en
Feedback
Orthodox My Religion Mary my Mother 21

Orthodox My Religion Mary my Mother 21

Open in Telegram

በዚህ ቻናል ላይ ኦርቶዶክሳዊ ❖ ❖ መዝሙሮችን ❖ ትምህርቶችን ❖ መንፈሳዊ ምስሎችን ❖ መንፈሳዊ ፅሁፎችን ያገኛሉ orthodox_photo

Show more
268
Subscribers
+224 hours
+157 days
+4430 days
Posts Archive
nolaawi_hheere_nolawi_tube_yeqere_selaalekanye_nawe_zamaari_di_n.m4a6.19 MB

🙏🙏🙏🥰🥰🥰
🙏🙏🙏🥰🥰🥰

_እኔ_አንተ_ፊት_Ene_Ante_Fit_ሊቀ_መዘምራን_ቴዎድሮስ_ዮሴፍ128k.m4a5.35 MB

🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏

player_local_media_share_img_v2.png0.33 KB

%F0%9F%94%B4_%E1%8B%A8%E1%8A%95%E1%88%B5%E1%88%83_%E1%8B%9D%E1%88%9B%E1%88%AC.m4a5.77 MB

_እሰይ_ነጋ_ላመሰግንህ_ነው_ሊቀ_መዘምራን_ቴዎድሮስ_ዮሴፍ_Gu_88l0yQvM_140.mp37.80 MB

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን __ 5️⃣#ትንሣኤ_ለምን_አስፈለገ? ለሰው ትንሣኤ ያስፈለገበት ምክንያት ሰው የተፈጠረው ነፍሱና ሥጋው በሕይወት ለመኖር እንጅ ለመሞት አልነበረም። ነገር ግን በኃጢአት ምክንያት በራሱ ላይ ሞቱን በማምጣቱ ሞት የማይገባው አምላክ ሞቶ ከኃጢአት ፍርድ በማዳን ሞትን በማጥፋት በቀደመው ሕይወቱ እንዲኖር ለሰው ልጅ ተንሣኤ ሰጠው። (1ኛ ተሰ 13፥16  ፤  ዳን 12፥2) ሥለዚህ ወደ ቀደመ ሕይወታችን ለመመለስ ትንሣኤ አስፈለገ። 6️⃣#ሥለ_ምሥጢረ_ትንሣኤ_ሙታን_የተነገሩ_ትንቢቶች ምሥጢረ ተንሣኤ ሙታን ቀደም ብሎ በነቢያት ታውቆ ስለነበር ስለ ትንሣኤ ሙታን ብዙ የተነገሩ ትንቢቶች አሉ። (ኢሳ 26፥19  ፤  ትን ዳን 12፥2) 7️⃣#ምሥጤረ_ትንሣኤ_ሙታን_መጽሐፍ_ቅዱሳዊ_ምሳሌ ◾️በአቤል ሞት ሞታችን፣ በሔኖክ እርገት ትንሣኤያችን ተረጋግጧል። (ዘፍ 4፥8  /  5፥24) ◾️ኖኅ በጥፋት ውሃ ጊዜ ወደ መርከብ መግባቱ ለመቀበራችን፤ መውጣቱ ለመነሳታችን ምሳሌ ነው። (ዘፍ 7፥1 / 8፥6፥12) ◾️የአሮን ብትር ቀድሞ በልምላሜ መኖሯ በሕይወተ ሥጋ ለመኖራችን፣ ኋላ መድረቋ ለመሞታችን፣ ዳግመኛም መለምለሟ ለተንሣኤያችን ምሣሌ ነው። (ዘኁ 17፥6-10) 8️⃣#ሞት_ምንድን_ነው? ሳይሞቱ ትንሣኤ የለምና የዚህን ዓለም ኑሮ መግቻ፣ የነፍስ ከስጋ መለየት፣ ወይም ሞት የምንለው በቅድስት ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ እርፈት፣ እንቅልፍ ይባላል። ➼እርፈት፦ የተባለ ከዚህ አለም እንግለት ስምናርፍ ነው። ➼እንቅልፍ፦ የተባለ ደግሞ እንቅልፍ ለሆነ ጊዜ ተኝተን እንደምንነሳ ሁሉ ሞትም እስከ ዳግም ምጻአት አንቀላፍተን ለዘላለም ስለምንነሳ ነው። "ወዳጃችን አልዓዛር ተኝቷል ነገር ግን ከእንቅልፉ ላስነሳው እሄዳለሁ አላቸው" (ዮሐ 16፥16)። እኛ ክርስቲያኖች ይህንን ሞት (የነፍስ ከሥጋ መለየት) በፍፁም ልንፈራው አይገባም። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ "ልሔድ ከክርስቶስም ጋር ልኖር እናፍቃለሁ ከሁሉ ይልቅ እጅግ የሚሻል ነውና"(ፊል 1፥23) ሲል እራሳችንን በንስሐ አዘጋጅተን የማይቀር መሆኑንም ተረድተን ልንጠብቀው ይገባል። ልንፈራው የሚገባውስ ሁለተኛውን ሞት እንደ ሥጋ ሞት ማረፍ ሳይሆን ማብቂያ የለለው ዘላለማዊውን ሞት ነው። "ሥጋንም የሚገድሉትን ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ ይልቅስ ነፍስንም ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚችለውን ፍሩ" (ማቴ 10፥28) ይህ የሞት ሞት/ሁለተኛ ሞት በዳግም ትንሣኤ ጊዜ ከግራ ቁመት በኋላ ይፈጸማል። (ማቴ 25፥41-46) ~~~~

3️⃣#የሦስት_ቀንና_የሦስት_ሌሊት_አቆጣጠር ይሄን ጥያቄ በብዙ ቦታ ቡዙ ሰዎች ሲያነሱት ይደመጣል። ነገር ግን ችግሩ ከኛ የአቆጣጠርና የአረዳድ ውስንነት እንጂ ጌታ በከርሰ መቃብር ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ቆይቷል። "ኢየሱስም መልሶ ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ አላቸው" (ዮሐ 2፥19) ቤተ መቅደስ እያለ የሚጠራው የራሱን ሥጋ ሲሆን አነሣዋለሁ ማለቱ የለበሰው ሥጋ በተዋሐደው መለኮት ኃይል እንደሚነሳ ሲያስረዳ ነው። በጥሞና ተከታተሉ፦ በቅድሚያ ይህ አቆጣጠር የእብራይስጥ አቆጣጠር መሆኑን ማስታወስ ይገባል። እብራውያን አንድን አዲስ ዕለት ሲቆጥሩ ከምሸቱ 12 ሰዓት ጀምረው በመቀበል ነው። ለምሳሌ ቅዳሜ የሚገባው አርብ ማታ 12 ሰዓት ነው። ከ12 ሰዓት በፊት ያሉት ሰዓታት ግን አንድ ሰዓትም ብትሆን እንደ አንድ መዓልትና ሌሊት የሚቆጠርበት አግባብ ነው ያለው። ቀኑ ሌሊቱን ሌሊቱም ቀኑን እየሳበው ነው የሚቆጥሩት። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተቀበረው አርብ ከ12 ሰዓት በፊት ነው። ማር 15፥42-46 ስለዚህ የተቀበረበት ሰዓት የአርብን ማዓልት/ቀን እና ሌሊት ስቦና ጠቅልሎ ይይዛል። ይህም ማለት፦ ◾️ጌታ የተቀበረባት ያቺ የአርብ 11 ሰዓት ከ12 ሰዓት በፊት በመሆኗ ከኋላዋ ያለፉቱን ቀንና ሌሊት ስባ እንደ አንድ ሙሉ ቀን ትቆጠራለች። (አንድ ሌሊትና አንድ ቀን) ◾️ቅዳሜ በራሷ ስትቆጠር ዓርብ ከማታ 12 ሰዓት ትጀምርና ሌሊቱን ጨምራ እስከ ቅዳሜ ማታ 12 ሰዓት ድረስ ትውላለች። (አንድ ቀንና አንድ ሌሊት) ◾️እሑድ ከቅዳሜ ማታ 12 ሰዓት ጀምራ ትገባና እስከ እሑድ ማታ 12 ሰአት ስለምትቆይ አንድ ቀን እና አንድ ሌሊት ትሰጠናለች።  በድምሩ ሦስት ማዕልትና ሦስት ሌሊት ሆነ ማለት ነው። 4️⃣#ትንሣኤ_ያለው_ፍጡር_ማን_ነው? ከ22ቱ ሥነ ፍጥረት መካከል የትንሣኤ ሙታን ባለቤት የሆነው ሰው ብቻ ነው። መላእክት የማይሞቱ ሲሆኑ እንሰሳትና የመሳሰሉትም ደግሞ ደመ ነፍስ እንጅ ሕያውነት የላቸውም ሰው ግን ጥንትኑ ሲፈጠር ነፍስና ሥጋው በሞት ሳይለያዩ ለዘላለም እንዲኖሩ ነበር። ስለዚህ የመላእክትን/ህያውነትን እና የመሞትን ፀጋ የያዘ ሰው ብቻ ስለሆነ የተንሣኤ ሙታን ባለቤት ሁኗል። 1ኛ ቆሮ 15፥42 ~~~~ ቀጣይ ትምህርታችን የትንሣኤ ሙታን አስፈለጊነት #ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!! ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇 •➢ ሟር // SHARE ╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮ @ctwobek @ctwobek @ctwobek ╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን                                                __      🌹#ምሥጢረ_ተንሣኤ_ሙታን🌹 1️⃣የትንሣኤ ሙታን ትርጉም ምንድነው? 2️⃣ትንሣኤን ማን መሠረተው? 3️⃣የሦስት ቀንና የሦስት ሌሊት አቆጣጠር እንዴት ነው? 4️⃣ትንሣኤ ያለው ፍጡር ማን ነው? 5️⃣ትንሣኤ ለምን አስፈለገ? 6️⃣ሥለ ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን የተነገረ ትንቢት ታውቃለህ? 7️⃣ለምሥጤረ ትንሣኤ ሙታን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ምሳሌ ጥቀስ? 8️⃣ሞት ምንድን ነው? 9️⃣ትንሣኤ ሙታን የሚሆነው መቼ ነው? 🔟የሰው አነሳስ እንዴት ነው? 1️⃣1️⃣ጻድቃን በበግ ኃጥአን በፍየል የተመሰሉት ለምንድንነው? 1️⃣2️⃣ጻድቃን በቀኝ ኃጥአን በግራ መቆማቸው ስለምንድነው? 1️⃣3️⃣የጌታ አመጣጥ እንዴት ነው? 1️⃣4️⃣ሕያዋንና ሙታን የሚባሉት እነማን ናቸው። በዚህ ትምህርት እነዚህንና የመሳሰሉትን ጥያቄዋች እንማማርበታለን። 1️⃣ #የትንሣኤ_ሙታን_ትርጉም ✅"ትንሣኤ" ለሚለው ቃል መነሻ ግሱ "ተንሥአ" የሚለው የግዕዝ ቃል ሲሆን "ተነሣ" (መነሣት፣ አነሣስ፣ አዲስ ሕይወት) ማለት ነው። ✅"ትንሣኤ ሙታን" ማለት ተለያይተው በተለያየ ሥፍራ ይኖሩ የነበሩ ነፍስና ሥጋ እንደገና ተዋህዶ መነሣትና ከሞት በኋላ በነፍስና በሥጋ ሕይወት  ማግኘት ማለት ነው። 2️⃣ #ትንሣኤን_ማን_መሠረተው? ✅ልዑለ ባሕርይ ፍጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤን ገናናነት በሁሉት መንገድ ገልጦ አሳይቶናል በነቢብና በገቢር (በመናገርና በመተግበር) ለምሳሌ፦ "አሁን ወደ እየሩሳሌም እንወጣለን የሰውን ልጅ ይይዙታል፣ ይሰቅሉታል፣ ይገድሉታልም በሦስተኛውም ዕለት ይነሳል። (ማቴ 20፥18-29)  በማለት በነቢብ እና በመናገር/በማስተማር መነሳቱን አስረድታል። ✅ሌላው የአራት ቀን በድን የነበረውን አላዛርን ከመቃብር ጠርቶ በማስነሳት፤ ናይን በምትባል ሀገር የአንዲትን መበለት ልጅ በድን ከተኛበት ካሬዛ ላይ በማስነሳት፣ የምኩራብን አለቃ የኢያኢሮስን ሴት ልጅ በድን በቤቱ ተገኝቶ በማስነሳት ወ.ዘ.ተ (ዮሐ 16፥1 ፤ ሉቃ 7፥11) ትንሣኤ ሙታን መኖሩን በገቢር በተግባር አሳይቶናል። ✅በኋላ 3 ማዕልትና 3 ሌሊት በከርሰ መቃብር አድሮ መቃብር ክፈቱልኝ መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል ከሙታን ቀድሞ ተነሣ። በትንሣኤውም ትንሣኤያችንን ገለጠልን። ✅ስለዚህ የትንሣኤ በኩር፤ የትንሣኤ መሥራች እርሱ ነው። 1ኛ ቆሮ 15፥20-24  ፤  የሐ 10፥14-18 ዮሐ 20 ማቴ 28። ~~~~ 3️⃣የሦስት ቀንና የሦስት ሌሊት አቆጣጠር እንዴት ነው? #ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!! ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇 •➢ ሟር // SHARE ╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮ @ctwobek @ctwobek @ctwobek ╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯

ዐቢይ ጾም ዐቢይ ለምን ተባለ ቢሉ ‹‹ዐበየ›› ማለት ከፍ አለ ማለት ሲሆን ከዚህም ግስ አቢይ የሚለው ቅጽል ይገኛል፡፡ ዐቢይ ማለት ከፍ ያለ ትልቅ ማለት ነው፡፡ ዐቢይ ጾም የተባለበት ምክንያት፡- ሀ. ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው ጾም ስለሆነ ለ. በቀኑ ቁጥር ከሌሎች አጽዋማት የሚበልጥ ስለሆነ ሐ. ሦስቱ ታላላቅ የሰይጣን ፈተናዎች ማለትም 'ትዕቢት' 'ስስት' 'ፍቅረ ነዋይ' ድል የተመቱበት ስለሆነ ነው፡፡ በቤተክርስቲያን ስያሜ መሰረት በዐቢይ ጾም ውስጥ የሚውሉ ሰንበታት እያንዳንዳቸው መጠሪያ ስም ሲኖራቸው እነርሱም፡- 1. ዘወረደ የዐቢይ ጾም የመጀመሪያው ሰንበት ሲሆን ይህም ቅድመ ዓለም የነበረ ዓለምን ፈጥሮ የሚኖር አልፋና ኦሜጋ ከሰማየ ሰማያት መውረዱንና ከእመቤታችን ከቅድስተ ቅዱሳን ከንጽሕተ ንጹሐን ከድንግል ማርያም መወለዱን የሚያመለክት ሥያሜ ነው፡፡ 2. ቅድስት ይህ የሁለተኛው ሰንበት ስያሜ ሲሆን የተባለበትም ምክንያት ሾለ ዕለተ ሰንበት ቅድስና ስለሚያወሳ ነው፡፡ እንዲሁም ይህ ዕለት ዕለተ እግዚአብሔር የተባለች የሰንበት ክርስቲያን ቅድስናን ያመለክታል ምክንያቱም የዚች ዕለት ጌታ እርሱ ቅዱስ እግዚአብሔር ነውና ስለዚህም ዕለተ ሰንበት ቅድስት ተብላለች፡፡ 3. ምኩራብ ይህ የሦስተኛው ሰንበት ስያሜ ሲሆን በዚህ ሰንበት ጌታ በመዋዕለ ትምህርቱ በምኩራብ ገብቶ ማስተማሩ ይነገራል፡፡ እንዲሁም ይህች ዕለት መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኩራብ ገብቶ እንዳስተማረ የሚታሰብበት ዕለት ነው፡፡ ምኩራብ ማለት የቤተ አይሁዳውያን የጸሎት ቤት ነው፡፡ 4. መጻጉዕ ይህ የአራተኛው ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ድውያንን መፈወሱ እውራንን ማብራቱ ለምጻምን ማንጻቱ ሽባዎችን መተርተሩ የሚያነሳ መዝሙር የሚዘመርበት እንዲሁም እነዚህ ሁሉ ድንቅ ገቢራተ ታምራቶች የሚዘከሩበት ዕለት ነው፡፡ 5. ደብረ ዘይት ይህ የአምስተኛው ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ሆኖ ነገረ ምጽአቱን እንዳስተማረ የሚወሳበት ሰንበት ነው፡፡ ደብረ ዘይት ማለት ወይራ የበዛበት ተራራ ማለት ነው፡፡ 6. ገብርኄር ይህ የስድስተኛው ሳምንት ሰንበት ስያሜ ሲሆን ይህም ዕለት ለጌታው ታማኝና በጎ የሆነው ባርያ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ ተብሎ እንደተመሰገነ የሚነገርበት ዕለት ነው፡፡ 7. ኒቆዲሞስ ይህ የሰባተኛው ሰንበት ስያሜ ነው፡፡ ይህም ዕለት ኒቆዲሞስ የተባለው የአይሁድ መምህር በሌሊት ወደ ጌታው ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ እየመጣ ይማር እንደነበረ ይታሰብበታል በዚም ዕለት የኒቆዲሞስን ታሪክ የሚያስታውስ መዝሙር ይዘመርበታል፡፡ 8. ሆሳዕና ይህ የስምንተኛው ሳምንት ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት በነቢዩ በዘካርያስ ላይ የተጻፈው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ጌታችም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያይቷ እና በውርንጭላይቷ ላይ ተቀምጦ ሆሳዕና በአርያም ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ ተብ እየተመሰገነ ወደ ቤተ መቅደስ መግባቱ የሚተሰብበት ዕለት ነው፡፡ ሆሳዕና ማለት ‹‹እባክህ አሁን አድን አሁን ባርከን›› ማለት ነው፡፡ በሰሙነ ሕማማት ጸሎተ ፍትሃት ጸሎተ አስተስርዮ ስለማይፈጸም ጸሎተ ፍትሃትና አስተስርዮ የሚደረገው በዚሁ ዕለት ነው::    ጾሙን የበረከት ጾም ያድርግልን፡፡ ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇 •➢ ሟር // SHARE ╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮ @ctwobek @ctwobek @ctwobek ╰══•|❀:✞✟✞❀|•══

አሜን አሜን የምለው ቃል ከተለመደው ሰፋ ያለ ትርጉም ያለው ቃል ሲኾን “አስፈላጊነትን (significance)” የያዘ ቃል ነው።  ብዙዎች ብዙ ትርጉም ባለው መልኩ አይመለከቱትም። ቅዱስ ጳውሎስ “እግዚአብሔር ለሰጠው የተስፋ ቃል ሁሉ አዎን ማለት በእርሱ ነውና፥ ስለዚህ ለእግዚአብሔር ሾለ ክብሩ በእኛ የሚነገረው አሜን በእርሱ ደግሞ ነው” ይላል 2 ቆሮ.1:20 አሜን እንደ ፈለግን አልያ በልማድ የምንጠራው ቃል አይደለም። የዘልማድ ቃል መኾን የለበትም።  አሜን የእግዚአብሔርን ቃል ኪዳን መፈጸመን ማረጋገጫና በእግዚአብሔር መታመንን የያዘ ነው።  የእብራይስጡ ቃል   አሜን (אָמֵן) አረብኛና ሲሪያክ አሚን ይላል። በእግዚአብሔር የኾነ እምነት፣ ማመን፣  መታመን ማለትን ያመለክታል።  እንዲኹ አሜንም ስምምነት agreement ፣ ማረጋገጥን affirmation ፣ ምስጋናን እምነትን prais and faith ይይዛል። አሜን የሚለው ቃል እንደ ንባቡ አውድና አገባብ ትርጉሙ ይለያያል።  ወደ እኛ መጽሐፍትና አጠቃቀም ስናይ ደግሞ :- አሜን "እውነት ነው" ማለት ነው። በሌላው ትርጉሙ "አዎን" ማለት ነው በቡራኬ በምርቃት ጊዜ ደግሞ ይደረግልኝ፣ አዎ ይድረሰኝ ማለት ነው።  መ/ር ንዋይ ካሳሁን ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇 •➢ ሟር // SHARE ╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮ @ctwobek @ctwobek @ctwobek ╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯

Share 'የዓቢይ ፆም 8ቱ ሳምንታት.pdf'