en
Feedback
Rt News Amharic

Rt News Amharic

Open in Telegram

እንኳን ወደ "Rt news amharic"ቻናላችን በሰላም መጡ በዚህ ቻናል ወቅታዊ እና ፈጣን የሆኑ የማህበራዊ ፣ኢኮናሚያዊ እና ፓለቲካዊ ይዘት ያላቸውን መረጃዎች ያገኛሉ!!! ቻናላችንን ለወዳጅ ቤተሰብዎ ያጋሩ። 🙏🙏🙏🙏🙏

Show more
206
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
የአማራ ክልል ምክር ቤት የአቶ ዮሐንስ ቧያለውን ያለመከሰስ መብት አነሳ። የአማራ ክልል ምክር ቤት እያካሄደ ባለው 6ኛ ዙር 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 7ኛ መደበኛ ጉባኤ የክልሉ ምክር ቤት አባል የነበ
የአማራ ክልል ምክር ቤት የአቶ ዮሐንስ ቧያለውን ያለመከሰስ መብት አነሳ። የአማራ ክልል ምክር ቤት እያካሄደ ባለው 6ኛ ዙር  3ኛ ዓመት  የስራ ዘመን 7ኛ መደበኛ ጉባኤ የክልሉ ምክር ቤት አባል የነበሩትን የአቶ ዮሐንስ ቧያለውን ያለመከሰስ መብት አነሳ።

አማርኛ የአፍሪካ ህብረት የስራ ቋንቋ እንዲሆን ኢትዮጵያ ጠየቀች 44ኛው የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ነው። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት ውጭ
አማርኛ የአፍሪካ ህብረት የስራ ቋንቋ እንዲሆን ኢትዮጵያ ጠየቀች 44ኛው የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ነው። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት ውጭ ጉዳይ ሚንስትሮች የሚሳተፉበት ይህ የህብረቱ ሚንስትሮች ስብሰባ ዛሬ እና ነገ ይካሄዳል። በዚህ ጉባዔ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ አፍሪካ ህብረት የአማርኛ ቋንቋን የስራ ቋንቋው እንዲያደርግ ጥያቄ አቅርበዋል። ሚንስትሩ በንግግራቸው አክለውም "የቀድሞው አፍሪካ አንድነት ድርጅት አማርኛ አንደኛው የስራ ቋንቋ እንደሚያደርግ በወቅቱ ተነግሮ ነበር፣ ይህ እስካሁን ውሳኔ ሳያገኝ ቆይቷል" ብለዋል። አፍሪካ ህብረት ከአንድ ዓመት በፊት በምስራቅ አፍሪካ በስፋት እሚነገረው ስዋህሊ ቋንቋን የህብረቱ የስራ ቋንቋ እንዲሆን ወስኖ ነበር። አፍሪካ ህብረት አሁን ላይ ስዋህሊን ጨምሮ እንግሊዝኛ ፣ፈረንሳይኛ፣ አረብኛ፣ ስፓኒሽ እና ፖርቹጊዝ የስራ ቋንቋው አድርጓል። የህብረቱ የሚንስትሮቹ ስብሰባ የፊታችን ቅዳሜ እና እሁድ በሚካሄደው የህብረቱ መሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ አንኳር አጀንዳዎች ላይ በመወያየት የውሳኔ ሀሳቦችን ማዘጋጀት ላይ ያተኩራል ተብሏል። ዘንድሮው የህብረቱ መሪዎች ጉባኤ ዋነኛ ትኩረቱን በትምህርት ልማት ላይ እንደሚያደርግ ተገልጿል።

ህጻናትን የሚደፍሩ ወንዶች ብልት እንዲቆረጥ የሚያዝ ህግ ተዘጋጀ በደቡብ ምዕራብ አፍሪካ የምትገኘው ማዳጋስካር ህጻናትን የሚደፍሩ ወንዶችን ብልት እንዲቆረጥ የሚያስገድድ ህግ አውጥታለች፡፡ ሀገሪቱ ህ
ህጻናትን የሚደፍሩ ወንዶች ብልት እንዲቆረጥ የሚያዝ ህግ ተዘጋጀ በደቡብ ምዕራብ አፍሪካ የምትገኘው ማዳጋስካር ህጻናትን የሚደፍሩ ወንዶችን ብልት እንዲቆረጥ የሚያስገድድ ህግ አውጥታለች፡፡ ሀገሪቱ ህጻናቶቿን ከመደፈር አደጋ ለመጠበቅ ጥብቅ ረቂቅ ህግ ያዘጋጀች ሲሆን በዚህ ህግ መሰረት ደፋሪዎች ብልታቸው እንዲቆረጥ ይገደዳሉ፡፡ ከ10 ዓመት በታች የሆኑ ህጻናትን የደፈሩ ወንዶች ብልታቸው በቀዶ ጥገና ሐኪም ተቆርጦ እንዲጣል ይደረጋል የተባለ ሲሆን፣ ከ13 እስከ 18 ዓመት የሆናቸው ህጻናትን የደፈሩ ሰዎች ደግሞ በኬሚካል  አማካኝነት ብልታቸው እንዲጎዳ ይደረጋል ተብሏል፡፡

የኢትዮጵያ ስርዓት ወደ ፕሬዝዳንታዊ ስርዓት ሊቀየር ነው ተባለ በኢትዮጵያ የስራ አስፈፃሚውን በጠ/ሚር ከሚመራ (parliamentarian) ወደ ፕሬዝደንታዊ (presidential) ስርዐት የመለወጥ ሂደት መጀመሩ ተሰምቷል። ጠ/ሚር አብይ አህመድ ወደ ስልጣን የመጡ ሰሞን በስፋት ይነሳ የነበረው ይህ የፕሬዝደንታዊ ስርዐትን የመዘርጋት ሂደት አሁን ከታሰበው የህገ መንግስት ማሻሻያ ጋር አያይዞ በስፋት ስለተሄደበት በቅርብ ግዜያት ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግ የደረሰኝ መረጃ ይጠቁማል። በፓርላመንታዊ ስርዐት ዜጎች የመረጧቸው የህዝብ ተወካዮች ጠ/ሚሩን ሲመርጡ በፕሬዘደንታዊ ስርዐት ደግሞ ዜጎች በቀጥታ ፕሬዝደንት የሚሆነውን ይመርጣሉ። Via:- EliasMeseret

ተምስገን ጥሩነህ የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሁም አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን በ15ኛ መደበኛ
+1
ተምስገን ጥሩነህ የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሁም አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን በ15ኛ መደበኛ ስብሰባ የአምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ሹመት አጽድቋል። ምክር ቤቱ በተመሳሳይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዕጩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነት ያቀረቡት ተመስገን ጥሩነህ ሹመትንም ማጽደቁን ብሔራዊ ቴሌቭዥኑ ሰምተናል፡፡ የአምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ  የሥራ ልምድ ዘርዝረው ለምክር ቤቱ ባቀረቡት መሰረት ምክር ቤቱ በሙሉ ድምጽ ሹመቱን አጽድቋል፡፡

አትሌት ጎይትቶም ገብረስላሴን የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን የአቦ ሸማኔ የክብር አምባሳደር አድርጎ ሾመ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ታዋቂዋን አትሌት ጎይትቶም ገብረስላ
አትሌት ጎይትቶም ገብረስላሴን የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን የአቦ ሸማኔ የክብር አምባሳደር አድርጎ ሞመ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ታዋቂዋን አትሌት  ጎይትቶም ገብረስላሴን የክብር አምባሳደር አድርጎ በዛሬው እለት ሾሟል።በባለስልጣኑ የኮሙኒኬሽን ባለሙያ የሆኑት አቶ ናቃቸው ብርሌው ለብስራት ሬድዮና ቴሌቭዥን እንደተናገሩት በሰው ሰልሽ ጫና ምክንያት በርካታ የኢትዮጲያ የተፈጥሮ ሀብቶች የመጥፋት አደጋ ተጋርጦባቸዋል። ከእነዚህም መካከል ደግሞ በዓለም በፍጥነቱና በልዮ ባህርይው የሚታወቀው የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት በሆነው  አቦ ሸማኔ ላይ እየደረሰ ያለው ህገወጥ አደንና ዝውውር መበራከት ህልውናውን ለከፍተኛ አደጋ ዳርጎታል። ይህን አደጋ ለመከላከልና የአቦ ሸማኔን ህልውና ለመታደግ ፈጣን የማራቶን ሯጭ አትሌት የሆነችውን አትሌት ጎይትቶም ገብረስላሴን ባለስልጣኑ በአምባሳደርነት ሾሟል ያሉት የኮሚኒኬሽን ባለሙያው ይፋ የማድረጊያ መርሀ ግብሩን በዛሬው እለት አከናውኗል። አትሌቷ የአቦ ሸማኔ የክብር አምባሳደር በመሆኗም በቀጣይ  የእንስሳቱን ህልውና ለመታደግ የግንዛቤና የማስተዋወቅ ስራዎችን እንደምታከናውን ይጠበቃል።

ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በተለያዩ ርቀቶች ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ ድል አደረጉ  በቶሩን፣ ፖላንድ እየተካሄደ ባለው የዓለም የቤት ውስጥ ሩጫ ውድድር በተለያዩ ርቀቶች ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ እና ክብረ ወሰን በመስበር ጭምር አሸንፈዋል። አትሌት ፍሬወይኒ ኃይሉ በ1 ሺህ 500 የቤት ውስጥ ሩጫ በዓለም አራተኛውን ፈጣን ሰዓት  3:55.28 በማስመዝገብ አሸንፋለች ። በሌላ በኩል አትሌት ቢኒያም መሐሪ ከ20 ዓመት በታች በተደረገ የ1 ሺህ 500 ሜትር ሩጫ 3:34.83 በሆነ ሰዓት በመግባት ክብረ ወሰን አሻሽሏል ። በሴቶች የ800 ሜትር ሩጫ ደግሞ አትሌት ሀብታም ዓለሙ 1:57.86 የሆነ ፈጣን ሰዓት አስመዝግባ ውድድሩን አሸንፋለች። ከዓለም አትሌቲክስ ያገኘነው መረጃ እንደሚያሳየው አትሌት ሰለሞን ባረጋ በወንዶች የ3 ሺህ ሜትር ሩጫ 7:25.82 በሆነ ሰዓት በመግባት ለራሱም አምስተኛው ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ አሸንፏል ።

photo content
+2

"ወደ ሀገር እንዳልገባ ከልክለውኝ በመጣሁበት አውሮፕላን እየተመለስኩ ነው"--- ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ከደቂቃዎች በፊት በስልክ ነገሩኝ የተወሰደ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በአሜሪካ ከነበራቸው አጭር ቆይታ በኋላ ዛሬ ወደ ሀገር ቤት ሲመለሱ መግባት ተከልክለው በመጡበት አውሮፕላን እየተመለሱ እንደሆነ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት በስልክ አሳውቀውኛል። "እንዴ ኮበለለ፣ ሌላ ግዜ ሀገር ጥሎ ጠፋ ሲባል እኛም አውቀነው ነበር... ድርጊቱ ግን ቤተክርስቲያናችንን ለማዋረድ የተደረገ ነው" በማለት አስተያየታቸውን ሰጡኝ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ብፁዕ አቡነ አብርሀምን ጨምሮ በርካታ የቤተ ክህነት ሀላፊዎች አየር ማረፊያ በመገኘት መፍትሄ ቢፈልጉም ሳይሳካ ቀርቷል ብለዋል። ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ከሀገር አመለጡ፣ ኮበለሉ፣ ተሰደዱ... ወዘተ የሚሉ መረጃዎች በሰበር ዜናነት የዛሬ ሶስት ሳምንት ገደማ በስፋት እየተሰራጩ ነበር። በወቅቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ መረጃው ሀሰተኛ መሆኑን ገልፀው በዛሬው እለት እንደሚመለሱ አሳውቀው ነበር። Via Elias meseret

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ወደ ሀገር እንዳይገቡ ተከለከሉ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በአሜሪካ የነበራቸው
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ወደ ሀገር እንዳይገቡ ተከለከሉ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በአሜሪካ የነበራቸውን ሐዋርያዊ አገልግሎት ጨርሰው ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ እንዳይገቡ መከልከላቸው ተሰምቷል። ብፁዕነታቸው ከሳምንታት በፊት በቋሚ ሲኖዶስ እውቅና ወደ ሀገረ ስብከታቸው በመሄድ የአጋእዝተ ዓለም ሥላሴ ዓመታዊ በዓል፣ የከተራና የጥምቀት በዓላትን ከመንፈስ ልጆቻቸው ጋር ያከበሩ ሲሆን ለአዳጊ ሕጻናትም ማዕረገ ዲቁና መስጠታቸው ይታወቃል። ብፁዕነታቸው በአሁኑ ሰዓት ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያው ይገኛሉ ሲሉ መረጃ ሰጭዎቻችን አድርሰውናል ሲል ማኅበረ ቅዱሳን ቴቪ አስታውቋል።

‹‹ ጉም አትደገፉ ›› - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ‼️ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በእንደራሴዎች ምከር ቤት እየሰጡት ባለው ማብራሪያ በተለይ የአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ሰላምና ጸጥታን በተመ
‹‹ ጉም አትደገፉ ›› - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ‼️ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በእንደራሴዎች ምከር ቤት እየሰጡት ባለው ማብራሪያ በተለይ የአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ሰላምና ጸጥታን በተመለከተ በሰጡት ገለጻ ‹‹ ሕዝቡ የሚደገፈውን ቢያውቅ ጥሩ  ነው ›› የሚል ምክረ ሀሳብ ሰንዝረዋል፡፡ ‹‹ ጉም ምንም ያህል ተራራ ቢያህል፣  ክምር ድንጋይ ቢያህል፣ ጉሙን አትንተራሰውም፤ ጉም ጉም ነው ›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ በጉም ወክለው ያስተላለፉትን መልዕክት ሲቀጥሉ ‹‹ መንተራስ ያለብን ነገር ደገፍ የሚያደርገንን ነው፤ ዝም ብሎ የማይዘልቅህን ነገር ተንተርሰህ፣ ወደጥፋት እንዳናመራ፣ በተቻለ መጠን ሰላም፣ ሰላማዊ ውይይት፣ ንግግር፣ የሚለውን አማራጭ ብንከተል መልካም ይሆናል ›› ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ምንም እንኳን ዐብይ ‹‹ ጉም ›› ሲሉ የጠሯቸው አካላት እነማን እንደሆኑ በግለጽ ባይዘረዝሩም ከዚህ የጉም ተምሳሌታዊ ንግግራቸው አስቀድሞ ግን መንግስታቸው ‹‹ ሸኔ ›› ሲል በሽብርተኛነት በፈረጀው፣ ራሱን ደግሞ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት እያለ ስለሚጠራው ታጣቂ፣ እንዲሁም በእርሳቸው አገላለጽ ‹‹ በአማራ ክልል ስላሉ ጽንፈኛ ሀይሎች ›› ስለተደረገው የሰላም ጥረት ማብራሪያ እየሰጡ ነበር፡፡ በእርግጥ ዐብይ ‹‹ ጉም ›› ሲሉ በምሳሌ ያስረዱ እንጂ በእርሳቸው አገላለጽ ‹‹ ሸኔ ›› ይሁን አልያም ‹‹ የአማራ ክልል ጽንፈኛ  ›› ያሏቸው ‹‹ ሀይሎች ››    የትኞቹ ‹ ጉም › እንደሆኑ በቀጥታ አላብራሩም፡፡ ከሁለት አመት በፊት ዶ/ር ዓብይ አህመድ በፓርላማ  ባደረጉት ንግግር ህውሃት ማለት በንፋስ ላይ እንደተበተነ ዱቀት ማለት ነው። ከእንግዲህ ሠብስበን ዱቄት ማድረግ አንችልም" ብለው እንደነበር አይዘነጋም፡፡

የኮኬይን አደንዛዥ ዕፅ ውጠው የተገኙ የዉጪ ሀገራት ዜግነት ያላቸው ተጠርጣሪዎች በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በቁጥጥር ሥር ዋሉ የኮኬይን አደንዛዥ ዕፅን ውጠው የተገኙ የብራዚልና የኢንዶኔዥያ ዜግነት ያላቸው ተጠርጣሪዎች በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታዉቋል። አደገኛ ዕፅ አዘዋዋሪዎቹ ከብራዚልና ከኢንዶኔዥያ ሀገር ወደ ኢትዮጵያ ሲገቡ ፖሊስ ከሲቪል አቪዬሽን ደህንነት ዋና መምሪያ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ሴኩሪቲ፣ ከኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን እና ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር በመተባበር በኤክስሬይ ማሽን በተደረገው ፍተሻ ኮኬይን የተባለ አደገኛ ዕፅ ውጠው ስለተገኙ በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እያጣራባቸው እንደሚገኝ ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ሰምቷል። በአጠቃላይ የብራዚል ዜግነት ካላት ተጠርጣሪ በእንክብል መልክ የተዘጋጀ 2.900 ኪሎ ግራም ኮኬይን የተያዘ ሲሆን እስከአሁን ሰባት ፍሬ ኮኬይን ደግሞ ከሆዷ መውጣቱን የገለፀው ፖሊስ ሌላኛዋ የኢንዶኔዥያ ዜግነት ያላት ተጠርጣሪ ደግሞ 6.70 ኪሎ ግራም በሻንጣ ውስጥ ሰፍታ ፍተሻውን ለማለፍ ስትሞክር ከነ-ኤግዝብቱ በቁጥጥር ሥር መዋሏን አረጋግጧል።

photo content
+7

ማክሰኞ ጥር 28/2016 ዓ.ም ዕለታዊ ዜናዎች @rt_amharic1 #በሶማሊያ ኢትዮጵያዊያን ተገደሉ
በሱማሊያ ዕሁድ ምሽት ባልታወቁ ታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት ቢያንስ ስድስት ኢትዮጵያዊያን መገደላቸውን የሱማሊያ ዜና ምንጮች የዓይን እማኞችን ጠቅሰው ዘግበዋል። ዘገባዎቹ፣ በጥቃቱ ሌሎች ስድስት ኢትዮጵያዊያን እንደቆሰሉ አመልክተዋል። ጥቃቱ የተፈጸመው፣ በኢትዮጵያ እና ሱማሊያ ድንበር በለድ-ሃዎ ከተማ በኢትዮጵያዊዋኑ መኖሪያ ቤተ ውስጥ እንደኾነ ተገልጧል።
@rt_amharic1 #የትግራይ አቋም
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር፣ የፌደራል መንግሥቱ ቃል አቀባይ ጽሕፈት ቤት በአዋዛጋቢ አካባቢዎች "ሕዝበ ውሳኔ" እንዲካሄድ ከትግራይና አማራ ክልሎች አመራሮች ጋር መግባባት ላይ ተደርሶ ነበር በማለት ያወጣውን መግለጫ ውድቅ አደርጎታል። የቃለ አቀባዩ መግለጫ “ተቀባይነት የለውም” ያለው ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ መግለጫው ከፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት መንፈስ ጋር የሚጋጭ መኾኑን ገልጧል። አንዳንድ "ትክክለኛ ተፈናቃዮች ወደቀያቸው ተመልሰዋል" መባሉንም “አደገኛ አባባል” በማለት፣ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ውድቅ አድርጎታል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ በኃይል በተያዙ አካባቢዎች ሕገወጥ አስተዳዳሪዎች ከቦታቸው ሳይነሱ፣ እንደዚህ ዓይነት መግለጫዎች መስጠት ፌደራል መንግሥቱ ከመፍትሄው ይልቅ "የችግሩ አካል" መኾን የሚፈልግ አስመስሎበታል በማለትም ተችቷል። የፕሪቶሪያውን ስምምነት የሚቃወሙ ወገኖች “የተሳሳተ" አቋማቸውን እንዲገፉበት የሚያበረታቱ መግለጫዎች አደገኛ መዘዝ ያስከትላሉ በማለትም ጊዜያዊ አስተዳደሩ አስጠንቅቋል።
@rt_amharic1 #የዛሬ ፓርላማ
ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ዛሬ  በ14ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ የምክር ቤቱ አባላት ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ። ዐቢይ በምክር ቤቱ ተገኝተው ምላሽና ማብራሪያ የሚሰጡት፣ ምክር ቤቱ በአማራ ክልል የታወጀውን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለአራት ወራት ባራዘመ ማግስት ነው። ዐቢይ፣ ከሶማሊላንዱ ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ ጋር ከአንድ ወር በፊት በተፈራረሙት አወዛጋቢ የባሕር በር የመግባቢያ ስምምነት ዙሪያ እስካኹን ለሕዝብ ይፋዊ ማብራሪያ እንዳልሰጡ ይታወቃል።
@rt_amharic1 @rt_amharic1

ሰኞ ጥር 27/2016 ዓ.ም ዕለታዊ ዜናዎች @rt_amharic1 #የትዴፓ ጉባኤ መታገድ
የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ትዴፓ) ትላንት እና ዛሬ በመቀሌ ከተማ ሊያደርገው የነበረውን ጠቅላላ ጉባዔ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር መከልከሉን ፓርቲው ለዋዜማ ገልጧል። የፓርቲው መስራች እና ሊቀመንበር አረጋዊ በርሄ ለዋዜማ እንደተናገሩት፣ ፓርቲያቸው ለሁለት ቀናት ሊያደርገው ያሰበው ጠቅላላ ጉባዔ መስተጓጎሉን ተናግረው፣ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ግን የጉባዔውን መካሄድ አልከለከልኩም በማለት እያስተባበለ ይገኛል ብለዋል። ፓርቲያቸው ጉዳዩን እየተከታተለ እንደኾነ የገለጹት አረጋዊ፣ ፓርቲው በቀጣዮቹ ሁለት እና ሦስት ቀናት በጉዳዩ ላይ አንድ እልባት ላይ እንደሚደርስ ተናግረዋል። የጉባዔው ዓላማ፣ በክልሉ ያለው የመልካም አሥተዳደር እጦትና የምግብ እጥረት ለፖለቲካ ፍጆታ መዋሉ ንጹሃንን እየጎዳ እንደሆነ ለመግለጽ ያለመ እንደኾነ ዋዜማ ተረድታለች።
@rt_amharic1 #የብሪታኒያ የአለም አቀፍ
የብሪታንያ የዓለማቀፍ ልማት ሚንስትር ደዔታ አንድሪው ሚቸል፣ በኢትዮጵያ የተከሰተው ከፍተኛ የምግብ እጥረት ከባድ የሰብዓዊ ቀውስ ስጋት ፈጥሯል ማለታቸውን ፋይናንሻል  ታይምስ ዘግቧል። ሚቸል፣ በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል ሦስት ሚሊዮን ሰዎች ከፍተኛ የርሃብ አደጋ እንዳንዣበበባቸው የገለጡት፣ ባለፈው ሳምንት በትግራይ ጉብኝት አድርገው ከተመለሱ በኋላ በሰጡት ቃል ነው። የብሪታንያ መንግሥት ነፍሰ ጡር እናቶችን ጨምሮ ለሦስት ሚሊዮን ተረጅዎች የተመጣጠነ ምግብ እና መድሃኒት ለማቅረብ የሚውል 100 ሚሊዮን ዩሮ መመደቡን ሚቸል መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ሚቸል፣ በኢትዮጵያ ያንዣበበው የርሃብ አደጋ በዩክሬን፣ ጋዛ እና ሱዳን ባሉ ሰብዓዊ ቀውሶች ተውጧል ማለታቸውንም ጋዜጣው አውስቷል። የኢትዮጵያ መንግሥት፣ በሰሜኑ ክፍል ርሃብ እንዳልተከሰተ በመግለጽ፣ ድርቁን ለፖለቲካዊ ዓላማ የሚያውሉ አካላት አሉ በማለት ይከሳል።
@rt_amharic1 #የኤርትራ ውጭ ጉዳይ
የኤርትራ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር በብሪታንያ መንግሥት ላይ ያለውን ቅሬታ ለመግለጽ በአሥመራ የብሪታንያ ጉዳይ አስፈጻሚን መጥራቱን የኤርትራ መንግሥት ቃል አቀባይ የማነ ገ/መስቀል በ"ኤክስ" ገጻቸው አስታውቀዋል። የብሪታንያ ጉዳይ አስፈጻሚ ማብራሪያ እንዲሰጡና የአሥመራን ቅሬታ ለመንግሥታቸው እንዲያስተላልፉ የተጠሩት፣ የብሪታንያ ባለሥልጣናት በኤርትራ ላይ የ"ሐሰት" ውንጀላ" ማቅረብ በመቀጠላቸው እንደኾነ የማነ ገልጸዋል። ጉዳይ አስፈጻሚው የተጠሩት፣ የብሪታንያ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ደዔታ አንድሪው ሚቸል ባለፈው ሳምንት በትግራይ ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት የኤርትራ ወታደሮች ከኢትዮጵያ እንዲወጡ ስለመጠየቃቸው በተዘገበ ማግስት ነው።
@rt_amharic1 @rt_amharic1

ከዛሬ ጀምሮ ነፃ የህክምና አገልግሎት እንደሚሰጥ የቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አስታወቀ ህክምናው የሚሰጠው ከጥር 27 áŠĽáˆľáŠ¨ የካቲት 1 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ መሆኑን ሆስፒታሉ አስታውቃል። የቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዋና ሾል አስፈፃሚ ዶ/ር አብርሀም እሸቱ ለብስራት ሬድዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት ህክምናው የሚሰጠው ከግብፅ ኮፕቲክ ሚሽነሪ ከተባለ ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ከአሜሪካን ሀገር በመጡ የህክምና ባለሙያዎች ነው። የነፃ ህክምና የሚሰጥባቸው የህክምና ዓይነቶች የውስጥ ደዌ  ፣ የህፃናት ፣ የጥርስ ፣ የልብ፣ የቆዳና አባላዘር ህክምና እና የፕላስቲክ ቀዶ-ህክምና አገልግሎቶች መሆናቸውም ተገልፃል። በመሆኑም የነፃ ህክምና ማግኘት የምትፈልጉ ታካሚዎች በተጠቀሱት ቀናት በሆስፒታሉ በመገኘት የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ሆስፒታሉ አስታውቃል።

በርካታ የፌደራልና ክልል መንግሥታት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ትናንት በአማራ ክልል 15 ከተሞች ከሕዝቡ ጋር ውይይት አድርገዋል። #በባሕርዳር፣# ጎንደር፣ #ፍኖተሰላም፣ #ደብረታቦር፣ #ሰቆጣና ሌሎች ከተሞች የተካሄዱትን ውይይቶች ከመሩት ባለሥልጣናት መካከል፣ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሺመልስ አብዲሳ፣ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፋ ኡመር፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ተጠሪ ተስፋይ በልጅጌ፣ የገንዘብ ሚንስትር አሕመድ ሽዴና የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ይገኙበታል። ውይይቶቹ "ሕብረ ብሄራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነት ለዘላቂ ሰላምና ኹለንተናዊ ብልጽግና" በሚል ርዕስ የተካሄዱት፣ የክልሉን ሕዝብ ችግሮች ለመረዳትና የመፍትሄ ሃሳቦችን ለመስማት እንደኾነ ተገልጧል። ባለሥልጣናቱ፣ የአማራን ሕዝብ ጥያቄ በነፍጥ ማሳካት እንደማይቻል በውይይቶቹ ላይ አጽንዖት ሰጥተው ተናግረዋል።

የዲሲ ድልድይ 💚💛❤️ ዛሬ የጥቁሮችን ወርን በማስመልከት ኢትዮጵያ ለጥቁሮች ነጻነት የከፈለችውን ዋጋ ለመዘከር እንዲህ እንደምታዩት የዲሲ ድልድይ በአረንጏዴ ቢጫና ቀይ ቀለም አሸብርቋል።
የዲሲ ድልድይ 💚💛❤️ ዛሬ የጥቁሮችን ወርን  በማስመልከት ኢትዮጵያ ለጥቁሮች ነጻነት የከፈለችውን ዋጋ ለመዘከር  እንዲህ እንደምታዩት የዲሲ ድልድይ  በአረንጏዴ ቢጫና ቀይ ቀለም አሸብርቋል።

የናሚቢያ ፕሬዚዳንት ሀጌ ጌንጎብ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ! የናሚቢያ ፕሬዚዳንት ሀጌ ጌንጎብ፣ በካንሰር መጠቃታቸው ከታወቀ በሳምንታት በኋላ፣ በ82 ዓመታቸው በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተ
የናሚቢያ ፕሬዚዳንት ሀጌ ጌንጎብ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ! የናሚቢያ ፕሬዚዳንት ሀጌ ጌንጎብ፣ በካንሰር መጠቃታቸው ከታወቀ በሳምንታት በኋላ፣ በ82 ዓመታቸው በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። እኤአ ከ2015 ጀምሮ አፍሪካዊቷን ሀገር ናሚቢያን በፕሬዚዳንትነት ሲመሩ የቆዩት ጌንጎብ፤ ያኔ ወደ ስልጣን በመጡበት ወቅት ከፕሮስቴት ካንሰር ማገገም መቻላቸውን ገልፀው ነበር። ከ10 ቀናት በፊት ፕሬዚዳንቱ ለልዩ የካንሰር ሕክምና ወደ አሜሪካ ማቅናታቸውን የፕሬዚዳንቱ ጽሕፈት ቤት መግለፁ ይታወሳል። ፕሬዚዳንቱ በአሜሪካ የ2 ቀናት ልዩ ሕክምናቸውን በማጠናቀቅ ባለፈው ረቡዕ ወደ ሀገራቸው ተመልሰው ነበር። ፕሬዚዳንቱ በዊንድሆክ በሚገኝ ሆስፒታል ሕክምና በማድረግ ላይ ሳሉ ሕይወታቸው አልፏል። የፕሬዚዳንት ሀጌ ጌንጎብን ሕልፈት ተከትሎ በዓመቱ መጨረሻ ፕሬዚዳንታዊ እና ፓርላሜንታዊ ምርጫ እስኪካሄድ ድረስ ምክትል ፕሬዚዳንት ናንጎሎ ምቡምባ ፕሬዚዳንቱን ተክተው ናሚቢያን እንደሚያስተዳድሩ የሮይተርስ ዘገባ ያመለክታል።

እቴጌ ጣይቱ በደብረ ታቦር ከተማ አሥተዳደር ሐውልት ቆመላቸዉ የዓድዋ ጀግናዋ ንግሥት እቴጌ ጣይቱ በደብረ ታቦር ከተማ አሥተዳደር ሐውልት ቆሞላቸዋል። የሐውልት አሠሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ ቄስ መልካሙ ላቀው
እቴጌ ጣይቱ በደብረ ታቦር ከተማ አሥተዳደር ሐውልት ቆመላቸዉ የዓድዋ ጀግናዋ ንግሥት እቴጌ ጣይቱ በደብረ ታቦር ከተማ አሥተዳደር ሐውልት ቆሞላቸዋል። የሐውልት አሠሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ ቄስ መልካሙ ላቀው ሾመ ጥር የኾኑ ጀግኖችን መዘከር፣ ለተተኪው ትውልድ ታሪክን ለማስተማር ይረዳል ነው ያሉት። ለእቴጌ ጣይቱ ሐውልት ማቆም ትውልድን ማስተማር፣ ታሪክን ማክበር ነው ብለዋል። ገድላቸውን መዘከር ስላስፈለገ ከተማዋን የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ እና በእቴጌ ታሪክ ትውልድን ለማስተማር መኾኑን አንስተዋል።  የካቲት 23/2015 ዓ.ም የመሠረተ ድንጋዩ የተቀመጠለት ሐውልቱ ጥር 25 /2016 ዓ.ም ተመርቋል። ሐውልቱን በልደታቸው ነሐሴ 12 ቀን ለማስመረቅ ታስቦ እንደነበር እና በጸጥታ ችግር ምክንያት መቆየቱም ተመላክቷል። ሐውልቱ በከተማዋ ነዋሪዎች እና በመንግሥት በጋራ የተሠራ ነው መኾኑም ተገልጿል። Via አሚኮ