en
Feedback
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ

አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ

Open in Telegram
5 081
Subscribers
+1124 hours
-157 days
-7730 days
Posts Archive
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አውራጃዎች የተሰማራው የአገዛዙ ጠባቂ ጥምር ጦር እየፈረሰ መሆኑ ተገለጸ! ነሐሴ 03/2018 ዓ.ም የአማራን ሕዝብ ለመጨፍጨፍና ለመዝረፍ ሥርዓታዊ ተልዕኮ የተሰጠው የአገዛዙ ኃይ
+3
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አውራጃዎች የተሰማራው የአገዛዙ ጠባቂ ጥምር ጦር እየፈረሰ መሆኑ ተገለጸ!      ነሐሴ 03/2018 ዓ.ም የአማራን ሕዝብ ለመጨፍጨፍና ለመዝረፍ ሥርዓታዊ ተልዕኮ የተሰጠው የአገዛዙ ኃይል መበተን ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ ይገኛል። በአራት ቀናት ውስጥ ብቻ 11 የጠላት ኃይሎች የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝን ተቀላቅለዋል። «እኛ የሠለጠንው ሕዝብና ሀገርን ለመጠበቅ እንጂ ወገንን ለማሰቃየትና ለማጥፋት አይደለም» በማለት ፋኖን ለመቀላቀል ችለዋል። 1.  የኔሰው ምሳየ – የ6ኛ ዕዝ 605ኛ ኮር መረጃና መሐንዲስ ኃላፊ (ፍቼ)፤ 1 ጥቁር ክላሽ 2.  ገዳሙ በለጠ – የ6ኛ ዕዝ 605ኛ ኮር መረጃና መሐንዲስ አባል (ፍቼ)፤ 1 ጥቁር ክላሽ 3.  ዓለማየሁ ሳሙኤል – የ6ኛ ዕዝ 605ኛ ኮር መረጃና መሐንዲስ አባል (ፍቼ)፤ 1 ጥቁር ክላሽ 4.  ፲ አለቃ ደስታ ደርቤ – ከገርባ ቀበሌ [ሚሊሻ]፤ በጀሌ 5.  ብርሃን ግዛው – ከገርባ ቀበሌ [ሚሊሻ]፤ 2 እግር ክላሽ 6.  ፀጉ ማሞ – ከገርባ ቀበሌ [ሚሊሻ]፤ 2 እግር ክላሽ ከላይ የተጠቀሱት አባላት አፄ አምደጽዮን ኮር ራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦርን ተቀላቅለዋል ሲቀላቀሉ፡ 7.   ***  አንድ(1)ብሬን እና 2 ባለመቶ ሸሸል በመያዝ መሐመድ ቢሆነኝ ኮር አስቴጎማ ክፍለ ጦርን ተቀላቅሏል። 8.  አራት(4) የሚሊሻ አባላት ከነሙሉ ትጥቃቸው ከሠም ፪ኛ ኮርን ተቀላቅለዋል። " ክብር ለትግሉ ሦማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

በአፋብን ሸዋ ጠቅለይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ አምደ ጽዮን ኮር አካል የሆነው ከራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦር 1ኛ እና 3ኛ ሻለቆች ጋር ባተካሔደው መድረክ ላይ ወቅታዊ የፖለቲካ ጉዳዮችን በተመለከተ የተሳካ ውይይትና የፖለቲካ የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራም ማድረጉን ክፍለ ጦሩ አስታወቀ። ነሐሴ 02/2018 ዓ.ም "ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!

እሳትነት  ያልበገረው የአርበኛ ዘገየ ዳኜ የትግል እና የፅናት ህይወት ​ይህ እውነተኛ የታሪክ ድርሳን ስለ አወዛጋቢ የፖለቲካ መንገድ ወይም ተራ የታሪክ ገጽ አይደለም፤ ይህ ታሪክ ሙሉ ህይወቱን፣ ያፈራውን ሀብት እና የደከመበትን ጥረት ሁለት ጊዜ ለቆመለት አላማ አመድ አድርጎ ሰጥቶ፣ አሁንም በፅናት ስለቆመ አንድ የቁርጥ ቀን ልጅ የሚያወራ የህይወት ጀብድ እንጅ የእምቢተኝነት ዋጋ ከ2002  እስከ 2007 እውነትን አንግቦ ከግዙፍ የመንግስት መዋቅር ጋር መጋፈጥ ቀላል አልነበረም። በ2002 ዓ.ም. የፍትሕ እና የእኩልነት ጥያቄን በልቡ ያነገበው አርበኛ ዘገየ ዳኜ፣ በወቅቱ የነበረውን የወያኔ ጨቋኝ ሥርዓት በግልጽ በመቃወም የመንገዱን መጀመሪያ ያደረገበት ታምራዊ ቀን ነበር። ​ይህ እምቢተኝነት ግን ያለ ከባድ መስዋዕትነት አልተሻገረም። በ2007 ዓ.ም. በስርዓቱ በደረሰበት የታለመ ጥቃት፣ በዓመታት ወጣትነቱ፣ በደምና ላቡ ያፈራው ንብረት ሙሉ በሙሉ እንዲወድም ተደረገ። ንብረቱ አመድ ቢሆንም፣ በልቡ ውስጥ የተቀጣጠለው የነፃነት እሳት ግን በፍጹም ሊጠፋ አልቻለም። ንብረት ይተካል፤ የማንነት እና የእውነት ትግል ግን አይቆምም። ​የሸዋ ምድር እሳት እና የህዝብ አለኝታነት ​ከአጣዬ እስከ ሸዋሮቢት የወረራው እና የቃጠሎው ጭስ ሲቀጣጠል፣ አርበኛ ዘገየ እጁን አጣጥፎ አልተቀመጠም። የህዝቡ ህልውና አደጋ ላይ መውደቁን በመረዳት፣ ከጓደኞቹ ጋር በመሆን በራሳ አካባቢ ህዝቡን ማስተባበር እና መከላከል ጀመረ። ​በወቅቱ የነበረውን የብልፅግና ሥርዓት መዋቅር በመበጠስ፣ ህዝቡ በራሱ ተደራጅቶ ህልውናውን እንዲያስከብር የማድረግ ከፍተኛ ተጋድሎ አከናወነ። ይህ ህዝባዊ አለኝታነት፣ የወደፊቱ ወታደራዊ እና ድርጅታዊ አመራር መሰረት የተጣለበት ጊዜ ነበረ። እሳት ያልበገረው  አርበኛ ዘገየ ዳኘ በ2015 ዓ.ም ከባድ ፈተና ​የህዝቡ ምሬት እና የህልውና ሥጋት እያደገ ሲመጣ፣ አርበኛ ዘገየ የፋኖን አደረጃጀት ተቀላቀለ። በትግል ጉዞውም ከመቶ አለቃነት ጀምሮ በቆራጥነት በማገልገል፣ የይፋት ፋኖ ምክትል አዛዥነት ደረጃ ላይ ደረሰ። ​ነገር ግን በ2015 ዓ.ም. በሕይወቱ ከባድ የሚባል ሁለተኛው ጥቁር ፈተና ገጠመው። በአብይ አህመድ ወንበር አስጠባቂ መከላከያ ኃይሎች በተወሰደ እርምጃ፣ ሙሉ የመኖሪያ ቤቱ፣ የቤት እቃዎቹ፣ እንዲሁም ለዓመታት ለፍቶ ያቆመው የእንጨት እና ብረታ ብረት ማምረቻ ማሽኖችና ቁሳቁሶች ከነቤቱ ተቃጠሉበት። ​በሁለት አጋጣሚዎች የለፋበት ሀብትና ንብረት ሙሉ በሙሉ አመድ ቢሆንበትም፣ የአርበኛ ዘገየ መንፈስ ግን አልተሰበረም። ይህቁስ ትግሌ በንብረት አይለካም!" በማለት መሳሪያውን አጥብቆ በመያዝ፣ የአማራ ህዝብ ጥሪ ተቀብሎ የመስዋዕትነት መንገዱን ቀጠለ። በመጨረሻም የአንድነት እና የአመራር ምዕራፍ ​የትግሉ ስፋት እና አስፈላጊነት እያደገ ሲመጣ፣ በሸዋ ምድር "የአንድነት ምክር ቤት" ሲመሰረት፣ ቀጠናውን በመወከል በአባልነት ንቁ ተሳትፎ አደረገ። በመቀጠልም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ውስጥ በነበረው ድርጅታዊ ብቃት እና ታማኝነት ምክንያት የሎጅስቲክስ መምሪያ ምክትል ሀላፊ ሆኖ ተሾመ። በአሳምነው ዕዝ እና የይፋት አውራጃ መሪነት ​ዛሬ ላይ አርበኛ ዘገየ ዳኜ በቆራጥነት፣ በፅናት እና በብዙ መስዋዕትነት ያለፈ የወቅቱ ቁልፍ አመራር ነው። ​በአሁኑ ወቅት በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ውስጥ የሎጅስቲክስ መምሪያ ዋና ሀላፊ በመሆን የዕዙ  የቁሳቁስ አቅርቦት ሥራዎችን በበላይነት ይመራል። በተደራቢነትም፣ በስምሪቱ መሠረት የይፋት አውራጃ ሰብሳቢ ተደርጎ የተጣለበትን ህዝባዊ እና ወታደራዊ ሀላፊነት በቁርጠኝነት በመወጣት ላይ ይገኛል። ​ ከ2002 እስከ ዛሬ የተጓዘበት መንገድ የውድመት፣ የመስዋዕትነት እና የብዙ ፈተናዎች መንገድ ቢሆንም፣ አርበኛ ዘገየ ዳኜ አሁንም ቢሆን የቆመለት ዓላማ ሳይበገር፣ በፅናት ትግሉን በማስቀጠል ላይ የሚገኝ፣ ለብዙዎች አርአያ የሆነ እውነተኛ የታሪክ ባለቤት ነው።

ጀግናው የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር በብልፅግናው አየር ወለድ ሰራዊት ላይ ባካሄደው የተቀናጀ ኦፕሬሽን ድል መቀዳጀቱን አስታወቀ! ነሐሴ 01/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዓምደ ጽዮን ኮር አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር፣ እራሱን "101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር" ብሎ በሚጠራው የአገዛዙ ሰራዊት ላይ ትላንት ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 1:00 ሰዓት ባደረገው የተቀናጀ ወታደራዊ ኦፕሬሽን አኩሪ ድል መጎናፀፉን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል አስታወቀ። የአገዛዙ ኃይል መነሻውን ከመርሐቤቴ አውራጃ ሬማ ከተማ በማድረግ፣ የህዝብ አለኝታ የሆነውን የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ሰራዊት ለማጥቃት ወደ መጅት እና ቢራባ ቀበሌዎች እንቅስቃሴ አድርጎ ለማጥቃት ቢሞክርም የክፍለ ጦሩ የጦር ጠበብቶች በወታደራዊ ስልት የጠላትን ኃይል ወዳዘጋጁለት የውጊያ ቀጠና በስቦ መምታት ስልት፡ በወታደራዊ የበላይነት የሬማ ዙሪያ አካባቢዎችን በወቅቱ በቁጥጥር ስር በማስገባት ጠላት ወደ ኋላ እንዳይመለስ መንገድ በመዝጋት በተከናወነው በዚህ የተሳካ ኦፕሬሽን፣ የአገዛዙ ኃይል ከፍተኛ ወታደራዊና ቁሳዊ ኪሳራ አስተናግዷል። በዜሮ መስዋዕትነት በተጠናቀቀው በዚህ ልዩ ኦፕሬሽን የተገኙ ዋና ዋና ውጤቶች፦ ➠ የተደመሰሰ የጠላት ኃይል፡ 09 ➠ የቆሰለ የጠላት ኃይል፡ ከ14 በላይ እንዳቀደው ያልተሳካለት ጠላት ከፋኖ በደረሰበት ሽንፈት የተበሳጨው ወደ መጣበት ሲመለስ እንደለመደው ንፁሀንን የበቀል እርምጃ፡ የብስጭት ማብረጃ እያለ ንፁሀን ወገኖች ከፍተኛ ድብደባ የተፈፀመባቸው ሲሆን የመጅት ቀበሌ የ8 ዓመት ታዳጊ ህፃን ቶፋው ጋሻው የተባለች እንስት በጥይት ተመታ መቁሰሏን የአይን እማኞች ተናግረዋል። ሽንፈቱን የተከናነበው ጠላት የቆሰሉት አባላቱን ለሕክምና በሬማ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና በሬማ ከተማ ጤና ጣቢያ የመጀመሪያ ደረጃ ህክምና እየተደረገላቸው ሲሆን፣ ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው አባላቱን ዛሬ ነሐሴ 01/2018 ዓ.ም ከንጋቱ 12:30 ላይ ወደ መርሐቤቴ ዓለም ከተማ እናት ሆስፒታል መዛወራቸውን የኮሩ መረጃዎች አረጋግጠዋል። "ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

+9
የንስር ሻለቃ የትግል ዝግጁነቱን ላቀ ደረጃ ያሸጋገረ ልዩ የተሀድሶና የፖለቲካ ንቃተ-ህሊና መድረክ ተካሔደ!! ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ተወርዋሪው የንስር ሻለቃ፣ ህዝባዊ ትግሉን በተሻለ ስትራቴጂያዊ ዝግጁነትና ወታደራዊ ዲስፕሊን ለማጠናከር ያለመ ልዩ የተሀድሶና የፖለቲካ ንቃተ-ህሊና ማሳደጊያ መድረክ በታላቅ ድምቀት አካሂደዋል። በዓላማ ፅናትና በወታደራዊ ስትራቴጂ ዝግጁነት የታነፀው ይህ መድረክ የአማራ ህዝብ እያካሄደ ባለው ፍትሃዊ የህልውና ተጋድሎ ውስጥ የኃይል ሚዛኑን ሙሉ በሙሉ ወደ ድል ለመቀየር ያለሙ ቁልፍ ውሳኔዎች የተበሰሩበት ሆኖ አልፏል። በመድረኩ ላይ የአፋብን ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር አርበኛ መከታው ማሞ፣ የአፋብን መካናይዝድ ጦር መምሪያ ሃላፊ አርበኛ አብረሃም ኩራባቸውን ጨምሮ የዕዙ ከፍተኛ ወታደራዊና ፖለቲካዊ አመራሮች፣ የንስር ሻለቃ መሪዎች እንዲሁም በክብር እንግድነት የተገኙት የአፄ አምደፂዎን ኮር አመራሮች ተሳትፈዋል። የመድረኩ ዋና ዋና ዓላማዎች ~ የአመራርና የሻለቃውን ወታደራዊ ብቃት ማሳደግ፡ ~የተሀድሶ መድረኩ የወታደራዊ ስልቶች ማሻሻያዎች ~ የግዳጅ አፈፃፀም ግምገማዎችንና የወደፊት ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎችን በጥልቀት በመገምገም የትግል ዝግጁነቱን ወደ ላቀ ደረጃ ተማሻገር ~ርዕዮተ-ዓለማዊና ፖለቲካዊ አንድነትን ማጠናከር ~የትግሉን ፖለቲካዊ ግቦች ማስረፅ የሠራዊቱንና የአመራሩን የእርስ በእርስ ውህደትና የዓላማ አንድነት የበለጠ ለማጠናከር ~የጋራ ትብብርና አድነትን ማጠናከር እንደ ስማቸው ሁሉ በከፍታ ላይ በመብረር የጠላትን እንቅስቃሴ ከሩቅ የሚቃኙትና የመመታት አቅማቸው ከፍተኛ የሆነው የንስር ሻለቃ አባላት በዚህ የፖለቲካና የውጊያ ተሀድሶ ይበልጥ ታድሰውና ተዘጋጅተው ለተጨማሪ ግዳጅ መቅረባቸው ተገልጿል። ይህ የተሀድሶ መድረክ አመራርና አባላት የህዝባቸውን ነፃነት፣ ክብርና ህልውና ለማረጋገጥ የሚያደርጉትን ተጋድሎ እስከ አሸናፊነት ለመምራት ያላቸውን የማይናወጥ ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጡበት ሆኗል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

የንስር ሻለቃ የትግል ዝግጁነቱን ላቀ ደረጃ ያሸጋገረ ልዩ የተሀድሶና የፖለቲካ ንቃተ-ህሊና መድረክ ተካሔደ!! ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ተወርዋሪው የንስር ሻለቃ፣ ህዝባዊ ትግሉን በተሻለ ስትራቴጂያዊ ዝግጁነትና ወታደራዊ ዲስፕሊን ለማጠናከር ያለመ ልዩ የተሀድሶና የፖለቲካ ንቃተ-ህሊና ማሳደጊያ መድረክ በታላቅ ድምቀት አካሂደዋል። በዓላማ ፅናትና በወታደራዊ ስትራቴጂ ዝግጁነት የታነፀው ይህ መድረክ የአማራ ህዝብ እያካሄደ ባለው ፍትሃዊ የህልውና ተጋድሎ ውስጥ የኃይል ሚዛኑን ሙሉ በሙሉ ወደ ድል ለመቀየር ያለሙ ቁልፍ ውሳኔዎች የተበሰሩበት ሆኖ አልፏል። በመድረኩ ላይ የአፋብን ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር አርበኛ መከታው ማሞ፣ የአፋብን መካናይዝድ ጦር መምሪያ ሃላፊ አርበኛ አብረሃም ኩራባቸውን ጨምሮ የዕዙ ከፍተኛ ወታደራዊና ፖለቲካዊ አመራሮች፣ የንስር ሻለቃ መሪዎች እንዲሁም በክብር እንግድነት የተገኙት የአፄ አምደፂዎን ኮር አመራሮች ተሳትፈዋል። የመድረኩ ዋና ዋና ዓላማዎች ~ የአመራርና የሻለቃውን ወታደራዊ ብቃት ማሳደግ፡ ~የተሀድሶ መድረኩ የወታደራዊ ስልቶች ማሻሻያዎች ~ የግዳጅ አፈፃፀም ግምገማዎችንና የወደፊት ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎችን በጥልቀት በመገምገም የትግል ዝግጁነቱን ወደ ላቀ ደረጃ ተማሻገር ~ርዕዮተ-ዓለማዊና ፖለቲካዊ አንድነትን ማጠናከር ~የትግሉን ፖለቲካዊ ግቦች ማስረፅ የሠራዊቱንና የአመራሩን የእርስ በእርስ ውህደትና የዓላማ አንድነት የበለጠ ለማጠናከር ~የጋራ ትብብርና አድነትን ማጠናከር እንደ ስማቸው ሁሉ በከፍታ ላይ በመብረር የጠላትን እንቅስቃሴ ከሩቅ የሚቃኙትና የመመታት አቅማቸው ከፍተኛ የሆነው የንስር ሻለቃ አባላት በዚህ የፖለቲካና የውጊያ ተሀድሶ ይበልጥ ታድሰውና ተዘጋጅተው ለተጨማሪ ግዳጅ መቅረባቸው ተገልጿል። ይህ የተሀድሶ መድረክ አመራርና አባላት የህዝባቸውን ነፃነት፣ ክብርና ህልውና ለማረጋገጥ የሚያደርጉትን ተጋድሎ እስከ አሸናፊነት ለመምራት ያላቸውን የማይናወጥ ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጡበት ሆኗል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

በማጀቴ ቀጠና የቀበሌዎች አስተዳደራዊ መዋቅር ማሻሻያ ማካሄዱ ተገለፀ! በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የይፋትና ጥሙጋ አውራጃ የማጀቴ ቀጠና የትግል እንቅስቃሴን ይበልጥ ለማጠናከር እና የህዝቡን
+4
በማጀቴ ቀጠና የቀበሌዎች አስተዳደራዊ መዋቅር ማሻሻያ ማካሄዱ ተገለፀ! በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የይፋትና ጥሙጋ አውራጃ የማጀቴ ቀጠና የትግል እንቅስቃሴን ይበልጥ ለማጠናከር እና የህዝቡን የደጀንነት ሚና ለማሳደግ ያለመ ሰፊ ህዝባዊ መድረክ አካሄደ። ከዕዙ አመራሮች በተጨማሪ ከኮር እና ከክፍለ ጦር አመራሮች ጋር በመቀናጀት በተለያዩ ቀበሌዎች በመገኘት ከህዝቡ ጋር ጥልቅ ውይይት ተደርጎ መዋቅራዊ ማሻሻያ ማድረጋቸውን ኮሩ ገለፀ። ውይይቱ በሦስት ቀበሌዎች  በገተም ጎጆ ውሃ፣ በካብና ሳር አምባ ደጉቼ እንዲሁም በሰለሎ ሚራሚር ቀበሌዎች ተካሒዷል። በውይይቱ የመዋቅር ማሻሻያ ማድረግ ያስፈለገበትን ወታደራዊ እና ህዝባዊ ምክንያት በተመለከተ ከአመራሮች ሰፊ ማብራሪያ የተሠጠ ሲሆን፣ ከህዝቡ ለተነሱ ጥያቄዎች ግልጽ ምላሽ ተሠጥቷል። በመድረኩ የተገኙ የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች ወቅታዊውን የትጥቅ ትግል ደረጃ፣ የኃይል ቁመና እና የቀጣይ ግቦችን በተመለከተ ማብራሪያ በመስጠት፤ ህዝቡ ለተቀናጀው የነጻነት እና የህልውና ትግል ደጀንነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥልና ለቀጣይ ወታደራዊ ስምሪቶች የነቃ ዝግጁነት እንዲኖረው ጥሪ አቅርበዋል። የአካባቢው ነዋሪዎችም በበኩላቸው የትግሉ ባለቤት እና ዋና ደጀን መሆናቸውን በመግለጽ፤ ከልማት፣ ከመልካም አስተዳደር እና ከመሰረታዊ አቅርቦቶች ጋር ተያይዘው ለቀረቡ ጥያቄዎች ከአመራሩ አጥጋቢ ምላሽ ማግኘታቸውን አረጋግጠው፡ አዲስ የተሾሙት አመራሮችም ሕዝባቸውን በኃላፊነት፣ በታማኝነት፣ በቅንነት ለማገልገል ቃለ መሀላ በመፈፀም ውይይቱ ተጠናቋል። ምንጭ፦ በአፋብን አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ! የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24

💛🦁 እኛ አማራዎች 🦁💛 "ኩራታችን ታሪካችን ነው፤ ጥንካሬያችን አንድነታችን ነው!" እኛ አማራዎች፤ አገር መሥራች፣ ፍርድ አዋቂ፣ ታሪክ ጠባቂ፣ የራሳችንን የማንሰጥ፣ የሰውን የማንፈልግ፣ ንጹሕ እምነት ያለን፣ ተፈጥሮ በራሷ ውብና ጀግና አድርጋ የፈጠረችን ኩሩ ማኅበረሰብ ነን። የተከበረ ባህል፣ የጠነከረ ታሪክ፣ የጸና እምነት ይዘን፣ አባቶቻችን ባቆዩልን ምድር ላይ በኩራት የምንኖር አማራ ኢትዮጵያውያን ነን። "ማንነታችንን በኩራት፣ ታሪካችንን በክብር፣ ወደፊታችንን በአንድነት እንገነባ!" — የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ምክትል ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ዶ/ር አብደላ እንድሪስ ━━━━━━━━━━━━━━ 📲 ለተጨማሪ መረጃዎችና ወቅታዊ ዝመናዎች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ፦ 👉 https://t.me/YimerChannel

🦁 ሸዋ‼ ሸዋ የነገሥታት መፍለቂያ፣ የአርበኞች አንባ፣ የጀግኖች መወለጃ። የታሪክ ምዕራፍ በክብር የተጻፈባት፣ የነፃነት መንፈስ ዘላለም የሚኖርባት። አማራ ኩራት ናት ሸዋ፤ የጀግኖች ስም የማይጠፋባት፣ የክብር ባንዲራ ለዘላለም የሚውለበለብባት❗ ሸዋ ታሪክ ናት፤ ሸዋ ክብር ናት፤ ሸዋ ኩራት ናት‼

የአፋብን ወታድራዊ  ቃል ቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ    ''ከላይ በፈጣሪ - ከታች በክንዳችን'' ህዝባዊ ውይይት በከሚሴ ዙሪያ ስሙልን እስከ መጨረሻው

ከአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የተሰጠ የሀዘን መግለጫ ​በዛሬው ዕለት ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም በታላቋ ደብረ ምጥማቅ ፃድቃኔ ማርያም ገዳም በደረሰው ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደ
ከአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የተሰጠ የሀዘን መግለጫ ​በዛሬው ዕለት ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም በታላቋ ደብረ ምጥማቅ ፃድቃኔ ማርያም ገዳም በደረሰው ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ የበርካታ ወገኖቻችን ሕይወት ማለፉና ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱ ለአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ እንዲሁም ለጠቅላላው ሕዝባችን ጥልቅና እጅግ ከባድ የሆነ ሐዘንን ፈጥሯል። ​ይህ ታሪካዊና ቅዱስ ስፍራ የብዙዎች መጽናኛና የጸሎት ቦታ በሆነበት ቅጽበት ደረሰ የተባለው ይህ አሰቃቂ አደጋ፥ የ14 ወገኖቻችንን ሕይወት ቀጥፎ የሄደ፣ 5 ወገኖቻችንን ለከባድ አካል ጉዳት እንዲሁም 2 ወገኖቻችንን ለቀላል ጉዳት የዳረገ ልብ ሰባሪ ክስተት ሆኗል። የወገኖቻችን ድንገት ማለፍና መጎዳት ልብ ሰባሪ ክስተት ነው። ​የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ በአደጋው ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን የተሰማውን መራርና ጥልቅ ሐዘን እየገለጸ፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው፣ ለገዳሙ ማህበረሰብ እና ለሙላው ሕዝባችን መጽናናትን ይመኛል። ​ልዑል እግዚአብሔር የሞቱትን ወገኖቻችንን ነፍስ በአብርሃም፣ በይስሐቅና በያዕቆብ አጠገብ በገነት ያኑርልን፤ በጽኑ ተጎድተው በሕክምና ላይ የሚገኙትን ወገኖቻችንን ፈጣሪ በቸርነቱ ቁስላቸውን ይዳብስልን፣ ፈጣን ምህረቱንም ያውርድላቸው። ​አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም

👏 7ለ70 ክፍለ ጦር 👏 የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የጀግናው 7ለ70 ክፍለ ጦር አናብስቶች በአንድነት መድረክ ላይ!

በማጀቴ ቀጠና በተካሄደ ህዝባዊ ውይይት የቀበሌዎች መዋቅራዊ ማሻሻያ ተደረገ!! ሐምሌ 26/2018 ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ማጀቴ ቀጠና የስራ ስምሪት የተሰጣቸው ከፍተኛ አመራሮች፣ ከአጼ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር እና ከአጼ ይኩኖ አምላክ ክፍለ ጦር አመራሮች ጋር በመቀናጀት በማጀቴ ቀጠና በሚገኙ ሶስት ቀበሌዎች ላይ ሰፊ ህዝባዊ ውይይት በማድረግ የቀበሌዎች መዋቅራዊ ማሻሻያ ማድረጉን የኮሩ ሕዝብ ግንኙነት ገለፀ። እንደ ኮሩ ሕዝብ ግንኙነት ገለፃ፤ ይህ የመዋቅር ማሻሻያና የህዝብ ውይይት መድረክ የተካሄደው በአግላ ማጀቴ፣ በአንቃር ኮበኮብ እና በማጀቴ 01 ቀበሌዎች ውስጥ ሲሆን፤ የህዝቡን ተሳትፎና ውሳኔ ማዕከል ባደረገ መልኩ በስኬት መጠናቀቁን አክሎ ገልጿል። በመድረኩ ላይ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች አማካይነት ስለ ትግሉ ወቅታዊ ቁመና ሰፊና ዝርዝር ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን፣ ህዝቡም ጥያቄዎቹንና ሀሳቦቹን በነጻነት አፀባርቋል። ይሕ የተደረገው አዲስ የድርጅታዊ መዋቅር ማሻሻያ በአካባቢው አስተዳደራዊ አገልግሎቶችን የበለጠ ለማፋጠን፣ የአካባቢውን ሰላምና ደህንነት ለማጠናከር እንዲሁም ከህዝቡ ጋር ያለውን ቀጥተኛ ግንኙነት ወደተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር ያለመ መሆኑ ተብራርቷል። የየቀበሌው ነዋሪዎች በበኩላቸው በተካሄደው ውይይትና በተደረገው የአመራር ምርጫ ላይ ያላቸውን ደስታ ገልጸው፤ ከአዲሶቹ የቀበሌ አመራሮች ጋር በመተባበር ለአካባቢው ልማትና ሰላም እንዲሁም ትግሉን ለማፋጠን በትጋት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። በሶስቱም ቀበሌዎች በህዝቡ ሙሉ ፍላጎትና ነጻ መራጭነት አዳዲስ የቀበሌ መዋቅር አመራሮች ተመርጠዋል። አዲስ የተመደቡት አመራሮችም ህዝቡንና አካባቢያቸውን በቅንነት፣ በታማኝነት፣ በፍትሃዊነትና በጽናት ለማገልገል በህዝቡ ፊት ቃለ መሃላ ፈጽመዋል። " ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

ነበልባል ክ/ጦር የጨፍጫፊውን አገዛዝ ጥምር ጦር ዕቆድ አከሸፈ! ​ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ​የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት የአሳምነው ዕዝ ከሰም 2ኛ ኮር ነበልባል ክፍለ ጦር የአገዛዙን ጥምር ኃይል በንጹሃን ዜጎች ላይ ያቀደውን የጥቃትና የዝርፊያ እንቅስቃሴ አከሸፈ። ​የአገዛዙ ጥምር ሀይል በቀን 24/11/2018 ዓ.ም በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች ማለትም ሲቪለን፣ ምነበላ፣ አዳማ ወንዝእና ቱሊ በተባሉ አካባቢዎች ሰፊ እንቅስቃሴ ያደረገ ቢሆንም በነበልባል ክ/ጦር ፈጣን የማጥቃት እነሰቅስቃሴ በማድረግ የአገዛዙን ሀይል ያዋረደ ድል ተቀዳጅተዋል። አገዛዙ በነበረው እልህ አስጨራሽ ውጊያ በአርሶ አደር ቤት እና ንብረት ላይ ያለውን ሁሉ መሳሪያ የተጠቀመ ቢሆንም የአርሶ አደሮች ንብረት እና ህይወት ማጥፋቱን ቀጥሎበታል። የነበልባል ክ/ጦር የሲቪሎችን ህይወት ለመታደግ ሲባል የስልት ለውጥ መውሰዳቸውን ገልጸዋል። ነበልባል ክፍለ ጦር አባላት ከአገዛዙ ኃይል ጋር ባደረጉት ፍልሚያ የተቃጣውን የጥቃት እቅድ አክሽፈዋል። ​ የጠላት ኃይል አርሶ አደሮችን ለውጊያ መከታነት ለመጠቀም በሞከረበት ወቅት የፋኖ ሰራዊታችን የውጊያ ስልቱን በመቀየር የንጹሃንን ህይወት መታደግ ችሏል። በተለይም በሲቪለንእና ምነበላ ግንባሮች የነበረው ከፍተኛ ውጊያ የጠላትን ሀይል ሙትና ቁስለኛ ማድረጋቸውን የኮሩ ሕዝብ ግንኙነት ክፍል ገልጿል። ​በተጨማሪም በአዳማ ወንዝ አካባቢ በተደረገ የተቀናጀ ደፈጣ በጥምር ኃይሉ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሳቸውን ያሳወቁ ሲሆን፤ የአገዛዙ ጨፍጫፊ ኃይል በሰነዘረው የከባድ መሳሪያ ድብደባ በንጹሃን አርሶ አደሮች ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን የግንባር መረጃችን አክሎ ገልጿል። " ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ