en
Feedback
ቅዱሳት ሥዕላት 🎨

ቅዱሳት ሥዕላት 🎨

Open in Telegram

ይህ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ትክክለኛ ቅዱሳት ሥዕላትን በብራና በገበታ እና በሸራ ላይ የሳልናቸውን ምንለቅበት ነው። ትእዛዝ ለማዘዝ ይህንን ይጠቀሙ @jermi123 ☎0941256792 ይደውሉ!!!

Show more
421
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-1430 days
Posts Archive
Repost from Ermi Art studio
በሸራ የተሰራ የእመቤታችንን ሥዕለ አድኅኖ በትዕዛዝ ለማሰራት👇👇👇 0941256792 ይደውሉ
በሸራ የተሰራ የእመቤታችንን ሥዕለ አድኅኖ በትዕዛዝ ለማሰራት👇👇👇 0941256792 ይደውሉ

Repost from Ermi Art studio
🌼🌼ከምግብ በኋላ ለምን በእንተ አቡነ አቢብ እንላለን?🌼🌼 ‹‹በእንተ አቡነ አቢብ›› ብሎ ከምግብ ብኋላ የተማፀነውን እምርልሃለው... እነሆ ሰማዕቱ አቡነ አቢብ ምእመናን በሚቀምሱት የዕለት ምግብ አማካኝነት በነፍስም በሥጋም እንዲድኑ አስገራሚ የምሕረት ቃልኪዳን እንደተቀበሉ የሚናገር የገድል ተአምራታቸው ይህ ነው፡- ብዙዎች ስማቸውን ጠርተው በሚቀምሱት ምግብ አማካኝነት ከተለያዩ በሽታዎች የተፈወሱ አሉ፡፡ ይህ ቃልኪዳናቸው ለኹላችን ይደረግን ዘንድ ከመመገባችን አስቀድሞ የእግዚአብሔርን ስም እንጥራ (አቡነ ዘበሰማያትን ማለቱ ነው፡፡) ከተመገብን በኋላም የዕለት ምግባችንን ስለሰጠን እግዚአብሔርን እናመስግን፡፡ ዘወትር ከተመገብን በኋላ ሦስት ጊዜ ‹‹ስለ ወዳጅህ ስለ አቡነ አቢብ›› እያልን ሦስት ጊዜ እንቅመስ፡፡ አስቀድሞ ጌታችን መድኃኒታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአቡነ አቢብ ተገልጦላቸው ‹‹…ወዳጄ አቢብ ሆይ! የሰውን ልጅ ለማዳን የተቀበልኩትን ሕማማተ መስቀል እያሰብህ ይህንን ሁሉ ገድል ፈጽመሃልና ምን እንዳደርግልህ ትወዳለህ?›› አላቸው፡፡ ንዑድ ክቡር ቅዱስ አባታችን አቡነ አቢብም ‹‹ጌታዬ አምላኬ መድኃኒቴ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! መቼም ሰው ሁሉ ሳይመገብ አይውልም አያድርምና በተመገበ ጊዜ ስሜን ጠርቶ የተማጸነውን ማርልኝ›› አሉት፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም አባታችን አቡነ አቢብ ለሰው ልጆች ያላቸውን ፍቅር ካደነቀ በኋላ ‹‹…ከማዕድ በኋላ ስብሃት ተብሎ የተረፈውን ‹በእንተ አቢብ› ብሎ ሦስት ጊዜ የተመገበውን ሰው ሁሉ እምርልሃለሁ›› በማለት ታላቅ የምሕረት ቃልኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡ ያልተጠመቀ አረማዊ አሕዛብም እንኳን ቢሆኖ "ስለ አቡነ አቢብ" ብሎ ከተማጸነ ጌታችንን ያንን ሰው ወደቀናች የእምነት መንገድ ሳይመራወና በንስሓ ሳይጠራው በሞት እንደማይወስደው ለአባታችን ቃልኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡ ለማዳን ትንሽ ምክንያትን የሚፈልግ ያለ ምክንያትም የማያድን ልዑል እግዚአብሔር ስሙ እስከዘላለም ድረስ ይክበር ይመስገን! ሰው ተመግቦ እንኳን መዳን እንዲችል ይህን ድንቅ ቃልኪዳን ለአባታችን ሰጥቷቸዋልና በየቀኑ በዚህ ቃልኪዳን እንጠቀምበት፡፡ ተመግበን ከጨረስንና ስብሃት ካልን በኋላ ሦስት ጊዜ ‹‹በእንተ አቡነ አቢብ›› ብለን እንቅመስ፡፡ በምናቀርበው የስንፍና ምክንያት ለማመሰገን ጊዜ ብናጣ እንኳን ቢያንስ ከተመገብን በኋላ ከስብሃት ቀጥሎ ሦስት ጊዜ በመቅመስ ‹‹በእንተ አቡነ አቢብ›› ብንል እግዚአብሔርን በቀን ሦስት ጊዜ ማመስገን ቻልን ማለት ነው፡፡ ከጻድቁም ቃልኪዳን ተካፋዮች ሆንን ማለት ነው፡፡ በግእዝ ስብሃት ማለት የማንችል ሰዎች ካለን ደግሞ በአማርኛው የዘወትር ጸሎትን ክፍል ላይ የምናገኘውን (‹‹ለአብ ምስጋና ይገባል፣ ለወልድ ምስጋና ይገባል፣ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይገባል፣ ለእመቤታችን ማርያም ምስጋና ይገባል፣ ለክርስቶስ መስቀልም ምስጋና ይገባል፣ ይህን ኅብስት ላበላን፣ ይህንን ጽዋ ላጠጣን፣ ምግባችንና ልብሳችንን ላዘጋጀን፣ ሀጥያታችንንም ሁሉ ለታገሰልን፣ ክቡር ደሙን ቅዱስ ስጋውን ለሰጠን፣ እስከዚችም ሰአት ላደረሰን ለልዑል እግዚአብሔር ምስጋና ይገባል፣ ለወለደችው ለማርያም ምስጋና ይገባል፣ ለክቡር መስቀሉ ምስጋና ይገባል ለዘለአለሙ አሜን›› እያልን እናመስግን። በጥቅምት 25 ቀን በዓመታዊ የዕረፍት በዓላቸው ታስበው የሚውሉት ጻድቁና ሰማዕቱ አቡነ አቢብ ከቃልኪዳናቸው ረድኤት በረከት ይክፈሉን! ‹‹በእንተ አቡነ አቢብ!›› (ምንጭ፡- ደብረ ሰላም ቃጭልቃ አቡነ አቢብ ገዳም ያሳተመው ገድለ አቡነ አቢብ፣ ገጽ 105) @enabib

ይህ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ትክክለኛ ቅዱሳት ሥዕላትን በብራና በገበታ እና በሸራ ላይ የሳልናቸውን ምንለቅበት ነው። ትእዛዝ ለማዘዝ ይህንን ይጠቀሙ @jermi123 ☎0941256792 ይደውሉ!!!

ቅዱስ ሚካኤል ከቅዱስ ሙሴ እሥራኤልን ሲመራ እየተሰራ ያለ ጥንታዊ ሥዕል
ቅዱስ ሚካኤል ከቅዱስ ሙሴ እሥራኤልን ሲመራ እየተሰራ ያለ ጥንታዊ ሥዕል

የመድኃኒዓለም ሥዕለ አድኅኖ Size 50 በ 58 ዋጋ 5000 ብር በ0941256792 እንዲሁም ሌሎች ቅዱሳት ሥዕላትን በመደወል ማዘዝ ይቻላል።
+2
የመድኃኒዓለም ሥዕለ አድኅኖ Size 50 በ 58 ዋጋ 5000 ብር በ0941256792 እንዲሁም ሌሎች ቅዱሳት ሥዕላትን በመደወል ማዘዝ ይቻላል።

Repost from Ermi Art studio
በብሉይ ኪዳን የነበረ የክርስቶስ ምሳሌ የሆነው የቅዱስ መልከጼዴቅ እናት እና አባት ስማቸው ማነው? @enabib
Anonymous voting

አመጻችን በአንተ ፊት በዝቶአልና ኃጢአታችንም መስክሮብናልና አመጻችን ከእኛ ጋር ነውና ጽድቅንም አላወቅንምና በድለናል ዋሽተናልም አምላካችንንም መከተል ትተናል አመጻን ተናግረናል ከድተንሀልም የኃጢአትንም ቃል ፀንሰን ከልብ አውጥተናል። ፍርድን ከመከተል ወደኋላ ርቀናል ጽድቅም በሩቅ ቁሞአል ኢሳ 59፥12-14

በገበታ የተሰራ የ ቅዱስ ጊዮርጊስ የቅዱስ ገብረ መንፈስ ቅዱስ የቅዱስ ተክለ ሐይማኖት ሥዕለ አድኅኖ ይህ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ትክክለኛ ቅዱሳት ሥዕላትን በብራና በገበታ እና በሸራ ላይ የሳ
+1
በገበታ የተሰራ የ ቅዱስ ጊዮርጊስ የቅዱስ ገብረ መንፈስ ቅዱስ የቅዱስ ተክለ ሐይማኖት ሥዕለ አድኅኖ ይህ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ትክክለኛ ቅዱሳት ሥዕላትን በብራና በገበታ እና በሸራ ላይ የሳልናቸውን ምንለቅበት ነው። ትእዛዝ ለማዘዝ ይህንን ይጠቀሙ @jermi123 ☎0941256792 ይደውሉ!!!

እንኳን ለወረኃ ጽጌ እንድሁም ለጽጌ ጾመ በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ "እነሆ ክረምት አለፈ፣ ዝናብም አልፎ ሄደ፣ አበቦች በምድር ላይ ተገለጡ ፣ የዜማም ግዜ ደረሰ "። (መኃ ፪፥11)

ስለ ሀይማኖቱ ሲከራከር ጥርሱን በድንጋይ ያወለቁበት እና ጽህሙን የነጩት የሀይማኖት ጠበቃ የሆነው አባት ማነው?
Anonymous voting

በገበታ ላይ በመሰራት ላይ ያለ የእመቤታችን የ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ የአቡነ ተክለ ኃይማኖት ሥዕለ አድህኖ🙏
በገበታ ላይ በመሰራት ላይ ያለ የእመቤታችን የ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ የአቡነ ተክለ ኃይማኖት ሥዕለ አድህኖ🙏

Repost from Ermi Art studio
††† እንኳን ለቅዱሳን አባቶቻችን ሊቃውንት ዓመታዊ የጉባኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። ††† ††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ††† ††† ጉባኤ ኤፌሶን ††† ††† ቤተ ክርስቲያን እግዚአብሔርን ያከበሩትን: እርሱም ያከበራቸውን ሰዎች 'ቅዱሳን' ትላለች:: ራሱ ባለቤቱ "ኩኑ ቅዱሳነ እስመ ቅዱስ አነ-እኔ ቅዱስ ነኝና እናንተም ቅዱሳን ሁኑ" ብሏልና:: (ዼጥ. 1:15) እነዚህንም ቅዱሳን 'መላእክት: አበወ ብሊት: ነቢያት: ሐዋርያት: ሰማዕታት: ጻድቃን: ሊቃውንት: ደናግል: መነኮሳት: ባሕታውያን' ወዘተ. ብለን: ክፍለ ዘመን ሰጥተን በአበው ሥርዓት እናስባለን:: ከእነዚህ ቅዱሳን መካከልም አንዱንና ትልቁን ቦታ ቅዱሳን ሊቃውንት ይወስዳሉ:: 'ሊቅ' ማለት 'ምሑር: የተማረ: ያመሰጠረ: ያራቀቀ: የተፈላሰፈ: በእውቀቱ የበለጠ: የበላይ: መሪ: ሹም: ዳኛ' . . . ወዘተ ተብሎ ሊተረጐም ይችላል:: ወንጌል ላይም ጌታችን መድኃኔ ዓለም ኒቆዲሞስን "አንተ ሊቆሙ ለእሥራኤል-አንተ የእሥራኤል መምሕር (አለቃ) ነህ" ብሎታል:: (ዮሐ. 3:10) ስለዚህም 'ሊቃውንት' ማለት በእውቀት ከሁሉ በላይ የሆኑ እንደ ማለት ነው:: ዘመነ ሊቃውንት ተብሎ የሚታወቀው ከ3ኛው ክ/ዘመን መጨረሻ እስከ 6ኛው መቶ ክ/ዘመን አጋማሽ ያለው ሲሆን በዚህ ዘመን እንደ እንቁ ያበሩ: ብርሃንነታቸው በሰው ፊት የበራ ብዙ አበው ተነስተዋል:: ቅዱሳን ሊቃውንት ከሌሎች ምሑራን ቢያንስ በእነዚህ ነገሮች ይለያሉ:- 1.እንደ ማንኛውም ሰው ከተማሩ በኋላ እውቀቱ ይባረክላቸው ዘንድ ጠዋት ማታ በጾምና በጸሎት ይጋደላሉ:: 2.አብዛኞቹ ቅዱሳን ሊቃውንት ገዳማዊ ሕይወትን ጠንቅቀው ያውቃሉ:: 3.ምሥጢር ቢሰወርባቸው ሱባኤ ይገባሉ እንጂ በደማዊ ጭንቅላት አይፈላሰፉም:: 4.ፍጹም መናንያን በመሆናቸው ሃብተ መንፈስ ቅዱስ እንጂ የሚቀይሩት ልብስ እንኳ የላቸውም:: 5.እያንዳንዷን የመጽሐፍ ቃል ከማስተማራቸው በፊት በተግባር ይኖሯታል:: 6.እረኞች ናቸውና ዘወትር ለመንጋው ይራራሉ:: 7.ስለ ቀናች ሃይማኖት ብዙ ግፍን ተቀብለዋል:: 8.በኃይለ አጋንንት የመጡ መናፍቃንን ኃይለ መንፈስ ቅዱስን ለብሰው: መጻሕፍትን አልበው: ጥቅስ ጠቅሰው መክተዋል:: 9.ምግብናቸውንም ፈጽመው ዛሬ በገነት ሐሴትን ያደርጋሉ:: ††† የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የምትቀበላቸው የቅዱሳን ጉባኤያት 3 ብቻ ናቸው:: 1ኛ.በ325 (318) ዓ/ም በኒቅያ 318ቱ ሊቃውንት ያደረጉትን 2ኛ.በ381 (373) ዓ/ም በቁስጥንጥንያ 150ው ሊቃውንት ያደረጉትን: እንዲሁም 3ኛ.በ431 (424) ዓ/ም በዚህች ቀን 200ው ሊቃውንት ያደረጓቸውን ጉባኤያት ትቀበላለች:: ይሕስ እንደ ምን ነውቢሉ:- በወቅቱ ስመ ክፉ መናፍቅ ንስጥሮስ ተነስቶ የእስያ አብያተ ክርስቲያናትን አወካቸው:: ትምሕርቱ ክርስቶስን 2 አካል: ባሕርይ ነው (ሎቱ ስብሐት!) የሚል ነበር:: በእውነት እንየው ከተባለ ግን ጠቡና ጥላቻው ከድንግል ማርያም ጋር ነበር:: ምክንያቱም ጌታችንን ወደ 2 የከፈለው እመቤታችንን የአምላክ እናት አይደለሽም ለማለት ነው:: (ላቲ ስብሐት) ነገሩን ቅዱስ ቄርሎስ በሰማ ጊዜ ወዳለበት ሒዶ ቢመክረውም ንስጥሮስ ሊሰማ አልፈለገም:: በዚህ ምክንያት በትንሹ ቴዎዶስዮስ (የቁስጥንጥንያ ንጉሥ) ትዕዛዝ በኤፌሶን ታላቅ ጉባኤ እንዲሰበሰብ ሆነ:: ይህ ጉባዔ በቤተ ክርስቲያናችን የመጨረሻው የተቀደሰ ጉባዔ ነው:: በ431 ዓ/ም በኤፌሶን ከተማ የመናፍቃኑን ጥርቅም ሳንቆጥር ሃይማኖታቸው የቀና 200 ቅዱሳን ሊቃውንት ተገኙ:: የሚገባው ጸሎትና ሱባዔ ከተፈጸመ በኋላ ጉባዔው ተጀመረ:: አፈ ጉባዔው ሊቀ ማሕበር ማር(ቅዱስ) ቄርሎስ ነበርና በጉባዔ ፊት ንስጥሮስን ተከራክሮ ረታው:: ምላሽም አሳጣው:: ከቅዱሳት መጻሕፍት ክርስቶስ አንድ ባሕርይ መሆኑን: ድንግል ማርያምም ወላዲተ አምላክ መሆኗን እየጠቀሰ: በምሳሌም እያሳየ አስረዳ:: የሰይጣን ማደሪያ ንስጥሮስ ግን እንቢ: አላምንም በማለቱ ተወግዞ ተለየ:: ቅዱሳን ሊቃውንቱም በቅዱስ ቄርሎስ አርቃቂነት 12 አንቀጾችን አዘጋጅተው ወደ ዓለም ሁሉ ላኩ:: እሊህ አንቀጾች ዛሬም በሊቃውንቱ እጅ አሉ:: ይነበባሉ: ይተረጎማሉ:: ከእነዚህም አንዱ ድንግል ማርያም "ታኦዶኮስ (የእግዚአብሔር እናቱ) ናት" የሚል ነው:: እመቤታችንን የአምላክ እናት: ዘላለማዊት ድንግል: ፍጽምት: ንጽሕትና አማላጅ ብሎ ማመን ለሰማያዊ ርስት የሚያበቃ በጐ ሃይማኖት ነውና:: ጉባዔው ከተጠናቀቀ በኋላ ቅዱስ ቄርሎስ ንስጥሮስን ጠርቶ "በድንግል ማርያም እመን:: እርሷ ከልጇ ታስታርቅሃለች" ቢለው በድጋሚ "እንቢ" አለው:: ያን ጊዜ ሊቁ "ለአምላክ እናት ያልታዘዘ ምላስህ ላንተም አይታዘዝህ" ብሎ ረገመው:: ወዲያው ምላሱ ተጐልጉሎ ወጥቶ ደረቱ ላይ ወደቀ:: እንደ ውሻ እየተዝረከረከ ሂዶ ከወዳጆቹ ጋር ቁሞ ሳለ መሬት ተከፍታ ውጣዋለች:: ††† አምላከ ሊቃውንት ዛሬም ያሉንን አባቶች ይጠብቅልን: ያንቃልን:: ከቅዱሳን ሊቃውንት በረከትም አይለየን:: የእመ ብርሃን ፍቅሯንም ያሳድርብን:: ††† መስከረም 12 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ቅዱሳን 200ው ሊቃውንት (በኤፌሶን የተሰበሰቡ) 2.ቅዱስ ቄርሎስ ዓምደ ሃይማኖት 3.ጻድቅ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ 4.ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት 5.ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና 6.ቅዱስ ኢሳይያስ ነቢይ ††† ወርሐዊ በዓላት 1.ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት 2.ቅዱስ ላሊበላ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ) 3.ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ 4.ቅዱስ ድሜጥሮስ 5.ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ 6.ቅዱስ ቴዎድሮስ ምሥራቃዊ (ሰማዕት) 7.ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ 8.አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ ††† "ስለዚህ በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያንን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ዻዻሳት አድርጎ ለሾመባት: ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ:: ከሄድሁ በኋላ ለመንጋው የማይራሩ ጨካኞች ተኩላዎች እንዲገቡባችሁ እኔ አውቃለሁ:: ስለዚህ 3 ዓመት ሌሊትና ቀን በእንባ እያንዳንዳችሁን ከመገሰጽ እንዳላቋረጥሁ እያሰባችሁ ትጉ::" ††† (ሐዋ. ፳፥፳፰) ††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††

Repost from Ermi Art studio
እንኳን #ለእመቤታች_ለቅድስት_ድንግል_ማርያም #በፄዴንያ_አገር_በማርታ_ቤት ሥጋ የለበሠች ከምትመስል #ከእመቤታች_ሥዕል ከሠሌዳዋ #ቅባት_እየተንጠፈጠፈ ተአምር ለሠራችበት ቀን መታሰቢያ በዓል፣ #አምላክን_ለወለደች_ለእመቤታችን #ለቅድስት_ድንግል_ማርያም_ለተወለደችበት_ለልደቷ በዓል መታሰቢያ (ይህም የአስቄጥስ ገዳም #የከበረ_አባት_አባ_መቃርስ በጻፈው መጽሐፈ ግጻዌ ተጽፏል እንዲሁም ደግሞ በላዕላይ ግብጽ በሚገኝ መጽሐፈ ግጻዌ #የከበረች_ድንግል_እመቤታችንን #የከበረች_ቅድስት_ሐና በታኅሣሥ ወር በዐሥራ ሰባት እንደፀነሰቻትና መስከረም በዐሥር ቀን እንደወለደቻት ተጽፏል)፣ ለከበረች #ለቅድስት_መጥሮንያ_ሰማዕትነት ለተቀበለችበት በዓል ዕረፍት፣ በሰላም አደረሰን። በተጨማሪም በዚህች ቀን ከሚታሰቡ፦ #የጌታችን_የአምላካችን_የመድኃኒታችን_የኢየሱስ_ክርስቶስ #ቅዱስ_መስቀል_ወደ_አገራችን_ኢትዮጵያ ድንበር ከደረሰበት (ተቀጽል ጽጌ) አፄ መስቀል) ቀን ለመታሰቢያ በዓልና ከከሀዲው #ሆሎፎርኒስ እጅ በጥበቧ እሥራኤልን ካዳነቻቸው ከጥበበኛ ከከበረች #ከቅድስት_ዮዲት_በዓለ_ዕረፍትና #ከቅድስት_አትናስያናና_ሦስት_ልጆቿ #ከቅዱስ_ሉቃስ_ወንጌላዊ፥ ከኢትዮጵያዊው ንጉሥ #ከአጼ_ዳዊት፥ እና ከታላቋ የኢትዮጵያ ንግሥት #ከንግሥተ_አዜብ_ወይም_ንግሥተ_ሳባ_አልያም_ንግሥት_ማክዳ ከመታሰቢያ በዓላቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።

እግዚአብሔር በኃጥአን ላይ የሚያሳየው ትልቁ ቁጣ አለመቆጣቱ ነው ምክንያቱም “እግዚአብሔር የወደደውን ይገሥጻልና፥ አባት የሚወድደውን ልጁን እንደሚገሥጽ።”ምሳ 3፥12 [አባ ጄሮም]

ዐቢይ ዓመታዊ ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ መስከረም 4 2017 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ጀምሮ በሐመረ ብርሐን የብራና ሥራ ድርጅት
ዐቢይ ዓመታዊ ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ መስከረም 4 2017 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ጀምሮ በሐመረ ብርሐን የብራና ሥራ ድርጅት