ቦታዎች በመቅረብ ውላቸውን እንዲያድሱ ቢሮው ጥሪ አቅርቧል።
ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ/ም
@Ethiopian_ICS0💌 | 428 |
| 16 | No text... | 424 |
| 17 | ፎቶ ፦ የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በቲክቫህ ኢትዮጵያ ካሜራ
ይህ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያን ከታላቁ ህዳሴ ግድብ እና ከጊቤ 3 ቀጥሎ ሦስተኛው ግዙፍ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ባለቤት ያደርጋታል።
ኮይሻ
ነሐሴ 29 ቀን 2018 ዓ/ም
@Ethiopian_ICS0💌 | 542 |
| 18 | No text... | 440 |
| 19 | ⚠️ GRAPHIC CONTENT
ይህ ቪድዮ አስደንጋጭና የሚረብሽ ይዘት ስላለው በጥንቃቄ ይመልከቱ።
በአሜሪካ በመብረቅ ተመቶ በተአምር ከሞት የተረፈው ግለሰብ መነጋገሪያ ሆኗል።
በአሜሪካን፣ ኒውዮርክ ውስጥ " ስታተን አይላንድ " የተባለ አካባቢ ነዋሪ የሆነው ቶማስ ፋህሚ የተባለ ግለሰብ ከመኪናው 15 እስከ 20 ጫማ ርቀት ላይ ሳለ በድንገት በመብረቅ ተመቶ በተአምር ከሞት ተርፏል።
ግለሰቡ ከመኪናው ወርዶ ብዙም ሳይሄድ ነው በከባድ መብረቅ ተመትቶ ከሞት አፋፍ የተረፈው።
በአካባቢው በነበረው አስቸጋሪ የአየር ሁኔታ ውስጥ የተከሰተው ይህ አስደንጋጭ አደጋ ፋህሚ ላይ ከፍተኛ የሆነ የአካል እና የስነ-ልቦና ስቃይ ፈጥሯል።
በመብረቅ በተመታበት ወቅት በሁለቱም እግሮቹ ላይ ከባድ የመቃጠል ስሜት፣ የመደንዘዝ እና ከፍተኛ የህመም ስሜት እንደተሰማው ምስክርነቱን ሰጥቷል።
አደጋው ከተከሰተ በኋላ " በሌላ መብረቅ እመታለሁ " የሚል ከፍተኛ ስጋትና ፍርሃት አድሮበት እንደነበር ተናግሯል።
በአሁኑ ወቅት በህክምና ክትትል ከጉዳቱ በማገገም ላይ ያለው ቶማስ ፋህሚ፣ ይህ አስከፊ አደጋ በህይወት ላይ ያለውን አመለካከት ሙሉ በሙሉ እንደቀየረው ይናገራል።
አደጋው ህይወትን ማድነቅ፣ ንጹህ አየርን መተንፈስ፣ ለዕለት ተዕለት ኑሮ ትልቅ ዋጋን መስጠት እንዳለበት አስተምሮታል። እንዲሁም ህይወትን በጭንቀት ውስጥ ማሳለፍ እንደማይገባ ግንዛቤ እንደጨበጠበት ገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከ 'ስካይ ኒውስ' ነው ያገኘው።
ነሐሴ 29 ቀን 2018 ዓ/ም
@Ethiopian_ICS0💌 | 508 |
| 20 | #ችሎት
በሽብር ተግባር ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር በዋሉት የኢህአፓ አባላት ላይ የቀረበውን የተጨማሪ ምርመራ ጊዜ ጥያቄ ውድቅ በማድረግ፣ ፍርድ ቤቱ ተጠርጣሪዎቹ በዋስትና እንዲፈቱ ወሰነ።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አንደኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት፣ ዛሬ ነሐሴ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተጠርጣሪዎቹ እያንዳንዳቸው በ50 ሺህ ብር የገንዘብ ዋስትና ከእስር እንዲፈቱ ወስኗል።
ትላንት ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት፣ ፖሊስ የተሰጠው የ7 ቀናት "የመጨረሻ" የምርመራ ጊዜ መጠናቀቁ ቢገለጽም፣ የፎረንሲክ ውጤቶችን ለመጠበቅና ተጨማሪ ምስክሮችን ለመስማት በሚል የ14 ቀናት ተጨማሪ ጊዜ ጠይቆ እንደነበር ይታወሳል።
የተጠርጣሪዎቹ የአቶ ይስሃቅ ወልዳይ፣ የአቶ አበበ አካሉ እና የአቶ አበራ ንጉስ ጠበቃ በበኩላቸው፣ ተጠርጣሪዎቹ ላለፉት 31 ቀናት በቁጥጥር ስር መቆየታቸውንና ፖሊስ ምርመራውን ለማጠናቀቅ በቂ ጊዜ ነበረው በማለት የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ተከራክረዋል።
ፍርድ ቤቱም የሁለቱንም ወገን ክርክር ከመረመረ በኋላ፦
- ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ውድቅ አድርጓል።
- ተጠርጣሪዎቹ እያንዳንዳቸው በ50,000 (ሃምሳ ሺህ) ብር የገንዘብ ዋስትና እንዲፈቱ ትዕዛዝ መስጠቱን የተጠርጣሪዎቹ ጠበቃ አቶ ሰለሞን ገዛኸኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነሐሴ 29 ቀን 2018 ዓ/ም
@Ethiopian_ICS0💌 | 535 |
