en
Feedback
ደቡብ ምዕራብ ቀጣና ቃ/ሕ/ጽ/ቤት South West Zone KHC office

ደቡብ ምዕራብ ቀጣና ቃ/ሕ/ጽ/ቤት South West Zone KHC office

Open in Telegram

ወልድ ያለው ሕይወት አለው

Show more
425
Subscribers
No data24 hours
+47 days
+2330 days
Posts Archive
የደቡብ ምዕራብ ቀጣና ቃለ ሕይወት ቤተ ክተ ክርስቲያን ዋና ፀሐፊ መ/ር ኢያሱ እንዳሻው በደቡብ ክልል ከ96 ወረዳዎች ከተወጣጡ ከ2ሺ በላይ ባለድርሻ አካላት ጋር በሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ማሰባሰብ
የደቡብ ምዕራብ ቀጣና ቃለ ሕይወት ቤተ ክተ ክርስቲያን ዋና ፀሐፊ መ/ር ኢያሱ እንዳሻው በደቡብ ክልል ከ96 ወረዳዎች ከተወጣጡ ከ2ሺ በላይ ባለድርሻ አካላት ጋር በሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ማሰባሰብ የውውይት መድረክ ላይ እየተካፈሉ ይገኛሉ።

የ እምነት አባቶች በዲግዶ ታዳጊ ኅብረት ምሥረታ ላይ ተገኝተው ጌታን አመስግነዋል ።
የ እምነት አባቶች በዲግዶ ታዳጊ ኅብረት ምሥረታ ላይ ተገኝተው ጌታን አመስግነዋል ።

በደቡብ ምዕራብ ቀጣና የድግዶና አከባቢው ታዳጊ አጥቢያዎች ህብረት የምስረታና የምስጋና በዓሉን እያከበረ ይገኛል። ከጋሞ አጥቢያ ቤተክርስቲያናት ህብረት ከተወለዱ ታዳጊ ህብረቶች አንዱ የሆነው ድግዶና አከባቢው ታዳጊ አጥቢያ ቤተክርስቲያን ህብረት ጥቅምት 14/2017 ዓ.ም የደቡብ ምዕራብ ቀጣና ጠቅላላ ጉባዔ እና የድታ ወረዳ የመንግሥት ተወካዮች የአከባቢው ሕዝብ የቤተክርስቲያን አባላት በተገኙበት በታላቅ ድምቀት የምስረታ በዓሉን አክብሯል። ምስረታውን ለማክበር በአከባቢው ከተለያየ አቅጣጫ በእግርና በተሽከርካሪ የወጣው ሕዝብ ለቁጥር የሚያዳግት ነበር። ይህ እንድህ የሆነው ከዛሬ 75 ዓመት ጀምሮ አባቶችና እናቶች በከፈሉት ታላቅ መስዋዕትነት መሆኑን በሥፍራው የተገኙ በወንጌል ምክንያት ሞት ተፈርዶባቸው ያመለጡ አባባ ተስፋየ ቶሌ አባባ ጳውሎስ ዛቶና ሌሎች የእምነት አባቶች ተናግረዋል። አንዳንዶች ስለከፈሉት ዋጋ ሲናገሩ በጨለማ ያለ መብራት በእግር ያለ ጫማ በዝናብና ፀሐይ ያለ ጀንጥላ በማህረሰቡ በመገለል በረሃብና ጥማት ጋራውንና ሸንተረሩን ወጥተን ወረደናል። በለቅሶ ዘርተናል ዛሬ ግን በደስታ አጭደናል ብለዋል ለጌታም ክብርን ሰጥተዋል። አቶ አብርሃም አንጁሎ የህብረቱ ሰብሳቢ ሕዝቡን እንኳን ደህና መጣችሁ ንግር በማድረግ የደቡብ ምዕራብ ቀጣና ሰብሳቢ አቶመንግሥቱ ቦሼን የጋበዙ ሲሆን ሰብሳቢው ለሕዝቡ እንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። የእግዚአብሔር ቃል በደቡብ ምዕራብ ቀጣና ም/ዋና ፀሐፊ መጋቢ እንድርያስ ላሌ ከ2ኛ ዜና 14-16 ካለው ክፍል እግዚአብሔርን ፈልጉ በሚል ሐሳብ የቀረበ ሲሆን የመዝሙር አገልግሎት በዘማሪ ጳውሎስ ካባቶ ቀርቧል። የምስጋና ፕሮግራም ቀጣይ ሁለት ቀናትን የሚቀጥል መሆኑን ማረጋገጥ ተችሏል።

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የደቡብ ምዕራብ ቀጠና ቃለ ህይወት ቤተክርስትያን በጋሞ ዞን በማከናወን ላይ ያሉ የልማት ስራዎች በመጎብኘት ላይ ይገኛሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የደቡብ ምዕራብ ቀጠና ቃለ ህይወት ቤተክርስትያን በጋሞ ዞን፤ በአርባ ምንጭ ከተማ እያከናወነች የሚገኙ የልማት ስራዎችን በመጎብኘት ላይ ናቸው። የደቡብ ምዕራብ ቀጠና ቃለህይወት ቤተክርስትያን በአርባምንጭ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን በማከናወን ላይ ትገኛለች፡፡ ለአብነት፤ ቤተክርስትያኗ ከ1 ሺህ 4 መቶ በላይ ተማሪዎችን በመቀበል ከኬጂ እስከ 12ኛ ክፍል የሚያስተምር ሞዴል ትምህርት ቤት፣ ከ2 ሺህ በላይ ወላጆቻቸውን ያጡ ህፃናትን የመደገፍ እንዲሁም ኤች አይ ቪ በደማቸው የተገኝባቸው ግለሰቦች የህክምና ክትትል እንዲገኙ የማድረግ እና የመደገፍ ስራዎችን በማከናወን ላይ ትገኛለች። በተጨማሪ ቤተክርስትያኗ የቁጠባ ባህልን የሚያጠናክር የፋይናንስ ስረዓት በመዘርጋት፤ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ እያደረገች ሲሆን፤ በአነስተኛ ዋጋ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ሴቶችን ተጠቃሚ ያደረጉ የሙያ ስልጠናዎችም በመስጠት ላይ ትገኛለች። ርዕሰ መስተዳድሩ በጉብኝቱ ወቅት፤ ቤተክርስቲያኗ እያከናወነች የምትገኘው ሰው ተኮር ተግባር ሊበረታታ የሚገባው እና ለሎች ሞዴል ሊሆን የሚችል መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በተለይ በትምህርት ዘርፍ ከታችኛው እርከን ጀምሮ በማስተማር እያበረከተች ያለው አስትዋጽኦ፤ እንደ ሀገር የገጠመንን የትምህርት ስብራት ለመጠገን በማድረግ ላይ ያለውን ርብርብ በእጅጉ የሚያግዝ ነው ብለዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ አክለው፤ በቀጣይም ቤተክርስትያኗ በማከናወን ላይ ያለችው የልማት ስራዎችን ከዞኑ እና ከከተማው አስተዳደር ጋር በመቀናጀት ማጠናከርና ተደራሽነቱን ለማስፋት መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል። #ርዕሰመስተዳድርጽቤት

የድግዶ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት ታዳጊ ኅብረት የምስረታ ኘሮግራም በድምቀት እየተካሄደ ነው ።

ከጥቅምት 12 -13/2017 ዓ.ም የደቡብ ምዕራብ ቀጣና ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ለኅብረቶችና ለቀጣናው ዋና ፀሐፊዎች፣ ም/ዋና ፀሐፊዎች፣ ለሴቶችና ለወጣቶች አስተባባሪዎች በዶ/ር መጋቢ አለማየሁ
ከጥቅምት 12 -13/2017 ዓ.ም የደቡብ ምዕራብ ቀጣና ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ለኅብረቶችና ለቀጣናው ዋና ፀሐፊዎች፣ ም/ዋና ፀሐፊዎች፣ ለሴቶችና ለወጣቶች አስተባባሪዎች በዶ/ር መጋቢ አለማየሁ ጎሹና በአገልጋይ ዘላለም ስሰጥ የነበረው 3ተኛው ዙር የመሪነት ሥልጠና በሠላም ተጠናቀቀ ፡፡ የዚህ ዙር ሥልጠና ያተኮረው "ለውጥን መምራት" የሚል ነው ። 4ተኛው ሥልጠና በጥር ወር እንደሚሰጥ ቀጠሮ ተይዟል ። እስከዛው ድረስ ሠልጣኞችን ሌሎችን አሠልጥው ሪፖርት ይዘው እንደሚመለሱ ቃል ገብተዋል ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ጥቅምት 11/2017 ዓ.ም በጋሞ ዞን አርባምንጭ ከተማ የደቡብ ምዕራብ ቀጣና ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ጽ/ቤትና ጋሞ ቃለ ሕይወት አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት ህብረት ጽ/ቤት ተገኝተው የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ ከልዑካቸው ጋር በቀጣናው ጽ/ቤት በመገኘት የተሰሩ የመጋዘን ግንባታ፣ በከተማው ስሜጥር የሆነውን የርኆቦት ትምህርት ቤት ከአፀደ ህፃናት ጀምሮ 12ኛ ክፍል ያለውን የሴቶች የልብስ ስፌትና ውቤት ሙያ ማሰልጠኛዎችን በኤች አይቪ የተጎዱ ወገኖችን የሚያግለግለውን የልማት ፕሮጀክት ጎብኝተዋል። የቀጣናው ጽ/ቤት ኃላፊዎችና የየክፍሉ ኃላፊዎች በእያንዳንዱ ጉዳይ ለጎበኚዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ በተጨማሪም ተስፋ ማይክሮ ፋይናንስ አርባምንጭ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጎብኝቶ ሁሉን የማህበረሰብ ክፍል የምያገለግል እንድሆን መመሪያ ሰጥተዋል። የቀጣናውን ጽ/ቤት ጉብኝት ሲያጠቃልሉ ሁለንተናዊ ስለሆነው አገልግሎት አመስግነው አንዳንድ ሥራዎች ተሞክሮ ወደ ክልል ደረጃ እንዲያድግ መሠራት እንዳለበት ጠቁመው ከልዑካቸው ጋር ወደ ጨንቻ ተጉዘው ቤተክርስቲያን በደጋማው አከባቢ በአፕል የተሠራውን ሥራ የጎበኙ ሲሆን ቤተ ክርስቲያን ጠብቃ ስላቆየቻቸው መልካም ሥራ አመስግነው በቀጣይ በክልሉ ከቤተ ክርስቲያንቱ ጋር በአፕል ዙሪያ መሠራት ያለባቸውን የሥራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። የደቡብ ምዕራብ ቀጣና ዋና ፀሐፊ መምህር ኢያሱ እንዳሻው ርዕሰ መስተዳድሩንና ልዑካቸውን አመስግነው ሁለንተናዊ የሆነ ሥራ እንድንሰራ በምትጠይቁን ሁሉ ቤተ ክርስቲያን ከመንግሥት ጋር የምትሠራ መሆኑን ተናግሯል። በፌስቡክ ገጻቸው ርዕሰ መስተዳድሩ እንድህ ብለዋል "በክልላችን ካሉን ፀጋዎች አንዱ የሆነዉ የደጋ ፍራፍሬ አፕል ከ100 በላይ ዝሪያዎች በጨንቻ ወረዳ እንዳሉ ባለሙያዎች አብራርተዋል። ዛሬ ጥቅምት ፩፩/፩፯ የጎበኘነዉ የችግኝ ዝግጅት የተለያዩ ዝሪያዎች መኖራቸውን አረጋግጠናል። ይህንን ፀጋ ያቆዩልን በኢትዮጵያ ቃለህይወት ቤተክርስቲያን የደቡብ ምዕራብ ቀጠና አመራሮች፣ በጨንቻ ከተማ አስተዳደር የጦሎላ ቃለህይወት ቤተክርስቲያን የኃይማኖት አባቶች እና ምዕመናን ምስጋና ይድረሳችሁ። ፀጋችንን ለክልላችን ብልጽግና !"

በክልላችን ካሉን ፀጋዎች አንዱ የሆነዉ የደጋ ፍራፍሬ አፕል ከ100 በላይ ዝሪያዎች በጨንቻ ወረዳ እንዳሉ ባለሙያዎች አብራርተዋል። ዛሬ ጥቅምት ፩፩/፩፯ የጎበኘነዉ የችግኝ ዝግጅት የተለያዩ ዝሪያዎች
+9
በክልላችን ካሉን ፀጋዎች አንዱ የሆነዉ የደጋ ፍራፍሬ አፕል ከ100 በላይ ዝሪያዎች በጨንቻ ወረዳ እንዳሉ ባለሙያዎች አብራርተዋል። ዛሬ ጥቅምት ፩፩/፩፯ የጎበኘነዉ የችግኝ ዝግጅት የተለያዩ ዝሪያዎች መኖራቸውን አረጋግጠናል። ይህንን ፀጋ ያቆዩልን በኢትዮጵያ ቃለህይወት ቤተክርስቲያን የደቡብ ምዕራብ ቀጠና አመራሮች፣ በጨንቻ ከተማ አስተዳደር የጦሎላ ቃለህይወት ቤተክርስቲያን የኃይማኖት አባቶች እና ምዕመናን ምስጋና ይድረሳችሁ። ፀጋችንን ለክልላችን ብልጽግና ! የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ የተመራው ልዑክ በጋሞ ዞን እየተከናወኑ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን እየጎበኘ ይገኛል። አርባምንጭ ፣ ጥቅምት 11/2017 ዓ.ም (ጋሞ ዞን መ/ኮሚዩኒኬሽን )፦ በርዕሰ መስተዳድሩ የተመራው ልዑክ በደቡብ ምዕራብ ቀጠና ቃለ ሕይወት ቤተክርስትያን አርባምንጭ ርኖቦት አርባምንጭ ከቅድመ አንደኛ እስከ ሁለተኛ ደረጃ መሰናዶ ትምህርት ቤት እና በተለያዩ የሙያ መስኮችን የሚሰጡ የስልጠና መስኮችን ተመልክቷል። በጣሊያናዊቷ ማርያ ሞንቶሶሪ የተመሰረተው ት/ቤት የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ አለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው የ'ሞንቶሶሪ ማስተማሪያ ' ዘዴን እንደሚከተሉ ታውቋል ። በጊቢው ውስጥ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤትን፣ በሴቶች የውበት ሳሎን ስልጠና፣ የልብስ ስፌት ፣ ከኤችአይቪ/ኤድስ ቫይረስ ጋር የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የመደገፍ የመንከባከብ በኢኮኖሚ እራሳቸውን እንዲችሉ በማድረግ ፣ የፍይናንስ ተቋማትን በስሩ በማቀፍ እና በርካታ ተግባራት እያከናወነ ስለመሆኑ ገለጻ ተደርጓል ። በጉብኝቱ ወቅትም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ርዕሰ መስተዳድ አቶ ጥላሁን ከበደ ባስተላለፉት መልዕክት የትምህርት ስብራትን ለመጠገን እና በከተማዎ ተሰፋን የተላበሰ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ለማፍራት ብሎም የሞያ ትምህርት በመስጠት የስራ ዕድል ለመፍጠር የሚያደርጉትን ጥረት አጠናክረው እንዲቀጥሉም አሳስበዋል። ተቋሙ እያከናወናቸው ያሉ የማስፋፊያ ስራዎች ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍል ያሳተፈ እንዲሆንም ርዕሰ መስተዳድሩ መልዕክት አስተላልፈዋል ። በመረሃ ግብሩም ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ፣ የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ፣ የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አባይነህ አበራ የዞኑ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ ።