cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking ÂŤAccept allÂť, you agree to the use of cookies.

avatar

Addis Mohammed & Associates Law firm👩‍⚖

ማንኛውም የህግ መረጃዎች እና ጉዳዮች የሚዳሰሱበት፣ ሀገራችን ላይ የሚፈጠሩ አሳዛኝና አስደንጋጭ ወንጀሎችን እንዲሁም ቀላል የሚመስሉ ጉዳዮች ላይ የኢትዮጵያ ህጎች ምን ይላሉ የሚሉትን የምናይበት ቻናል ነው። ማንኛውንም የህግ ጥያቄዎች በዚህ ይመለሳሉ

Show more
Advertising posts
670
Subscribers
+2424 hours
+437 days
+6530 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

በህይወታችን ውስጥ ባለማወቅ ብዙ የህግ ጥሰቶች ሊደርሱብን ይችላሉ፣ ብዙ የሴራ ወንጀሎች በኛ ስም እኛ ሳናውቅ ሊፍፅም ይችላል፤ ድንገት እንዴት ነው ከዚህ ውጥንቅጥ ራሳችን ማውጣት እምንችለው ? አስቡት እንግዲህ በሰላም ከቤታችሁ ስራ ጋር ብላችሁ ወታችሁ ቀናችሁን ሲበላሽ ምንም በማታውቁት አንድ ቀን በተሳሳተ አድሬስ በተሳሳተ የወንጀል ዶክመንት እናንተ ወንጀለኛ ሆናችሁ ፍርድ ቤት በድንገት ስትቀርቡ ፍርድ ቤቱም ግሯ ነ ቀኝ አይቶ በወንጀለኛ ህግ መቀጫ አንቀፅ አጣቅሶ ረጅም ዓመት ዕስር ሲያከናንባችሁ ከዚያ ተሰፈ በቆረጠ ስሜት ዘብ ጥያ ስትወርዱ ያለው ተስፈ አስቆራጭ ስሜትህ Ohhhh A heavy feeling of sadness 😔😔 ለዚህ ሁላ መፍቴሄ አለ በዛውም የህግ ዕውቀቶን ያሰፈሉ በሃገራችን ጥቂት ከሚባሉ በህጉ ዘርፍ አንቱታን ካተረፉት ሰዋች መሃል #ጠበቃ_አዲስ_መሃመድ ትገኛለች ይህቺ ድንቅ ዕንስት አሁን አዲስ መፍቴሄ ይዛ ወደ ሚድያው አለም ለማስተማር መታለች ከዚህ ብታች ባለው የዩቱብ ሊንክ 👇እየገባችሁ አዲሱ ቤትዋን ሰብስክራይብ እያደረጋችሁ የህግ ዕውቀቶን በዛውም ያስፉ ቤቱንም ሼር በማድረግ ተደራሽነት እንዲኖረው ያድርጉ እናመሰግናለን🙏 https://youtu.be/3hi0pQ_xnXI?si=ce-AgpMtqkHnB15w
Show all...
ህገ መንግስት ምንድን ነው እንዲሁም ዝርዝር ጉዳዮች || ህግን በአዲስ እይታ || አዲስ መሀመድ ከመሀመድ መብራቱ ጋር አሪፍ ቆይታ አድርገዋል

251920298841For more information Telegram:

https://t.me/addismohlawfirmWebsite

:

https://addisassolawfirm.comtik

tok:tiktok.com/@tbqaaddisyoutube:

https://youtu...

👍 5
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 32ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል **** ግንቦት 7 ቀን 2016 ዓ.ም አዲስ አበባ 32ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔዎች የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 32ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ 1. ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው በ4 የፋይናንስ ድጋፍ እና ብድር ስምምነቶች ላይ ነው፡፡ ለምስራቅ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ግሪድ ማጠናከሪያ ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ ከአፍሪካ የልማት ባንክ የተገኘ የ52 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር፣ ለስራ ፈጠራ እና የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሚውል ከጣልያን መንግስት የተገኘ 10 ሚሊዮን ዩሮ፣ ለቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ ከዓለም ዐቀፍ የልማት ማህበር የተገኘ 255 ሚሊዮን ዶላር አንዲሁም ለፓወር ሴክተር ሪፎርም፣ ኢንቨስትመንትና ሞደርናዜሽን ፕሮጀክት ምዕራፍ አንድ ማስፈፀሚያ የሚውል 393 ሚሊዮን ዶላር ከዓለም ዐቀፍ የልማት ማህበር የተደረጉ የብድር ናቸው፡፡ ከአፍሪካ የልማት ባንክ የተገኘው ብድር 0.01% ወለድ እና ብድሩን በማስተዳደር ረገድ ለሚወጡ ወጭዎች 0.1% የአገልግሎት ክፍያ የሚታሰብበት ሆኖ የ15 ዓመታት የችሮታ ጊዜን ጨምሮ በ40 ዓመት ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ነው፡፡ ከጣልያን መንግስት የተገኘው ብድር ከወለድ ነጻ ከመሆኑም በላይ የ16 ዓመት የችሮታ ጊዜ ያለውና በ30 ዓመት ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ነው፡፡ ከዓለም ዐቀፍ የልማት ማህበር የተገኙት ብድሮች ወለድ የማይታሰብባቸው፣ ብድሮቹን በማስተዳደር ረገድ ለሚወጡ ወጪዎች 0.75% የአገልግሎት ክፍያ ብቻ የሚታሰብባቸው፣ የ6 ዓመት የችሮታ ጊዜ ያላቸው እና በ38 ዓመት ተከፍለው የሚጠናቀቁ ናቸው፡፡ ምክር ቤቱ ሁሉም ብድሮች ከሀገራችን የብድር አስተዳደር ፖሊሲ ጋር የሚጣጣሙ መሆናቸውን በማረጋገጥ በሙሉ ድምጽ ተቀብሎ ረቂቅ አዋጆቹ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 2. ሌላው ምክር ቤቱ የተወያየው የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ባቀረባቸው 3 ረቂቅ አዋጆች እና 1 ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ የመጀመሪያው የኢሚግሬሽን አዋጅ ቁጥር 354/1995ን ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅ ሲሆን መሰረታዊ ከሆኑ መብቶች አንዱ የሆነውን የመዘዋወር ነፃነትን ለማስከበር፣ የኢሜግሬሽን አገልግሎቶችን ለኢትዮጵያዊንና ለውጭ አገር ዜጎች በተሻለ ጥራትና ቅልጥፍና መስጠት እንዲቻል፣ የተቀናጀ የድንበር ቁጥጥር እና አስተዳደር ስርዓት በመዘርጋት የተሟላ የመንገደኛ ቅድመ ጉዞ መረጃ መያዝ አስፈላጊ በመሆኑ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጁ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡ ሁለተኛው የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎትን በድጋሚ ለማቋቋም የወጣ ረቂቅ አዋጅ ሲሆን ተቋሙ በሚሰጠው አገልግሎት የዜጎችን ፍላጎት የሚያሟላ፣ የግልጽነትና የተጠያቂነት ስርዓት የሰፈነበት እንዲሆን፣ የአገራችንን ብሄራዊ ጥቅምና ደህንነት በሚገባ የሚያስጠብቅ ስልጣንና አደረጃጀት እንዲኖረው ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡ 3. ሶስተኛው የሲቪል እና ቤተሰብ ምዝገባ ረቂቅ አዋጅ ሲሆን የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ ስርዓትን በማሻሻል አገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ፣ ተደራሽ፣ ግልጽና ውጤታማ ማድረግ፣ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት መሰረታዊ የዜጎችን መብትና ነፃነት ለማክበርና ለማስከበር ሁሉን አቀፍ የምዝገባ ስርዓት መዘርጋት የሚገባ በመሆኑ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በቀረቡት 3 ረቂቅ አዋጆች ላይ በሰፊው ከተወያያ በኋላ ግብዓቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 4. አራተኛው ምክር ቤቱ የተወያየበት ጉዳይ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ለሚሰጣቸው አገልግሎቶች የሚያስከፍለውን ክፍያ ለመወሰን በቀረበ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ ተቋሙ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ማስፋት፣ የአገልግሎቶቹን የጥራት ደረጃ ማሻሻል፣ ብሎም የተጠቃሚውን ማህበረሰብ አቅም ባገናዘበ መልኩ አገልግሎት ለመስጠት ያወጡትን ወጪ መሸፈን የሚያስችል ስርዓት መዘርጋት በማስፈለጉ ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 5. በመጨረሻም ምክር ቤቱ የተወያያው በውጭ ጉዳይ ሚኒስተር በቀረቡ 2 የሁለትዮሽ ስምምነቶች ላይ ነው፡፡ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እና የሩሲያ መንግስታት መካከል ያለውን የአየር አገልግሎት ስምምነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የተፈረመ ስምምነት ነው፡፡ ሌላው ስምምነት በኢትዮጵያ እና በኢንዶኔዥያ መንግሥታት መካከል የዲፕሎማቲክ እና ሰርቪስ ፓስፖርት ለያዙ ሰዎች ቪዛን ለማስቀረት የተደረገ ስምምነት ነው፡፡ ምክር ቤቱም ስምምነቶቹ ቢጸድቁ ኢትዮጵያ ከሁለቱ ሀገራት ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ የሚያጠናክሩ እና በአገራቱ መካከል ያለውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ትስስር የሚያጎለብቱ መሆኑን በመገንዘብ፣ የስምምነቶቹ መጽደቅ የአገራችንን ጥቅም የማይጎና የተለየ ግዴታም የማያስከትል መሆኑን በማረጋገጥ ረቂቅ አዋጆቹን በሙሉ ድምጽ አጽድቆ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፉ ወስኗል፡፡ ምንጭ fb
Show all...
👍 2
#ህግን_በአዲስ_እይታ ህገ መንግስት ምንድን ነው? የህገ መንግስት አጣሪ ጉባኤ ስራው ምንድን ነው? ትርጉሞቹስ እንዴት ይተረጎማሉ የሚሉ ጥያቄዎችን የሚመልስ እና ሌሎችም ዝርዝር ጉዳዮችን የሚዳስሰው ክፍል ተለቋል የፕሮግራሙን link በመጫን መመልከት ይችላሉ subscribe, like እና share በማድረግ ቤተሰብ መሆን አይርሱ
Show all...
👍 9
Show all...
ህገ መንግስት ምንድን ነው እንዲሁም ዝርዝር ጉዳዮች || ህግን በአዲስ እይታ || አዲስ መሀመድ ከመሀመድ መብራቱ ጋር አሪፍ ቆይታ አድርገዋል

251920298841For more information Telegram:

https://t.me/addismohlawfirmWebsite

:

https://addisassolawfirm.comtik

tok:tiktok.com/@tbqaaddisyoutube:

https://youtu...

የጠበቆች ማህበር ... ስብሰባ ዛሬ ፕሬዝደንት ለመምረጥ ፣ መተዳደሪያ ደንብና መመሪያዎች ላይ ተወያይቶ ለማጽደቅ ስብሰባ ነበር ። የተሳካ አልነበረም ። ብዙ ሲጠበቅበት የነበረው ማህበር ገና ከጅምሩ ያለፕሬዝደንት ለረዥም ጊዜ መቆየቱ ከ efficiency አንጻር ብቻ ሳይሆን ለስምም ለባለሙያውና ለማህበሩ ክብርም የሚመጥን አልነበረም ፣ በበኩሌ ሁሌም ቅር ይለኝ ነበር ። በምርጫ ጊዜ የታዘብኩዋቸው ቅር ያሉኝ ጉዳዬች ዛሬም እየተልከሰከሱ ማህበሩን እየፈተኑት ይመስለኛል ። ማህበሩን ማን ፣ እነማን በብቃት ሊመሩት ይችላሉ የሚለው መመዘኛ ብቸኛ መመዘኛ ሆኖ የመምረጫ መርሀችን ካላደረግነው በስተቀር ፣ ሁሌም የሚፎከርብን ፣  በራሳችሁ ችላችሁ ማህበሩን መምራት አትችሉም የሚለውን እያረጋገጥንላቸው መሄዳችን አይቀርም ። from co regulation to self regulation የሚደረገው ጉዞ ጥላ እንዳያጠላበት ያሰጋል ። በአገራችን በመንግስትና በባለሙያው የጋራ አስተዳደር የተቁዋቁዋመ  የሙያ ማህበር የለም ። የመጀመሪያው የፌዴራል ጠበቆች ማህበር ነው ። በግርድፍ ረቂቅ ሕግ ደረጃ የተሞከረው የጤና ባለሙያዎች መማክርት ጉባኤ ነበር ፣ ግን አልተሳካም ። በጤና ባለሙያዎችም በኩል ፣ ወደ self regulation የሚሸጋገር ቅድመ co regulated የሆነ ማህበር የመመስረት ፍላጎት ነበር ። እኔም በማማከሩና በሕግ ማርቀቁ ተሳታፊ የነበርኩበት የጤና ሚኒስቴር initiative ነበር ። የፌዴራል ጠበቆች ማህበር ማቁዋቁዋሚያ አዋጅ ላይ የታዩት የትርጉምና የአፈጸጸም ችግሮች መሰረታቸው በባህሪው የተለየ ህግ ከመሆኑ ፣ በተግባርም ተመሳሳይ ተሞክሮ የሌለው መሆኑ ጭምር ይመስለኛል ። የጠበቆች ማህበር በሲቪል ሶሳይቲ ማህበርነቱም ብዙ የተፈተነና የተንገራገጨ ማህበር ስለነበር ለፌዴራል ጠበቆች ማህበር መሰረት ሊሆን የሚችል ተቁዋማዊ ባህል ፣ አሰራርና አደረጃጀትንም ማውረስ አልቻለም ። ስለሆነም በሕጉም መዳበርና በተቁዋም ግንባታውም ብዙ ፈታዎችን እየተጋፈጠ መሄድ ይጠበቅበታል ። የ አንድ ወጥ የ leadership team spirit በፍጥነት መገንባት ግን የግድ ይመስለኛል ። በዚህ ፣ በተቁዋም አመራር ክህሎትና ተየያዥ የስራ አመራር ጉዳዮች ላይ አመራሩ የማኔጅመንት ስልጠናዎችን ቢወስዱ ጥሩ ይመስለኛል ። ዘመኑ በመሰል ስልጠና ክህሎትን እያዳበሩና የልምድና የእውቀትን ክፍተት እየሞሉ ብቁ ለመሆን ጥረት የሚደረግበት ነው ። የስብሰባ ቦታና ጊዜም ሌላው ጉዳይ ነው ። የመንግስትን አዳራሽ መጠቀም ፣ የውሀና ሻይ ጋጋታውን ትቶ የግማሽ ቀን ስብሰባ እያደረጉ የተንጠለጠሉ ገዳዮችን በፍጥነት እልባት እየሰጡ መሄድ ያስፈልጋል ። ጠበቃው ከግማሽ ቀን በላይ ተስብስቦ መዋል የሚችል አይመስልም ።  ሁሌም የግድ ውድ ሆቴል ውስጥ መደረግ የለበትም ። በተረፈ ፣ ማህበር መምራት ከባድ ፣ ፈተናው ብዙ እንደሆነ ፣ ጊዜ ትኩረትና ኮሚትመንት እደሚጠይቅ ስለማውቀው  ፣ ስራ አስፈጻሚውን ፈጣሪ ያበርታችሁ እላለሁ ... መልካም ቀሪ የስራ ዘመን ይሁንላችሁ ። #Abebe Asamere
Show all...
👍 2🥰 2
ለፌዴራል ጠበቆች ማህበር ኘሬዝደንት ለመምረጥ ነገ ግንቦት 3 ቀን በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል ቀጠሮ ተይዟል። ጠበቃ አዲስ ሙሀመድ ኘሬዝደንት ለመሆን እጩ ሆኘ ቀርቤአለሁ የማህበሩ አባላት በቦታው ተገኝታችሁ ድምፅ እንድትሰጡ በክብር ተጋብዛችኋል ። አመሰግናለሁ
Show all...
👍 15❤ 1
አቶ ታዬ ደንደአ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ብይን ተሰጠ አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የቀድሞ የሰላም ሚኒስትር ዴዔታ አቶ ታዬ ደንደአ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ብይን ተሰጥቷል፡፡ ዋስትና ላይ የግራ ቀኝ ክርክር መርምሮ ብይኑን የሰጠው በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ህገመንግስትና ህገመንግስት ስርዓት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀል ጉዳዮችን የሚመለከተው ችሎት ነው። የፍትህ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዳይሪክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በተከሳሽ ታዬ ደንደአ ላይ ሦስት ክሶችን ማቅረቡ ይታወሳል። ይኸውም ክስ፥ ተከሳሹ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀጽ 251/ሐ እና አንቀጽ 257/ሰ ስር የተመላከተውን ድንጋጌ እና የጦር መሳሪያ አዋጅን መተላለፍ የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ሲሰሩ የሀገርን፣ የመንግስት እና የህዝብን ደህንነት ማስጠበቅ፣ ማረጋገጥ ሲገባቸው ይህን ወደጎን በመተው ፀረ-ሰላም ኃይሎችን የሚደግፉ መልዕክቶችን በስማቸው በተከፈተ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሲያስተላልፉ ነበር የሚል ነው፡፡ በተጨማሪም ተከሳሹ ፍቃድ ሳይኖራቸው የጦር መሳሪያ አዋጁን በመተላለፍ በታኅሣስ 1 ቀን 2016 ዓ.ም ከረፋዱ 5:00 ሰዓት ላይ በልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 6 በሚገኝ መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ በተደረገ ብርበራ አንድ ታጣፊ ክላሽንኮቭ ከሁለት የክላሽንኮቭ ካዝና ከ60 ጥይት ጋር ይዞባቸዋል የሚል ነው። አቶ ታዬ ከጠበቆቻቸው ጋር ችሎት ቀርበው የክስ ዝርዝሩ ከደረሳቸውና በንባብ ከተሰማ በኋላ የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው ጥያቄ ቀርቧል። በዐቃቤ ሕግ በኩል የዋስትና ጥያቄያቸው በሰበር ሰሚ ችሎት ዋስትናን በልዩ ሁኔታ ሊከለክል የሚችልባቸው ነጥቦችን ማለትም በተደራራቢ ክስ መከሰሳቸውንና የተከሰሱበት ድንጋጌ ከፍ ያለ ቅጣት የሚያስጥል ከሆነ ዋስትና ሊያስከለክል ይችላል በማለት ተከራክሯል። በተከሳሽ ጠበቆች በኩል ሰበር ሰሚ ችሎት ያስቀመጣቸው ዋስትናን ሊያስከለክሉ የሚችሉ ድንጋጌዎች ተከሳሹ ላይ በቀረበው ክስ የሚመለከቱ አለመሆናቸው ጠቅሰው መልስ ስጥተዋል። በተጨማሪም ህጻን ልጃቸውን ጥለው መታሰራቸውን ጠቅሰው፥ በህገመንግስቱ የተቀመጠው የህጻናት መብት ታሳቢ ተደርጎ በውጭ ሆነው እንዲከታተሉ ጠይቀዋል። የግራ ቀኝ ክርክሩን የተከታተለው ፍርድ ቤቱም ያቀረቡትን የዋስትና የመብት ጥያቄን መርምሮ ዛሬ በዋለው ችሎት አቶ ታዬ በወ/መ/ስ/ህ ቁጥር 67 መሰረት በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ብይን ሰጥቷል። አቶ ታዬ በጠበቆቻቸው አማካኝነት ያቀረቡትን የክስ መቃወሚያ ላይ ዛሬ ከሳሽ ዐቃቤ ሕግ አስተያየቱን በጽሁፍ የሰጠ ሲሆን፥ ፍርድ ቤቱም የክስ መቃወሚያው ላይ መርምሮ ብይን ለመስጠት ለግንቦት 13 ቀን 2016 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። በታሪክ አዱኛ
Show all...
👍 1
#ህግን_በአዲስ_እይታ በተከሳሽ ቃል አሰጣጥ ዙሪያ የተነሱት ሀሳቦች ዛሬም ይቀጥላሉ አዲስ መሀመድ ከሀምዲያ ናስር ጋር የግል ገጠመኛቻቸውን እያነሱ ቆይታ አድርገዋል የፕሮግራሙን link በመጫን መመልከት ይችላሉ subscribe, like እና share በማድረግ ቤተሰብ መሆን አይርሱ
Show all...
Show all...
የተከሳሽነት ቃል አሰጣጥ ክፍል 2 || ህግን በአዲስ እይታ || አዲስ መሀመድ እና ሀምዲያ ናስር || ድንቅ ገጠመኞችን ያካፈሉበት መድረክ

251920298841For more information Telegram:

https://t.me/addismohlawfirmWebsite

:

https://addisassolawfirm.comtik

tok:tiktok.com/@tbqaaddisyoutube:

https://youtu...

በተሰራው ኦዲት መሰረት ክፍያውን እንዲከፍል መጠየቅ ፈቃደኛ ካልሆነ በፍትሐ ብሔር ክስ መስርቶ ማስመለስ ይቻላል
Show all...