Ikhlas Institute
Open in Telegram
بِسْـــــــــــــمِ اللهِ الرَّحْمَنِ الرَّحِـــــــــــــيم إِنَّمَا الْمُؤْمِنُونَ الَّذِينَ إِذَا ذُكِرَ اللَّهُ وَجِلَتْ قُلُوبُهُمْ وَإِذَا تُلِيَتْ عَلَيْهِمْ آيَاتُهُ زَادَتْهُمْ إِيمَانًا وَعَلَىٰ رَبِّهِمْ يَتَوَكَّلُون For any contact @Nur_a01
Show more2 023
Subscribers
-224 hours
No data7 days
-2130 days
Posts Archive
2 023
💭ሙስዐብ ኢብኑ ዑመይር (ረዲየላሁ ዐንሁ) የህይወት ታሪክ
ከመካ ቅንጦት እስከ ኡሑድ ሸሂድነት🥀
#ክፍል 3(ሦስት)
የሙስዐብ ኢብኑ ዑመይር (ረዲየላሁ ዐንሁ) የዳዕዋ ሥራ በየስሪብ በፍጥነት እየተስፋፋ ሄደ። በእርሳቸው ጥረትና በአላህ ፈቃድ ብዙ ሰዎች ወደ ኢስላም ገቡ።
የአውስና የኸዝረጅ ጎሳዎች መካከል የኢስላም መልእክት ተስፋፋ። የሙስዐብ መልካም ባህሪ፣ ጥበብና የቁርአን ትምህርት በሰዎች ልብ ላይ ታላቅ ተፅዕኖ አሳደረ።
በዚያን ጊዜ የየስሪብ ሙስሊሞች ከነቢዩ ﷺ ጋር ለመገናኘት ወደ መካ መጡ። ከነቢዩ ﷺ ጋር በዐቀባህ ተራራ አካባቢ በምስጢር ተገናኙ።
በዚህ ስብሰባ የየስሪብ ሰዎች ኢስላምን እንደሚጠብቁና ለአላህና ለመልእክተኛው ﷺ ታማኞች እንደሚሆኑ ቃል ገቡ።
ይህ በኢስላም ታሪክ የዐቀባህ ቃል ኪዳን ተብሎ የሚታወቅ ታላቅ ክስተት ነበር።
ከዚያም በኋላ የየስሪብ ሰዎች ለነቢዩ ﷺ እና ለሙስሊሞች መጠጊያ እንዲሆኑ ተዘጋጁ። የኢስላም መልእክት በየስሪብ ውስጥ ከቤት ወደ ቤት መድረስ ጀመረ።
ሙስዐብ (ረዲየላሁ ዐንሁ) የተሰጣቸውን ተልዕኮ በታማኝነት አከናውነዋል። ከመካ የነበራቸውን ቅንጦትና ምቾት ትተው፣ ለኢስላም መስፋፋት ሕይወታቸውን ሰጡ።
እንዲሁም በየስሪብ የኢስላም መሠረት እንዲጠነክር ትልቅ ሚና ተጫውተዋል። በሙስዐብ ጥረት የየስሪብ ከተማ ለነቢዩ ﷺ ሂጅራ ዝግጁ መሆን ጀመረች።
ነገር ግን የሙስዐብ ሕይወት ውስጥ ገና ታላቅ ፈተና ይጠብቃቸው ነበር…
ከነቢዩ ﷺ ሂጅራ በኋላ ሙስዐብ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ከሙስሊሞች ጋር በብዙ ክስተቶች ተሳትፈዋል። በተለይም በኡሑድ ጦርነት ያሳዩት ጀግንነትና መስዋዕትነት ለዘላለም የሚታወስ ሆነ…
➡️ በቀጣዩና በመጨረሻው ክፍል፣ የኡሑድ ጦርነትና የሙስዐብ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ሸሂድነት እናያለን… 🥀
➡️ ክፍል 4 (የመጨረሻው) ይቀጥላል…
@ikhlasikhlas1
@ikhlasikhlas2
2 023
❤️🩹
እነዛ ብዙ ኪሎ ግራም የሚመዝኑትን በሮች ብቻውን ገነጣጥሎ የጣላቸው አሊ.... የልቡን ፍቅር የፋጢማን ጀናዛ ሲሸከም ግን አግዙኝ አለ 💨
እና ምን መሰላችሁ
.
.
የልብ ህመም ቀላል አይደለም. . . .
@ikhlasikhlas1
@ikhlasikhlas2
2 023
❋ ረሱል እንዲህ ብለዋል﴿
من لم يشكرِ القليلَ
لم يشكرِ الكثيرَ،
ومن لم يشكرِ الناسَ، لم يشكرِ اللهَ، والتحدُّثُ بنعمةِ اللهِ شكرٌ، وتركُها كفرٌ، والجماعةُ رحمةٌ، والفُرقةُ عذابٌ ﴾
𑁍 “በጥቂቱ የማያመሰግን በብዙ አያመሰግንም፣ ሰዎችን የማያመሰግን አላህን አያመሰግንም፣ አላህ የዋላቸውን ውለታዎች (ፀጋዎች) ማውራት ምስጋና ነው፣ እሱን መተው ክህደት ነው፣ ህብረት (አንድነት) እዝነት ሲሆን መለያየት ደግሞ ቅጣት ነው።”
ሶሂህ አተርጊብ፡ 986
.
.
.
@ikhlasikhlas1
@ikhlasikhlas12 023
ولربما تأتي المسرة بغتةً وتراك تنسى كل أيام الألم ثق بالذي أعطاك قلباً طيباً ستطيب دنيانا وتزدحم النعم@ikhlasikhlas1 @ikhlasikhlas2
2 023
የሰው ልጅ ልብ ከአላህ ሲርቅ፣ የዱንያ ምቾትና ውበት ሁሉ ቢጎናጸፍ እንኳን፣ ውስጣዊ እርካታን ያጣል፤ በውስጡ ያለውም ባዶነት አይሞላም።
﴿ أَلَا بِذِكْرِ اللَّهِ تَطْمَئِنُّ الْقُلُوبُ ﴾ “እወቁ! ልቦች በአላህ ዚክር ይረጋጋሉ።” ሱረቱ አር-ረዕድ 13፥28ወደ አላህ ተመለስ፤ ልብህ የናፈቀውን እውነተኛ ሰላምና እረፍት በእርሱ ዘንድ ታገኛለህ። @ikhlasikhlas1 @ikhlasikhlas2
2 023
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته 🤍
Telegram ፕርሚየም ተጠቃሚ የሆናችሁ ውድ ወንድምና እህቶች፣ ይህንን ሊንክ በመጫን Boost በማድረግ ድጋፋችሁን እንድታደርጉልን በአክብሮት እንጠይቃለን። 🤍
ለምታደርጉልን ድጋፍ አላህ ይክፈላችሁ።🌷 https://t.me/boost/ikhlasikhlas1
2 023
💭🪷
في يومِ الجُمُعَة
أَكْثرُوا مِنَ الصَّلَاةِ عَلَى النَّبِيِّ ﷺ، وَاقْرَؤُ سُورَة الْكَهْفِ، وَاغْتَنِمُوا سَاعَةَ الإِجَابَة بِالدُّعَاءِ
اللهم صل وسلم على نبينا وحبيبنا محمد 🗯@ikhlasikhlas1 @ikhlasikhlas2
2 023
.
.
واتقِ اللهَ، فتقوى اللهِ ما
جاورتْ قلبَ امرئٍ إلا وصلْ.......🪐💭
@ikhalsikhla1
@ikhlasikhlas2
2 023
💭🌷
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿مَن قال: سُبْحانَ اللَّهِ وبِحَمْدِهِ، في يَومٍ مِائَةَ مَرَّةٍ؛ حُطَّتْ خَطاياهُ وإنْ كانَتْ مِثْلَ زَبَدِ البَحْرِ.﴾
“በቀን ውስጥ መቶ ጊዜ ሱብሓነላሂ ወቢሐምዲህ ያለ ሰው ሃጢያቶቹ ይረግፉለታል፤ እንደ ባህር አረፋ የበዛ ቢሆኑ እንኳ።”
📚 ቡኻሪ ዘግበውታል፡ 6405
@ikhlasikhlas1
@ikhlasikhlas2
2 023
💭ጠቃሚና አሪፍ ቻናል ልናስተዋውቃችሁ ወደናል!
......
በዚህ ቻናል ጠቃሚና ማራኪ ይዘቶች ያሏቸው ነገሮችን ታገኛላችሁ።
ቻናላቸውን ተቀላቀሉ....! 👇👇
[[[[[ @al_Fattah1 ]]]]]]]]]]]
2 023
..🗯🫥
አንድ ወንድ የሚለብስሽ ዘውድ ሁኚ ስትባል እምቢ ብላ ብዙ ወንዶች የሚለብሷት ጫማ ሆነች!
ለገባው ብቻ🙌
@ikhlasikhlas1
@ikhlasikhlas2
2 023
💭🌷
ኸሊፋው ዑመር (ረዲየሏሁ ዐንሁ) እንዲህ ብለዋል፦
➣እኔ ሁሉንም ዓይነት ጓደኞች አይቻለሁ፤ ነገር ግን ምላስን ከመጠበቅ የበለጠ ጓደኛ አላገኘሁም።
➣እኔ ሁሉንም ዓይነት ልብሶች አይቻለሁ፤ ነገር ግን ከተቅዋ የበለጠ ልብሶችን አላገኘሁም።
➣እኔ ሁሉንም ዓይነት ሀብት አይቻለሁ፤ ነገር ግን ከመብቃቃት የበለጠ ሀብት አላገኘሁም።
➣እኔ ሁሉንም ዓይነት መልካም ስራዎች አይቻለሁ፤ ነገር ግን መልካም ምክር ከመስጠት የበለጠ መልካም ስራ አላገኘሁም።
➣እኔ ሁሉንም ዓይነት ምግብ አይቻለሁ፤ ነገር ግን እኔ ከትዕግስት የበለጠ ጣፋጭ ምግብን አላገኘሁም።
@ikhlasikhlas1
@ikhlasikhlas2
