en
Feedback
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ

አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ

Open in Telegram
5 081
Subscribers
+1124 hours
-157 days
-7730 days
Posts Archive
የአርበኞች ጦር በተሬ ክላስተር ወደ ዘመናዊ የክፍለ ጦር አደረጃጀት እየተሸጋገረ ነው ​ ጳጉሜ 01/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ የይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ተሬ ክላስተር የአርበኞች ጦር ሠራዊቱን ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር በጠንካራና ዘመናዊ አደረጃጀት እየሠራ እንደሚገኝ የዕዙ የስምሪት አመራሮች ገለጹ። የአማራ ሕዝብ ሕልውናውን ለማስከበርና የትውልዱን ነፃነት ለማረጋገጥ አደረጃጀቱን ማዘመን፣ ጠንካራ ተቋም መፍጠርና ቆራጥ አመራር መሰየም ወሳኝ መሆኑን በመገንዘብ የአባት አርበኞች ጦር አደረጃጀቱን በማጠናከር ላይ ይገኛል። ቀደም ሲል በብርጌድ ደረጃ ተደራጅቶ ሲንቀሳቀስ የቆየው የተሬ ሕዝብ ድሉን ለማፋጠንና ቀጠናውን ለማስተሳሰር ብርጌዶችን ወደ አርበኞች ክፍለ ጦር በማዋሃድ ለመዋቀር ተዘጋጅቷል። በቀጠናው ታላላቅ ወታደራዊ ጀብዶችን ሲያስመዘግቡ የቆዩት ብርጌዶች ጥልቅ ወታደራዊና ፖለቲካዊ ግምገማ በማድረግ ውስጣዊ አንድነታቸውን በመፈተሽና ክፍተቶችን በመሙላት አወቃቀራቸውን በማዘመን ላይ ናቸው። በዚህ የግንባታ መርሃ ግብር ላይ ከፍተኛ የድርጅት አመራሮች፣የቀጣናው ስምሪት አካል የዕዝ ከፍተኛ አመራሮች እና የኮር አመራሮች የተገኙ ሲሆን፤ የአፋብን ተቀዳሚ ም/ል ሊቀመንበር አርበኛ መከታው ማሞ ድርጅቱ ወጥ አሰራሮችን በመተግበር ለማይቀረው የነፃነት ጉዞ መዋቅሮቹን እያጠናከረ መሆኑን ገልጸዋል።በዚህም ሁሉም በየደረጃው ለትግሉ የሚጠበቅበትን አበርክቶ በማድረግ ሁልጊዜም ንቁና ቆራጥ ተሳትፎ ማድረግ እንዳለበት አሳስበዋል። በዚህም መሐመድ ስንዴው ብርጌድ እና ታደለ ወርቁ ብርጌድ አመራሮቻቸውን በማዋሃድ አንድ ታላቅ ክፍለ ጦር እንዲመሰርቱ አቅጣጫ ተቀምጧል። ለአዲሱ አርበኞች ክፍለ ጦር በውጊያ ሜዳ ብቃታቸው የተመሰከረላቸው ቆራጥ መሪዎች የተሰየሙ ሲሆን፣ በተደራጀ ሁኔታ ወደ ሥራ በመግባት የሕዝቡን ሰቆቃ ለመታደግ መዘጋጀታቸው ተገልጿል። ​"ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!" "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!" የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦርና የካራ ምሽግ አርበኞች ጦር በመርሀቤቴ አውራጃ በቅንጅት በነበረ ውጊያ ድል መቀዳጀታቸው ተገለፀ!! ጳጉሜ 01/2018 ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሀቤቴ አውራጃ በተደረገ የጨበጣ ውጊያ በ101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር ላይ ከፍተኛ ድል መቀዳጀቱን የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ፣ አፄ ዓምደ ጽዮን ኮር አፄ ዳዊት ክፍለጦርና ካራ ምሽግ አርበኞች ጦር ድል መቀዳጀታቸውን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል አስታወቀ። ቅዳሜ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም ከንጋቱ 11፡30 ጀምሮ የ101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር ከሚዳ ሬማ ወረዳ በመነሳት በሶስት አቅጣጫዎች ማለትም በሰንቀሌ ቆፌ፣ በቃራመጅት ሸንኮራ እና በሬማ ከተማ ቢራባ መስመሮች ወደ ፋኖ ቀጠና በማንቀሳቀስ ከበባ ለመፈፀም ሙከራ አድርጎ በነበረ ጠላት ላይ መሆኑን ገልጿል። ነገር ግን በአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር አሃዶች እና በካራ ምሽግ አርበኞች ጦር በተደረገ የተቀናጀ የጨበጣ አፀፋዊ ውጊያ ''ወደይላ'' በተባለው ልዩ ቦታ የመልሶ ማጥቃት እርምጃ በመውሰድ ታላቅ ድል መቀዳጀት እደቻሉ አብራርቷል። እስከ ቀኑ 8:00 ድረስ በቆየው በዚህ አውደ ውጊያ፡ አንድ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዥን ጨምሮ ከስምንት(8) የአገዛዙ ሰራዊት አባላት ጋር የተደመሰሱ ሲሆን፣ በርካቶች ደግሞ መቁሰላቸውን አክሏል። የቆሰሉት የጠላት አባላት በሬማ ከተማ ጤና ጣቢያ፣ በሬማ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ካምፕ እና በአለም ከተማ አናት ሆስፒታል ህክምና እየተከታተሉ እንደሚገኙ አረጋግጦ ተጠቅሶ፡ የሟችና የቁስለኛ ትክክለኛ ማንነት በመረጃ አጣርተን የምንመለስ ይሆናል ሲል ገልጿል። በዚሕ የአፀፋ ውጊያ ሽንፈት የተበሳጨው ጠላት የቃራ መጅት ነዋሪ የሆኑትን አርሶ አደር አቶ አቡሽ ሰጠኸኝን በጥይት ደብድቦ መግደሉ ሲረጋገጥ፤ ከ13 በላይ የሚሆኑ ወጣቶችን በአስገዳጅ ሁኔታ አፍኖ በመውሰድ "የተማረኩ ፋኖዎች ናቸው" በሚል ሀሰተኛ ፕሮፓጋንዳ ለመስራት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተረጋግጧል ብሏል። በተጨማሪም የአርሶ አደሮችን የሶላር ንብረቶች ጨምሮ ሌሎች ቁሳቁሶች በመዝረፍ ሙትና ቁስለኞቹን በሸራ ሸፍነው ወደ ሬማ ከተማ ከነ ሽንፈቱ መመለሱን ጠቅሷል። 👉 በመጨረሻም፣ በአካባቢው የሚገኙ ወጣቶች ከግዳጅ ወታደራዊ አፈሳ እራሳቸውን እንዲጠብቁ እያሳሰበ፣ አቅምና ፍላጎት ያላቸው ወጣቶች ትግሉን በመቀላቀል ራሳቸውንና ህዝባቸውን እንዲታደጉ ጥሪ አስተላልፏል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሥር የሚገኙ ሁለት ክፍለ ጦሮች በተለያዩ ግንባሮች በተደረጉ ውጊያዎች፤ በአገዛዙ ሰራዊት ላይ ከፍተኛ ድል መቀዳጀታቸው ተገለፀ!!            ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ)ዕዝ፡ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር፡ አስቴጎማ ተራራ ክፍለ ጦርና እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር በተለያዩ ግንባሮች በጠላት ላይ ድል መቀዳጀታቸውን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኃላፊ አስታወቀ። የአገዛዙ ኃይል፤ ከመኮይ ከተማና ከኬሚሴ ከተማ ተጨማሪ ኃይል ወደ ሴራር ጉር ቀበሌ አዳሩን በማንቀሳቀስ፡ አስቴ ጎማ ተራራ ክፍለ ጦር 4ኛ ሻለቃን ለማፈንና ለመደምሰስ ሲደናበር አይበገሬዎቹ በመልሶ ማጥቃት እርምጃ የጠላትን እቅድ ሙሉ ለሙሉ ማክሸፋቸውን ገልጿል።  በሌሊት የተደናበረው ጠላት ተሸንፎ በመሸሽ ላይ እያለ፡ የክፍለ ጦሩ ሌሎች ሻለቆች ማለትም ሸጌ ሻለቃና አያሌው መክት ሻለቃ የጠላትን ኃይል እስከ መኮይ ከተማ ድረስ በመከተል ተጨማሪ ኪሳራ ሲደርሱበት ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሙትና ቁስለኛ እዳስተናገደ ተረጋግጧል። ወደ ካምፓቸው ድረስ ለመደምሰስ የተጓዘው የአገዛዙ ጠባቂ፡ በፋኖ ፈጣን የመልስ ምት ክፉኛ ተመቶ ወደ መጣበት ሲፈረጥጥ፡ እራሱን ለማትረፍ ከባድ መሳሪያን ወደተራራ ሲተኩስ በንፁሐን ሃብት ንብረት ላይ ውድመት ፈፅሟል ብሏል። 〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰 በሌላ በኩል የመሀመድ ቢሆነኝ ኮር እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር በአንኮበር ቀጠና አመርቂ ድል መቀዳጀቱን አክሎ ገልጿል። መነሻውን ከአንኮበር አድርጎ ወደ ጎረቤላ ቀበሌ ቤት ለቤት በመግባት ወጣቶችን ለማፈስ ሲንቀሳቀስ በነበረው የአድማ ብተና ኃይል ላይ የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር 2ኛ ሻለቃ ፈጣን እርምጃ ወስዷል።  በልዩ ቦታው "ጠምቄ" በተባለ ቦታ በቀን 28/12/2018 ዓ.ም ከቀኑ 11:00 ሰዓት ላይ መረጃው የደረሰው የወገን ጦር ፈጣን የደፈጣ ውጊያ በመክፈት ወታደራዊ የበላይነትን በማሳየት፡ ጠላት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሲያደርሱበት፥ በዚህ አውደ ውጊያ 5 የጠላት አባላት ሲደመሰሱ፣ ቁጥራቸው ያልታወቀ በርካቶች መቁሰላቸውን መረጃዎቼ አረጋግጠዋል ሲል ኮሩ አስታውቋል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ከድል መልስ ሽለላ እና ቀረርቶ ጀብደኛው 7/70 ክፍለ ጦር‼️ ሲገሉ ነበር ሲያፈናቅሉን ለ500 ዓመት፤ ህያው ምስክር ነው አሁን ላለንበት ፤ አባቶቻች የታገሉበት ፤ ሳህለሥላሴ ኃይለ መለኮት ፤ አጋድመው ወቁት ነዱት እንደከብት ፤ በአፈ ድምድሙ በአብራሪው ጥይት ፤ ይመስከር ጓንዴ የጥንቱ ብረት ፤ አውቶ መሣሪያ ባልነበረበት ፤ ከዚህ አርሲ ነገሌ ነፃ ያወጡበት ፤ ርዕስታችን ነው ሞጆ እና ናዝሬት ፤ የማኛው ጤፉን ያበቀልንበት ፤ ኃይለማሪያም ማሞ ስም የፃፉበት ፤ ይህ ነው ታሪክህ በል ዕወቅበት፤ እኳ ነው ሚባለው አንት ። አስተውል እንጂ ታሪክ አትርሳ ፤ የሞተላትን መይሳው ካሳ ፤ አስተውል እንጂ ታሪክን ከላይ ፤ የሞታለትን አምበሳው በላይ ፤ አስተውል እነጂ ታሪክን በልክ ፤ የሞተላትን አፄ ሚኒልክ፤ ታሪክን ሳታውቅ ሀገር አትውቀስ ፤ የሞቱላትን አቡነ ጼጥሮስ ፤ የኖህ መርከብ ነች የማቱ ሳላ ፤ ጥበብን ለብሳ ከላሊበላ ፤ ጠላቷ ሙሉ አይኑ ሲቀላ ፤ በፋኖ አንድነት ታሪክሽ ጎላ ። እንዲህም እንዲያ እቃኘዋለው ፤ የናንተ ወንድም ምን እሆነለው ፤ ዳዊት በሽንጡ ሀሌ እያዘለ፤ ቁራን በሽንጡ ሁሌ እያዘለ፤ ቅኔ እንደ ስጋ የዘለዘለ ፤ ለአእውንት የሚሞት ሀቅ የተኮለ፤ እየቀነሱት ሰማይ እያከለ ፤ ዝመተኛ ነው ቀድሞ የነቃ ፤ ታሪኩ ደማቅ እንደ ጨረቃ ። እንደ ጎልያድ እንደ ፈርኦን ልቡ ደንድኖ፤ አጋድሞት ሄደ ዳዊት ሆኖ ፤ ጥቃት አይወድም ቆፋጣናው ፋኖ ፤ ወጣና ታገል ቆመ አታልቅስ ፤ መጥቶ እስኪገልህ ደም እስኪፈስ ፤ የሞተው ሞቶ አፈር ቢጫነው ፤ ፋኖ ለሀገሩ ባለውለታ ባለታሪክ ነው ። ጊዜ እንዳትሰጠው ሙት ይደረጃል ፤ ቆፍጣናው ፋኖ ክንዱ ይፋጃል ፤ በል ተነስ ግፋ በል እነሂድ ፤ አልወድም እኔ ሆሊት መንገድ ፤ ጠላትም ይውደም እሳት ይንደድ ፤ በእናት እህቴ እንዳትቀልድ ፤ ደምሽ ደሜ ነው አንሻ ሰይድ ። የአፄ ቴዌድሮስ የነካሳ ልጅ ፤ የነሺፈራው የነበላይ ልጅ ፤ የልጅ አያሱ የአሳምነው ልጅ ፤ የአፄ ሚኒልክ የነአስማረ ልጅ ፤ ወላሂ ብሎ ሃዛን ሲያወድስ ፤ ማሪያምን ብሎ ቄሱ ሲቀድስ ፤ ተስቦ ገዳይ እንደ እባብ ንጉስ ፤ ባንዳውን ጥሎ ታሪክ የሚያድስ ፤ የነፃነቱን ችቦ ሲለኩስ፤ በፀሃይ ቀልጦ ደሙንም ቢያፈስ፤ አማራ እኳ ነኝ የፊደል ንጉስ። እነድ መይሳው ሞትን አይፈሬ ፤ አንደ ሚኒልክ በማሪያም ምዬ ፤ እንደ አባ ኮስትር ገመድ አስሬ ፤ ታማኝ ነኝ በመሆን እነደገብርዬ ፤ ፅፌ ልፎክር ጠላቴን ጥዬ ፤ ክብሬ ሲነካ አልወድም እና ፤ የአማራ ልጅ ነኝ የቆርጦ በላ ። ታላቅ ክብሬ ነው አባ ኮስትር ለኔ ፤ ታላቅ ክብሬ ነው ሚኒሊክ ለኔ ፤ ታላቅ ክብሬ ነው ቴዌድሮስ ለኔ ፤ የአማራ ልጅ ነኝ የጀግኖች ፍሬ ፤ የማልደራደር በሀገር ድምበሬ ፤ ማነህ አትበለኝ አልወድም እኔ ፤ ማነህ አትበለኝ ያመኛል እኔ ፤ አማራ በለኝ። በክብር ስሜ። ህልመኛው ወሎ ህልመኛው ሸዋ፤ ህልመኛው ጎንደር ህልመኛው ጎጃም ፤ ነቅሎ ይጥላል ካልሆነ መልካም ፤ ቆፍጠን ያለ ነው ክንድ አይነካም ፤ ለአብይ ወታደር ለዛ ዱካካም ፤ ማዕተነቡን ሽጦት ቀረ እንደዋዛ ፤ ዕምነቱን ሽጦት ቀረ እንደዋዛ ፤ ካለበላ አይስቅም ፊቱ ካልወዛ ፤ በ5ሺ ብር እየተገዛ ፤ ሚሊሻ ቀልጧል ልክ እንደ ጤዛ ከሹርባሽ ዝናሽ ሚኒልክ ፤ ጥልቀቱ ረጅም የታሪክሽ ልክ ፤ ትወልደ ትወልድ ሁሌ ሚሰበክ ፤ ለሀገር መሞት የለው ኩነኔ ፤ ለወገን መሞት የለው ኩነኔ ፤ ከዳር እስከ ዳር ፣ ከጫፍ እስከ ጫፍ ፤ተነስ ወገኔ ፤ አማራ እኳ ነች የአይን ብሌኔ ፤ እሷ ከሌለች የለሁም እኔ። አንተ ማነህ ? አማራ ፤ አንተ ማነህ ? አማራ ፤ በደም እና በአጥነት ሀገር የምትሰራ ፤ ሀገር አቃፊ ታሪከ ሰፊ ፤ ሀገር መስራች ስለሀገር ሞች ፤ እንደ ጅቦች የማትከዳ ፤ እነደከብቶች የማትነዳ ፤ አንተ አማራ ነህ የሀገር በላዕዳ ፤ ለምድረ ጣልያን የማትደነግጥ ፤ ከአፄ ፋሲል እስከ ቴዌድሮስ ፤ የላሊበላ የቅዱስ ንጉስ ፤ የሼህ ሁሴን ልጅ የአቡነ ጼጥሮስ ፤ የንጉስ ሚካኤል የአፄ ሚኒልክ ፤ በክላሽ ገጥሞ ታንክ የሚማርክ ፤ ተነግሮ አያልቅም የፋኖ ታሪክ። አስማረ ዳኜ አበበ አረጋይ ፤ እሱ ነበረ ትልቁ ታጋይ ፤ አሸናፊ አለሙ ፣ ሞላ ደስዬ ፤ ሺ ውን ይጠላል አንዱ ሰውዬ ፤ አምባቸው መኮንን ስመኝው በቀለ፤ እውቀተ በርሃን ፅፎ የታገለ ፤ አሳምነው ፅጌ አስቻለው ደሴ ፤ ጋሻ ክንዴ ነው ክብሬ ነው ዋሴ ፤ አፄ ሚኒልክ ንጉስ ሚካኤል ፤ በላይ ዘለቀ አፄ ቴዌድሮስ ፤ ወደፊት ነበር የሚገሰግስ ፤ እነሱ ናቸው ለኛ ምስክር ፤ አልም ፅፎታል ይውጣ ይነገር ፤ እንዲህ ነው እንጂ ታሪክ ሲዘከር ፤ ልጅ ለአባቱ ነው ሁሌ የሚፎክር ። ትውልድን ሁሉ የቀረፀ ፤ ሀገር አቁሞ ዕምነት ያነፀ፤ ለአፋሪካዊያን ብሎም ኢትየጵያ ተስፋ የጣለ፤ የጥቁሮች አባት ዘር ያለከለለ፤ በዕውቀት ጥበቡ እያባበለ፤ ዓለምን ሁሉ ጉድ አያስባለ ፤ ጣልያን በዐድዋ ያንበረከከ ፤ በጋሻ ጦሩ እየታከከ፤ አፄ ሚኒልክ ነጭ ማረከ ፤ እኳ ነው ሚባው አንተ ። ተነስ ግጠመው ቁመህ አትየው፤ ጥጋበኛ ነው ፊት ከሰጠህው፤ የአፄ ቴዋድሮስ የአፄ ሚነልክ ፤ የአነ አስማረ ልጅ የአፄ የኩኑ ፤ አጣፍቶ ሰርቶት ጠላት ከሽኖ ፤ እጁን አይሰጥም የአማራ ፈኖ። መያዝ ነው እንጂ አንገቱን ብሎ፤ ካሊያዙትእማ የበቅላል ዘሎ ፤ ሞትን አይፈራም አይቀርም ብሎ፤ ነፃ ይወጣል አማራ ታግሎ፤ ይገሰግሳል ወደፊት ታግሎ፤ የአባት ቤት ነው በል ግባ ቶሎ፤ ስም ይፃፋል ነገ አራት ኪሎ። እንደመቀመጥ እንደመናሳት ፤ ደግሞ ምን ይሆን ተኩሶ መሳት ፤ አልመ በለው በክላሽ ጥይት ፤ ይገሰግሳል ገና ወደፊት ፤ የአባቶቹ ነው ጥንትም ጀግንነት ፤ አራት ኪሎ ነው የፋኖዎች ቤት ። የነፍጠኛ ልጅ በነፍጥ ያደገው ፤ ጠላትን ጥሎ ስሙን ለወጠው ፤ ፋኖ አይደለም ወይ የሚያስጨንቀው ፤ በክላሽ ጥይት ሲጠቀጥቀው ፤ የያዘውብ ቦንብ አላምጢ ዋጠው ። ሰንጥቀ ጣለው ያንን ሚኒሻ ያን የሀገር ሸክም ፤ በል ፋኖ ታጠቅ ጠላትክን ልቀም ፤ ብልፅግና እንደው ልኩ አያቅም ፤ አማራ ገዝቶ እንጂ ተገዝቶ አያውቅም ። የሚኒልክ ልጅ የዘመናዊው፤ ፋሲል እያሱ አፄ ባካፋ ፤ የምትኮራበት ታሪክ መች ጠፋ ፤ የትዬ እለሌ የነጣይቱ ነው ታሪካችን፤ የማይደበዝዝ ነው አሻራችን ፤ የቆራው ትንታግ መይሳው ካሳ፤ ጀግናው ሚኒልክ ጀግናው አምበሳ፤ ያስደነግጣል ስሙ ሲነሳ ። ሀገር ነፃ አውጪ ነብሱን ገብሮ ፤ ይሰነጥቃል ደርሶ ከላይ ፤ የጀግና ልጅ ነኝ የነበላይ ፤ ደል ሳላደርግ የማልመለስ ፤ የጀግና ልጅ ነኝ የአፄ ቴዎድሮስ ፤ በጀግንነቱ የማልታማ ፤ የነብሩ ልጅ ነኝ የአሳምነው ልጅ ፤ የአምበሳው ጋማ ፤ አዎ ፋኖ ነኝ የወንዶች ልክ ፤ የዛ ጀግና ልጅ የሚኒልክ ፤ ጠላቴን ማላቅ ከመሠረቱ ፤ የእምዬ ልጅ ነኝ የነጣይቱ ፤ በጀግንነቱ አይበገሬ ፤ ጥንትም ከዘሬ ፤ ጠላት ሳለመክት ትጥቅ የማልፈታ ፤ ከአላማዬ የማለመነታ ፤ ሀገር የማቆም በደም ጠብታ፤ እኔ ፋኖ ነኝ የሀገር አለኝታ። የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ወታደራዊ ኪነት ቡድን ፋኖ አርበኛ ነዋይ ገብሬ ……. ……. #ስርነቀልለውጥ #ሥርዓትነቀልለውጥ #AmharaGenocide #AmharaResistance

"በአዲስ አበባ ከተማ እና ነዋሪወቿ ላይ የተደቀነው የህልውና አደጋ በድርጅታችን ቁርጠኝነት፣ በህዝባችን ፅናትና በፀረ ብልፅግና ብሔራዊ ኃይሎች ትብብር በሚታጀበው የትግላችን አይቀሬ ድል የሚመመከት
+1
"በአዲስ አበባ ከተማ እና ነዋሪወቿ ላይ የተደቀነው የህልውና አደጋ በድርጅታችን ቁርጠኝነት፣ በህዝባችን ፅናትና በፀረ ብልፅግና ብሔራዊ ኃይሎች ትብብር በሚታጀበው የትግላችን አይቀሬ ድል የሚመመከት ይሆናል" ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን)፤ በአዲስ አበባ ጉዳይ የተሰጠ የአቋም መግለጫ ! ነሐሴ 09/2018 ዓ.ም ዘረ ፈጁ የብልፅግና አገዛዝ ''አገራዊ ምክክር'' በሚል ስም በኢትዮጵያ፤ በአዲስ አበባ ከተማ የሚያካሂደው የድራማ መድረክ የህዝብ ውክልና የሌለበት፣ ተጨማሪ ቀውስ የሚያዋልድ እና የአገዛዙን ዕድሜ ለማራዘም የተነደፈ የአረመኔው አገዛዝ የፖለቲካ አሻጥር መሆኑን ከዚህ በፊት ባወጣነው መግለጫ አቋም መውሰዳችን ይታወቃል። ሆኖም ግን አገዛዙና አጋሮቹ ይህንን ከጥፋት መንገዳቸው እንዲመለሱ ያቀረብንላቸውን ጥሪ በመተው ''በምክክር'' ስም የከተሞችንና አካባቢዎቻቸውን የታሪክ፣ የዴሞግራፊ፣ መልክአምድራዊና የይዞታ ቅርፃቸውን ለማዛባትና በተለይም ነባር የአዲስ አበባ ከተማ ኗዋሪዎችንና የአማራን ህዝብ ህልውና አደጋ ላይ ለመጣል የጥፋት መንገድ ላይ መሆናቸውን ተገንዝበናል። አዲስ አበባ ከተማ እንደገና ከመቆርቆሯና ከአሁኑ መጠሪያዋ ቀደም ብሎ ''በራራ'' በመባል የምትታወቅ፣ በመካከለኛው ክፍለ ዘመን በጦርነት ሳቢያ እስከወደመችበት ጊዜ ድረስ የአማራ ነገስታት መቀመጫና የአማራ ህዝብ ጥንተ-ርስት እንደሆነች የታሪክ መዛግብትና አርኪዮሎጂያዊ ማስረጃዎች በግልፅ ያረጋግጣሉ። ዳግማዊ አፄ ምኒልክ እና እቴጌ ጣይቱ ብጡል አዲስ አበባ ከተማን በድጋሚ ሲቆረቁሯት፣ ባዶ መሬት ላይ ሳይሆን የአባቶቻቸውን ታሪካዊ ይዞታ፣ ርስትና ውርስ መነሻ በማድረግ ነው። ይህ ታሪካዊ እውነት ሊሸረሸርም ሆነ ማንም አምባገነናዊ አገዛዝ በጊዜያዊ ስልጣን ህዝብ ባላመነበት ፖለቲካዊ ውሳኔ ሊሰርዘው የማይችለው ፅኑ የታሪካችን አንድ አካል ነው። ከተማዋ የአማራ ጥንተ-ርስት መሆኗ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ በሂደት የሁሉም የኢትዮጵያ ህዝብ መኖሪያ፣ የባህልና የኢኮኖሚ ማዕከል፣ እንዲሁም የአንድነት ተምሳሌት ሆና ተገንብታለች። ከዚህ አኳያ ድርጅታችን የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) አዲስ አበባ የኗዋሪዎቿ፣ የሁሉም ኢትዮጵያዊያን መኖሪያ፣ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ፣ የአፍሪካ መናገሻና የዓለም አገራት የዲፕሎማሲ ማዕክል መሆኗን ሙሉ በሙሉ ያምናል፤ ይቀበላልም። በዚህ መነሻ፣ ከተማዋ የብዝኃነትና የጋራ እድገት ማዕከል እንጂ የአንድ ዘረ ፈጅ አገዛዝ ብቸኛ መጫወቻ ስፍራ ልትሆን እንደማትችልም ድርጅታችን ያረጋግጣል። የአማራ ህዝብ፣ አዲስ አበባን ጨምሮ በመላ አገሪቱ በስፋት በሚኖርባቸው አካባቢዎች፤ ፍትሐዊ የስልጣንና የሀብት ተጠቃሚነቱ መረጋገጥ እንዳለበት ድርጅታችን ያምናል። በአሁኑ ወቅት፣ የኦህዴድ ብልፅግና አገዛዝ አዲስ አበባን በብቸኝነት የአንድ ወገንና ብሔር በበላይነት እንዲቆጣጠራት ለማስቻል የሚሰራው ሕግን የጣሰ፣ የዴሞግራፊና የጂኦግራፊ ለውጥ በምንም መልኩ ሕጋዊ፣ ሞራላዊ፣ ፖለቲካዊና ታሪካዊ ተቀባይነት የሌለው መሆኑን እንገልፃለን። አገዛዙ ''አገራዊ ምክክር'' በሚል የፖለቲካ ሽፋን በከተማዋ ላይ የሚያካሄደው ሴራና አሻጥር የከተማዋን ነባር ኗዋሪዎች መብት የሚጥስ፣ የሁሉም ኢትዮጵያዊያን የጋራ መኖሪያነቷን የሚክድና ታሪካዊ እውነታውን ለማዛባት የተሸረበና የአንድ ቡድን የበላይነትን በህዝባችን ላይ በኃይል ለመጫን ያለመ በመሆኑ፣ የዚህን አምባገነን አገዛዝ ዕድሜ ለማሳጠር መላው የአዲስ አበባ ከተማ ኗዋሪዎችን ጨምሮ ኢትዮጵያውያን ድርጊቱን እንዲያወግዙት፣ እንዲቃወሙትና እንዲታገሉት በድርጅታችን አፋብን ስም ጥሪ እናቀርባለን። እንዲሁም በከተማዋ ቀደም ብለው ይኖሩ የነበሩትም ይሁን አሁንም የሚኖሩት 80 በመቶ ( በ1999 ዓ.ም በተካሄደው ህዝብና ቤት ቆጠራ መሰረት) የሚሆኑት ነባር ኗዋሪዎች አማራዎች ናቸው። በመሆኑም የህዝብ ስብጥርንም ሆነ ታሪካዊ እውነታን በኃይልና በተሳሳተ ፖለቲካዊ ውሳኔ ለመቀየር የሚደረገውን ማንኛውም የአገዛዙን ሴራ አጥብቀን የምንታገለው መሆኑን እንገልፃለን። የአማራ ህዝብ በገዛ አገሩ ከገጠመው ሁለንተናዊ የህልውና አደጋ ባሻገር ድርጅታችን የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) የትጥቅ ትግል ውስጥ ለመግባት ካስገደዱት ምክንያቶች መካከል፦ በአዲስ አበባ ከተማ በአገዛዙ የተደቀነው የዴሞግራፊ ለውጥ አደጋ፣ የከተማዋን ቀደምት ባለቤቶችና ነባር ኗዋሪዎች በማፈናቀልና ማንነታቸውን በማጥፋት፣ የአማራ ህዝብ ከከተማዋ ጋር ያለውን ታሪካዊ እና ማህበራዊ ትስስር በመበጣጠስ ከህዝቦች ተፈጥሯዊ መስተጋብር ውጭ በሆነ መልኩ የባህል፣ የቋንቋና የተለያዩ አመለካከቶችን በኃይል ለመጫን የሚደረገው ሩጫ ይገኝበታል። በመሆኑም፣ ድርጅታችን አፋብን ከምንጊዜውም በላቀ ሁኔታ ውስጣዊ አንድነቱንና አደረጃጀቱን ጠብቆ በመጓዝ፣ አምባገነኑና ከፋፋዩን አገዛዝ በጀመርነው ትግል ከስሩ ነቅለን በመጣል፣ ለአማራ ህዝብ ብሎም ለሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚስማማ፣ የዜጎችን ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች የሚያከብር ሥርዓተ መንግስት በመገንባት ፍትህ፣ እኩልነትና የሕግ የበላይነትን ከመትከል ባሻገር አዲስ አበባ የኗዋሪዎቿ፤ የሁሉም ኢትዮጵያዊያን የጋራ መኖሪያና ዋና ከተማ፤ የአንድነትና የእድገት ማዕከል ሆና እንድትቀጥል ይታገላል። አገሪቱ ከገባችበት ጥልቅ የህልውና፣ የፍትህና የእኩልነት ቀውስ መውጣት የምትችለው የህዝቧን ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች በኃይል በማፈን፣ አገሪቱን የማያቋርጥ እርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ በማስገባት ወደ ገደል እየመራት ያለውን ዘረ ፈጁን የብልፅግና አገዛዝ፤ በሕዝባዊ ትግል ሙሉ በሙሉ መገርሰስ ሲቻል ብቻ መሆኑን አፋብን በፅኑ ያምናል። በስተመጨረሻ የኦህዴድ ብልፅግና አገዛዝ በአዲስ አበባ ከተማና በህዝባችን ላይ በምክክር ስም የጠነሰሰው ዓይን ያወጣ የፖለቲካ አሻጥር የፈጠረው የህልውና በድርጅታችን ቁርጠኝነት፣ በህዝባችን ፅናትና በፀረ ብልፅግና ብሔራዊ ኃይሎች ትብብር በሚታጀበው የትግላችን አይቀሬ ድል የሚመመከት ይሆናል። የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን)

ዶክተር ታደሰ part 2

አርበኛ አበበ ሙላቱ በመድረክ ላይ

ነዋይ ገብሬ 222

አርበኛ ነዋይ ገብሬ part one

አርበኛ አማን እሸቱ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዋና ወታደራዊ አዛዥ

አርቲስት ጌትነት ተስፋዬ

አርበኛ መከታው ማሞ

አርበኛ ደሳለኝ