en
Feedback
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ

አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ

Open in Telegram
5 081
Subscribers
+1124 hours
-157 days
-7730 days
Posts Archive
አርበኛ ደሳለኝ

7/70 ክፍለ ጦር ወታደራዊ ቁመናውን በማዘመን ለሁለንተናዊ ድልና ለግዳጅ ራሱን በተሃድሶ አዘጋጀ!! ነሐሴ 08/2018 ዓ.ም ጀብደኛው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ 7/70 ክፍለ ጦር ተቋማዊና ወታደራዊ ብቃቱን ይበልጥ የሚያጠናክርበትን ሰፊ የተሐድሶ መርሃ ግብር በደማቅ ሁኔታ አካሄደ። በሃይማኖት አባቶች ጸሎትና ቡራኬ የተከፈተው ይህ የተሀድሶ መርሃ ግብር የድርጅት፣ የዕዝ፣ የኮር እንዲሁም የክፍለ ጦር ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በዕዙ ባህልና መዝናኛ ቡድን ያሸበረቁ አማራዊ ተውኔቶች ታጅቦ ተከናውኗል። ለግማሽ ምዕተ ዓመት ያህል የዘነበበትን የመከራና የጭቆና ዶፍ ለመመከት የአማራ ህዝብ አምጦ የወለዳቸው እንቁ የዘመናችን የቁርጥ ቀን ልጆች መካከል አንዱ የሆነው 7/70 ክፍለ ጦር፣ ህዝቡን ከመጥፋትና ከውርደት ታድጎ ወደ ታሪካዊ የክብር ማማ ለማሸጋገር ራሱን ለህዝባዊ አላማ አሳልፎ የሰጠ የትግል ግንባር ቀደም ኃይል ነው። ለ13ኛ ጊዜ በጠላት ወረራና በእሳት ከተቃጠለው የደም ምድርና ጽኑ ማህበረሰብ ተሰባስቦ የተደራጀ መሆኑ ልዩ ያደርገዋል። በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ምድር በጀግንነት ታሪኩ የሚታወቀው፤ በመከራ ቀን እንደ ንብ የሚናደፍ ለመጣበት ጠላት የማይበገር የታሪካዊቷ የአጣዬ ምድር ፍሬና የአማራ ህዝብ የቁርጥ ቀን ጠበቃ ነው። ክፍለ ጦሩ በሂደት ያጋጠሙትን ውስጣዊ ክፍተቶች በመሙላት፣ በአዳዲስ አመራሮች ወታደራዊ ቁመናውን ለማዘመንና ለቀጣይ ድርጅታዊ ግዳጆች ራሱን በከፍተኛ ዝግጁነት አድሶ ተከስቷል። በዚሕ የተሐድሶ መድረክ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የአፋብን ተ/ምክትል ሊቀመንበርና የፖሊት ቢሮ አባል አርበኛ መከታው ማሞ ባስተላለፉት መልዕክት፦ የትግሉን ቁርጠኝነት ገልጸው፤ "ሶፍት ላኩላቸው" ላሉን መንጋዎች፡ እኛ ደግሞ "ዳይፐር ላኩላቸው" ነው መልሳችን ሲሉ ገልፀዋል። በሌላ በኩል የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሰብሳቢና የአፋብን ስራ አስፈጻሚ አባል አርበኛ ደሳለኝ ሲያስብሸዋ፦ "ትግላችን ግብን እንዲመታ መሰረታዊ ሀዲዱን ዘርግተን እየተጓዝን ነው" ሲሉ ገልጸዋል። እዲሁም የአሳምነው ዕዝ ዋና ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ አማን እሸቱ በበኩላቸው የወታደራዊ ዝግጅትን ደረጃ በማጎላት "ራሳችሁን ለቀበሌና ለወረዳ ሳይሆን፣ ለመጨረሻው ታላቅ ግዳጅ አዘጋጁ" ሲሉ ለሰራዊቱ ወታደራዊ መመሪያ አስተላልፈዋል። በመጨረሻም የተሐድሶ መርሃ ግብሩ ባሕልና መዝናኛ ክፍል ባዘጋጃቸው ህዝባዊና ወታደራዊ ኪነት ደምቆ ውሏል። ክፍለ ጦሩ አዳዲስ አመራሮችን በመመደብ፣ ሕዝባቸውንና ሠራዊታቸውን በተጣለባቸው ኃላፊነት አመራሮቹ፡ በታማኝነት፣ በቁርጠኝነት፣ በቅንነት እዲያገለግሉ ቃለ-መሀላ በመፈፀም መርሃ ግብሩ ተጠናቋል። " ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ

የአምባገነኑና ዘረኛው ስርዓት ሠራዊት ያለውጊያ መበተኑን ቀጥሎበታል! ነሃሴ 07/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ያለ ምንም ጦርነትና መስዋዕትነት የአገዛዙን ጦር በመረጃና ደሕንነት እዲፈርስ ማድረጉ ታወቀ። የአማራን ሕዝብ ከዘር መጥፋት ለመታደግ ዋስ ይሆነው ዘንድ ድርጅት መስርቶ በአራቱም አቅጣጫ እየተዋደቀ የሚገኘው "የአፋብን" ሠራዊት የጠላትን ኃይልን በመቀበል ወደ ፋኖ እዲቀላቀሉ እያደረገ ይገኛል። በዚሕም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝን በጥቂት ቀናቶች በርካታ የስርዓቱ ጠባቂ ኃይሎች ከድተው እዲቀላቀሉ ለማድረግ ተችሏል። 1.ሀብታሙ ብርሀኑ--የሻለቃ መሪ አጃቢ 2.በለጠ አዳነ--ዶሽቃ ተኳሽ ➠2 ጥርጥር ክላሽ ➠230 ተተኳሽ ➠2ቦንብ ➠ 2 ትጥቅ 👉 ከ112ኛ አየር ወለድ ክ/ር --ወደ አፄ ምኒልክ ክ/ር 3.ም/፲ አለቃ ስመኝ ሙላቱ--መሰናክል አስወጋጅ 4.ም/፲ አለቃ ኤሊያስ ዳምጤ-- '' '' '' '' ➠2 ጥቁር ክላሽ ➠2 የደረት ትጥቅ ➠2ቦንብ ➠180 ተተኳሽ 👉 ከ605ኛ ኮር ኮማዶ ክ/ር--ወደ ራስ አበበ አረጋይ ክ/ር 5.ክንዱ ቸሩ ስናይፐር ተኳሽ 6.ይሳቅ ፈቃዱ ዶሽቃ ተኳሽ ➠3F1 ቦንብ ➠1 ሳንጃ(ጩቤ) 👉 ከ101ኛ አየር ወለድ ክ/ር 5ኛ ሻለቃ-ወደ አፄ ዳዊት ክ/ር 7.መሠረታዊ ወ/ር ኤልያስ ፀጋዬ(RSF) 8." " " ጊዜው የማታ(RSF) ➠2 ጥርጥር ክላሽ ➠ 4ቦንብ ➠2ትጥቅ ➠440 ተተኳሽ 👉 ከ112ኛ አየር ወለድ ክ/ር--ወደ ንጉሥ ሣህለ ሥላሴ ክ/ር 9. ሁለት(2) ለደሕንነታቸው ስማቸው ያልተጠቀሱ ➠2ክላሽ ➠2ትጥቅ ➠3 ቦንብ ➠175 ተተኳሽ 👉 ከ111ኛ ኮማዶ ክ/ር--ወደ ሀ/ማርያም ማሞ ክ/ር ✔ በጠቅላላ፦ 10 =የሠራዊት አባል 8=ትጥቅ 14=ቦንብ 1025= ተተኳሽ 8= ክላሽኮቭ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አምደ ጽዮን ኮር ገቢ ማድረግ መቻሉን የኮሩ ሚዳያና ኮሙኒኬሽን አስታውቋል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ ​ቀን፦ ነሐሴ 06 ቀን 2018 ዓ.ም ​በንጹሐን ወጣቶች ላይ የሚፈጸመውን የግፍ ግድያ፣ ወታደራዊ የግዳጅ አፈሳ እና የአዲስ አበባን የፖለቲካ ሴራ አስመልክቶ ከአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የተሰጠ መግለጫ ​የአማራ ህዝብ የተደቀነበትን የህልውና አደጋ ለመመከት እና ተፈጥሮአዊ ወይም ሰብአዊ መብቱን ለማስከበር የሚያደርገው ፍትሃዊ ትግል በከፍተኛ ህዝባዊ ደጋፊነት ወደፊት እየገሰገሰ ይገኛል። ነገር ግን የስርዓቱ አስፈጻሚዎች ትግሉን ማቆም ሲሳናቸው በንጹሐን ወላጆች እና ወጣቶች ላይ የሚያደርሱትን የግፍ እርምጃ እና የሽብር ተግባር አጠናክረው ቀጥለውበታል። ​በመሆኑም አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ወቅታዊ እና አስቸኳይ የፖለቲካ እና ወታደራዊ ሁኔታዎችን አስመልክቶ የሚከተለውን የአቋም መግለጫ አውጥቷል፦ ​1. በንጹሐን ወጣቶች ላይ በአገዛዙ ብልፅግና የተፈጸመውን አሰቃቂ የእብሪት ግድያ ( መረሸንን) በተመለከተ:- በቀን 04/12/2018 ዓ.ም በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ከተሳፈሩበት የሕዝብ ማጓጓዣ መኪና ላይ “ፋኖ ናችሁ” በሚል መላ ምት እና ውንጀላ ተገደው እንዲወርዱ ከተደረጉ በኋላ በማንነታቸው ብቻ በአሰቃቂ ሁኔታ የተረሸኑትን የሶስት ንጹሐን አማራ ወጣቶች ግድያ እዛችን በጽኑ ያወግዛል። 1ኛ. ​ወጣት ተመስገን ጌታቸው 2ኛ. ​ወጣት ይታገሱ አሰግደው 3ኛ. ​ወጣት ግዛው ግርማ ​ፋኖነት የአማራ ህዝብ የታሪካዊ እሴቱ፣ የጀግንነቱ እና የህልውናው መገለጫ እንጂ ንጹሐን ዜጎችን ያለ ህግ አሰራር የሚያስገድል "ወንጀል" ወይም ኮድ አይደለም። በህዝብ ማጓጓዣ ላይ የሚጓዙ ንጹሐን ዜጎችን በማንነታቸው ብቻ ተለይቶ መረሸን የስርዓቱን አረመኔነት እና የሞራል ውድቀት ወይም መፍረስን የሚያሳይ ግልጽ የጦር ወንጀል ነው። ​2. የግዳጅ ወታደራዊ አፈሳ እና የከተሞች ወታደራዊ ከበባን አስመልክቶ :- ​በአሁኑ ወቅት በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ሁሉም ከተሞች ማለትም በአዲስ አበባ፣ በናዝሬት ፣ በደብረዘይት ፣ ደብረብርሃንን ጨምሮ በሁሉም አውራጃዎች ስር ባሉ ወረዳዎች ይህ አረመኔ ስርዓት ሰፊ ወታደራዊ የግዳጅ አፈሳ ጀምሯል። ወጣቶችን ከመንገድ፣ ከስራ ቦታ እና ከሙያ መስካቸው እያፈሰ የአማራን ህዝብ እየጨፈጨፈ ያለ ፀረ -ህዝብ እና ፀረ- አንድነት የሆነው አገዛዝ በግዳጅ ከተሸናፊነት ለማያድነው ጉዞ ወጣቶችን ወደ ጦርነት ማግዳ በመክተት ላይ ይገኛል። ​ይህ ህገ-ወጥ አፈሳ የስርዓቱን ውድቀት የሚያፋጥን እንጂ ህዝባዊ ትግሉን የሚያስቆም አይደለም። በመሆኑም በነዚህ ከተሞች የምትገኙ የአማራ ወጣቶች ለገዢው ቡድን የመሳሪያ ማኖሪያ ከመሆን ይልቅ፣ የህዝባችሁን ህልውና ለማስከበር በግንባር ቀደምትነት እየታገለ የሚገኘውን አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝን እንድትቀላቀሉ ጥሪ እናስተላልፋለን። ​3. የአዲስ አበባ ህልውና እና የፖለቲካ ደባ :- ​የአማራን ህዝብ "ወደ ዋና ከተማህ አዲስ አበባ አትገባም" ሲል የቆየው የገዢው ቡድን ፖለቲካዊ መዋቅር፣ ዛሬም በአዲስ ማጭበርበሪያ የከተማዋን ነዋሪዎች እና ተወላጆች ከመንግስታዊ እና ኢኮኖሚያዊ መዋቅር በማግለል ላይ ይገኛል። ​ከተማዋን ሙሉ በሙሉ ለመዋጥ እና የስነ-ሕዝብ (demographic) ስብጥርን ለመቀየር የሚደረገው የተቀናጀ ሴራ፣ መብታቸውን የሚጠይቁና የሚሟገቱ ሰዎችን በማሰር፣ በማሳደድ እና በማስፈራራት አደገኛ ደባውን እያከናወነ ይገኛል። ይህ የሀገርን ጥቅም ለመሸጥ እና ለመቀራመት የሚደረግ እቅድ የመላው ኢትዮጵያውያን ስጋት ነው። ​4. አጽንኦት የሚሰጠው የትግል አቅጣጫና ጥሪ • ​ለአማራ ወጣቶች፦ የግፍ ሰለባ ከመሆን እና በግዳጅ አፈሳ ወደማታምኑበት እቅድ ከመነዳት ይልቅ ህልውናችሁን እና የህዝባችሁን ክብር ለማስከበር የፋኖን ትግል ተቀላቀሉ። • ​ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች እና መላው ኢትዮጵያውያን፦ በከተማችሁ እና በሀገራችሁ ላይ እየተፈጸመ ያለውን ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖ በጋራ እንድትታገሉ፣ የፋኖን ህዝባዊ የህልውና ትግል በገንዘብ፣ በሀሳብ እና በፅናት እንድትደግፉ ጥሪያችንን እናቀርባለን። • ​ለስርዓቱ የፀጥታ መዋቅር/የደህንነት አባላት፦ ህዝብን ጨፍጫፊ እና ሀገር አፍራሽ ለሆነው አገዛዝ መሳሪያ ከመሆን ተቆጥባችሁ ወደ ህዝባችሁ ጎን እንድትቆሙ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ እንሰጣለን። ''ክብር ለትግሉ ሰማዕታት'' ​ ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ነሐሴ 06 ቀን 2018 ዓ.ም

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን)--ወታደራዊ የግንባር አውደ-ውሎ መረጃዎች ​      ነሐሴ 05 ቀን 2018 ዓ.ም። ​የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወታደራዊ ክንፍ በተለያዩ ግንባሮች የወሰዳቸውን የተቀናጁ ማጥቃቶች እና በንጹኃን ወገኖቻችን ላይ የተፈጸመውን የጭፍጨፋ ዝርዝር መረጃ ለሕዝብና ለብዙኃን መገናኛዎች እንደሚከተለው ያቀርባል። ​፩. አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዓፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር — ነጎድጓድ ክፍለ ጦር (፩ኛ እና ፪ኛ ሻለቃዎች) በእነዋሪ እና በጅሁር አቅጣጫዎች የአገዛዙ ጥምር ጦር ከማለዳው 12:00 ሰዓት ጀምሮ ከበባና ማፈን ለመፈጸም ያደረገውን እንቅስቃሴ የነጎድጓድ ክፍለ ጦር ሻለቃዎች በተቀናጀ እና ሥልታዊ መልሶ ማጥቃት መክተውታል። በተወሰደው ከባድ ወታደራዊ ምት በጠላት ሰው ኃይል እና ቁሳቁስ ላይ ከፍተኛ ኪሳራ በመጨረስ ኃይሉን ወደ መጣበት እንዲመለስ ተደርጓል። ​፪. አፋብን ወሎ ጠቅላይ ግዛት ምኒልክ ዕዝ 101ኛ ኮር — 35ኛ ክፍለ ጦር (1ኛ ሻለቃ) ሰሜን ወሎ ዞን፣ ሀብሩ ወረዳ፣ ኤላ አካባቢ (ከውርጌሳ ወደ መርሳ በሚወስደው መስመር) በካሶኒ መኪና ተጭኖ ሲጓዝ በነበረ የአገዛዙ ሚሊሻ ላይ በተወሰደ የተቀናጀ የደፈጣ ጥቃት ከአምስት (5) በላይ የአገዛዙ ሚሊሻዎች ሲደመሰሱ፣ በርካቶች ቆስለዋል። ጥቃቱን ለማምለጥ የካሶኒው ሾፌር ለማምለጥ ሲያበር ሁለት የግል ባጃጆችን ገጭቶ ቁስለኞቹን ወደ መርሳ ሆስፒታል ወስዷል። ​፫.  አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ እና የጉሙዝ ኃይል አንድነት ግንባር (የጋራ የግንባር ክዋኔ) ስንመለከት ✅አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ (105ኛ ኮር — 66ኛ ክፍለ ጦር) እና የጉሙዝ ኃይል አንድነት ግንባር (የቤንሻንጉል ጉሙዝ ነፃ አውጪ) የመተከል ዞን ዋና ከተማ — ግልገል በለስ ከጠዋቱ 12:00 እስከ 3:00 ሰዓት በተደረገ በከባድ መሣሪያ የታገዘ እልህ አስጨራሽ ፍልሚያ፣ በጠላት ሰራዊት ላይ ከፍተኛ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ በማድረስ የግልገል በለስ ከተማን በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል። ይቀጥላል.... ​ በወለጋ በንጹኃን ላይ እየተፈጸመ ያለ ጭፍጨፋ •  ​የተጎዱ አካባቢዎች፡ ◦ ​ምስራቅ ወለጋ ዞን፡ አንገር ጉትን፣ መንደር 04፣ መንደር 03፣ መንደር 12፣ መንደር 02፣ መንደር 14 እና ሌሊ ተክለሃይማኖት። ◦ ​ሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን፡ አቤደንጎሮ ወረዳ (ከመንደር 15 እስከ ቱሉጋና ከተማ እና አካባቢው)፣ ከትናንት ነሐሴ 04/2018 ዓ.ም ማለዳ ጀምሮ እስከ ዛሬዋ ዕለት ተባብሶ የቀጠለ አሰቃቂ ጭፍጨፋ ተከፍቷል። በዚህም ጥቃት ነፍሰጡር ሴቶች፣ እመጫት እናቶች ከነጨቅላ ሕፃናት ልጆቻቸው እና በርካታ ንጹኃን ዜጎች በተቀናጀ ሁኔታ ተገድለዋል። ​ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወታደራዊ ቃል አቀባይ https://www.facebook.com/share/p/14rmmDjbPpG/

ነሀሴ 5/2018 ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ከተሞች፦ አዲስ አበባና ናዝሬትን ጨምሮ በአጣዬ፣ ሸዋሮቢት፣ ደብረብርሃን፣ መሀልሜዳ፣ ሞላሌ፣ ዓለም ከተማ፣ ደብረሲና፣ አረርቲና መተሀራ ከተሞች ተሸናፊው
+2
ነሀሴ 5/2018 ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ከተሞችአዲስ አበባና ናዝሬትን ጨምሮ በአጣዬ፣ ሸዋሮቢት፣ ደብረብርሃን፣ መሀልሜዳ፣ ሞላሌ፣ ዓለም ከተማ፣ ደብረሲና፣ አረርቲና መተሀራ ከተሞች ተሸናፊው የብልፅግና ስርዓት ወጣቶችን እያፈሰ ነው። ደርግን ከውድቀት ያላዳነ ወታደራዊ አፈሳ መዋቅራዊ መበስበስ አጋጥሞት  ከተሸነፈ የከረመውን ብልፅግናን ከወድቀት አያድነውም። ወጣቶች ራሳችሁን ከብልፅግና አፈሳ ሰውራችሁ የአማራ የህልውና ትግልን በህዝባዊ ድጋፍ ከፍ ወዳለ እድገት ያሸጋገረውን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ፋኖን እድትቀላቀሉ ስል መልዕክት አስተላልፋለሁ።  የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አ/ዕዝ ከፍተኛ አመራር ኢንጂነር አዶናይ አበበ ድል ለአማራ !!

+3
✅አፄ ምኒልክ ክፍለ ጦር👏 የአፋብን ሸዋ ጠቅለይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ አምደ ጽዮን ኮር አካል የሆነው የአፄ ምኒልክ ክፍለ ጦር በዛሬው ዕለት ነሃሴ 04 ቀን 2018ዓ.ም ባተካሔደው መድረክ ላይ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ሲያደርግ፣በመድረኩም በየደረጃው በሚገኙ አመራሮች ለሰራዊቱ የፖለቲካ የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራም ማድረጉን የክፍለ ጦሩ ህዝብ ግንኙነት ክፍል አስታውቋል። "ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ነሃሴ 04/2018 ዓ.ም የአፄ ምኒልክ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ክፍል

ቀንሱኝ ቀንሱኝ እኔ አልደመረም ሰው ከሌለ ሀገር መበልፅግ አይኖርም ። ስንበዛ ሲገሉን ሲገሉን ስንበዛ ፣ ዘመን ተቆጠረ ፤ ከባንዳ ላይ ባንዳ እየተደመረ ። አልተሰበሰበም ያገሬ አዝመራው ፤ ዛላው ፣ ዛለው ወድቆል በየጎዳናው፤ ሀብት እና ንብረቱን ሜዳ ላይ በትኖ፤ ኢትየጵያ ለማዳን ነው የቆመው ፋኖ። እንዲህም እንዲያ እቃኘዋለው ፤ የናንተ ወንድም ምን እሆነለው ፤ ዳዊት በሽንጡ ሀሌ እያዘለ፤ ቁራን በሽንጡ ሁሌ እያዘለ፤ ቅኔ እንደ ስጋ የዘለዘለ ፤ ለአእውንት የሚሞት ሀቅ የተኮለ፤ እየቀነሱት ሰማይ እያከለ ፤ ዝመተኛ ነው ቀድሞ የነቃ ፤ ታሪኩ ደማቅ እንደ ጨረቃ ። እንደ ጎልያድ እንደ ፈርኦን ልቡ ደንድኖ፤ አጋድሞት ሄደ ዳዊት ሆኖ ፤ ጥቃት አይወድም ቆፋጣናው ፋኖ ፤ ወጣና ታገል ቆመ አታልቅስ ፤ መጥቶ እስኪገልህ ደም እስኪፈስ ፤ የሞተው ሞቶ አፈር ቢጫነው ፤ ፋኖ ለሀገሩ ባለውለታ ባለታሪክ ነው ። ጊዜ እንዳትሰጠው ሙት ይደረጃል ፤ ቆፍጣናው ፋኖ ክንዱ ይፋጃል ፤ በል ተነስ ግፋ በል እነሂድ ፤ አልወድም እኔ ሆሊት መንገድ ፤ ጠላትም ይውደም እሳት ይንደድ ፤ በእናት እህቴ እንዳትቀልድ ፤ ደምሽ ደሜ ነው አንሻ ሰይድ ። የአፄ ቴዌድሮስ የነካሳ ልጅ ፤ የነሺፈራው የነበላይ ልጅ ፤ የልጅ አያሱ የአሳምነው ልጅ ፤ የአፄ ሚኒልክ የነአስማረ ልጅ ፤ ወላሂ ብሎ ሃዛን ሲያወድስ ፤ ማሪያምን ብሎ ቄሱ ሲቀድስ ፤ ተስቦ ገዳይ እንደ እባብ ንጉስ ፤ ባንዳውን ጥሎ ታሪክ የሚያድስ ፤ የነፃነቱን ችቦ ሲለኩስ፤ በፀሃይ ቀልጦ ደሙንም ቢያፈስ፤ አማራ እኳ ነኝ የፊደል ንጉስ። እነድ መይሳው ሞትን አይፈሬ ፤ አንደ ሚኒልክ በማሪያም ምዬ ፤ እንደ አባ ኮስትር ገመድ አስሬ ፤ ታማኝ ነኝ በመሆን እነደገብርዬ ፤ ፅፌ ልፎክር ጠላቴን ጥዬ ፤ ክብሬ ሲነካ አልወድም እና ፤ የአማራ ልጅ ነኝ የቆርጦ በላ ። ታላቅ ክብሬ ነው አባ ኮስትር ለኔ ፤ ታላቅ ክብሬ ነው ሚኒሊክ ለኔ ፤ ታላቅ ክብሬ ነው ቴዌድሮስ ለኔ ፤ የአማራ ልጅ ነኝ የጀግኖች ፍሬ ፤ የማልደራደር በሀገር ድምበሬ ፤ ማነህ አትበለኝ አልወድም እኔ ፤ ማነህ አትበለኝ ያመኛል እኔ ፤ አማራ በለኝ። በክብር ስሜ። ሲገሉ ነበር ሲያፈናቅሉን ለ500 ዓመት፤ ህያው ምስክር ነው አሁን ላለንበት ፤ አባቶቻች የታገሉበት ፤ ሳህለሥላሴ ኃይለ መለኮት ፤ አጋድመው ወቁት ነዱት እንደከብት ፤ በአፈ ድምድሙ በአብራሪው ጥይት ፤ ይመስከር ጓንዴ የጥንቱ ብረት ፤ አውቶ መሣሪያ ባልነበረበት ፤ ከዚህ አርሲ ነገሌ ነፃ ያወጡበት ፤ ርዕስታችን ነው ሞጆ እና ናዝሬት ፤ የማኛው ጤፉን ያበቀልንበት ፤ ኃይለማሪያም ማሞ ስም የፃፉበት ፤ ይህ ነው ታሪክህ በል ዕወቅበት፤ እኳ ነው ሚባለው አንት ። ህልመኛው ወሎ ህልመኛው ሸዋ፤ ህልመኛው ጎንደር ህልመኛው ጎጃም ፤ ነቅሎ ይጥላል ካልሆነ መልካም ፤ ቆፍጠን ያለ ነው ክንድ አይነካም ፤ ለአብይ ወታደር ለዛ ዱካካም ፤ ማዕተነቡን ሽጦት ቀረ እንደዋዛ ፤ ዕምነቱን ሽጦት ቀረ እንደዋዛ ፤ ካለበላ አይስቅም ፊቱ ካልወዛ ፤ በ5ሺ ብር እየተገዛ ፤ ሚሊሻ ቀልጧል ልክ እንደ ጤዛ አስተውል እንጂ ታሪክ አትርሳ ፤ የሞተላትን መይሳው ካሳ ፤ አስተውል እንጂ ታሪክን ከላይ ፤ የሞታለትን አምበሳው በላይ ፤ አስተውል እነጂ ታሪክን በልክ ፤ የሞተላትን አፄ ሚኒልክ፤ ታሪክን ሳታውቅ ሀገር አትውቀስ ፤ የሞቱላትን አቡነ ጼጥሮስ ፤ የኖህ መርከብ ነች የማቱ ሳላ ፤ ጥበብን ለብሳ ከላሊበላ ፤ ጠላቷ ሙሉ አይኑ ሲቀላ ፤ በፋኖ አንድነት ታሪክሽ ጎላ ። ከሹርባሽ ዝናሽ ሚኒልክ ፤ ጥልቀቱ ረጅም የታሪክሽ ልክ ፤ ትወልደ ትወልድ ሁሌ ሚሰበክ ፤ ለሀገር መሞት የለው ኩነኔ ፤ ለወገን መሞት የለው ኩነኔ ፤ ከዳር እስከ ዳር ፣ ከጫፍ እስከ ጫፍ ፤ተነስ ወገኔ ፤ አማራ እኳ ነች የአይን ብሌኔ ፤ እሷ ከሌለች የለሁም እኔ። አንተ ማነህ ? አማራ ፤ አንተ ማነህ ? አማራ ፤ በደም እና በአጥነት ሀገር የምትሰራ ፤ ሀገር አቃፊ ታሪከ ሰፊ ፤ ሀገር መስራች ስለሀገር ሞች ፤ እንደ ጅቦች የማትከዳ ፤ እነደከብቶች የማትነዳ ፤ አንተ አማራ ነህ የሀገር በላዕዳ ፤ ለምድረ ጣልያን የማትደነግጥ ፤ ከአፄ ፋሲል እስከ ቴዌድሮስ ፤ የላሊበላ የቅዱስ ንጉስ ፤ የሼህ ሁሴን ልጅ የአቡነ ጼጥሮስ ፤ የንጉስ ሚካኤል የአፄ ሚኒልክ ፤ በክላሽ ገጥሞ ታንክ የሚማርክ ፤ ተነግሮ አያልቅም የፋኖ ታሪክ። አስማረ ዳኜ አበበ አረጋይ ፤ እሱ ነበረ ትልቁ ታጋይ ፤ አሸናፊ አለሙ ፣ ሞላ ደስዬ ፤ ሺ ውን ይጠላል አንዱ ሰውዬ ፤ አምባቸው መኮንን ስመኝው በቀለ፤ እውቀተ በርሃን ፅፎ የታገለ ፤ አሳምነው ፅጌ አስቻለው ደሴ ፤ ጋሻ ክንዴ ነው ክብሬ ነው ዋሴ ፤ አፄ ሚኒልክ ንጉስ ሚካኤል ፤ በላይ ዘለቀ አፄ ቴዌድሮስ ፤ ወደፊት ነበር የሚገሰግስ ፤ እነሱ ናቸው ለኛ ምስክር ፤ አልም ፅፎታል ይውጣ ይነገር ፤ እንዲህ ነው እንጂ ታሪክ ሲዘከር ፤ ልጅ ለአባቱ ነው ሁሌ የሚፎክር ። ትውልድን ሁሉ የቀረፀ ፤ ሀገር አቁሞ ዕምነት ያነፀ፤ ለአፋሪካዊያን ብሎም ኢትየጵያ ተስፋ የጣለ፤ የጥቁሮች አባት ዘር ያለከለለ፤ በዕውቀት ጥበቡ እያባበለ፤ ዓለምን ሁሉ ጉድ አያስባለ ፤ ጣልያን በዐድዋ ያንበረከከ ፤ በጋሻ ጦሩ እየታከከ፤ አፄ ሚኒልክ ነጭ ማረከ ፤ እኳ ነው ሚባው አንተ ። ተነስ ግጠመው ቁመህ አትየው፤ ጥጋበኛ ነው ፊት ከሰጠህው፤ የአፄ ቴዋድሮስ የአፄ ሚነልክ ፤ የአነ አስማረ ልጅ የአፄ የኩኑ ፤ አጣፍቶ ሰርቶት ጠላት ከሽኖ ፤ እጁን አይሰጥም የአማራ ፈኖ። መያዝ ነው እንጂ አንገቱን ብሎ፤ ካሊያዙትእማ የበቅላል ዘሎ ፤ ሞትን አይፈራም አይቀርም ብሎ፤ ነፃ ይወጣል አማራ ታግሎ፤ ይገሰግሳል ወደፊት ታግሎ፤ የአባት ቤት ነው በል ግባ ቶሎ፤ ስም ይፃፋል ነገ አራት ኪሎ። እንደመቀመጥ እንደመናሳት ፤ ደግሞ ምን ይሆን ተኩሶ መሳት ፤ አልመ በለው በክላሽ ጥይት ፤ ይገሰግሳል ገና ወደፊት ፤ የአባቶቹ ነው ጥንትም ጀግንነት ፤ አራት ኪሎ ነው የፋኖዎች ቤት ። የነፍጠኛ ልጅ በነፍጥ ያደገው ፤ ጠላትን ጥሎ ስሙን ለወጠው ፤ ፋኖ አይደለም ወይ የሚያስጨንቀው ፤ በክላሽ ጥይት ሲጠቀጥቀው ፤ የያዘውብ ቦንብ አላምጢ ዋጠው ። ሰንጥቀ ጣለው ያንን ሚኒሻ ያን የሀገር ሸክም ፤ በል ፋኖ ታጠቅ ጠላትክን ልቀም ፤ ብልፅግና እንደው ልኩ አያቅም ፤ አማራ ገዝቶ እንጂ ተገዝቶ አያውቅም ። የሚኒልክ ልጅ የዘመናዊው፤ ፋሲል እያሱ አፄ ባካፋ ፤ የምትኮራበት ታሪክ መች ጠፋ ፤ የትዬ እለሌ የነጣይቱ ነው ታሪካችን፤ የማይደበዝዝ ነው አሻራችን ፤ የቆራው ትንታግ መይሳው ካሳ፤ ጀግናው ሚኒልክ ጀግናው አምበሳ፤ ያስደነግጣል ስሙ ሲነሳ ። ሀገር ነፃ አውጪ ነብሱን ገብሮ ፤ ይሰነጥቃል ደርሶ ከላይ ፤ የጀግና ልጅ ነኝ የነበላይ ፤ ደል ሳላደርግ የማልመለስ ፤ የጀግና ልጅ ነኝ የአፄ ቴዎድሮስ ፤ በጀግንነቱ የማልታማ ፤ የነብሩ ልጅ ነኝ የአሳምነው ልጅ ፤ የአምበሳው ጋማ ፤ አዎ ፋኖ ነኝ የወንዶች ልክ ፤ የዛ ጀግና ልጅ የሚኒልክ ፤ ጠላቴን ማላቅ ከመሠረቱ ፤ የእምዬ ልጅ ነኝ የነጣይቱ ፤ በጀግንነቱ አይበገሬ ፤ ጥንትም ከዘሬ ፤ ጠላት ሳለመክት ትጥቅ የማልፈታ ፤ ከአላማዬ የማለመነታ ፤ ሀገር የማቆም በደም ጠብታ፤ እኔ ፋኖ ነኝ የሀገር አለኝታ። የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ወታደራዊ ኪነት ቡድን ፋኖ አርበኛ ነዋይ ገብሬ ……. ……. #ስርነቀልለውጥ #ሥርዓትነቀልለውጥ #AmharaGenocide #AmharaResistance

በሸዋ ጠቅላይ ግዛት የ«ኮሉ ብርጌድ» ደጀን አርበኞች ጦር እየተደራጀ ይገኛል!! ነሐሴ 04/2018 ዓ.ም በትጥቅ ትግሉ ስትራቴጂካዊ ምህዳር ውስጥ ጉልህ ስፍራ የሚይዘው የሸዋ ምድር፣ የትግሉን ወታደራዊና ፖለቲካዊ ሚዛን መልክ የሚቀይር አዲስ የሃይል አደረጃጀት እየተደራጀ ይገኛል። በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሀቤቴ አውራጃ በሚዳና ሬማ ክላስተር፣ በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ በአፄ ዓምደ ጽዮን ኮር አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር በሚቀሳቀስበት ቀጠና «ኮሉ ብርጌድ» የተሰኘ ግዙፍ የአርበኞች ጦር ሰራዊት በይፋ መመስረቱ ታውቋል። ከውስጣዊ ፈተና ወደ ወታደራዊ የበላይነት የተሸጋገረው ማሕበረሰብ በፖለቲካ ውስብስብ ጉዳዮች እየተፈተነ የህልውና አደጋ ይታይበት የነበረና ለጠላት ሃይሎች መፈንጫ ሆኖ የቆየ ስትራቴጂካዊ ቀጠና እንደሆነ ይታወቃል። ሆኖም የትግሉን ሚዛን ማስጠበቅ አስፈላጊ መሆኑን የተረዱት የቀጠናው ቁርጠኛ ታጋዮች፣ በጥቂት ቀናት ውስጥ የተካሄደውን የተናበበ የመልሶ ማደራጀት ስራ ተከትሎ ከመደበኛው የፋኖ ሰራዊት ውጭ ሁለት ግዙፍ የአርበኞች ጦር ብርጌድ «ካራምሽግ» እና «ኮሉ» ብርጌዶችን ማደራጀት ተችሏል። ከፍተኛ የአሳምነው ዕዝ እና የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር አመራሮች፣ የየቀበሌ አስተዳደሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በተካሄደው የዚሁ ምስረታ ስነ-ስርዓት ላይ፣ ለሰራዊቱ ሰፊ የፖለቲካና የወታደራዊ ስትራቴጂ/ግንባታ ትምህርቶች ተሰጥተዋል። የብርጌዱን አወቃቀር በተጠናከረ መልኩ ከመደራጀቱም በላይ፣ አመራሮችና አባላት ህዝባቸውንና ቀጠናቸውን በፍፁም ታማኝነት፣ በፍትሃዊነትና በጽናት ለማገልገል በህዝብ ፊት ቃለ-መሃላ ፈጽመዋል። አደረጃጀቱም የወታደራዊ ደጀንነቱን በቁርጠኝነት በማገዝ በአገዛዙ ሃይሎች ላይ ለሚሰነዘረው የማጥቃት ስምሪት ይበልጥ የተቀናጀ እንደሚያደርገው በመድረኩ የተገኙት የዕዝ አመራሮቹ ገልፀዋል ሲል ኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል አስታውቋል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ