en
Feedback
ቅዱሳት ሥዕላት 🎨

ቅዱሳት ሥዕላት 🎨

Open in Telegram

ይህ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ትክክለኛ ቅዱሳት ሥዕላትን በብራና በገበታ እና በሸራ ላይ የሳልናቸውን ምንለቅበት ነው። ትእዛዝ ለማዘዝ ይህንን ይጠቀሙ @jermi123 ☎0941256792 ይደውሉ!!!

Show more
421
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-1430 days
Posts Archive
Repost from Ermi Art studio
አምላከ ቅዱሳን በአንድነት ይማረን
+3
አምላከ ቅዱሳን በአንድነት ይማረን

ወበእንተዝ "ተሰመይከ"/፪/ ተክለ ሃይማኖት/፪/ "ስምዐ ጽድቅ ኮንከ"/፪/ተክለ ሃይማኖት/፪/

የቅዱስ እስጢፋኖስ ሥዕለ አድኅኖ በሸራ ላይ የተሰራ @kdusat_seelat
የቅዱስ እስጢፋኖስ ሥዕለ አድኅኖ በሸራ ላይ የተሰራ @kdusat_seelat

🌼🌼🌼🌼🌼ነሐሴ 24🌼🌼🌼🌼 እንኳን ለአቡነ ተክለ ኃይማኖት ለቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ለቅዱስ ቶማስ ዘመርአስ ለአበው አብርሐም ይስሐቅ ያእቆብ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!!

Repost from Ermi Art studio
🌼🌼ስርአተ ዋዜማ 🌼🌼 🌼🌼ዘነሐሴ 24 ተክለኃይማኖት🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼በ 1 ሀሌታ- 🌼🌼 እንተ አጽናዕኮሙ ለአድባር በኃይልከ፤ወቅኦታን እሙንቱ በኃይል፤ዝንቱሰ ብእሲ መምህርነ፤አባ፤ጸሊ በእንቲአነ 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼ምልጣን፦ ዝንቱሰ ብእሲ መምህርነ፤አባ ጸሊ በእንቲአነ፤አባ ጸሊ በእንቲአነ 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼አመላለስ፦ አባ ጸሊ በእንቲአነ/2/ አባ ጸሊ ጸሊ በእንቲአነ/4/ ለእግዚአብሔር ምድር በምላህ፦ አባ ጸሊ በእንቲአነ፤ ጸሎትከ ወትረ ይብጽሐነ፤ አባ ጸሊ በእንቲአነ። 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼እግዚአብሔር ነግሰ፦ ተክለኃይማኖት ፃመወ እምገድለ ቅዱስ ምክዕቢተ ከመ ይፍረይ ፍሬ ህየንተ አሀደ፴ወስምንተወ፻ተ ኢያድነነ ትልሞ ወኢገብዓ ድኅርተ እመንፈስ ቅዱስ ነሢዖ አሦተ 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼እግዚኦ ጸራዕኩ ሀቤከ ስምዐኒ፦ ዕፀ ጳጦስ ይዕቲ እንተ በአማን ለእንተ ይበልዋ ቅድስተ ቅዱሳን ዕፀ ጳጦስ ይዕቲ እንተ በአማን 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼ይትባረክ፦ ኪያከ መሠረት አንተ ብነ፤ አባ ጸሊ በእንቲአነ፤ እስመ ጸሎተ ጻድቅ ይሰምዕ እግዚአብሔር 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼ዓዲ(ሌላ)፦ ጸለየ ተክለኃይማኖት እንዘ ይብል ኀበ ተቀብረ ሥጋየ ወተክዕወ ደምየ ህየ በረከት 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼ሰለስት፦ በመንፈስ የሐውር እምኃይል ውስተ ኃይለ ተክለኃይማኖት ካህን ወድንግል 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼ሰላም፦ አበው ቅዱሳን ዔሉ ውስተ አድባር ወበዓታት፤ አዕረፉ በክብር ወበብዙኅ ሰላም። 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼 አመላለስ፦ አበው ቅዱሳን ዔሉ ውስተ አድባር ወበዓታት፤(2) አዕረፉ በክብር ወበብዙኅ ሰላም፤(4) 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼ዓዲ ሰላም፦ እስመ በኩሉ ይሴብሕ እግዚአብሔር በሰማይኒ ወበምድርኒ በፍስሐ ወበሰላም ንርአይ ስና ለቤተ ክርስትያን ወንግበር ተዝካሮሙ ለብፁዕ አበ ኩልነ አባ ተክለኃይማኖት አስተጋብዓነ ለስብሐት እግዚአብሔር 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼አመላለስ፦ አበ ኩልነ አባ ተክለኃይማኖት/2/ አስተጋብዓነ ለስብሐት እግዚአብሔር/4/ 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼via ያሬዳዊያን https://t.me/enabib

የሰማእታት አለቃ ሆኖ ከቅዱስ ጊዮርጊስ በማእረግ ዝቅ የሚለው ሰማዕት ማን ይባላል?
Anonymous voting

ኦ ፍጡነ ረድኤት እምሩፀተ ነፋስ ወአውሎ ለዘይጼውአከ በተወክሎ ጊዮርጊስ ቅረብ ለምህረት ወለተሳኅሎ እስመ ልበ አምላክ ርኅሩህ በኃቤከ ኃሎ

🌼🌼🌼የአራት አይናው ሊቅ የቅዱስ ወልደሚካኤል በረከት የስምንቱ ደቀ መዛሙርቶቻቸው በረከት በኛ ላይ ይደርብን !!! 🌼🌼🌼 አደራ አደራ እናስባቸው🙏🙏🙏

††† እንኳን ለሰላሳ ሺ ግብጻውያን ሰማዕታት ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። ††† 🌼🌼††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††🌼🌼 ††† ሠለስቱ እልፍ ሰማዕታት ††† ††† ዘመነ ሰማዕታት አርባ ሰባት ሚሊየን ክርስቲያኖችን በአርባ ዓመታት ከበላ በኋላ በ305 (312) ዓ/ም ቢጠናቀቅም ስለ ሃይማኖት መሞት ግን እስከ ምጽዓት ድረስ ይቀጥላል:: ለእያንዳንዱ ክርስቲያን ከሚቀርቡ ፈተናዎች ሁሉ እጅግ ከባዱ ይሔው ሰማዕትነት ነውና ሊቀበለው ያለው (ያደለው) ይቀበለዋል:: ቤተ ክርስቲያን በባሕር ላይ ያለች መርከብ ናትና ዘወትር በፈተና ውስጥ መኖሯ የሚጠበቅ ነው:: ዘመነ ሰማዕታትን ተከትሎ የመጣው የመናፍቃን ዘመን ሲሆን ለመቶ ሃምሳ ዓመታት ያህል መናፍቃን እንደ አሸን ፈልተዋል:: በዚያው ልክ ከዋክብት ቅዱሳን ሊቃውንት ነበሩና በየጊዜው ጉባኤያትን እየሠሩ: መናፍቃንን አሳፍረዋል:: ምዕመናንንም አጽንተዋል:: በ451 ዓ/ም የተፈጸመው ድርጊት ግን ዛሬም ድረስ ጠባሳው የሚለቅ አልሃነም:: ንጉሡ መርቅያንና ጳጳሱ ልዮን የንስጥሮስን ትምሕርት አለባብሰው ሊያስተምሩ ሲሞክሩ ግጭት በመፈጠሩ ቤተ ክርስቲያን ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ሁለት ተከፈለች:: በጉባኤው የነበሩ ስድስት መቶ ሰላሳ ስድስት ጳጳሳት ስቃይና ሞትን ፈርተው በኑፋቄ መጽሐፍ ላይ በመፈረማቸው "መለካውያን" (ከእግዚአብሔር ይልቅ ለንጉሥ የሚታዘዙ) ተባሉ:: ጉባኤውም "ጉባኤ ከለባት" (የውሾች ስብሰባ): "ጉባኤ አብዳን" (የሰነፎች ጉባኤ) ተብሏል:: የወቅቱ የእስክንድርያ ፓትርያርክ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ግን "በኑፋቄው ላይ አልፈርምም::" ከማለቱ አልፎ መናፍቃኑን አወገዛቸው:: በዚህ ምክንያት ጽሕሙን ነጭተው: ጥርሱንም አርግፈው: ወደ ጋግራ ደሴት ከሰባት ደቀ መዛሙርቱ ጋር አሳደዱት:: በዚያም ለሦስት ዓመታት ቆይቶ በ454 ዓ/ም ዐረፈ:: እግዚአብሔር ፈርዶባቸው ንጉሡ መርቅያን እና ንግሥቲቱ ብርክልያ (ክፉ ሴት ናት) ድንገት ሞቱ:: ፈተናው ግን በዚህ አላበቃም:: በዙፋኑ የተተካው ሌላኛው ጨካኝ ልዮን ነበር:: መንፈሳዊውን አርበኛ አባ ዲዮስቆሮስን በሞት ያጡት የግብጽ ክርስቲያኖች ደቀ መዝሙሩን "አባ ጢሞቴዎስን እንሾማለን::" ቢሉ ንጉሡ ከለከለ:: የሚሾመው መለካዊ ነው ብሎ አብሩታርዮስ የሚባል መናፍቅ ጳጳስ በላያቸው ላይ ሾመባቸው:: ይህንን መታገስ ለሕዝቡና ለካህናቱ ከባድ ነበር:: ተኩላ እንኳን በበጐች ላይ በይፋ ተሹሞ: ተደብቆም ቢሆን እየነጠቀ መብላት ልማዱ ነው:: መናፍቁ ጳጳስ በተለያየ መንገድ ሕዝቡን ለመሳብ ሞክሮ ነበር:: ለምሳሌ አውጣኪን (የክርስቶስን ሰው መሆን ምትሐት የሚል 'የቱሳሔ' አስተማሪ መናፍቅ ነው::) አወገዘው:: እነሱ ግን ተረድተውታልና ቦታ አልሰጡትም:: ምክንያቱም አውጣኪ ከቀድሞም የተወገዘ መናፍቅ ነውና:: የሚገርመው ከሕዝቡ አንድስ እንኳ ከመናፍቁ ጳጳስ የሚባረክ አልነበረም:: ሥጋውን ደሙንም ከእውነተኛ ካህናት በድብቅ ይቀበሉ ነበር:: አንድ ቀን ግን መናፍቁ ጳጳስ አብሩታርዮስ ተገድሎ ተገኘ:: (መልአክ ቀሥፎት ነው የሚሉ አሉ:: እስካሁን ድረስ የገዳዩ ማንነት አልታወቀም::) ግብጻውያን ክርስቲያኖች ግን የእርሱን ሞት ሲሰሙ ደጉን እረኛ አባ ጢሞቴዎስን ሾሙ:: ችግሩ የመጣው ከዚህ በኋላ ነው:: የመናፍቁ ተከታዮች ለንጉሡ ልዮን "አንተን ንቀው: የሾምከውን ገደሉ:: ሌላ ጳጳስም ሾሙ::" ብለው መልዕክት ላኩለት:: በዚህ የተበሳጨው ልዮን ኦርቶዶክሳውያንን ባገኛችሁበት ሁሉ ግደሉ የሚል አዋጅ አወጣ:: ይህን አዋጅ ተከትሎ ሰላሳ ሺ ሰዎች በእስክንድርያ ከተማ ተጨፈጨፉ:: ገዳዮቹ ወንድ: ሴት: ሕፃን: ሽማግሌ ሳይመርጡ የክርስቲያኖችን ደም አፈሰሱ:: ለሦስት ቀናትም ግድያው ቀጥሎ እንደ ነበር ይነገራል:: ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት "ወኀጥኡ ዘይቀብሮሙ" እንዳለ ቀባሪም አጡ:: ገዳዮቹ ቀጥለውም አባ ጢሞቴዎስን አስረው አጋዙት:: ለአሥር ዓመታትም አሰቃዩት:: ከእነዚህ ዓመታት በኋላ ግን ንጉሡ ተጸጽቶ አባ ጢሞቴዎስን ወደ መንበሩ መልሶታል:: ወገኖቻችን የግብጽ ክርስቲያኖች እንኳን ያኔ ዛሬም በጽናታቸው አብነት ልናርጋቸው የሚገቡ ናቸው:: ††† አምላከ ሰማዕታት በቸርነቱ ይጠብቀን:: ከበረከታቸውም ያድለን:: ††† ነሐሴ 23 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ሰላሳ ሺ የእስክንድርያ (ግብጽ) ሰማዕታት 2.ቅዱስ ድምያኖስ ሰማዕት ††† ወርኀዊ በዓላት 1.ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት 2.ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት 3.ነቢየ ጽድቅ ቅዱስ ሰሎሞን (ንጉሠ እሥራኤል) 4.አባ ጢሞቴዎስ ገዳማዊ 5.ቅዱስ ዳንኤል ነቢይ 6.አባ ሳሙኤል 7.አባ ስምዖን 8.አባ ገብርኤል ††† "በጐንም ለማድረግ ብትቀኑ የሚያስጨንቃችሁ ማን ነው? ነገር ግን ስለ ጽድቅ እንኳ መከራን ብትቀበሉ ብጹዓን ናችሁ:: ማስፈራራታቸውንም አትፍሩ: አትናወጡም:: ዳሩ ግን ጌታን እርሱም ክርስቶስን በልባችሁ ቀድሱት:: በእናንተ ስላለ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ:: ነገር ግን በየውሃነትና በፍርሃት ይሁን::" ††† (፩ጴጥ. ፫፥፲፫-፲፮) ††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††

ለመጀመርያ ግዜ የእመቤታችን ሥዕለ አድኅኖ እየሳለ ይሸጥ የነበረ ሐዋርያ ማነው?
Anonymous voting

ቅዱስ ሚካኤል አፎምያን ከጠላት ሰይጣን እንዳዳናት ያላለቀ ጅምር ሥዕል በሸራ ላይ @kdusat_seelat
ቅዱስ ሚካኤል አፎምያን ከጠላት ሰይጣን እንዳዳናት ያላለቀ ጅምር ሥዕል በሸራ ላይ @kdusat_seelat

ቅዱስ ያሬድ (repost)
ቅዱስ ያሬድ (repost)

Repost from Ermi Art studio
🌼🌼††† እንኳን ለታላቁ ነቢይ ቅዱስ ሚክያስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††🌼🌼 †††በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ††† ††† ቅዱስ ሚክያስ ነቢይ ††† ††† ነቢይ ማለት በቁሙ ኃላፍያትን (አልፎ የተሠወረውን ምሥጢር): መጻዕያትን (ገና ለወደ ፊት የሚሆነውን) የሚያውቅ ሰው ማለት ነው:: ሃብተ ትንቢት የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ሲሆን እርሱ ለወደደው ደግሞ በጸጋ ይሰጠዋል:: እነዚህም ከጌታ ሃብተ ትንቢት የተሰጣቸው አባቶችና እናቶች "ቅዱሳን ነቢያት" በመባል ይታወቃሉ:: ዘመነ ነቢያት ተብሎ የሚታወቀው ብሉይ ኪዳን ቢሆንም እስከ ምጽዓት ድረስ ጸጋውን እግዚአብሔር ለፈቀደላቸው አይነሳቸውም:: በሐዋርያት መካከልም ቅዱስ አጋቦስን የመሰሉ ነቢያት ነበሩ:: (ሐዋ. 11:27) ቅዱሳን ነቢያት ከእግዚአብሔር እየተላኩ ሰውን ከፈጣሪው እንዲታረቅ ይመክራሉ: ይገስጻሉ:: ከበጐ ሃይማኖታቸውና ንጽሕናቸው የተነሳም እግዚአብሔርን በተለያየ አርአያና አምሳል አይተውታል:: "እስመ በአንጽሖ መንፈስ ርዕይዎ ነቢያት ለእግዚአብሔር: ወተናጸሩ ገጸ በገጽ" እንዳለ አባ ሕርያቆስ:: (ቅዳሴ ማርያም) የብዙ ነቢያት ፍጻሜአቸው መከራን መቀበል ነው:: እውነትን ስለ ተናገሩ: አንዳንዶቹም በእሳት: አንዳንዶቹም በሰይፍ: አንዳንዶቹም በመጋዝ ተፈትነዋል:: ሌሎቹ ለአናብስት ሲጣሉ ቀሪዎቹ ደግሞ በድንጋይ ተወግረዋል:: ስለዚህም መከራቸው ለቤተ ክርስቲያን መሠረት ተብለዋል:: ጌታም ለደቀ መዛሙርቱ "ሌሎች ደከሙ: እናንተ በድካማቸው ገባችሁ::" ብሎ የነቢያቱን መከራ ተናግሯል:: (ዮሐ. 4:36) ነቢያት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እና ድንግል እናቱን ለማየት ብዙ ጥረዋል: ሽተዋልም:: "ብዙ ነቢያትና ጻድቃን እናንተ የምታዩትን ሊያዩ ሹ::" እንዳለ ጌታ በወንጌል:: (ማቴ. 13:16, 1ጴጥ. 1:10) ዛሬ ግን በሰማያት ጸጋ በዝቶላቸው: ክብር ተሰጥቷቸው ሐሴትን ያደርጋሉ:: ††† ቅዱሳን ነቢያት በዋነኝነት ¤አሥራ አምስቱ አበው ነቢያት: ¤አራቱ ዐበይት ነቢያት: ¤አሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያትና ¤ካልአን ነቢያት ተብለው በአራት ይከፈላሉ:: ††† አሥራ አምስቱ አበው ነቢያት ማለት:- *ቅዱስ አዳም አባታችን *ሴት *ሔኖስ *ቃይናን *መላልኤል *ያሬድ *ኄኖክ *ማቱሳላ *ላሜሕ *ኖኅ *አብርሃም *ይስሐቅ *ያዕቆብ *ሙሴና *ሳሙኤል ናቸው:: ††† አራቱ ዐበይት ነቢያት *ቅዱስ ኢሳይያስ ልዑለ ቃል *ቅዱስ ኤርምያስ *ቅዱስ ሕዝቅኤልና *ቅዱስ ዳንኤል ናቸው:: ††† አሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት *ቅዱስ ሆሴዕ *አሞጽ *ሚክያስ *ዮናስ *ናሆም *አብድዩ *ሶፎንያስ *ሐጌ *ኢዩኤል *ዕንባቆም *ዘካርያስና *ሚልክያስ ናቸው:: ††† ካልአን ነቢያት ደግሞ:- *እነ ኢያሱ *ሶምሶን *ዮፍታሔ *ጌዴዎን *ዳዊት *ሰሎሞን *ኤልያስና *ኤልሳዕ . . . ሌሎችም ናቸው:: ††† ነቢያት በከተማም ይከፈላሉ:: *የይሁዳ (ኢየሩሳሌም): *የሰማርያ (እሥራኤል)ና *የባቢሎን (በምርኮ ጊዜ) ተብለው ይጠራሉ:: ††† በዘመን አከፋፈል ደግሞ:- *ከአዳም እስከ ዮሴፍ (የዘመነ አበው ነቢያት): *ከሊቀ ነቢያት ሙሴ እስከ ነቢዩ ሳሙኤል (የዘመነ መሳፍንት ነቢያት) *ከቅዱስ ዳዊት እስከ ዘሩባቤል ያሉት (የዘመነ ነገሥት ነቢያት) *ከዘሩባቤል ዕረፍት እስከ መጥምቁ ዮሐንስ ያሉት ደግሞ (የዘመነ ካህናት ነቢያት) ይባላሉ:: ††† ስለ ቅዱሳን ነቢያት በጥቂቱ ይህንን ካልን ወደ ዕለቱ በዓል እንመለስ:: ቅዱስ ሚክያስ ቁጥሩ ከአሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት ሲሆን ዘመነ ትንቢቱም ቅ.ል. ክርስቶስ በ800 ዓ/ዓ አካባቢ ነው:: "ደቂቀ ነቢያት" ማለት በጥሬው "የነቢያት ልጆች" ማለት ነው:: አንድም የጻፏቸው ትንቢቶች ሲበዙ አሥራ አራት ምዕራፍ: ሲያንስ አንድ ምዕራፍ ያላቸው ናቸውና ደቂቅ ይላቸዋል:: ሚክያስ አባቱ ሞራት (ሞሬት) ይባላል:: ሚክያስ ማለት "መኑ ከመ አምላክ - እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው!" ማለት ነው:: አንድም "መልአከ እግዚአብሔር" ማለት ነው:: የአባቶቻችን ሁሉ ስማቸው እግዚአብሔርን የሚሰብክ ነው:: ቅዱሱ ነቢይ ገና ልጅ እያለ መላእክት ያነጋግሩት ነበር:: በዚህ ምክንያት ከሰው አይቀርብም:: ትክ ብለው ሲያዩት በፊቱ ላይ ብርሃን ቦግ ቦግ እያለ ይታይ ነበር:: በወጣትነት ዘመኑ እግዚአብሔር ለትንቢት ሲጠራው በእሺታ ታዘዘ:: በሦስቱ ነገሥታት (በኢዮአታም: አካዝና ሕዝቅያስ) ዘመንም ትንቢቶችን ተናግሯል:: ሕዝቡን: መሣፍንቱን: ነገሥታቱን አስተምሮ ገስጿል:: አንድ ቀን በቤተ ልሔም ሲያልፍ የዳዊት ከተማ ፈት ሁና: ዳዋ በቅሎባት ቢመለከት አዘነ:: ወዲያውም ትንቢት ተናገረላት:: "ወአንቲኒ ቤተ ልሔም ምድረ ኤፍራታ: ኢትቴሐቲ እምነገሥተ ይሁዳ: እስመ እምኔኪ ይወጽዕ ንጉሥ: ዘይርዕዮሙ ለሕዝብየ እሥራኤል::" "አንቺም የኤፍራታ ምድር ቤተ ልሔም: የይሁዳ ነገሥታት ከነገሡባቸው ከተሞች ከቶ አታንሺም:: ወገኖቼን እሥራኤልን የሚጠብቃቸው ንጉሥ (መስፍን) ካንቺ ዘንድ ይወጣልና::" አለ:: ይኸውም አልቀረ ለጊዜው ከሚጠት በኋላ ደጉ ዘሩባቤል ነግሦባታል:: በፍጻሜው ግን የባሕርይ ንጉሠ ነግሥት ኢየሱስክርስቶስ ከንጽሕት ድንግል ማርያም ተወልዶባታል:: ቅዱስ ሚክያስ ወገኖቹን ሲያስተምርና ሲመራ ኑሮ: ሰባት ምዕራፎች ያሉትን ሐረገ ትንቢት ተናግሮ: በመልካም ሽምግልና: በንጉሡ ሕዝቅያስ ዘመን ዐርፏል:: ወገኖቹ ቀብረውታል:: ጌታም በክብረ ነቢያት ከልሎታል:: ††† ቸር አምላከ ነቢያት የነቢያቱን መከራ አስቦ ከመከራ: በእንባቸውም ከእንባ ይሰውረን:: ከተረፈ በረከታቸውም አያጉድለን:: ††† ነሐሴ 22 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ቅዱስ ሚክያስ ነቢይ ††† ወርኀዊ በዓላት 1.ቅዱስ ዑራኤል ሊቀ መላእክት 2.ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ 3.ቅዱስ ደቅስዮስ (የእመቤታችን ወዳጅ) 4.አባ እንጦንስ አበ መነኮሳት 5.አባ ጳውሊ የዋህ ††† "ምን ይዤ ወደ እግዚአብሔር ፊት ልምጣና በልዑል አምላክ ፊት ልስገድ? የሚቃጠለውን መስዋዕትና የአንዱን ዓመት ጥጃ ይዤ በፊቱ ልምጣን? እግዚአብሔርስ በሺህ አውራ በጐች: ወይስ በእልፍ የዘይት ፈሳሾች ደስ ይለዋልን? . . . ሰው ሆይ! መልካሙን ነግሮሃል:: እግዚአብሔርም ከአንተ ዘንድ የሚሻው ምንድር ነው? ፍርድን ታደርግ ዘንድ: ምሕረትንም ትወድ ዘንድ: ከአምላክህም ጋር በትሕትና ትሔድ ዘንድ አይደለምን?" ††† (ሚክ. ፮፥፮) ††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር ††† Via dn yordanos

የኪዳነምህረት የኮርአተ ርእሱ የስቅለት የግንዘት ሥዕለ አድኅኖ በገበታ ላይ የተሰራ @kdusat_seelat
የኪዳነምህረት የኮርአተ ርእሱ የስቅለት የግንዘት ሥዕለ አድኅኖ በገበታ ላይ የተሰራ @kdusat_seelat

Repost from Ermi Art studio
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን የንስሐ_ጸሎት ➱ አቤቱ ፈጣሪዬ ሆይ አዳምን ከሲኦል ፣ ኖህን ከውሃ ጥፋት ፣ ይስሃቅን ከመታረድ ፣ እስራኤልን ከፈርኦን ፣ ዳዊትን ካሳኦል ፣ ኤልያስን ከኤልዛቤል ፣ መርዶክዮስን ከሀማ ፣ ሰልስቱን ደቂቅን ከእቶን እሳት ፤ ያዳንክ አምላክ ሆይ እኔንም ባሪያህን ከመከራ ስጋ ከመካራ ነፍስ አድነኝ ። በዚህ አለም ስኖር ከርሃብ ፣ ከጥማት ፣ ከመሰደድ ፣ ከመንገላታት ፣ በኃይለኞችና በጨካኞች እጅ ከመውደቅ አድነኝ ፤ ለንሰሐ ሞት አብቃኝ ፤ የሗላ ቤቴን አሳምርልኝ ፤ ከዳግም ሞት አድነኝ አሜን! አቤቱ አምላኬ ሆይ ኢዮብን ከቁስል ፣ አላዛርን ከመቃብር ፣ ሕዝቅያስን ከሰናክሬም ፣ ዮናስን ከአሳነባሪ ፣ ምናሴን ከብረት ቀፎ ፣ ሙሴን ከዳታንና ከአቤሮን ፣ አሮንን ከደቂቀ ቆሬ ያዳንክ አምላክ ሆይ እኔንም ከመከራ ስጋ ከመከራ ነፍስ አድነኝ ፤ አቤቱ ጌታዬ ሆይ ዳንኤልን አእፈ አናብስት ፣ ሶስናን ከእደ ረበናት ፣ ሎጥን ከሰዶምና ከገሞራ ፣ ዲቦራን ከሲሳራ ፣ ያእቆብን ከወንድሞቹ ፣ ሶምሶምን ከእርግውና ወደ ውርዝውና የመለስክ ፤ የበለአምን አህያ ያናገርክ እኔንም ባርያህን ከመከራ ስጋ ከመከራ ነፍስ ሰውረኝ ፤ በንፅህና ሆኜ ቅዱስ ስጋህን እና ክቡር ደምህን እየተቀበልኩኝ ለመኖር ፍቀድልኝ ከዚህ አለም እሾህና አሜኬላ አድነኝ አሜን! አቤቱ ፈጣሪዬ ሆይ ሰማእቱ ቅዱስ ጊዮርጊስን ከሰባ ነገስታት ፣ ጦቢትን ከአይን ህመም ፣ ብሩክ ታዊትን ከአፍ ደራጎን ፣እግዚሃርያን ከመቶሎሚ ፣ የአትናስያን ሞት ወደ ህይወት የመለስክ ፣ በላኤሰብን የማርክ ፤ አክሊለ እሾህን ያጠለክ ፣ በቅድመ አይሁድ እስራትና ግርፋት ለአለም ቤዛነትን የተቀበልክ ፣ በፆረ መስቀል በፍኖተ አምስት ጊዜ የወደቅህ ፣ በፊትህም በኃላህም ምራቀ አይሁድን የተቀበልክ ፣ በቀራንዮ በእለተ አርብ ደምህን ያፈሰስክ ስጋህን የቆረስክ ፣ ህማማተ መስቀልን የተቀበልክ ፣ የእውሩን አይን ያበራክ ፣ ለምፃሙን ያነፃክ ፣ ጎባጣውን ያቀናክ ፣ ዲዳን ያናገርክ ፣ አንካሳን የፈታህ ፣ ባህርን ያናወፅክ ፣ ፴፰ አመት በአልጋ ቁራኝነት የነበረውን መፃጉን ያዳንክ ፣ ያመኑብህን የማትጥል ፣ ሰማይና ምድርን በቃልህ ያቆምክ ፣ መአልቱን በሌሊት በጋውን በክረት የምታፈራርቅ ፣ አካልህ የማይዳሰስ ቃልህ የማይገሰፅ ፣ መንግስትህ አያልፍ ፣ ከተሾምክ ያልተሻርክ የማትሻር ፣ ከተወለድክ የማታረጅ ያላረጀክ ፣ ከአለም በፊት የተገኘህ አለምን አሳልፈህ ለዘለአለም የምትኖር አልፋና ኡሜጋ ኤልሻዳይ አዶናይ ፀባኦት ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ከክፋት ወደ በጎነት መልሰኝ ፤ ሀይል መዊእ ለዳዊት የሰጠህ ለእኔም ስጠኝ እድሜ ለማቱሳላ ፣ ፅድቅ ለቅዱስ ላሊበላ የሰጠህ ለእኔም እድሜ ለንሰሐ ፅድቅ ለፍሰሀ ስጠኝ ፤ መልአከ ጠባቂዬን አበርታልኝ ከሰውና ከእግዚአብሔር የሚስማማ ምግባርን ስጠኝ ፤ በተወለድኩበት አገር ክፋን ነገር አታሳየኝ ፤ የመላእክት የሰማእታት የፃድቃን የነቢያት የሐዋርያትና የምእመናን የደብርን የገዳማትን የእፅነ የእንስሳትን የአእሩግን የህፃናትን የንጉስን የመስተጋድል ልመና ፀሎት የተቀበልክ አምላክ የእኔንም ልመና ፀሎት ስማኝ ተቀበለኝ ። "መሐረኒ እመከራ ስጋ እመከራ ነፍስ ዓለም ለዓለም አሜን !!! ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር

ለመጀመርያ ግዜ የጌታችን ስነስቅለትን የሳለው አባት ማነው?
Anonymous voting

የቅዱስ ጊዮርጊስ ስዕለ አድኅኖ በሸራ ላይ እየተሰራ ያለ @kdusat_seelat
+1
የቅዱስ ጊዮርጊስ ስዕለ አድኅኖ በሸራ ላይ እየተሰራ ያለ @kdusat_seelat

በብራና በሸራም ሆነ በገበታ በምትፈልጉት size(መጠን) ለማዘዝ ይህንን ይጠቀሙ 👇👇👇👇 @jermi123 👆👆👆👆👆 ☎0941256792 ይደውሉ!!!

የስቅለት የኮርአተ ርእሱ የእመቤታችን የቅዱስ ጊዮርጊስ የገበታ ሥእለ አድኅኖ @kdusat_seelat
የስቅለት የኮርአተ ርእሱ የእመቤታችን የቅዱስ ጊዮርጊስ የገበታ ሥእለ አድኅኖ @kdusat_seelat

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የቅዱሳት ሥዕላት አቀማመጥ፡- ቅዱሳት ሥዕላት በየአብያተ ክርስቲያናቱ አሉ፡፡ ቅዱሳት ሥዕላት የሌሉበት ቤተክርስቲያን ካለ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ ነው ለማለት ፈጽሞ አይቻልም፡፡ ቢያንስ ምስለ ፍቁር ወልዳ የእመቤታችን ሥዕል ከመንበረ ታቦቱ ላይ መቀመጥ ይኖርበታል፡፡ ይህ በሁሉም ቤተ ክርስቲያን ያለ ሥርዓት ነውና፡፡ ቅዱሳት ሥዕላት በተቻለ መጠን በከበረ ቦታ መቀመጥ ይኖርባቸዋል በሚከበሩበት፣ በማይላላጥበት፣ በማይነካኩበት፣ ፀሐይና ዝናብ በማያገኝበት፣ ሕፃናት በማይደርሱበት፣… ቦታ ሊቀመጡ ይገባል፡፡ ለምሳሌ፡- ሀ. በቤተ መቅደስ፡- በአብያተክርስቲያናት ግድግዳዎች፣ ጣሪያዎችና በሮች ላይ ተሥለው ይቀመጣሉ፡፡ በየማእዘናቱ/በየአቅጣጫው/ የሚሣሉ ሥዕሎች ይለያያሉ፡፡ ቤተ መቅደስ በሮች 1. በምሥራቅ፡- ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የፈጸማቸው ገቢረ ተአምራት፣ ገቢረ ሐዋርያት እንዲሁም እመቤታችን ቅዱስ ኤፍሬምን ስትባርከው የሚያሳዩ ሥዕሎች ይሣላሉ፡፡ ከምሕዋሩ ባላይ ዕርገቱ ይሣላል፡፡ 2. በምዕራብ፡- ነገረ ስቅለቱና ልደቱ፣ ጥምቀቱ፣ ሕማማቱ መስቀሉ፣ ትንሣኤው፣ ምስለ ፍቁር ወልዳና ቅዱስ ጊዮርጊስ ይሣላሉ፡፡ ከምሕዋሩ በላይ የቅድስት ሥላሴ ሥዕል ይደረጋል፡፡ በበሩ ላይ ደግሞ ቅዱስ ሚካኤል ፈርዖንን ከነሠራዊቱ ሲያሰጥም፣ ቅዱስ ሩፋኤል ዓሣ አንበሪውን እንደወጋ ይሣልል፡፡ 3. በሰሜን፡- ሰማዕታት የሚሣሉበት አቅጣጫ ነው፡፡ የተለያዩ የቅዱሳን ሰማዕታት ሥዕል፣ ምስለ ፍቁር ወልዳ/የሰማዕታት እናታቸው ናትና/ ከምሕዋሩ በላይ ደግሞ ጌታችን ብርሃነ መንግሥቱን በደብረ ታቦር ሲገለጥ የሚያሳይ ይሣልበታል፡፡ 4. በደቡብ፡- ነገረ ማርያም የሚሣልበት ሲሆን ከልደቷ እስከ ዕርገቷ ያለውን ታሪክ የሚያሳይ ነው፡፡ ከምሕዋሩ በላይ እመቤታችን በደብረ ምጥማቅ ያደረገችውን ተአምር ይቀመጣል፡፡ ለ. በገበታ፡- አበው መንገድ ሲሄዱ ባሉበት ሆነው ፈጣሪያቸውን በጸሎት ለማመስገንና ለመማጸን ሲሉ በእንጨት ገበታ የተሣሉ ሥዕላትን እንደ መጽሐፍ የሚታጠፉ የሚዘረጉ እንዲሆን አድርገው በማዘጋጀት በአንገታቸው አንግተው ለመሔድ በሚያመቻቸው መልክ ያሰናዷቸው ነበር፡፡ ሐ. በመጽሐፍ፡- ስለ ትምህርተ ሃይማኖት በሚተነትኑ ቅዱሳት መጽሐፍት ላይ ከተጻፈው ትምህርት ጋር አብሮ በሚሔድ መልክ ቅዱሳት ሥዕላት ይሣላሉ፡፡ መ. በመኖሪያ ቤት፡- ምዕመና በተለየ የጸሎት ክፍላቸው ውስጥ መጋረጃ የተደረገላቸው ለጌጥ ሳይሆን ለመማጸኛ ይቀመጣሉ፡፡ እንግዲህ በቅድስት ቤተክርስቲያን ትውፊት መሠረት ቅዱሳት ሥዕላት የሚሣሉት በእውቀት ወይም በመራቀቅ ሳይሆን አበው እግዚአብሔርን ግለጥልን ብለው ሱባኤ ገብተው በጾም በጸሎት ተወስነው ያመኑት ፈጣሪያቸው የገለጠላቸውን በጥንቃቄ በማስቀመጥ ነው፡፡ ስለዚህ ቅዱሳት ሥዕላት የእግዚአብሔር ስጦታዎች እንጂ የሰው የእውቀት ደረጃ መለኪያዎች አይደሉም፡፡   ስለሆነም ኦርቶዶክሳውያን ሁሉ ምን ዓይነት ሥዕል ሊኖራቸው እንደሚገባ በጥንቃቄ መመርመር ይጠበቅባቸዋል፡፡ በየጎዳናው የተዘረጉትን ሁሉ የኛ ናቸው ብሎ መዘናጋት አይገባም፡፡ ወደ ቤተ መቅደስም በሥዕላት መልክ ወይም በስጦታ የምንወስዳቸው ሥዕላት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት የተሣሉ መሆናቸውን በጥንቃቄ መመልከት ይገባል፣ የእግዚአብሔርን በረከት ከምናገኝባቸው መንገዶች መካከል አንዱ ቅዱሳት ሥዕላት ናቸውና፡፡