en
Feedback
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ

አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ

Open in Telegram
5 084
Subscribers
+1124 hours
-157 days
-7730 days
Posts Archive
ነበልባል ክ/ጦር የጨፍጫፊውን አገዛዝ ጥምር ጦር ዕቆድ አከሸፈ! ​ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ​የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት የአሳምነው ዕዝ ከሰም 2ኛ ኮር ነበልባል ክፍለ ጦር የአገዛዙን ጥምር ኃይል በንጹሃን ዜጎች ላይ ያቀደውን የጥቃትና የዝርፊያ እንቅስቃሴ አከሸፈ። ​የአገዛዙ ጥምር ሀይል በቀን 24/11/2018 ዓ.ም በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች ማለትም ሲቪለን፣ ምነበላ፣ አዳማ ወንዝእና ቱሊ በተባሉ አካባቢዎች ሰፊ እንቅስቃሴ ያደረገ ቢሆንም በነበልባል ክ/ጦር ፈጣን የማጥቃት እነሰቅስቃሴ በማድረግ የአገዛዙን ሀይል ያዋረደ ድል ተቀዳጅተዋል። አገዛዙ በነበረው እልህ አስጨራሽ ውጊያ በአርሶ አደር ቤት እና ንብረት ላይ ያለውን ሁሉ መሳሪያ የተጠቀመ ቢሆንም የአርሶ አደሮች ንብረት እና ህይወት ማጥፋቱን ቀጥሎበታል። የነበልባል ክ/ጦር የሲቪሎችን ህይወት ለመታደግ ሲባል የስልት ለውጥ መውሰዳቸውን ገልጸዋል። ነበልባል ክፍለ ጦር አባላት ከአገዛዙ ኃይል ጋር ባደረጉት ፍልሚያ የተቃጣውን የጥቃት እቅድ አክሽፈዋል። ​ የጠላት ኃይል አርሶ አደሮችን ለውጊያ መከታነት ለመጠቀም በሞከረበት ወቅት የፋኖ ሰራዊታችን የውጊያ ስልቱን በመቀየር የንጹሃንን ህይወት መታደግ ችሏል። በተለይም በሲቪለንእና ምነበላ ግንባሮች የነበረው ከፍተኛ ውጊያ የጠላትን ሀይል ሙትና ቁስለኛ ማድረጋቸውን የኮሩ ሕዝብ ግንኙነት ክፍል ገልጿል። ​በተጨማሪም በአዳማ ወንዝ አካባቢ በተደረገ የተቀናጀ ደፈጣ በጥምር ኃይሉ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሳቸውን ያሳወቁ ሲሆን፤ የአገዛዙ ጨፍጫፊ ኃይል በሰነዘረው የከባድ መሳሪያ ድብደባ በንጹሃን አርሶ አደሮች ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን የግንባር መረጃችን አክሎ ገልጿል። " ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

የጠላት ኃይል ወደ ይፋት አውራጃ--ቀወት ለዘረፋ ያደረገው እንቅስቃሴ በፋኖ ከበባ ውስጥ ሲገኝ በጥቂት ሰዓታት ውጊያ ብዙ ሙትና ቁስለኛ ማስተናገዱ ተገለፀ!! ሐምሌ 25/2018 ዓ.ም የጠላት ሀይል ከባሽ ተነስተው ወደ ይፋት አቅጣጫ በሦስት መስመር የመውረር ሙከራ ያደረገ ሲሆን፦ ➛ከባሽ በንፋስ አምባ በኩል ወደ ዘከሬ ተራራ፣ ➛ከባሽ ቀጥታ ወደ ቀወት መስመር፣ ➛ከባሽ ወደ ቆሎማያ አቅጣጫ በሦስቱም አቅጣጫዎች የተንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ወደፊት ለመግፋትም ሆነ ወደኋላ ለመመለስ በማይችልበት ደረጃ በአፋብን ሸ/ጠ/ግ/አ/ዕዝ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር ደጃዝማች ተሰማ እርገጤ እና አስቻለው ደሴ ክፋለጦር ከበባ ውስጥ ይገኛል። ተጨማሪ ኃይል (ከሸዋሮቢት፣ ከሞላሌ እና ከመሐል ሜዳ) ቢጠይቅም፣ በወገን ሀይል ከበባ ውስጥ የሚገኘትን ደፈጣዎችና ከበባዎች ለማለፋ የተቸገረው ሀይል የደገፈውና የመጣለት ኃይል እደሌለ ተረጋግጧል። የባሽ ከተማ ሙሉ በሙሉ በደጃዝማች ተሰማ እርገጤ በክፍለ ጦሩ ቁጥጥር ስር የዋለች ሲሆን፤ በዚህ ውጊያ ላይ የባሽ ክላስተር እና የተሬ ክላስተር አባት አርበኞች ጦር ከፍተኛ ታሪክ እየሠሩ ይገኛሉ ሁለት የጠላት ኃይልን እስከወዲያኛው እዳሰናበቱ ተረጋግጧል። በሌላ እቅጣጫ ከመዘዞ አቅጣጫ የተቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ከመዘዞ ተነስቶ በአያበር ቀበሌ በኩል ወደ መንግስት ለመሸጋገር ሲንቀሳቀስ በአካባቢው በሚገኘው አስቻለው ደሴ ክፍለ ጦር ቅጽበታዊ እርምጃ ተወስዶበት ከበባ ውስጥ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት መሶቢት በተባለ ቦታ ተራራ ላይ ተሰቅሎ የሚገኝ ሲሆን፣ ተጨማሪ ደጋፊ ኃይል ቢጠይቅም የሚደርስለት በማጣቱ በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ይገኛል። በተያያዘ ዜና ከአጣዬና አላላ ተነስቶ በሁለት አቅጣጫ ማለትም የአጣየው በከሰያት ወደ ደረትማ እዲሁም የአላላው በብርቂቶ ወደ ደረትማ የተንቀሳቀሰውን ዘራፊ ጥምር ቡድን ጀግናው 7/ለ70 ክፍለጦር እዳመጣጡ እያሳደዱት ሲሆን መሸሽ ያልቻለው በየጉረኖው ተደፍቶ ቀርቷል። በዚሕም ጠላት የሞቱትን ትቶ የቆሰሉት ወደ አጣዬ ወስዶ በማሳከም ላይ ይገኛል። ክብር ለትግሉ ሠማዕታት ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!!

የነፃነት ነበልባል ከአንኮበር ተራሮች፦ የደጃዝማች አበባየሁ እና የደጃዝማች አየለ ብርጌዶች ታሪካዊ የምርቃት ስነ-ስርዓት በታላቅ የትግል ወኔ ተከበረ!! ሀምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም የህዝብን መራር ብሶት ወደ አልበገሬነት የትግል ወኔ የለወጠው የፋኖ የነፃነት እሳት፣ ታሪካዊቷና የቆራጥ አባቶች ምድር በሆነችው በአንኮበር ተራሮች ላይ በደማቅ ሁኔታ እንደገና ተቀጣጥሏል። በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሥር የሚንቀሳቀሱት ሁለቱ የትግል አምዶች ማለትም ደጃዝማች አበባየሁ ብርጌድ እና ደጃዝማች አየለ ብርጌድ በተደረገላቸው ወታደራዊና ፖለቲካዊ ስልጠና እና የትግል ዝግጅት ታላቅ የምርቃት በዓላቸውን በስኬት አጠናቀዋል። ይህ በደማቅ የታጠቁ አርበኞች ህብረ ዝማሬና ድምቀት የታጀበው ታሪካዊ መርሃ-ግብር፤ የህዝብን ደህንነትና መብት ለማስከበር በሚደረገው የትጥቅ ትግል ውስጥ ወኔ ቀስቃሽነትን ያበሰረ ሆኗል። በዝግጅቱ ላይ የትግሉን ፖለቲካዊና ወታደራዊ አቅጣጫን ያስቀመጡ የድርጅት፣ የዕዝ፣ የኮርና የክፍለ ጦር ከፍተኛ አመራሮች የተገኙ ሲሆን፣ የትግሉ ጠንካራ መሠረት የሆኑት የአገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች በመገኘት ለሰራዊቱ ምርቃታቸውን እና አጋርነታቸውን ሰጥተዋል። በወቅቱ ከፍተኛ አመራሮች ባደረጉት ቀስቃሽና ማጠቃለያ ንግግር፦ ወቅታዊ ሁኔታና የትግሉ ደረጃ፦ የአሁኑ የትግል ምዕራፍ በጽናትና በጥራት የሚመራበት መድረክ ላይ መድረሱ ተብራርቷል። የአርበኞች ጦር አደረጃጀት፦ የወታደራዊ አደረጃጀቱና የትግል ስልቱ ከጊዜው ጋር በተጣጣመ መልኩ ይበልጥ የተቀናጀና ዘመናዊ እየሆነ መምጣቱ ተገልጿል። የቀጣይ አቅጣጫ፦ የህዝብን ነፃነት ሙሉ በሙሉ ለማረጋገጥ የሚደረገው ፍልሚያ ባልተናወጠ ወኔና ቁርጠኝነት እንደሚቀጥል ጥብቅ የትግል አቅጣጫ ተሰጥቷል። በትግሉ ግንባር ቀደም ሆነው ላገለገሉ፣ ሰራዊቱን ላደራጁና የህዝቡን ደጋፊነት አስተባብረው በቁርጠኝነት ህዝባቸውን ላገለገሉ አርበኞች የሞራልና የትግል ማበረታቻ ስጦታዎች ተበርክተዋል። በዚሁ መሠረት፦ ✔ለክላስተር መሪዎች፣ ✔ለብርጌድ መሪዎች፣ እና ✔ለቀበሌ አመራሮች፣ የጀግንነት ምልክት የሆነውን የአርበኞች ምስል እና የፅናት ምስክር የሆነው የእውቅና ሰርተፊኬት ተበርክቶላቸዋል። ይህ ከአንኮበር ተራሮች የተሰማው የምርቃት ብስራትና የደስታ አየር፣ በትጥቅ ትግሉ ጉዞ ላይ አዲስ ጉልበትና ወታደራዊ ግርማ የፈጠረ ሲሆን፤ ጥሪያቸውን አድሰው የተመረቁት ብርጌዶችም የተሰጣቸውን ህዝባዊ አደራ ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!!

የአይበገሬዎቹ ደዳዝማች ተሰማ እርገጤ ክፍለጦር ውስን ሻለቆችና የእዙ ተወርዋሪ ንስር ሻለቃ በጋራ በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ አርማኒያ ቀበሌ የተጠና ኦፕሬሽን አድርገዋል።። ሀምሌ /20/2018 ዓ/ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው እዝ ግዙፉ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር አካል የሆነው አርበኞቹ የደጃዝማች ተሰማ እርገጤክ/ጦር ውስን ሻለቆችና ንስር ሻለቃ በአርማኒያ ክላስተር አርማኒያ ቀበሌ ሰፍሮ በነበረው የጠላት ሃይል የ103ኛ አየር ወለድ ክፍለጦር ከለሊቱ 10 :00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ጠዋቱ 2:00 ሰዓት ድረስ መብረቃዊ ጥቃት አድርገውበታል። አይበገሬወቹ የደጃዝማች ተሰማ እርገጤ ክፍለጦርና ንስር ሻለቃ የጠላትን ሶስት ምሽግ ማለትም ጠላት ሰፍሮበት የነበረው ኑሬ አፋፍ፣ አርማኒያ ገበያ፣ አርማኒያ ሀይስኩል ትምህርት ቤት እንዲሁም አርማኒያ ኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን አጠገብ በተመሳሳይ ሰዓት በመስበር የጠላትን ሙሉ ሀይል መደምሰስ ችለዋል ። ይህ አውደ ውጊያ በጀግኖቹ ታላቅ እርብርብ የጠላትን ሀይል ታላቅ ድንጋጤና ፍርሀት ፈጥሮበታል። በሁለተኛ ግንባር በዚሁ አርማኒያ ክላስተር ማፉድ ቀበሌ መሽጎ የነበረውን የጠላት ሀይል የአፄ አምደፂዮን ኮር አካል የሆነው ጀግናው ራንቦ ክፍለጦር ውስን ሻለቆች በማፉድ ውሀ ታንከር ፣ማፉድ ገበያ እና ማፉድ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አካባቢ ታላቅ ተጋድሎ አድርገዋል። በመሆኑም የአናብስቶቹ ክንድ እንደ እሳት የገረፈው የጠላት ሀይል ሙትና ቁስለኛውን ሰብስቦ ለመሄድ በመቸገሩ ከደብረሲናና ጣርማበር ከተማ ያለ የሌለ ሀይሉን ሰብስቦ ቢያመጣም አናብስቶቹ የጠላትን አፀፋ ምላሽ ከምንም ሳይቆጥሩት እቅዳቸውን በሚገባ አሳክተዋል። በአጠቃላይ በነበረው አውደውጊያ ጠላት ሁለት ሃይሱዙ ሙሉ ሙትና ቁሰለኛው ሰብስቦ ሾላሜዳና አርማኒያ ሆስፒታል መግባቱን ሲስማ በጠላት የሰው ሀይልና ንብረት ላይ ኪሳራ በወገን የድል የበላይነት መጠናቀቁ ታውቋል። " ክብር ለትግሉ ሰማዕታት" " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን" የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ

የራንቦ ክፍለ ጦር በብልፅግና 103ኛ ኮማንዶ ክፍለ ጦር ላይ ልዩ ኦፕሬሽን አካሄደ!! ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሣምነው ዕዝ የአፄ አምደ ጽዮን ኮር አካል የሆነው የራን
የራንቦ ክፍለ ጦር በብልፅግና 103ኛ ኮማንዶ ክፍለ ጦር ላይ ልዩ ኦፕሬሽን አካሄደ!!          ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሣምነው ዕዝ የአፄ አምደ ጽዮን ኮር አካል የሆነው የራንቦ ክፍለ ጦር በጠላት ኃይል ላይ በአይነቱ ለየት ያለ እና የተሳካ ኦፕሬሽን ማካሄዱን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል አስታወቀ።  የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ከግንባር ባደረሰን መረጃ፤ ኦፕሬሽኑ የተፈፀመው ሐምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም ከሌሊቱ 10:00 ሰዓት እስከ ጧት 2:00 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ በተካሄደ ጠንካራ ውጊያ ነው። ይህ ኦፕሬሽን በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ስር በሚገኙት አርማኒያ ክላስተር፥ አርማኒያ፣ ማፉድ፣ ገደባ፣ ማፉድ የውሃ ታንከር እና ማፉድ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አካባቢዎች ላይ የተደረገ ኦፕሬሽን መሆኑን ገልጿል።  በነዚህ ስፍራዎች ላይ ሰፍሮ በነበረው የብልፅግና 103ኛ የኮማንዶ ክፍለ ጦር ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱን የጠቀሰው ኮሩ፤ የራንቦ ክፍለ ጦር ባደረገው ስልታዊ ውጊያ የጠላትን ምሽግ ማስለቀቁን፣ የጠላት ኃይልን መደምሰሱን እንዲሁም ሙትና ቁስለኛ በማድረግ መብረቃዊ ጥቃት መፈጸሙን ሲያሳውቅ በወገን ሀይል በኩል ያለምንም ጉዳት የተሳካ ኦፕሬሽ መስራቱን ገልጿል። " ክብር ለትግሉ ሰማዕታት" " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን" የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሣምነው የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በብሔራዊ የምክክር ኮሚሽን ስም ዘረ ፈጁ አገዛዝ ያዘጋጀውን የብልጽግና እና ጀሌዎቹ ጉባኤ አስመልክቶ ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የተሰጠ መግለጫ ለልዩነት እና ለጦርነት ምክንያት በሆኑ አጀንዳወች ላይ አካታች ብሔራዊ ውይይት እና ምክክር ማድረግን በተመለከተ የኢትዮጵያ ህዝብ ለዘመናት ሲያቀርበው የቆዬ ጥያቄ መሆኑ ይታወቃል። ሀቀኛ ብሔራዊ ምክክር ማድረግ ለሀገር ዘላቂ ሰላም አስፈላጊ የመሆኑን ያህል የብሔራዊ ምክክር ሂደት በተለይም የምክክር ሂደቱ አካታችነት፣ የሚካሄድበት ነባራዊ ሁኔታ፣ ሂደቱን የሚመራው ተቋም አወቃቅር እና ተቋማዊ ገለልተኝነት፣ አሳታፊነት እና ሌሎችም ሁኔታወች በአግባቡ ካልታዩ ነባር ችግሮችን እና ቅራኔወችን ከማስፋት እና ከማወሳሰብ ያለፈ ፋይዳ አይኖረውም። በብልፅግና አገዛዝ ጦረኝነት እና ዘረ-ፈጅ የቀውስ አገዛዝ ምክንያት ዓመታትን የተሻገረ እና የሚሊዮኖችን ሕይወት ያመሰቃቀለ ደም አፋሳሽ ጦርነት ውስጥ ያለችው ሀገራችን፣ ይህን በህዝብ ላይ የተከፈተዉን ጦርነት ያወጀው አገዛዝ ጦርነትን ለማቆም ምንም አይነት ፍላጎት ባላሳየበት ሁኔታ ውስጥ የሚደረግ የምክክር ድግስ በጀት ከማባከን እና ለአገዛዙ የገጽታ ግምባታ ከመስራት ያለፈ ፋይዳ አይኖረውም። ባለፉት አመታት በዳበሳ ከሚታወቁ የሀገሪቱ እውነቶች መካክል ጦርነት ፣ ስደት፣ መፈናቀል ጅምላ ጭፍጨፋና ማንንነት መሰረት ያደረጉ ግልፅ ጥቃቶች በአገዛዝ ስፖንሰርነት እየተፈፀሙ ነው:: በብልፅግና የቀውስ አገዛዙ ምክንያት ሚሊዮኖች ተሰደዋል፣ በርካቶች በአገዛዙ የፀጥታ መዋቅር ንብረታቸዉን ተዘርፈዋል:: አማራ ክልልን ጨምሮ ከፊሉ የሀገሪቱ ክፍል በወታደራዊ አገዛዝ ስር ከወደቀ ሶስት አመታትን አስቆጥሯል። አገዛዙ በቀጥታ የእርስ በእርስ ግጭቶችን እና ጦርነቶችን በማዋለድ እና አለመተማመን እንዲነግስ በማድረጉ አብዛኛው የሀገሪቱ ክፍል ቀውስ ውስጥ ይገኛል። ይኸው ወታደራዊ አገዛዝ ምርጫ ለማድረግ የሚያበቃ የሰላም ሁኔታ ሳይኖር ራሱ ተመራጭ፣ ራሱ ታዛቢ፣ ራሱ መራጭ እና አስመራጭ በመሆን ትልቅ የፖለቲካ እና የዲሞክራሲ ክንዉን በሆነው የምርጫ ሂደት ላይ መቀለዱን ዓለም አቀፍ ማህበረሰቡም የመሰከረው እና የታዘበው ሐቅ ነው። ይህንንም ተከትሎ የ2018 ምርጫ ክንዉን አለመካሄዱን እና ብልፅግናም በምርጫ ያገኘው ቅቡልነት እንደሌለ ተረጋግጧል። አገዛዙ ይህንን በምርጫ ድግስ ያጣውን ቅቡልነት በምክክር ለማግፕት ጥረት እያደረገ ቢሆንም የብሔራዊ ምክክር ሂደቱን ለማሰናዳትም ሆነ በባለቤትነት ለማስኬድ የሚያበቃ የህግ መሰረት ግን የለዉም። ሀቀኛ ብሔራዊ ምክክርን መምራት የሚችል ኮሚሽን በኢትዮጵያ ውስጥ ባሉ ተፋላሚ ኃይሎች ይሁንታ የተሰጠው፤ ስቪክ ማህበራትን ጨምሮ በሁሉም ኃይሎች ተሳትፎ የተቋቋመ እና ገለልተኛነቱም የተረጋገጠ መሆን ይገባዋል። የወቅቱን የብሔራዊ ምክክር ጉዳይ እመራለሁ የሚለው ኮሚሽን ከአገዛዙ በስተቀር በየትኛውም የፖለቲካ ኃይል እውቅና እና ይሁንታ ያልተሰጠው ከመሆኑ ባሻገር የብልፅግናን በተለይም የጠቅላይ ሚኒስትሩን የግል ፍላጎት የብሔራዊ ምክክር ውጤት አድርጎ ይዞ ለመቅረብ የተዘጋጀ፣ ሂደቱ የሚመራበትን አሰራር የሚወስን ህግ እንኳን እንዲወጣ ያላደረገ የጏዳ ወዳጆችና የፖለቲካ ደላሎች ስብስብ ነው። ገለልተኛ ባልሆነ ተቋም የሚመራ ምክክር ደግሞ የብልፅግና ካድሬወች ውይይት እንጅ ብሔራዊ ምክክር አይሆንም። ለሀገሪቱ ችግርም ዘላቂ ሰላምም አያመጣም። ላለፉት በርካታ ዓመታት ሀቀኛ ወኪል ሳይኖረው በመቅረቱ እጣ ፋንታውን ሌሎች የፖለቲካ ኃይሎች ሲወስኑለት የቆዬው የአማራ ህዝብ በዚህ የምክክር ጉባኤም ተመሳሳይ ሂደት ውስጥ ይገኛል። በአብን እና በአማራ ብልፅግና ስም ከየጎሬው ተለቃቅመው በጉባኤው አማራን ወክለን እንሳተፋለን የሚሉትም በአማራው ላይ ይፋዊ ጦርነት ያወጀውን ዘረ ፈጅ አገዛዝ የተቀበሉ የብልፅግና ወኪሎች እንጅ ለአማራ ህዝብ መብት እና ጥቅም ቅንጣት ታክል አስተዋፅኦ ማድረግ የማይችሉ በመሆናቸው ይህ የምክክር ጉባኤ የአማራ ህዝብ ያልተወከለበት እና የማይሳተፍበት መሆኑ በታሪክ ፊት ተመዝግቧል። የአማራን ህዝብ ብቻ ሳይሆን ከብልፅግና አገዛዝ ጋር ይፋዊ ጦርነት ውስጥ ያሉ የፖለቲካ ኃይሎችን ያገለለ የምክክር ጉባኤ በመሆኑም ከአማራ ህዝብ ብቻ ሳይሆን ሌላው ኢትዮጵያዊም ቢሆን በዚህ ጉባኤ በትክክለኛ ወኪሎቹ አማካኝነት እየተሳተፈ ነው ብለን አናምንም። በመሆኑም ድርጅታችን አፋብን ለአማራ ሕዝብ፣ ለኢትዮጵያ ሕዝቦች እና ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚከተለውን ጥሪ ያቀርባል:- 1. ለአማራ ሕዝብ - ይህ ምክክር ተብሎ በአገዛዙ የሚደረገው እንቅስቃስ የአማራ ህዝብ ያልተወከለበት እና ትክክለኛ ወኪሎቹ የህልውና ትግል ላይ በመሆናቸው፣ ትግሉን ጫፍ በማድረስ ስር ነቀል ለውጥ በማምጣት ህልውናውን አረጋግጦ ለወደፉቱ ከሌሎች ህዝቦች ወኪሎች ጋር በግልፅ ተነጋግሮ ሀገራዊ እውነተኛ እርቅና ምክክር ለማምጣት እንዲቻል አሁን ላይ ሁሉንም አቅሞች አሰባስቦ በበለጠ ቁርጠኝነት እንዲታገል ጥሪ እናቀርባለን፤ 2. ለኢትዮጵያ ሕዝብ:- ይህ የምክክር የተባለው ክሹፉና አስመሳይ ሂደት የአማራን ሕዝብ ጨምሮ ሌሎች ጥያቄ ያላቸው የፖለቲካ ኃይሎችም የተሳተፉበት አለመሆኑን፣ የሀገሪቱን አንድነት የበለጠ አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን፣ የእርስ በርስ ጦርነቱን የማያስቆምና የሚያባብስ መሆኑን፣ የአንድ ግለሰብ እና የገዢ ቡድን ፍላጎት ለማሳካት እየተደረገ ያለ መሆኑን በማመን ከአማራ ሕዝብ ጎን ቆሞ ስርዓቱን መታገል ይገባል:: በቀጣይ በጋራ የሽግግር መንግስት መስርተን ሀገራችንን ማፅናት እንችል ዘንድ ብሎ እውንተኛ ምክክርና እርቅ እንፈፅም ዘንድ በተባባረ መልኩ ፀረ አገዛዝ ትግል እንዲደረግ ጥሪ እናቀርባለን፤ 3. ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ:- እንደሚታወቀው በትክክለኛው መንገድ የማይካሄድ ብሄራዊ እርቅና ምክክርን  ሂደቱ ካለ መኖሩ የከፋ ሀገራዊ ችግርን ያስከትላል። ብሄራዊ ምክክር ከከሸፈ አንድ ሀገር የምትገባበት ቀውስ እጅግ ከባድና በአዙሪት የተሞላና የማይገመት ይሆናል:: የብዙ ሀገራት ብሄራዊ እርቅና ምክክር የተኮላሸው ገለልተኛነትና አሳታፊነት የሌለውን ሂደት በመከተላቸው እንደሆነ ብዙ ምሳሌና ተሞክሮዎች አሉ:: የአሁኑ የአገዛዙ ብሔራዊ ምክክር የተባለው ሂደትም የህዝብ ቅቡልነት የሌለው፣ እውነተኛ ችግር ፈች ምክክር ሳይሆን ብልጽግና እና ደጋፊዎቹ የአገዛዙ ስልጣን ማጽኛ እንደሆነ እና ሀገሪቱን እንዲሁም የቀጣናውን ሰላም ከድጡ ወደማጡ የሚያስገባ መሆኑን ተገንዝባችሁ ለሀቀኛ ሽግግር እና ዘላቂ ሰላም እንድትሰሩ ጥሪ እናቀርባለን። 4. የአማራ ህዝብ ወኪል ነን ለምትሉ የሂደቱ ተሳታፊወች:-  ከዚህ ቀደም እንደሆነው ሁሉ የአገዛዙ ተላላኪ በመሆን እና ተገቢው የአማራ ህዝብ ውክልና ሳይኖራችሁ በሂደቱ የምትሳተፉ ግለሰቦች እና ቡድኖች በብሔራዊ ምክክር ስም በሚካሄድ የብልፅግና ጉባኤ በመሳተፍ ታሪካዊ ስህተት ከመፈፀም እንድትታቀቡ እያሳሰብን ይህን ማሳሰቢያ ችላ በማለት የምታደርጉት ሂደት የአማራን ህዝብ ጥያቄወች ለሌላ ምዕራፍ ለማዳፈን ለምታደርጉት ያልተገባ ተግባር ኃላፊነት የምትወስዱ መሆኑንም በህዝብ እና በታሪክ ፊት እናሳውቃለን። የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ

ጀብደኛዉ የራንቦ ክፍለ ጦር ልዩ የወታደራዊና ፖለቲካዊ አቅም ግንባታ ተሃድሶ መርሃ ግብር አካሔደ🔥🔥🔥 ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም የአፋበን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ አምደ ፅዮን ኮር አካል የሆነው የራንቦ ክፍለ ጦር የተሳካ ልዩ የፖለቲካና ወታደራዊ አቅም ግንባታ ስልጠና (ተሃድሶ) ማድረጉን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል አስታወቀ። ከሐምሌ 01-16/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት የድርጅትና የዕዝ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ስልጠናው ሲጠናቀቅ በተጋባዥነት የተገኙት የአፋብን ተ/ምክትል ሊቀመንበር አርበኛ መከታው ማሞ በተገኙበት ተጠናቋል። የዚህ ልዩ የተሃድሶ መርሃ ግብር ዋና ዓላማዎች፦ ➧ የዓላማ አንድነት መፍጠር፦ ስለ ትግሉ አሁናዊ ሁኔታ፣ ስለ ማህበረሰብ አያያዝ እና ስለ ውስጣዊ አንድነት ➧ ስለ ጠላት አሰላለፍና ቁመና ➧ በወታደራዊ ታክቲኮች ➧በፖለቲካ ግንባታ በነዚሕ አንኳር ነጥቦች ላይ ስልጠናውን አጠናቋል። በስልጠናው በማጠቃለያ መርሀግብር ላይ የተጋበዙት የአፋብን ተ/ምክትል ሊቀመንበር አርበኛ መከታው ማሞ " ከግል ቤታችን ወጥተን የጋራ ቤታችን በሆነው ድርጅት መሠባሠባችን ለአማራ ታሪካዊ" ያሠኘዋል ሲሉ ገልፀዋል። የመድረኩ ተሳታፊ የሆኑት የኮርና የክፍለ ጦሩ አመራሮችና አባላት በሰጡት አስተያየት፤ መድረኩ ቀደም ሲል የነበሩ በርካታ ብዥታዎችን ያጠራና የተናጠል ትግሉን ወደ ህብረትና ብቃት አረጋጋጭ ሊሆን እደሚችል ገልጸዋል። ለህልውና ትግሉ የሚከፈለውን መስዋዕትነት በሙሉ ልብ ለመወጣትና ድርጅቱ ካስቀመጠው ግብ ላይ ለመድረስ ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። "ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

+8
የራንቦ ክፍለ ጦር ልዩ የወታደራዊና ፖለቲካዊ አቅም ግንባታ ተሃድሶ መርሃ ግብር አካሔደ!! ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም የአፋበን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ አምደ ፅዮን ኮር አካል የሆነው የራንቦ ክፍለ ጦር የተሳካ ልዩ የፖለቲካና ወታደራዊ አቅም ግንባታ ስልጠና (ተሃድሶ) ማድረጉን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል አስታወቀ። ከሐምሌ 01-16/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት የድርጅትና የዕዝ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ስልጠናው ሲጠናቀቅ በተጋባዥነት የተገኙት የአፋብን ተ/ምክትል ሊቀመንበር አርበኛ መከታው ማሞ በተገኙበት ተጠናቋል። የዚህ ልዩ የተሃድሶ መርሃ ግብር ዋና ዓላማዎች፦ ➧ የዓላማ አንድነት መፍጠር፦ ስለ ትግሉ አሁናዊ ሁኔታ፣ ስለ ማህበረሰብ አያያዝ እና ስለ ውስጣዊ አንድነት ➧ ስለ ጠላት አሰላለፍና ቁመና ➧ በወታደራዊ ታክቲኮች ➧በፖለቲካ ግንባታ በነዚሕ አንኳር ነጥቦች ላይ ስልጠናውን አጠናቋል። በስልጠናው በማጠቃለያ መርሀግብር ላይ የተጋበዙት የአፋብን ተ/ምክትል ሊቀመንበር አርበኛ መከታው ማሞ " ከግል ቤታችን ወጥተን የጋራ ቤታችን በሆነው ድርጅት መሠባሠባችን ለአማራ ታሪካዊ" ያሠኘዋል ሲሉ ገልፀዋል። የመድረኩ ተሳታፊ የሆኑት የኮርና የክፍለ ጦሩ አመራሮችና አባላት በሰጡት አስተያየት፤ መድረኩ ቀደም ሲል የነበሩ በርካታ ብዥታዎችን ያጠራና የተናጠል ትግሉን ወደ ህብረትና ብቃት አረጋጋጭ ሊሆን እደሚችል ገልጸዋል። ለህልውና ትግሉ የሚከፈለውን መስዋዕትነት በሙሉ ልብ ለመወጣትና ድርጅቱ ካስቀመጠው ግብ ላይ ለመድረስ ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። "ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

+8
የራንቦ ክፍለ ጦር ልዩ የወታደራዊና ፖለቲካዊ አቅም ግንባታ ተሃድሶ መርሃ ግብር አካሔደ!! ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም የአፋበን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ አምደ ፅዮን ኮር አካል የሆነው የራንቦ ክፍለ ጦር የተሳካ ልዩ የፖለቲካና ወታደራዊ አቅም ግንባታ ስልጠና (ተሃድሶ) ማድረጉን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል አስታወቀ። ከሐምሌ 01-16/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት የድርጅትና የዕዝ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ስልጠናው ሲጠናቀቅ በተጋባዥነት የተገኙት የአፋብን ተ/ምክትል ሊቀመንበር አርበኛ መከታው ማሞ በተገኙበት ተጠናቋል። የዚህ ልዩ የተሃድሶ መርሃ ግብር ዋና ዓላማዎች፦ ➧ የዓላማ አንድነት መፍጠር፦ ስለ ትግሉ አሁናዊ ሁኔታ፣ ስለ ማህበረሰብ አያያዝ እና ስለ ውስጣዊ አንድነት ➧ ስለ ጠላት አሰላለፍና ቁመና ➧ በወታደራዊ ታክቲኮች ➧በፖለቲካ ግንባታ በነዚሕ አንኳር ነጥቦች ላይ ስልጠናውን አጠናቋል። በስልጠናው በማጠቃለያ መርሀግብር ላይ የተጋበዙት የአፋብን ተ/ምክትል ሊቀመንበር አርበኛ መከታው ማሞ " ከግል ቤታችን ወጥተን የጋራ ቤታችን በሆነው ድርጅት መሠባሠባችን ለአማራ ታሪካዊ" ያሠኘዋል ሲሉ ገልፀዋል። የመድረኩ ተሳታፊ የሆኑት የኮርና የክፍለ ጦሩ አመራሮችና አባላት በሰጡት አስተያየት፤ መድረኩ ቀደም ሲል የነበሩ በርካታ ብዥታዎችን ያጠራና የተናጠል ትግሉን ወደ ህብረትና ብቃት አረጋጋጭ ሊሆን እደሚችል ገልጸዋል። ለህልውና ትግሉ የሚከፈለውን መስዋዕትነት በሙሉ ልብ ለመወጣትና ድርጅቱ ካስቀመጠው ግብ ላይ ለመድረስ ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። "ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

አራት የአገዛዙ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦርን ተቀላቀሉ! ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም የብልፅግናው ስርዓት ግብዓተ-መሬቱ መቃረቡን ተከትሎ ከመቸውም ጊዜ በላይ ጦ
+4
አራት የአገዛዙ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦርን ተቀላቀሉ! ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም የብልፅግናው ስርዓት ግብዓተ-መሬቱ መቃረቡን ተከትሎ ከመቸውም ጊዜ በላይ ጦረኛው አገዛዝ የሚመካበት ወታደሮች አነ ሙሉ ትጥቃቸው ንቅናቄውን እየተቀላቀሉ ሲሆን ትላንት ረብዕ አራት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዓምደ ጽዮን ኮር የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦርን ከነ ሙሉ ትጥቃቸው መቀላቀላቸውን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል በምስል አስደግፎ ለዕዙ የዜና ክፍል በላከው የግንባር መረጃ አስታውቋል። ወደ ፋኖ ከተቀላቀሉት ውስጥ 3ቱ የ15ኛ ክፍለ ጦር አባላት ሲሆኑ አንዱ የ101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር አባል መሆኑን ኮሩ አክሎ ገልጿል። "ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

በጥዋት ዜና እወጃችን የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር በነጎድጓድ ክ/ጦር በተካሄደው የአንጨቆረር ከተማ ጀብድ የምርኮ ዝርዝር ይፋ እንደሚከተለው አቅርበናል!! ​
+9
በጥዋት ዜና እወጃችን የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር በነጎድጓድ ክ/ጦር በተካሄደው የአንጨቆረር ከተማ ጀብድ የምርኮ ዝርዝር ይፋ እንደሚከተለው አቅርበናል!! ​ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ቀን 14/11/2018 ዓ.ም በዛሬው ዕለት ጠዋት በወጣው ዜና በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘርያዕቆብ ኮር ነጎድጓድ ክ/ጦር በአገዛዙ ሀይል ላይ በወሰደው እርምጃ የአገዛዙ ጅምላ ተጋላቢ የሚሊሻ አባላት ላይ አመርቂ ድል መቀዳጀቱ ይታወሳል። አሁን ከሰዓት በደረሰን ተጨማሪ መረጃ መሠረት የተማረኩ አካላት እና የቁሳቁስ ዝርዝር መረጃ ይፋ ሆኗል። ​የተማረኩ አካላት እና ቁሳቁሶች ዝርዝር 1ኛ.የተማረኩ የሚሊሻ ብዛት 5 አባላት 2ኛ.12 ክላሽኒኮቭ ጠመንጃዎች 3ኛ.4 ኤስ-ኬ-ኤስ (SKS): ጠመንጃ 4ኛ.1 መትረዬስ ክላሽ 5ኛ. ልዩ ልዩ የወገብ ትጥቅና ተተኳሾች ናቸው። የኮሩና ክ/ጦሩ አመራሮች እንዳስታወቁት፣ በዚህ አውደ ውጊያ ላይ ለተሳተፉ አመራርና ሰራዊት አባላት ምስጋናቸውን በማቅረብ ይህና መሰል ስራዎችን ተጠናክረው በመቀጠል የድርጅታችን አፋብንን ጥሪ ባልተቀበሉ የአማራ ህዝብ ጠላቶች ላይ ሁሉ እርምጃው ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል። ክብር ለትግሉ ሰማዕታት ​ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን ​ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግኑኝነት መምሪያ