cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking ÂŤAccept allÂť, you agree to the use of cookies.

avatar

Muzamil tube🇩🇿

Advertising posts
199
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-1230 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

🥀የሩህ ንፋስ የታደላት ብቻ የሚያገኛት ናት... ሰዓቷ ግሩም ነው... አየሯ ጣፋጭ እና የሰከነ ነብሲያን ወደ ተረጋጋ መንገድ ትመራለች ... ከወተት የጠራ ንፁህ አየርን ታድላለች ሙዕሚኖች እንጂ አይቀምሷትም... ሰጋጆች እንጂ አያውቋትም... የኩፋሮች ሀሲዶች እና የሙናፊቆች እስትንፋስ የማይነካት ፈጅር... መልዕክቷ ምነኛ አማረ 🌺ቀናችንን በቁርዓን በዚክር እና አላህን ምህረት በመጠየቅ እናሳምረው @anbeb_islamic
Show all...
🥰 1
"ጅማሬህ ታናሽ ነው!" የሚሉ ....የፍፃሜህን ታላቅነት ሲያውቁ .....አፋቸውን ይዘጋሉ:: በትንሽ መጀመር .....ካለምጀመር ትልቅ ነው! ነገር ግን ትንሿን ትልቅ የሚያደርግ እምነትን ያዝ ....አምላክህ ማባዛትን ያውቅበትል:....መክፈል ያለብህን ዋጋ ስትከፍል አብዝቶ ይከፍልሃል :... ፈተና  በመንገድህ ሲቆም አታቁም:: @anbeb_islamic
Show all...
👍 1
🌹🌹#ውዷእህቴሆይ !🌹🌹 ለቤተሰቦችሽ የሚገባቸውን ሀቅና ክብር ስጭ! በተለይም! ደግሞ ገና እንዴት አድርጎ እንደሚያስተዳርሽ ሳታውቂ! ማለቴ ተንከባክቦ ይሁን ረግጦ የሚይዝ ብቻ ትዳር ልይዝ ነው ብለሽ! ቤተሰብሽን ሸሸት ሸሸት + ክብራቸውን ጎደፍ ጎደፍ ለምታደርጊዋ! 💐 #እህቴ_ሆይ! ቤተሰቦችሽ አንች ዛሬ ለደረሽበት መልካም ነገር ሁሉ! ☞በአላህ ፈቃድ በነሱ ሰበብ ነው!! ደሀም ይሁኑ ሀብታም ጥቁርም ይሁኑ ቀይ ሽማግሌ + አዛውንትም ይሁኑ ገና ጎረምሳ ዓሊምም ይሁኑ ጃሂል በሽርክ የተጨማለቁ ሙስሊምም ይሁኑ ካፊር (በአላህ የካዱ)/ የሌላ ዕምነት ተከታይ!! አካለ ጎደሎም ይሁኑ ሙሉ አካል ያላቸው!! ብቻ አንችን ለማሳደግ ብዙ ነገር ሆነዋል! በመጥፎ (አላህን በማያስቆጣ) ነገር እስካላዘዙሽ ድረስ! ☞ትዛዛቸውን ልታከብሪ ☞ሀቃቸውን ልጠብቂ ☞ክብራቸውን ላታወርጂ ግድ ይልሻል!!! ☜ ﻛﻤﺎ ﻗﺎﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﺗﻌﻠﻰ -: ﻭَﻗَﻀَﻰٰ ﺭَﺑُّﻚَ ﺃَﻟَّﺎ ﺗَﻌْﺒُﺪُﻭﺍ ﺇِﻟَّﺎ ﺇِﻳَّﺎﻩُ ﻭَﺑِﺎﻟْﻮَﺍﻟِﺪَﻱِﻥْ ﺇِﺣْﺴَﺎﻧًﺎ ﺇِﻣَّﺎ ﻳَﺒْﻠُﻐَﻦَّ ﻋِﻨﺪَﻙَ ﺍﻟْﻜِﺒَﺮَ ﺃَﺣَﺪُﻫُﻤَﺎ ﺃَﻭْ ﻛِﻠَﺎﻫُﻤَﺎ ﻓَﻠَﺎ ﺗَﻘُﻞ ﻟَّﻬُﻤَﺎ ﺃُﻑٍّ ﻭَﻟَﺎ ﺗَﻨْﻬَﺮْﻫُﻤَﺎ ﻭَﻗُﻞ ﻟَّﻬُﻤَﺎ ﻗَﻮْﻟًﺎ ﻛَﺮِﻳﻤًﺎ ، #ጌታህም እንዲህ ሲል አዘዘ እርሱን እንጂ ሌላን አትገዙ! በወላጆቻችሁም መልካምን ስሩ + በአንተ ዘንድ ኾነው አንዳቸው ወይም ሁለታቸው እርጅናን ቢደርሱ #ኡፍ አትበላቸው + አትገላምጣቸውም! ለነርሱም መልካምን ቃል ተናገራቸው!! [ ﺳﻮﺭﺓ ﺍﻹﺳﺮﺍﺀ ‏( ٢٣ )] በይ እንዳውም እ እዝነት አድርጊላቸው + ዱዓ አድርጊላቸው ነው የተባልሽው! ☜ ﻛﻤﺎ ﻗﺎﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﺗﻌﻠﻰ -: ﻭَﺍﺧْﻔِﺾْ ﻟَﻬُﻤَﺎ ﺟَﻨَﺎﺡَ ﺍﻟﺬُّﻝِّ ﻣِﻦَ ﺍﻟﺮَّﺣْﻤَﺔِ ﻭَﻗُﻞ ﺭَّﺏِّ ﺍﺭْﺣَﻤْﻬُﻤَﺎ ﻛَﻤَﺎ ﺭَﺑَّﻴَﺎﻧِﻲ ﺻَﻐِﻴﺮًﺍ ለሁለቱም ከዕዝነትህ የመዋረድን ክንፍ ዝቅ አድርግላቸው! #ጌታዬ ሆይ! በህፃንነቴ በርኅራኄ እንዳሳደጉኝ እዘንልላቸውም በል!! [ ﺳﻮﺭﺓ ﺍﻹﺳﺮﺍﺀ ‏( ٢٤ )] So ይግባሽ! ቤተሰቦችሽ ሁሌም ለአንች ብዙ ነገር ኋኚዎች ናቸው! ብታገቢ + ብትወልጂ + ስራ ብትይዥ +……………………… አንች ከምትደሰችው በላይ! እነሱ ናቸው የሚደሰቱት!! እህቴ ሆይ! 💐 #ይሄን_ስልሽ #አታግቢ + የምታገቢውን ሰው አትውደጂ ማለቴ አይደለም! ይሰመርበት! #ላኪን የምታገቢውን ሰው በስልክ + በቃላት/በንግግር አወ ሰዎች በነገሩሽ እንጂ! በተግባር አታውቂውም! #በተለይ ደግሞ በአሁኑ ጊዜ! በአፍ 1000 አውርቶ በተግባር 0 ሆነው ለሚገኙ! ከጥቂቶቹ አላህ ካዘነላቸው ውጭ! አብዘሀኛው አበድኩልሽ + ወደድኩሽ + ልሞትብሽ ነው ብሎ አግብቶ እየረገጠ ለሚይዘው! አው ቤተሰቦቹ ለልጄ ልጂህን ስጠኝ ብለው ተጎናብሰው ለምነው ከልጃቸው ጉያ + ከቀያቸው ከከረመች እንደስስት ለሚቀያየሩት! ታዳ እንዴት ለማታውቂው አካል አንችነትሽን + ቤተሰብሽን ታረክሻለሽ?? ወደድሽም ጠላሽም ቤተሰቦችሽ ቤተሰቦችሽ ናቸው! ሀቃቸውን + ክብራቸውን ጠብቂ!! ዛሬ ያበድሽለት ፍቅር ተብዬ ነገ ይጠለሻል!! ቤተሰቦችሽ ግን ለአንች ሁሌም በአላህ ፈቃድ የደስታ ሰበብ ናቸው! ☞ አንዴ ካመለጡሽ #መተኪያ የላቸውም!!! ﻗﺎﻝ ﺭﺳﻮﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ -: ﺭﺿﺎ ﺍﻟﺮﺏ ﻓﻲ ﺭﺿﺎ ﺍﻟﻮﺍﻟﺪﻳﻦ، ﻭ ﺳﺨﻄﻪ ﻓﻲ ﺳﺨﻄﻬﻤﺎ، ‏[ ﺻﺤﻴﺢ ﺍﻟﺠﺎﻣﻊ ‏( ٣٥٠٧ )] የአላህ መልዕክተኛ ( ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ ) እንዲህ ብለዋል:-የአላህ ውዴታ በሁለቱ ወላጆች ውዴታ ውስጥ ነው! #ጥላቻውም ሁለቱን ወላጆች በመጥላት ውስጥ ነው!!! እናም ጠንቀቅ በይ!! ወላሁ ተዓላ አዕለም! @anbeb_islamic
Show all...
🙏 2
Show all...
$APE AIRDROP

$APE GET THE MOON

ችግር በበዛብህ ጊዜ ያ መልካሙን አርዓያህን ነብዩ ﷺ አስታውስ! ገና በጨቅላ ዕድሜያቸው የቲም ሆኑ። ድግምተኛ፣ እብድ፣ ውሸታም… ተባሉ ክብራቸውን ጎደፈ፣ ጥርሳቸው ተሰበረ፣ በድንጋይ ተፈነከቱ፣ ከሀገራቸው አባረሯቸው፣ ሊገድሏቸውም ሞከሩ… ድሀ ሆነው ይህችን ዱንያ ኖሯት፣ ከረሀብ የተነሳ ሆዳቸው ላይ ድንጋይ ያስሩ ነበር፣ ከ7 ልጆቻው ስድስቱን አጡ… ይህን ሁሉ መከራን ተጋፍጠው አላህን አመስጋኝ ነበሩ። አርዓያህ ሀቢቢ (ﷺ ) ናቸው? ለችግሮችህ አመስጋኝና ታጋሽ ሁን! @anbeb_islamic
Show all...
✍ አንድ ገበሬ የሚወደው ፈረሱ ይታመምበትና ወደእንስሳት ሀኪም ጋር ይዞት ይሄዳል። ሀኪሙም ፈረሱ ጉረኖ ድረስ በመሄድ በሚገባ መረመረው። ለገበሬውም - "ተላላፊ በሽታ ስላለበት ለሶስት ቀን መድሀኒት እንስጠውና ካልተሻለው ወደሌሎቹ ፈረሶች እንዳይዛመት እንገለዋለን" ብሎት ሄደ። ይሄንን ሲያወሩ ፍየል ተደብቃ ሰምታቸው ኖሯል ለፈረሱ እያለቀሰች ያወሩትን ነገረችውና "እንደምንም ብለህ ተነስ! ያለበዛ ይገሉሀል" እያለች ተንሰቀሰቀች። የመጀመርያው ቀን ሀኪሙ መጥቶ መድሀኒቱን ሰጥቶት ወጣ። ወድያው ፍየል ለምለም ሳርና አተላ ይዛለት መጣች ና "እንደምንም ተነስ!" ብላ ተማፀነችው። በሁለተኛውም ቀን ሀኪሙ ሲመጣ ፈረሱ ምንም ለውጥ አላመጣም መድሀኒቱን ወግቶት እስከ ቀጣዩ ቀን ጠብቆት ካልተሻለው እንደሚገለው ለገበሬው ነግሮት ሄደ። ይሄን ግዜ ፍየል ለምለም ሳር ፈልጋ ለፈረሱ በማምጣት አፅናናችው። የመጨረሻ ቀን ሀኪሙ ሲመጣ አሁንም ፈረሱ ምንም ለውጥ አላመጣም ይሄን ጊዜ ከገበሬው ጋር ቢገሉት እንደሚሻል በር ላይ ቆመው ሲያወሩ ፍየል ቀስ ብላ ተደብቃ ፈረሱ ጋር ገብታ እየተንሰቀሰቀች- " በናትህ አኔንም ጓደኛ አታሳጣኝ ካልተነሳህ ይገሉሀል" ብላ አለቀሰች። ፈረሱ በፍየሏ ግፊት ቀስ ብሎ ተነሳ። ፍየል ደስ አላት። "ጎበዝ አስኪ እሩጥ" እያለች አበረታችው። ፈረሱ በወኔ በፊት ከሚሮጥበት ፍጥነት በላይ ሮጠ። ይሄን ጊዜ ፍየል በደስታ ጮሇች። ገበሬውና ሀኪሙ የምን ጩሇት ነው ብለው ሲያዩያዩትን ማመነን አቃታቸው። ፈረሱ በሓይል አየሮጠ ነው። ገበሬው በደስታ ብዛት ሀኪሙን አንቆ ሳመው። እረኛውን ጠርቶት "ዛሬ እኔ ቤት ትልቅ ድግስ አለ! ስለዚህ ቶሎ በሉ #ፍየሏን_እረዱልኝ! ምሳ እዚህ ነው" አለ።🤦‍♂😁 ✍አንዱ የሌላው መሰላል ነው። ለአንዱ ሂወት ለሌላው ሞት ነው። ለሀብታም ሂወት የደሀው ችግር ግድ ነው። ለአንዱ ማለፍ የሌላው ውድቀት ወሳኝ ነው። አለም የምትመራበት ህግ ነው። ሼር በማድረግ ለወዳጆቾ ያድርሱ @anbeb_islamic
Show all...
👍 1❤ 1
«የስስታምነት ጥግ    ሰውየው እጅግ በጣም ስስታም ሰው ናቸው። አንድ ቀን ከቤታቸው እንግዳ ይመጣና ልጃቸውን ጠርተው ልጄ ሆይ! ወደ ገበያ ሂድና ምርጥ የተባለ ስጋ መርጠህ ገዝተህ አምጣ ይሉታል። (ይህንን ትዕዛዝ ሲሰጡት እንግዳው እየሰማ ነበር።) ሆኖም ልጅ ወደ ገበያ ሄዶ ቆይቶ ስጋውን ሳይገዛ ወደ ቤት መጣ።ባዶ እጁን መምጣቱን የታዘቡት አባት ምነው የት አለ ስጋው ? ሲሉ ጠየቁት። ልጁም እንዲህ አላቸው፦ ስጋ ቤት ሄድኩና ምርጥ ስጋ ስጠኝ ስለው ቅቤ የመሰለ ስጋ ነው የምሰጥህ ሲለኝ አይ ቅቤ የመሰለ ስጋ ከምገዛማ ቅቤ አልገዛም እንዴ አልኩና ቅቤ ነጋዴ ጋር ሄድኩ። ቅቤ ነጋዴውን ደግሞ ምርጥ የሆነ ቅቤ ስጠኝ ስለው ኸረ አብሽር ማር የሆነ ቅቤ እሰጥሃለሁ አለኝ። እኔም ማር የሆነ ቅቤ ከምገዛ ማር አልገዛም እንዴ ብዬ ማር ነጋዴ ጋር ሄድኩኝ። ማር ነጋዴውን ሄጄ ምርጥ የሆነ ማር ስጠኝ አልኩት። እሱ ደግሞ በተራው ኩልል ያለ ውሃ የመሰለ ማር ነው የምሰጥህ አለኝ እኔም ንፁህ ውሃማ ቤት አለ አይደል እንዴ ብዬ ሳልገዛ ትቼ መጣሁ አላቸው። አባትየውም በልጃቸው ውሳኔ ተደስተው ማሻ አላህ ልጄ ልክ እንደ አባትህ ቸርና ለጋስ የሆንክ ልጅ እኮ ነህ ብለው ያሞካሹት ጀመር። እንግዳው ይህንን ሁሉ ይሰማ ይታዘብ ነበር ና በንዴት ፊቱ ቀላ አረረ። ብዙም ሳይቆዩ አባት ወደ ልጁ ጠጋ አሉና በጆሮው ፦ ግን አንድ ነገር ተሸወድክ ከአንዱ ሱቅ ወደ ሌላው ሱቅ ስትዟዟር እኮ ጫማህን ጨረስከው ሲሉት ልጁ ቀበል አድርጎ አብሽር አባቴ የእንግዳውን ጫማ ነበር ለበሼ የዞርኩት አላቸው።» የአጣቢ ልጅ አለቅላቂ ይሉሀል ይህ ነው🫤 @anbeb_islamic
Show all...
ስለዚህ ሰው ምን ትላላችሁ ? 🌹🌹🌹  💎💎   🌹🌹🌹   💚 በእናቱ ሆድ ውስጥ እያለ ወላጅ አባቱን በሞት ተነጠቀ። 💛 የስድስት ዓመት ህፃን እያለ ወላጅ እናቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች።                ስለዚህ ሰው ምን ትላላችሁ ? ❤️ የስምንት ዓመት ህፃን እያለ በፍቅር ተንከባክበው ያሳደጉት አያቱን አይቀሬ የሆነው ሞት ወሰዳቸው። 💚 እንደ አይን ብሌናቸው የሚሳሱለት አጎቱ እና በማራኪ ስብዕናው ተረታ የትዳር አጋሩ ለመሆን የበቃቸው ውድ ባለቤቱ በአንድ ዓመት ውስጥ ከአይኑ ተሰወሩ። ለህይወቱ ወሳኝ የነበሩትን ምሰሶዎች ሞት ነጠቀው። ያ ፈታኝ ጊዜ «የሀዘን ዓመት» የሚል ስያሜ ተሰጠው።               ስለዚህ ሰው ምን ትላላችሁ ?? 💛 በምድር ላይ ከሁለት ዓመታት ዕድሜ በላይ ያልቆዩ ሁለት ህጻናት ወንድ ልጆቹን በማለዳ ሞት ቀጠፋቸው። በህፃናቱ ፈገግታ ደምቆ የነበረው ቤት የሀዘን ጥላ አጠላበት። ❤️ ከእርሱ ህልፈት በኋላ በስድስተኛው ወር በሞት ከተከተለችው ተናፋቂ ልጁ በስተቀር ሁሉም ሴቶች ልጆቹ በህይወት እያለ ወደ መጪው ዓለም ተጓዙ።              ስለዚህ ሰው ምን ትላላችሁ ? 💚 የአባቱ ጥሪት የነበሩት አጎቱ ተገደሉ። መገደል ብቻም ሳይሆን የሰው ልጅ ያደርገዋል ተብሎ የማይታሰብ ጭራቃዊ ተግባር በአካላቸው ላይ ተፈፀመ። አንዲት እንስት አስክሬኑን በሰንጢ አስቀድዳ ጉበቱን በላችው። የዚህ ሰው ሀዘን ከሚገመተው በላይ በረታ። 💛 ጧኢፍ ነዋሪዎቿን በነቂስ አውጥታ የስድብ እና የድንጋይ ናዳ እንዲወርድበት ፈቀደች። ምድር ከሰውነቱ የሚፈሰውን ደም መጠጠች። ታሪክ ክስተቱን በደማቅ ገጹ አስፍሮ ለትውልድ አስተላለፈ። ጧኢፍ መስክሪ ለዚያ አርበኛ ለሰላሙ አባት ለዓለም ሁነኛ ነዋሪዎችሽ የሰሩት ግፍ በሙሐመድ ላይ ባንቺው ደጃፍ መላ አካሉን አሰቃዩት ሰላም ባመጣ በደም ሸኙት ያሆደ ባሻ ይቅር አላቸው ሊጠፉ ደርሰው ደረሰላቸው                           ስለዚህ ሰው ምን ትላላችሁ ?? ❤️ በአንድ ታላቅ ዘመቻ የፈት ጥርሱ ተሸረፈ። ብርሃናማ ፊቱ በደም ተለወሰ።  💚 ግንባሩን ከመሬት አዋዶ ከፈጣሪው ጋር በለሆሳስ ሲያወራ የመካ ቂሎች በትከሻዎቹ መሃል የግመል አንጀት እና ደም ሲያፈሱበት ግንባሩን ከመሬት ለአፍታ አላነሳም ነበር።                 ስለዚህ ሰው ምን ትላላችሁ ? 💛 በመተት እና ድግምት ሲያሰቃኙት፣ በመርዝ የተለወሰ ምግብ ሲሱጠት፣ ከሚናፍቅው የትውልድ ቀዬ ሲባረር «ይቅር ባይነት» የዘውትር ስንቁ ነበር ። ❤️ ይህን ሁሉ ስቃይ በተሸከመ አካልና መንፈሱ ታግዞ እግሮቹ አስከሚያብጡ ድረስ ሌሊቱን ሙሉ በመቆም አመስጋኝ ባሪያ ለመሆን ከአምላኩ ጋር ያወጋል።     እናት ለልጇ በትምህርቱ ዓለም ብቻ የከፈለችውን መስዋዕትነት ብንፈትሽ አንድ ነገር ይከስትልናል። ለአብራኳ ክፋይ ከልጅነት እስከ ወጣትነት የዕድሜ ዘመኑ የዋለችው ውለታ መለኪያ የለውም። ከማዋዕለ-ህፃናት እስከ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ይዘልቅ ዘንድ በትንሹ 23 ዓመታትን የፈጀ ጥረት ታደርጋለች። የእናት እያንዳንዱ የህይወት ምዕራፍ በአደገኛ ምጥ የተሞላ ነው። አንተን ከወለደችበት ምጥ ባሻገር ሌላ ስፍር ቁጥር የለሽ የህይወት ምጥ አለ።             ይህን ከግንዛቤ ካስገባችሁ  ውስን በሆኑ 23 ዓመታት ውስጥ ብቻ የሰውን ልጅ ከፍጡራን ባርነት አላቆ አላህን ወደማምለክ ነፃነት ያሻጋገረ ፣ ከጠባብ ዓለማዊ ህይወት አውጥቶ ወደ ሰፊው የመንፈስ ዓለም ያመጠቀ ፣ ከምድራዊ እምነቶችና ስርዓቶች ጭቆና አላቆ ለኢስላም ፍትህ ያበቃ ፈርጡ የሰው ልጅ ሙሐመድ (صلى الله عليه وسلم) ውለታ ምን ያህል የከበደ መሆኑን ትገነዘባለህ።  ልቦቻችን ውሃ እንዳጣ የዓረቢያ ምድረ በዳ ስንጥቅ በዝቶባቸዋልና ፈለግህን በመከተል በፍቅርህ ይረሰርሱ ዘንድ አላህ ያግዘን  !!! @anbeb_islamic
Show all...
❤ 1
❤️ከእንቅልፍ መነሳትህ አላህ ተውባ እንድታረግ ሌላ ቀን ሰጥቶህ ነው እንጂ... የትላንትናውን ወንጀል እንድታሟላው አይደለም:: ሰባሁል ኸይር😊
Show all...
💦ሸይኽ ዑሰይሚን  (ረሂመሁላህ) እንዲህ ብለዋል ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ 🔻"#ስትጠም መንገድ የሚያመላክቱህ ሲጠፋህ የሚጠቁሙህ፣ 👉#ስትረሳ የሚያስታውሱህን፣ #ያላወቅክ ከሆነ የሚያስተምሩህን #ምርጥ ሰዎችን ለመጉዳኘት #ጥረት ይኑርህ።"                           [ሸርሕ አልቡኻሪ:(1/62]
Show all...
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.