en
Feedback
StMarkIS Community

StMarkIS Community

Open in Telegram

St. Mark Int. school offers its service in accordance with national and Finland's curriculum. 👉 Join for latest update and info #StMarkIntSchool ☎️ 0912-506470/71 Telegram Message - @StMarkSchool

Show more
1 694
Subscribers
+424 hours
+567 days
+7230 days
Posts Archive
ሚያዝያ 7/2018 ዓ.ም. ማስታወቂያ የ4ኛ ሩብ ዓመት ክፍያ ያልከፈላችሁ ወላጆች፣ ክፍያውን በአቢሲኒያ ባንክ ቁጥር 163193477 ብቻ ፈጽማችሁ ደረሰኝ በ0912-50-64-71 እንድትልኩ እናሳስባለን። መልካም የትንሳኤ በአል! ት/ቤቱ

ማስታወቂያ ለተማሪዎች! (Grades 1-8) ጥናታችሁን አጠናቃችኋል? እንግዲያውስ ምን ያህል እንደተዘጋጃችሁ እራሳችሁን ለመፈተሽ፣ አሁኑኑ ወደ ትምህርት ቤቱ ፖርታል (https://portal.saintmarkschool.net) በመግባት የተለቀቁትን ወርክሽቶች (Online Worksheets) እንድትሰሩ እናበረታታለን። መልካም የጥናት ጊዜ! ት/ቤቱ

ሚያዝያ 6/2018 ዓ.ም. ማስታወቂያ የ4ኛ ሩብ ዓመት ክፍያ ያልከፈላችሁ ወላጆች፣ ክፍያውን በአቢሲኒያ ባንክ ቁጥር 163193477 ብቻ ፈጽማችሁ ደረሰኝ በ0912-50-64-71 እንድትልኩ እናሳስባለን። መልካም የትንሳኤ በአል! ት/ቤቱ

photo content

ሚያዝያ 5/2018 ዓ.ም. ማስታወቂያ የ4ኛ ሩብ ዓመት ክፍያ ያልከፈላችሁ ወላጆች፣ ክፍያውን በአቢሲኒያ ባንክ ቁጥር 163193477 ብቻ ፈጽማችሁ ደረሰኝ በ0912-50-64-71 እንድትልኩ እናሳስባለን። ት/ቤቱ

🔤🔤🔤🔤🔤🔤🔤🔤 Dear parents and students, please log in to the portal to view the third-quarter final exam schedule - SET 2. https://portal.saintmarkschool.net

photo content

photo content

Δανιήλ: ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን — በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን አሰሮ ለሰይጣን — አጋዕዞ ለአዳም ሰላም — እምይእዜሰ ኮነ — ፍሥሐ ወሰላም!“እርሱ ተነሥቷል፤ እንደተናገረ እዚህ የለም!” (ማቴዎስ 28:6) ​ለሴንት ማርክ  ትምህርት ቤት ወላጆች፣ መምህራን፣ የሥራ ባልደረቦችና ተማሪዎች በሙሉ፤ ​ታላቁ የቤተክርስቲያን አባት ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ ትንሣኤው ብርሃን ሲናገር፦ “ሞት ተሸነፈ፣ ሲኦልም ተበረበረ፣ መቃብርም ባዶ ሆነ፤ ዛሬ ሰማይና ምድር በአንድነት ደስ ይላቸዋል!” እንዳለው፤ ሞትን ድል አድርጎ ለተነሳው ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል እንኳን በሰላም አደረሳችሁ። ​የትንሣኤ በዓል የጨለማው ኃይል ተሸንፎ የብርሃን ድል የታወጀበት፣ ተስፋ መቁረጥ ተወግዶ የሕይወት አዲስ ጅማሬ የተበሰረበት የታላቅ ደስታ ምሥጢር ነው ይህ መቃብርን የሰበረው መለኮታዊ ብርሃን በሴንት ማርክ ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ ለምንዘራው የእውቀትና የሥነ-ምግባር ዘር ሁሉ ኃይልና በረከት እንደሚሆን እናምናለን ​ለእናንተ ለተከበራችሁ ወላጆችና በትጋት ለምታገለግሉ መምህራን፤ የትንሣኤው ጌታ ለሥራችሁ ብርታትን፣ ለቤታችሁ ሰላምን፣ ለልባችሁ ደግሞ የማይጠፋ ደስታን እንዲሰጣችሁ ምኞታችን ነው ለተወዳጅ ተማሪዎቻችንም፤ የትንሣኤው ብርሃን አእምሯችሁን አብርቶ፣ በስንፍና ላይ ትጋትን፣ በጨለማ ላይ እውቀትን ድል እንድታደርጉ የትንሣኤው ኃይል ዘወትር ከእናንተ ጋር ይሁን ​በዚህ ቅዱስ ዕለት፣ ቅዱሳን አባቶቻችን እንዳስተማሩን፤ ከክፋት ወደ ደግነት፣ ከመከፋፈል ወደ አንድነት፣ እንዲሁም ከአለማወቅ ወደ ብርሃን የምንሸጋገርበት ይሁንልን የታመሙ የሚፈወሱበት፣ ያዘኑ የሚጽናኑበት እና በሁላችንም ልብ ውስጥ የትንሣኤው ፍቅር የሚነግስበት የበረከት ዘመን እንዲሆንልን እንመኛለን ። ​ትንሣኤው የሰላም፣ የፍቅርና የአንድነት ይሁንላችሁ!መልካም የትንሣኤ በዓል!ከሴንት ማርክ  ትምህርት ቤት  አስተዳደር Christ is risen from the dead — With great power and authority He has bound Satan — And set Adam free Peace — From this time forth There is — Joy and Peace!“He is not here; for He is risen, as He said!” (Matthew 28:6) ​To the esteemed parents, dedicated teachers, staff, and beloved students of St. Mar School; ​As the great Church Father St. John Chrysostom proclaimed regarding the light of the Resurrection: “Death is conquered, Hell is despoiled, and the grave is emptied; today, heaven and earth rejoice together!” In the spirit of this profound victory, we wish you a blessed Feast of the Resurrection of our Lord and Savior Jesus Christ. ​The Feast of the Resurrection is a sublime mystery of joy where the powers of darkness are defeated, despair is uprooted, and a new beginning of life is declared. We believe that this divine light, which shattered the tomb, will bring power and blessing to every seed of knowledge and moral virtue we sow within the gates of St. Mar School. ​For you, our honored parents and hardworking teachers, it is our prayer that the Risen Lord grants strength to your endeavors, peace to your homes, and an everlasting joy to your hearts. To our beloved students: may the light of the Resurrection illuminate your minds, empowering you to triumph over ignorance with knowledge and over sloth with diligence, through the eternal power of the Resurrection. ​On this holy day, as our Holy Fathers taught us, let us transition from malice to kindness, from division to unity, and from darkness to light. We pray for this to be a season of blessing where the sick are healed, the grieving find comfort, and the love of the Risen Christ reigns in all our hearts. ​May the Resurrection bring you Peace, Love, and Unity!Happy Easter!The Administration of St. Mar School

ቀዳም ሥዑር (የተሻረች ቅዳሜ) ተብላ የተጠራችው፣ በሕግ አምላክ ቅዳሜ እንዳትጾም የታዘዘው ሥርዓት ተሽሮ የጌታን መከራ በማሰብ በጾም የምትታለፍ ልዩ ዕለት በመሆኑ ሲሆን፤ ይህም ስያሜ የበዓልነት መሻርን ሳይሆን የሥርዓተ ጾምን መለወጥ ያመለክታል። ዕለቱ በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት "ቅዱስ ቅዳሜ" እና "ለምለም ቅዳሜ" እየተባለችም ትጠራለች፤ ይህም እግዚአብሔር በፍጥረት ማብቂያና በማዳን ሥራው ማጠናቀቂያ ላይ ያረፈባት በመሆኑና ካህናቱ የክርስቶስን ትንሣኤ ብስራት እንዲሁም የኃጢአት ውኃ መድረቁን (የነፍስ ነጻነትን) የሚያበስር ለምለም ቄጤማ ለምእመናን የሚያድሉባት ዕለት በመሆኗ ነው። ምእመናንም የአይሁድን የሾህ አክሊል በማሰብ ቄጤማውን በራሳቸው ላይ በማሰርና በጾም በመጸለይ የትንሣኤውን ብርሃን በጉጉት ይጠባበቁባታል።

photo content

ዓርብ :- ስቅለት የስቅለት ዓርብ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጅ ፍቅር ሲል በመስቀል ላይ ተሰቅሎ የዓለምን ኃጢአት የደመሰሰበትና በሞቱ ሞትን ድል አድርጎ ሕይወትን የሰጠበት ዕለት በመሆኑ "የድኅነት ቀን" ይባላል በዚህ ዕለት ጌታችን ሰባቱን አጽማደ መስቀል (ሰባቱን ቃላት) በመናገር፣ ለሰቃዮቹ ምሕረትን  እስከ መጨረሻው በመታገሥ ፍጹም ፍቅሩንና መለኮታዊ ትዕግሥቱን ገልጧል በአጠቃላይ ዕለቱ የሰው ልጅ ወደ ቀደመ ክብሩ የተመለሰበት ፣ የዲያብሎስ የባርነት ቀንበር የተሰበረበትና እኛም በመስቀሉ የተገኘውን ነጻነት እያሰብን በሃይማኖትና በምግባር እንድንጸና የሚያስተምር የታላቅ ውለታ ቀን ነው።

photo content

ዓርብ :- ስቅለት የስቅለት ዓርብ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጅ ፍቅር ሲል በመስቀል ላይ ተሰቅሎ የዓለምን ኃጢአት የደመሰሰበትና በሞቱ ሞትን ድል አድርጎ ሕይወትን የሰጠበት ዕለት በመሆኑ "የድኅነት ቀን" ይባላል በዚህ ዕለት ጌታችን ሰባቱን አጽማደ መስቀል (ሰባቱን ቃላት) በመናገር፣ ለሰቃዮቹ ምሕረትን  እስከ መጨረሻው በመታገሥ ፍጹም ፍቅሩንና መለኮታዊ ትዕግሥቱን ገልጧል በአጠቃላይ ዕለቱ የሰው ልጅ ወደ ቀደመ ክብሩ የተመለሰበት ፣ የዲያብሎስ የባርነት ቀንበር የተሰበረበትና እኛም በመስቀሉ የተገኘውን ነጻነት እያሰብን በሃይማኖትና በምግባር እንድንጸና የሚያስተምር የታላቅ ውለታ ቀን ነው።

ጸሎተ ሐሙስ ፦ የትሕትናና የምሥጢር ቀን የሕማማት ሐሙስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የደቀ መዛሙርቱን እግር በማጠብ ፍጹም ትሕትናን ያስተማረበት፣ በጌቴሴማኒ በጸሎት በመትጋት አርአያ የሆነበትና ከሁሉ በላይ ደግሞ ሥጋውንና ደሙን ለዓለም ድኅነት የሰጠበት ታላቁ የቍርባን ምሥጢር የተመሠረተበት ዕለት በመሆኑ "የምሥጢር ቀን" ይባላል። ይህ ዕለት የብሉይ ኪዳን መስዋዕት አብቅቶ አማናዊው የሐዲስ ኪዳን ሥርዓት የተተካበት በመሆኑ፣ እኛም በጌታችን ፍጹም ትሕትና ተመስለንና በጸሎት በርትተን ለቅዱስ ምሥጢራቱ እንድንዘጋጅ የሚመክር የታላቅ ትምህርት ቀን ነው።

photo content

ጸሎተ ሐሙስ ፦ የትሕትናና የምሥጢር ቀን የሕማማት ሐሙስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የደቀ መዛሙርቱን እግር በማጠብ ፍጹም ትሕትናን ያስተማረበት፣ በጌቴሴማኒ በጸሎት በመትጋት አርአያ የሆነበትና ከሁሉ በላይ ደግሞ ሥጋውንና ደሙን ለዓለም ድኅነት የሰጠበት ታላቁ የቍርባን ምሥጢር የተመሠረተበት ዕለት በመሆኑ "የምሥጢር ቀን" ይባላል። ይህ ዕለት የብሉይ ኪዳን መስዋዕት አብቅቶ አማናዊው የሐዲስ ኪዳን ሥርዓት የተተካበት በመሆኑ፣ እኛም በጌታችን ፍጹም ትሕትና ተመስለንና በጸሎት በርትተን ለቅዱስ ምሥጢራቱ እንድንዘጋጅ የሚመክር የታላቅ ትምህርት ቀን ነው።

የሕማማት ረቡዕ፦ የምክርና የእንባ ቀን ​የሕማማት ረቡዕ የካህናት አለቆች፣ ጸሐፍትና የሕዝብ ሽማግሌዎች ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እንዴት አድርገው እንደሚይዙትና እንደሚገድሉት በቃያፋ ግቢ ተሰብስበው ክፉ ምክር የመከሩበት ዕለት በመሆኑ "የምክር ቀን" ይባላል በአንጻሩ ደግሞ በዝሙት ስም የምትታወቀው ሴት  ውድ ዋጋ ያለውን ሽቶ በጌታችን ራስ ላይ በማፍሰስ፣ በእንባዋ እግሩን አጥባ በጠጉሯ በማበስ የንስሐ ፍቅሯን የገለጸችበት ዕለት ነው። ​በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን የይሁዳን ክህደትና የክፉዎችን ምክር ስታስብ፣ በሌላ በኩል ደግሞ የሴቲቱን የንስሐ ዕንባና ቅን ፍቅር ለትምህርት ታቀርባለች በአጠቃላይ ዕለቱ የሰው ልጅ በንስሐ ታጥቦ ወደ አምላኩ የሚመለስበትን አስፈላጊነት የሚያሳይና በክፋት ከሚመክሩት ወገኖች ተለይተን በንጹሕ ልብ ለጌታችን የምንገዛበት የታላቅ ትምህርት ቀን ነው።

photo content

ማስታወቂያ ለውድ ወላጆች፣ በዛሬው የሕፅበተ እግር በዓል ሥነ-ሥርዓት ላይ የተገኛችሁ እና በራሳችሁ ስልክ ወይም ካሜራ ፎቶዎችን ያነሳችሁ ወላጆች፣ እባክዎን ያነሳችኋቸውን ፎቶዎች ከታች ባለው የቴሌግራም ሊንክ በመግባት እንድታጋሩን (Share እንድታደርጉን) በአክብሮት እንጠይቃለን። 👉 https://t.me/+but06E_DjQw2NDZk ስለ ትብብራችሁ እናመሰግናለን! ት/ቤቱ