en
Feedback
ኢየሱስ

ኢየሱስ

Open in Telegram
311
Subscribers
No data24 hours
-27 days
No data30 days
Posts Archive
#የቃሉን_ወተት_ተመኙ ውድ ወንድሞቼ የጌታ ፀጋ ይብዛላችሁ! Our basic need are only Jesus !! የምንለብሰው ክርስቶስን ከሆነ ሮሜ 13፤14 የምንጠጣው ክርስቶስን ከሆነ ዮሐ 6፥54-56 የምንበላው ክርስቶስን ከሆነ የሐ 6፥32-36 መኖራችን በክርስቶስ ከሆነ ዮሐ 15፥4-6 ታድያ ለምንድነው ምንጨነቀው??አትጨነቁ አባታችሁ ያውቃል ብለዋልና ማቴ 6፥32 ስለዚህ ማስብ ያለብን ስለፅድቅ መንግስት ነው መፀለይ ያለብን ስለፅድቅ መንግሥት ነዉ መማርም ያለብን ስለ ፅድቅ መንግሥት ነዉ መዘመር ያለብን ሰለ ፅድቅ መንግሥት ነዉ ሁሉም ነገረ ፅድቅ መንግሥት መሆን አለበት ። እግዘብሔር ይህንን ሕይወት ያኖረን አሜን። ተባርኳቸዋል!!! እየሱስ ጌታ ነዉ !!!           🔆ሁለም ስለ ኢየሱስ ሁሉም ለኢየሱስ 🔆 ♡ㅤ      ❍ㅤ      ⎙        ⌲ ˡᶦᵏᵉ   ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ    ˢᵃᵛᵉ     ˢʰᵃʳᵉ ◈◈◈◈👇ይ🀄️ላ🀄️ሉን◈◈◈◈◈◈◈    📖  @biblereading7    📖  @biblereading7 ◈◈◈◈◈👆ይ🀄️ላ🀄️ሉን ◈◈◈◈◈◈ #እኛ_ግን_የተሰቀለውን_ክርስቶስን_እንሰብካለን

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ ኤፌሶን 3 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁴-¹⁵ ስለዚህ ምክንያት በሰማይና በምድር ያለ አባትነት ሁሉ ከሚሰየምበት ከአብ ፊት እንበረከካለሁ፤ ¹⁶-¹⁷ በመንፈሱ በውስጥ ሰውነታችሁ በኃይል እንድትጠነክሩ ክርስቶስም በልባችሁ በእምነት እንዲኖር እንደ ክብሩ ባለ ጠግነት መጠን ይስጣችሁ፤ የእናንተ ሥርና መሠረት በፍቅር ይጸና ዘንድ፥ ¹⁸-¹⁹ ከቅዱሳን ሁሉ ጋር ስፋቱና ርዝመቱ ከፍታውም ጥልቅነቱም ምን ያህል መሆኑን ለማስተዋል፥ ከመታወቅም የሚያልፈውን የክርስቶስን ፍቅር ለማወቅ ትበረቱ ዘንድ፥ እስከ እግዚአብሔርም ፍጹም ሙላት ደርሳችሁ ትሞሉ ዘንድ። ²⁰ እንግዲህ በእኛ እንደሚሠራው ኃይል መጠን ከምንለምነው ወይም ከምናስበው ሁሉ ይልቅ እጅግ አብልጦ ሊያደርግ ለሚቻለው፥ ²¹ ለእርሱ በቤተ ክርስቲያን በክርስቶስ ኢየሱስ እስከ ትውልዶች ሁሉ ከዘላለም እስከ ዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን።

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ ዮሐንስ 15 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ፤ ገበሬውም አባቴ ነው። ² ፍሬ የማያፈራውን በእኔ ያለውን ቅርንጫፍ ሁሉ ያስወግደዋል፤ ፍሬ የሚያፈራውንም ሁሉ አብዝቶ እንዲያፈራ ያጠራዋል። ³ እናንተ ስለ ነገርኋችሁ ቃል አሁን ንጹሐን ናችሁ፤ ⁴ በእኔ ኑሩ እኔም በእናንተ። ቅርንጫፍ በወይኑ ግንድ ባይኖር ከራሱ ፍሬ ሊያፈራ እንዳይቻለው፥ እንዲሁ እናንተ ደግሞ በእኔ ባትኖሩ አትችሉም። ⁵ እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ። ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉምና በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ፥ እርሱ ብዙ ፍሬ ያፈራል። ⁶ በእኔ የማይኖር ቢሆን እንደ ቅርንጫፍ ወደ ውጭ ይጣላል ይደርቅማል፤ እነርሱንም ሰብስበው ወደ እሳት ይጥሉአቸዋል፥ ያቃጥሉአቸውማል። ⁷ በእኔ ብትኖሩ ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ የምትወዱትን ሁሉ ለምኑ ይሆንላችሁማል። ⁸ ብዙ ፍሬ ብታፈሩና ደቀ መዛሙርቴ ብትሆኑ በዚህ አባቴ ይከበራል።

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ ተዉ! ግዴላችሁም ተዉ! የዝና ግልድም የእኔነት ግልድም የንዋይ ግልድም የቁስ ግልድም እያለበሳችሁ ነፍሳችሁን አታጎሳቁሉአት! ኢየሱስ ያላረካት ነፍስ ግልድም አያረካትም:: ክብርም ባለጠግነትም እርካታም ህይወትም የሆነውን ኢየሱስን አልብሱአት!! ያኔ እፎይ ብላ በህያዋን ምድር ታድራለች:: ህይወትና ህይወት በሆነው በኢየሱስ!!!           🔆ሁለም ስለ ኢየሱስ ሁሉም ለኢየሱስ 🔆 ♡ㅤ      ❍ㅤ      ⎙        ⌲ ˡᶦᵏᵉ   ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ    ˢᵃᵛᵉ     ˢʰᵃʳᵉ ◈◈◈◈👇ይ🀄️ላ🀄️ሉን◈◈◈◈◈◈◈    📖  @biblereading7    📖  @biblereading7 ◈◈◈◈◈👆ይ🀄️ላ🀄️ሉን ◈◈◈◈◈◈ #እኛ_ግን_የተሰቀለውን_ክርስቶስን_እንሰብካለን

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ መመስከር መመስከር ማለት በጥሬው ሲተረጎም ያዩትን የሆነውን የደረሰውን መናገር ማለት ነው። አንድ ሰው ለምስክርነት ሲቆም የሚምለው “እውነትን ብቻና እውነትን በሙሉ እናገራለሁ” ብሎ ነው። በክርስትና አተረጓጎም ደግሞ መመስከር ማለት ወንጌልን ማብሰር ማለት ነው። ወንጌል (evangellion) የግሪክ ቃል ሲሆን በአማርኛ ትርጓሜው የምስራች ማለት ነው። ወንጌልን የምስራች ያደረገው ዋና ነገር ሰው ከእግዚአብሔር ጋር ተጣልቶ ከተለያየ በኋላ ነው። በአዲስ ኪዳን እንደምናገኘው ይህ የምስራች በጌታችን  በኢየሱስ የመስቀል ላይ ሞት ኃጢአተኞች መዳንንና የዘላለም ህይወትን ማግኘታቸው ነው። አንድ ክርስቲያን ሲመሰክር ማጋነንም ሆነ ከእውነቱ መቀነስ አይገባውም። መመስከር ደግሞ ለመርታት መከራከር ማለት አይደለም። አንድ ክርስቲያን ጌታ ያደረገለትን ነገር ለሌሎች ሲናገር በተለይም የጌታን አዳኝነትና በጌታ ያገኘውን ይህን ደኅንነት ለሌላ ላልዳነ ሰው ሲናገር ያ መመስከር ይባላል። ጴጥሮስና ዮሃንስ ተዝቶባቸው በኢየሱስ ስም ከቶ እንዳይናገሩ ሲነገራቸው የተናገሩት እኛስ ያየነውንና የሰማነውን ከመናገር ዝም ማለት አንችልም።” ብለው ነበር (ሐዋ.4፡20)። ለምንድነው? መመስከር ያስፈለገው? ጥቂት ዋና ዋና ምክንያቶችን እንመልከት፦ ሰዎች ክርስቶስን ሊያውቁ የሚችሉበት ምስክርነት ብቻ ነው። ሰዎች የሚድኑት በጌታ በማመን ብቻ ከሆነ ይህን ጌታ ማወቅ አለባቸው (ሮሜ.10፡13-14) የዳንን ሌሎችም ድነው እኛ ያገኘነውን በረከት እንዲያገኙ እንመኛለን፤ በዮሐ4፡35-52 ሁለት ሰዎች ለሌሎች ሁለት ሰዎች እንዴት እንደመሰከሩ እናገኛለን። በዮሐ 4 ደግሞ አንዲት ሌላ ሴት እናያለን። ያገኙትን መናገር የታማኝነት መለኪያ ነውና፤ በመመስከር እምነታችንና መንፈሳዊ ህይወታችን ያድጋል። እንድንመሰክር ታዝዘናል (ማቴ 28፡19-20፣ ማር 16፡15፣ ሐዋ 1፡8) መመስከር ደግሞ የታደልንበት መጠራታችን አንድ ዓላማም ነው (1ጴጥ 2፡9-10)። የምንመሰክረውስ ለማን ነው? እግዚአብሔር ሰዎች ሁሉ ይድኑ ዘንድ ይወድዳል። ስለዚህ ያልዳኑ ሁሉ ሊመሰከርላቸው ይገባል ማለት ነው። እኛ ለመመስከር በተዘጋጀንና በተመኘን መጠን እግዚአብሔርም የምንመሰክርላቸውን ሰዎች ያጋጥመናል፤እነዚህ ሰዎች ቤተሰብ፣ጓደኛና ወዳጆች፣የስራ ባልደረቦች፣ለትንሽ ጊዜ የምንተዋወቃቸው ሰዎች ወይም በመንገድ ላይ የምናገኛቸው የማንተዋወቃቸው ሰዎች ሊሆኑ ይችላሉ። የምንመሰክረውስ እንዴት ነው ልንል እንችላለን? ወንጌልን በሁለት መንገዶች ነው ማስተላለፍ የምንችለው፦ የመጀመሪያው የህይወታችን ምስክርነት ነው፤ በመልካም እግዚአብሔር መታየትና መክበር አለበት (ማቴ.5፡16)። አኗኗራችን፣ አመለካከታችንና ለነገሮች የምንሰጠው ግምትና ክብደት ከሌሎች ክርስቲያን ካልሆኑ ሰዎች የተለየ መሆኑ ማንነታችንን ያሳያል (1ጴጥ.2፡12)። ህይወታችን ድምጽ አልባ መስካሪ ነው። በህይወት መመስከር አስፈላጊ ቢሆንም ይህ ብቻውን ግን በቂ አይደለም። ሁለተኛው መንገድ በአንደበታችንም የጌታን አዳኝነት መናገር አለብን። በህይወታችን የምናረጋግጠው በቃላችን የተናገርነውን ነው። ስለዚህ አንደበታችን  በጎንውን ለመናገር ሁሌም የተከፈተ መሆን አለበት። ጌታ “ምስክሮቼ ናችሁ” ብሎ ለምስክርነት ጠርቶናል። መልካም ምስክሮችና አስጠንቃቂዎች ልንሆን ይገባናል (ሕዝ 3፡17)። ስንመሰክር ምን ማለት ይኖርብናል? ምስክርነታችን በአንድ ቀመር ብቻ ላይ የተመሰረተ ሊሆን አይገባውም። አቀራረባችን ሊለያይ ይችላል። ነገር ግን አቀራረቡ ቢለያይም ዋና አሳቡ ተመሳሳይ ነውና ዋናው አሳብ አራት ዋና ዋና ነጥቦች እንመልከት፦ የእግዚአብሔር ፍቅርና ለሰው ልጆች ያለው ዓላማ የሰው ሁሉ ኃጢአተኛነት፣ ከእግዚአብሔር መለየትና የዚህ መለየት ዘላለማዊ ውጤት እግዚአብሔር የዕርቅ መንገድን በልጁ በክርስቶስ በኩል ማዘጋጀቱ የመታረቂያውን መንገድ ማለትም ክርስቶስን በእምነት የመቀበል አስፈላጊነት ናቸው። ምስክርነታችንን የተቀበሉትን ወደጌታ በጸሎት ልንመራቸው ይገባናል። ያልተቀበሉት ደግሞ በነሱ አስተሳሰብ ከ እኛ አሳብ ብቻ ጋር ያልተስማሙ ይመስላቸዋል። ነገር ግን እኛን ወይም የኛን አሳብ ሳይሆን ጌታ ነው ያልተቀበሉት ልንጸልይላቸው ያስፈልጋል። ምስክርነት ደግሞ ዘርን እንደመዝራት ያለ ሂደት ነውና ፍሬው እስኪታይ ድረስ ተስፋ ባለመቁረጥ ልንጠብቅና ከዚያ በኋላም ያሉትን አጋጣሚዎች ልንዋጃቸው ይገባል። ስንመሰክር መጠንቀቅ ያለብን ጉዳዮች፦ እኛ የምንመሰክር እንጂ የማንለውጥ መሆናችንን እንወቅ፤ የሚለውጥ እግዚአብሔር ብቻ ነው። በመንፈስ ቅዱስ መደገፍን መርሳት የለብንም።] የግብር ይውጣ ስራ አንስራ። “ከኔ አይቅር እንጂ” ብለን አንመስክር ከልብ ወደንና ጥፋታቸውም ተሰምቶን እንመስክርን። አንከራከር ብዙ በማይጠቅሙ ርዕሶች ላይ ብዙ ጊዜ አናባክን። አስፈላጊ በሆኑ ቦታዎች የእግዚአብሔርን ቃል እንጠቀስ፤ የእርሱ ቃል ከኛ ንግግር ይበልጥ ኃይል እንዳለው አንርሳ። የማናውቀውን ጥያቄ ቢጠይቁን ከመዘባረቅ “አላውቅም” እንበል። ያለማወቅ ሰው የመሆን አንድ ባህርይ እንጂ ነውር አይደለም። ስንመሰክር ሰባኪ ለመሆን አንሞክር። ንግግር መደማመጥም እንዳለው አንዘንጋ ታማኝ እንሁን፤ እውነተኛውን እኛነታችንን ደብቀን ሸንጋይ መልክ ይዘን አንቅረብ። በተቻለ ወደ ውስኔ ማለትም ጌታን ወደመቀበል ወይም አለመቀበል ውሳኔ መድረስ እንቻል። #እኛ_ግን_የተሰቀለውን_ክርስቶስን_እንሰብካለን

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ #ከሮቤል ሕይወት ምን እንማር?! @በመጽሐፍ ቅዱስ የበርካታ ሰዎች የሕይወት ታሪክ በመልካምም ሆነ በመጥፎ ጎኑ ቁልጭ ብሎ ተቀምጧል። ይኸው እኛ በድካማቸው እንዳንደክም በጥንካሬአቸው እንድንበረታ ለትምህርታችን ተጽፎልናል። #ለዛሬ ከሮቤል ሕይወት አንድ ሁለት ነጥቦችን እንመልከት :- @ለመሆኑ ሮቤል ማነው ? =>የያዕቆብ የበኩር ልጅ ከልያ የተወለደ ነው ። “ልያም ፀነሰች፥ ወንድ ልጅንም ወለደች፥ ስሙንም ሮቤል ብላ ጠራችው ።”   — ዘፍጥረት 29፥32 #የሮቤል #ሁለቱ #ድክመቶች:- 1ኛ-የንጽሕና(የቅድስና )ችግር ያለበት ሰው ነው ። =>“እስራኤልም በዚያች አገር በተቀመጠ ጊዜ ሮቤል ሄደ የአባቱንም ቁባት ባላን ተገናኛት፤”   — ዘፍጥረት 35፥22 =>“... ወደ #አባትህ #መኝታ #ወጥተሃልና፤ #አረከስኸውም፤ ወደ አልጋዬም ወጣ።”   — ዘፍጥረት 49፥4 2ኛ=የሮቤል ችግር #የመዋለል (በአቋም ያለመጽናት) ችግር ነው ። =>“እንደ ውኃ #የምትዋልል ነህ፤” — ዘፍጥረት 49፥4 =>“የይሳኮርም አለቆች ከዲቦራ ጋር ነበሩ፤ ይሳኮርም እንደ ባርቅ ነበረ፤ ከእግሩ በኋላ ወደ ሸለቆው ቸኰሉ፤ #በሮቤል ፈሳሾች አጠገብ #ብዙ #የልብ #ማመንታት ነበረ።”— መሳፍንት 5፥15 #ውጤቱም:- አለቅነቱን (ብኩርናውን) አሳጥቶታል። =>“የእስራኤልም በኵር የሮቤል ልጆች እነዚህ ናቸው። #እርሱ #የበኵር #ልጅ ነበረ፤ ነገር ግን የአባቱን ምንጣፍ ስላረከሰ #ብኵርናው ለእስራኤል ልጅ ለዮሴፍ ልጆች #ተሰጠ፤ ትውልዱ ግን ከብኵርና ጋር #አልተቈጠረም።”   — 1 ዜና 5፥1 =>“እንደ ውኃ የምትዋልል ነህ፤ አለቅነት ለአንተ አይሁን፤ ወደ አባትህ መኝታ ወጥተሃልና፤ አረከስኸውም፤ ወደ አልጋዬም ወጣ።”   — ዘፍጥረት 49፥4 #እኛስ የአዲስ ኪዳን አማኞች በንጽሕና ጉዳይ ምን እንድናደርግ ነው የጌታ ቃል የሚመክረን? “እንግዲህ፥ ወዳጆች ሆይ፥ የዚህ ተስፋ ቃል ካለን፥ #በእግዚአብሔር #ፍርሃት #ቅድስናን #ፍጹም #እያደረግን #ሥጋንና #መንፈስን #ከሚያረክስ #ሁሉ #ራሳችንን #እናንጻ።”— 2ኛ ቆሮ 7፥1 #በአቋምም  ወላዋይነት ጉዳይም  የጌታ ቃል እንዲህ ይመክረናል :- “ሁለት አሳብ ላለው በመንገዱም ሁሉ #ለሚወላውል ለዚያ ሰው ከጌታ ዘንድ አንዳች እንዲያገኝ አይምሰለው።” — ያዕቆብ 1፥7-8 ቃሉን በልቡናቸው ያሳድርልን። አሜን 🙏 በወ/ዊ ሄኖክ ጌታቸው (ዶ/ር)

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ ራእይ 7 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ ከዚህም በኋላ በአራቱ በምድር ማዕዘን ቆመው አራት መላእክት አየሁ፥ እነርሱም ነፋስ በምድር ቢሆን ወይም በባሕር ወይም በማንም ዛፍ እንዳይነፍስ አራቱን የምድር ነፋሳት ያዙ። ² የሕያው አምላክ ማኅተም ያለውም ሌላ መልአክ ከፀሐይ መውጫ ሲወጣ አየሁ፥ ምድርንና ባሕርንም ሊጐዱ ለተሰጣቸው ለአራቱ መላእክት በታላቅ ድምፅ እየጮኸ፦ ³ የአምላካችንን ባሪያዎች ግምባራቸውን እስክናትማቸው ድረስ ምድርን ቢሆን ወይም ባሕርን ወይም ዛፎችን አትጕዱ አላቸው። ⁴ የታተሙትንም ቍጥር ሰማሁ፤ ከእስራኤል ልጆች ነገድ ሁሉ የታተሙት መቶ አርባ አራት ሺህ ነበሩ። ⁵ ከይሁዳ ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ ታተሙ፥ ከሮቤል ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥ ከጋድ ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥ ⁶ ከአሴር ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥ ከንፍታሌም ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥ ⁷ ከምናሴ ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥ ከስምዖን ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥ ከሌዊ ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥ ከይሳኮር ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥ ⁸ ከዛብሎን ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥ ከዮሴፍ ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥ ከብንያም ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ ታተሙ። ⁹ ከዚህ በኋላ አየሁ፥ እነሆም፥ አንድ እንኳ ሊቆጥራቸው የማይችል ከሕዝብና ከነገድ ከወገንም ከቋንቋም ሁሉ እጅግ ብዙ ሰዎች ነበሩ፤ ነጭ ልብስም ለብሰው የዘንባባንም ዝንጣፊዎች በእጆቻቸው ይዘው በዙፋኑና በበጉ ፊት ቆሙ፤ ¹⁰ በታላቅም ድምፅ እየጮሁ፦ በዙፋኑ ላይ ለተቀመጠው ለአምላካችንና ለበጉ ማዳን ነው አሉ። ¹¹ መላእክቱም ሁሉ በዙፋኑና በሽማግሌዎቹ በአራቱም እንስሶቹ ዙሪያ ቆመው ነበር፤ በዙፋኑም ፊት በግምባራቸው ተደፉ፥ ለእግዚአብሔርም እየሰገዱ፦ ¹² አሜን፥ በረከትና ክብር ጥበብም ምስጋናም ውዳሴም ኃይልም ብርታትም ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ለአምላካችን ይሁን፤ አሜን አሉ። ¹³ ከሽማግሌዎቹም አንዱ ተመልሶ፦ እነዚህ ነጩን ልብስ የለበሱ እነማን ናቸው? ከወዴትስ መጡ? አለኝ። ¹⁴ እኔም፦ ጌታ ሆይ፥ አንተ ታውቃለህ አልሁት። አለኝም፦ እነዚህ ከታላቁ መከራ የመጡ ናቸው፥ ልብሳቸውንም አጥበው በበጉ ደም አነጹ። ¹⁵ ስለዚህ በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት አሉ፥ ሌሊትና ቀንም በመቅደሱ ያመልኩታል፥ በዙፋኑም ላይ የተቀመጠው በእነርሱ ላይ ያድርባቸዋል። ¹⁶ ከእንግዲህ ወዲህ አይራቡም፥ ከእንግዲህም ወዲህ አይጠሙም፥ ፀሐይም ትኵሳትም ሁሉ ከቶ አይወርድባቸውም፤ ¹⁷ በዙፋኑ መካከል ያለው በጉ እረኛቸው ይሆናልና፥ ወደ ሕይወትም ውኃ ምንጭ ይመራቸዋልና፤ እግዚአብሔርም እንባዎችን ሁሉ ከዓይናቸው ያብሳል።

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ #ባርኮት_ነው_ተቀበሉ🤲🤲 ወንድሞቼ እንድህ ብየ ሊባርካችሁ 🖐 እግዚአብሔር በእናንተ ላይ ይሳካባችሁ፣ ሰው እናንተ ጋ ሜቶ እናንተ ሳይሆን ኢየሱስን ብቻ ይጨብጡ፣ በእናንተ ውስጥ ኢየሱስ ብቻ ይታይባችሁ፣ ውላችሁ መስቀል ስር ብቻ ይሁን፣ ንግግራችሁ ወሬያችሁ ድንገት ከአፋችሁ ሚወጣው ንግግር ኢየሱስ ብቻ ይሁን፣ ኢየሱስን ካላወራችሁት ሕመም ይሰሟችሁ፣ እግዚአብሔር ዋናዬ ነው ቁምነገረ ነው ካላችሁበት ነገር እያስለቀቀ ዋናችሁና ቁምነገራችሁ ኢየሱስን ያድርግላችሁ፣ ጸልያችሁ ከእግዚአብሔር ምትቀበሉ ነገር ኢየሱስ ብቻ፣ የፀሎቶታችሁ መልስ ኢየሱስ ይሁን። አሜን አሜን አሜን 🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲           🔆ሁለም ስለ ኢየሱስ ሁሉም ለኢየሱስ 🔆 ♡ㅤ      ❍ㅤ      ⎙        ⌲ ˡᶦᵏᵉ   ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ    ˢᵃᵛᵉ     ˢʰᵃʳᵉ ◈◈◈◈👇ይ🀄️ላ🀄️ሉን◈◈◈◈◈◈◈    📖  @biblereading7    📖  @biblereading7 ◈◈◈◈◈👆ይ🀄️ላ🀄️ሉን ◈◈◈◈◈◈ #እኛ_ግን_የተሰቀለውን_ክርስቶስን_እንሰብካለን

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ ስለ ክርስቶስ “ፈቃድ” አንዳንድ አሳቦች ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ከጥንት ጀምሮ የሚነሡ ጥያቄዎች በዋናነት ከአምላክነቱ እና ከሰው-ነቱ ጋር የተያያዙ ነበሩ። ቤተ ክርስቲያን ለመጀመሪያዎቹ 500 ዓመታት በእነዚህ ጉዳዮች ዙሪያ በርካታ ጥናቶችን፣ ውይይቶችንና ሙግቶችን አድርጋ የደረሰችበት መደምደሚያ እስከ ዛሬም እንደ ጸና ነው። እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ “ፍጹም አምላክ፣ ፍጹም ሰው” የሆነ አንድ አካል (person) መሆኑ ነው። ቅዱሱ መጽሐፍም ቢሆን የሚያስተምረው ይህንኑ በመሆኑ ኦርቶዶክሳውያንም፣ ካቶሊካውያንም ሆኑ ወንጌላውያን በዚህ ያምናሉ፤ አንድ ዐይነት አገላለጥ ባይኖራቸውም። ስለዚህ ከዚህ ውጭ ያለውንም አስተምህሮ ያወግዛሉ። “ፍጹም አምላክ፣ ፍጹም ሰው” በሚለው አገላለጽ ውስጥ “ፍጹም” የሚለው ቃል “ምሉዕ” ማለት እንደሆነ መታወቅ አለበት። ይኸውም ኢየሱስ ክርስቶስ በአምላክነቱ ምሉእ፣ በሰው-ነቱም ምሉዕ፣ ማለትም ከአምላክ ባሕርይ አንዳችም ያልጎደለው፣ ከሰው-ነት ባሕርይም አንዳችም ነገር ያልጎደለው መሆኑን ያስተምራል። ጌታ ኢየሱስ በአምላክነቱ ከአብ ጋር የተካከለ ነው፤ በሰው-ነቱም ልክ እንደ እኛ ዐይነት ሰው ነው። እንግዲህ የክርስቶስ ኢየሱስ የፈቃድ ሁኔታም ከዚህ ጋር ይያያዛል። ኢየሱስ ክርስቶስ በአምላክነቱ ከአብ ጋር የተካከለ ወይም ከአምላክነት አንዳችም የማይጎድለው ከሆነ፣ መለኮታዊ ፈቃድ አለው ማለት ነው። ኢየሱስ አምላካዊ ባሕርዩ የአምላክ ፈቃድ የሌለው ከሆነ፣ ኢየሱስ አምላክነቱ ምሉዕ አይደለም ማለት ነው። ስለዚህም ከአምላክነት ይጎድላል። ነገር ግን ኢየሱስ ፍጹም አምላክ በመሆኑ፣ ከአምላክነት አንዳችም አይጎድለውም። ይህ ደግሞ ፈቃድንም እንደሚያካትት ሳይታለም የተፈታ ነው። ኢየሱስ ምሉዕ አምላክ ነውና አምላካዊ ፈቃድ አለው። ጌታ ኢየሱስ የሰው-ነት ባሕርይ በሙላት ያለው ወይም ከሰው-ነት አንዳችም የማይጎድለው በመሆኑ፣ ሰዋዊ ፈቃድም አለው። አለዚያ ምሉዕ ወይም ፍጹም ሰው ሊሆን አይችልም። የሰው ሥጋ፣ የሰው ነፍስ፣ የሰው መንፈስ፣ የሰው ሥነ ልቦና፣ . . . እንዳለው ሁሉ የሰው ፈቃድም አለው። አለዚያ ከሰው-ነት ይጎድላል። ጌታ ኢየሱስ የሰው ፈቃድ እንዳለው ቤተ ክርስቲያን የምታምነው ለዚህ ነው። ስለዚህ ጌታ ኢየሱስ በአምላክነቱ የአምላክ ፈቃድ፣ እንዲሁም በሰው-ነቱ የሰው ፈቃድ ያለው ፍጹም አምላክ፣ ፍጹም ሰው ነው። ወንጌላውያን አማኞች (ካቶሊካውያንን እና የምሥራቅ ኦርቶዶክሳውያንን ጨምሮ) ኢየሱስ ክርስቶስ ሁለት ባሕርይ እንዳለው ሲናገሩ ይህን ታሳቢ በማድረግ ነው። (ኦርየንታል ኦርቶዶክሳውያንም ጌታ ኢየሱስ አንድ ባሕርይ እንዳለው ሲያምኑ ፍጹም አምላክ፣ ፍጹም ሰው መሆኑን ሳይዘነጉ ነው።) የጥንቷ ቤተ ክርስቲያን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሁለት ፈቃድ እንዳለው እንደምታምን በ6ኛው ዓለም አቀፍ ጉባኤዋ ላይ ያሳወቀችው ርእሰ ጉዳዩ የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነትና ሰው-ነት የሚመለከት መሆኑን በመረዳት ነው። #እኛ_ግን_የተሰቀለውን_ክርስቶስን_እንሰብካለን

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ “የቅንነት ቃል እንዴት ኃይለኛ ነው!   ኢዮ 6፥25 ቃል ያክማል ቃል ያስታምማል። ቃል ይሰብራል ቃል ይሰራል። ቃል ያበግናል ቃል ያስመሰግናል። ቃል... ቃል የነበሩ ነገሮች ወደ ሁነት ይለወጣሉ። ቃል እና ዘር እንደ ዘሪው ናቸው። ቃል የሰው ልጅ ውድ ሀብት ነው። ውድ ሀብት ደግሞ በተራ ቦታ አይቀመጥም። እግዚአብሔር ለትውልድ የሚሆን የቅንነትን ቃል በልቦናዎቻችን ውስጥ አሳድሮ በአንደበቶቻችን ላይ ያኑርልን። የቅንነት ቃል የሰውን ሸፋች ልብ ይመልሳል የቅንነት ቃል ደካማውን በተስፋ ሞልቶ በሀይል ይስነሳል። እግዚአብሔር ትውልድን ወደ እርሱ የምንመልስበትን የቅንነት ቃልን ያድለን። እኛ ዘንድ ለትውልድ የሚሆን የተስፋ ቃል የቅንነት ቃል አይታጣ። #እኛ_ግን_የተሰቀለውን_ክርስቶስን_እንሰብካለን

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ 🔱🔱 ኢየሱስ ይመጣል ይወስደናል 🔱🔱 ⛩⛩ ዛሬ የተዋረደ ክርስቶስን ነው የተቀበልነው፣ ደግሞ በቅርቡ የከበረው ክርስቶስ እንወርሳለን። ደግሞ ለዘላለም ከበጉ ጋር እንሆናለን። 🔱🔱 ኢየሱስ ስመጣ ሁሉም ለእርሱ ይንበረከካሉ፣ የወጉትም ሁሉ ያዩታል፣ ደግሞ በጉ ብርሃን ወደ ሚያበራበት ከተማ አንድ ቀን እንሄዳለን።“እነሆ፥ ከደመና ጋር ይመጣል፤ ዓይንም ሁሉ የወጉትም ያዩታል፥ የምድርም ወገኖች ሁሉ ስለ እርሱ ዋይ ዋይ ይላሉ። አዎን፥ አሜን።” — ራእይ 1፥7 ⭕️⭕️ የተጠማ ቢኖር ና ይበል እንደሚልህ መጽሐፍ ጌታ ሆይ ተጠምተናል ናልን። ማራናታ ጌታ ሆይ ቶሎ ና።“መንፈሱና ሙሽራይቱም፦ ና ይላሉ። የሚሰማም፦ ና ይበል። የተጠማም ይምጣ፥ የወደደም የሕይወትን ውኃ እንዲያው ይውሰድ።” — ራእይ 22፥17 “ለከተማይቱም የእግዚአብሔር ክብር ስለሚያበራላት መብራትዋም በጉ ስለ ሆነ፥ ፀሐይ ወይም ጨረቃ እንዲያበሩላት አያስፈልጓትም ነበር።” — ራእይ 21፥23           🔆ሁለም ስለ ኢየሱስ ሁሉም ለኢየሱስ 🔆 ♡ㅤ      ❍ㅤ      ⎙        ⌲ ˡᶦᵏᵉ   ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ    ˢᵃᵛᵉ     ˢʰᵃʳᵉ ◈◈◈◈👇ይ🀄️ላ🀄️ሉን◈◈◈◈◈◈◈    📖  @biblereading7    📖  @biblereading7 ◈◈◈◈◈👆ይ🀄️ላ🀄️ሉን ◈◈◈◈◈◈ #እኛ_ግን_የተሰቀለውን_ክርስቶስን_እንሰብካለን

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ 1ኛ ዮሐንስ 5 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ ክርስቶስ ነው ብሎ በኢየሱስ የሚያምን ሁሉ ከእግዚአብሔር ተወልዶአል፥ ወላጁንም የሚወድ ሁሉ ከእርሱ የተወለደውን ደግሞ ይወዳል። ² እግዚአብሔርን ስንወድ ትእዛዛቱንም ስናደርግ የእግዚአብሔርን ልጆች እንድንወድ በዚህ እናውቃለን። ³ ትእዛዛቱን ልንጠብቅ የእግዚአብሔር ፍቅር ይህ ነውና፤ ትእዛዛቱም ከባዶች አይደሉም። ⁴ ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ዓለምን ያሸንፋልና፤ ዓለምንም የሚያሸንፈው እምነታችን ነው። ⁵ ኢየሱስም የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ከሚያምን በቀር ዓለምን የሚያሸንፍ ማን ነው? ⁶ በውኃና በደም የመጣ ይህ ነው እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ፤ በውኃውና በደሙ እንጂ በውኃው ብቻ አይደለም። ⁷ መንፈስም እውነት ነውና የሚመሰክረው መንፈስ ነው። ⁸ የሚመሰክሩት መንፈሱና ውኃው ደሙም ሦስት ናቸውና፤ ሦስቱም በአንድ ይስማማሉ።

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ ራእይ 4 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ ከዚያ በኋላም አየሁ፥ እነሆም በሰማይ የተከፈተ ደጅ፥ እንደ መለከትም ሆኖ ሲናገረኝ የሰማሁት ፊተኛው ድምፅ፦ ወደዚህ ውጣና ከዚህ በኋላ ሊሆን የሚያስፈልገውን ነገር አሳይሃለሁ አለ። ² ወዲያው በመንፈስ ነበርሁ፤ እነሆም፥ ዙፋን በሰማይ ቆሞአል በዙፋኑም ላይ ተቀማጭ ነበረ፤ ³ ተቀምጦም የነበረው በመልኩ የኢያስጲድንና የሰርዲኖን ዕንቍ ይመስል ነበር። በመልኩም መረግድን የመሰለ ቀስተ ደመና በዙፋኑ ዙሪያ ነበረ። ⁴ በዙፋኑ ዙሪያም ሀያ አራት ዙፋኖች ነበሩ፥ በዙፋኖቹም ላይ ነጭ ልብስ ለብሰው በራሳቸውም የወርቅ አክሊል ደፍተው ሀያ አራት ሽማግሌዎች ተቀምጠው ነበር። ⁵ ከዙፋኑም መብረቅና ድምፅ ነጐድጓድም ይወጣል፤ በዙፋኑም ፊት ሰባት የእሳት መብራቶች ይበሩ ነበር፥ እነርሱም ሰባቱ የእግዚአብሔር መናፍስት ናቸው። ⁶ በዙፋኑም ፊት ብርሌ የሚመስል የብርጭቆ ባሕር ነበረ። በዙፋኑም መካከል በዙፋኑም ዙሪያ፥ በፊትና በኋላ ዓይኖች የሞሉአቸው አራት እንስሶች ነበሩ። ⁷ ፊተኛውም እንስሳ አንበሳን ይመስላል፥ ሁለተኛውም እንስሳ ጥጃን ይመስላል፥ ሦስተኛውም እንስሳ እንደ ሰው ፊት ነበረው፥ አራተኛውም እንስሳ የሚበረውን ንስር ይመስላል። ⁸ አራቱም እንስሶች እያንዳንዳቸው ስድስት ክንፎች አሉአቸው፥ በዙሪያቸውና በውስጣቸውም ዓይኖች ሞልተውባቸዋል፤ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ የነበረውና ያለ የሚመጣውም ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ እያሉ ቀንና ሌሊት አያርፉም። ⁹ እንስሶቹም በዙፋን ላይ ለተቀመጠው ከዘላለምም እስከ ዘላለም በሕይወት ለሚኖረው ለእርሱ ክብርና ውዳሴ ምስጋናም በሰጡት ጊዜ፥ ¹⁰-¹¹ ሀያ አራቱ ሽማግሌዎች በዙፋን ላይ በተቀመጠው ፊት ወድቀው፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም በሕይወት ለሚኖረው እየሰገዱ፦ ጌታችንና አምላካችን ሆይ፥ አንተ ሁሉን ፈጥረሃልና ስለ ፈቃድህም ሆነዋልና ተፈጥረውማልና ክብር ውዳሴ ኃይልም ልትቀበል ይገባሃል እያሉ በዙፋኑ ፊት አክሊላቸውን ያኖራሉ።

የፊልምና መልእክት ስጽፍ ጳውሎስ የት ነበረ? @biblereading7
Anonymous voting

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ 2ኛ ጢሞቴዎስ 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እንግዲህ፥ ልጄ ሆይ፥ አንተ በክርስቶስ ኢየሱስ ባለው ጸጋ በርታ። ² ብዙ ሰዎች የመሰከሩለትን ከእኔም የሰማኸውን ሌሎችን ደግሞ ሊያስተምሩ ለሚችሉ ለታመኑ ሰዎች አደራ ስጥ። ³ እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ በጎ ወታደር ሆነህ፥ አብረኸኝ መከራ ተቀበል። ⁴ የሚዘምተው ሁሉ ለጦር ያስከተተውን ደስ ያሰኝ ዘንድ ትዳር በሚገኝበት ንግድ ራሱን አያጠላልፍም። ⁵ ደግሞም በጨዋታ የሚታገል ማንም ቢሆን፥ እንደሚገባ አድርጎ ባይታገል፥ የድሉን አክሊል አያገኝም። ⁶ የሚደክመው ገበሬ ፍሬውን ከሚበሉት መጀመሪያ እንዲሆን ይገባዋል። ⁷ የምለውን ተመልከት፤ ጌታም በነገር ሁሉ ማስተዋልን ይስጥህ።

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ ዕብራውያን 7 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ የሳሌም ንጉሥና የልዑል እግዚአብሔር ካህን የሆነ ይህ መልከ ጼዴቅ አብርሃም ነገሥታትን ገድሎ ሲመለስ ከእርሱ ጋር ተገናኝቶ ባረከው፤ ² ለእርሱም ደግሞ አብርሃም ከሁሉ አስራትን አካፈለው። የስሙም ትርጓሜ በመጀመሪያ የጽድቅ ንጉሥ ነው፥ ኋላም ደግሞ የሳሌም ንጉሥ ማለት የሰላም ንጉሥ ነው። ³ አባትና እናት የትውልድም ቍጥር የሉትም፥ ለዘመኑም ጥንት ለህይወቱም ፍጻሜ የለውም፥ ዳሩ ግን በእግዚአብሔር ልጅ ተመስሎ ለዘላለም ካህን ሆኖ ይኖራል። ⁴ የአባቶች አለቃ አብርሃም ከዘረፋው የሚሻለውን አስራት የሰጠው ይህ ሰው እንዴት ትልቅ እንደ ነበረ እስኪ ተመልከቱ። ⁵ ከሌዊ ልጆችም ክህነትን የሚቀበሉት ከህዝቡ ማለት ከወንድሞቻቸው፥ እነርሱ ምንም ከአብርሃም ወገብ ቢወጡ፥ ከእነርሱ አሥራትን በሕግ እንዲያስወጡ ትእዛዝ አላቸው፤ ⁶ ትውልዱ ከእነርሱ የማይቈጠረው ግን ከአብርሃም አሥራትን አውጥቶአል፥ የተስፋ ቃል የነበረውንም ባርኮአል። ⁷ ትንሹም በታላቁ እንዲባረክ ክርክር የሌለበት ነገር ነው። ⁸ በዚህስ የሚሞቱ ሰዎች አሥራትን ያስወጣሉ፥ በዚያ ግን የሚያስወጣ በሕይወት እንዲኖር የተመሰከረለት እርሱ ነው። ⁹ ይህንም ለማለት ሲፈቀድ፥ አሥራትን የሚያስወጣ ሌዊ እንኳ በአብርሃም እጅ አሥራትን ሰጥቶአል፤ ¹⁰ መልከ ጼዴቅ በተገናኘው ጊዜ ገና በአባቱ ወገብ ነበረና። ¹¹ እንግዲህ ህዝቡ በሌዊ ክህነት የተመሠረተን ሕግ ተቀብለዋልና በዚያ ክህነት ፍጹምነት የተገኘ ቢሆን፥ እንደ አሮን ሹመት የማይቈጠር፥ እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ግን የሆነ ሌላ ካህን ሊነሳ ወደፊት ስለ ምን ያስፈልጋል? ¹² ክህነቱ ሲለወጥ፥ ሕጉ ደግሞ ሊለወጥ የግድ ነውና። ¹³ ይህ ነገር የተነገረለት እርሱ በሌላ ወገን ተካፍሎአልና፥ ከዚያም መሠዊያውን ያገለገለ ማንም የለም፤ ¹⁴ ጌታችን ከይሁዳ ነገድ እንደወጣ የተገለጠ ነውና፥ ስለዚህም ነገድ ሙሴ ምንም እንኳ ስለ ክህነት አልተናገረም። ¹⁵-¹⁶ በማያልፍም ሕይወት ኃይል እንጂ በሥጋ ትእዛዝ ሕግ ሳይሆን ሌላ ካህን በመልከ ጼዴቅ ምሳሌ ቢነሳ፥ ይህ እጅግ አብልጦ የሚገለጥ ነው። ¹⁷ አንተ እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ለዘላለም ካህን ነህ ብሎ ይመሰክራልና። ¹⁸-¹⁹ ሕጉ ምንም ፍጹም አላደረገምና፥ ስለዚህም የምትደክም የማትጠቅምም ስለሆነች የቀደመች ትእዛዝ ተሽራለች፥ ወደ እግዚአብሔርም የምንቀርብበት የሚሻል ተስፋ ገብቶአል። ²⁰-²¹ እነርሱም ያለ መሐላ ካህናት ሆነዋልና፤ እርሱ ግን፦ ጌታ፦ አንተ እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ለዘላለም ካህን ነህ ብሎ ማለ አይጸጸትም ብሎ በተናገረለት ከመሐላ ጋር ካህን ሆኖአልና ያለ መሐላ ካህን እንዳልሆነ መጠን፥ ²² እንዲሁ ኢየሱስ ለሚሻል ኪዳን ዋስ ሆኖአል። ²³ እነርሱም እንዳይኖሩ ሞት ስለ ከለከላቸው ካህናት የሆኑት ብዙ ናቸው፤ ²⁴ እርሱ ግን ለዘላለም የሚኖር ስለሆነ የማይለወጥ ክህነት አለው፤ ²⁵ ስለ እነርሱም ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራልና ስለዚህ ደግሞ በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል። ²⁶ ቅዱስና ያለ ተንኮል ነውርም የሌለበት ከኃጢአተኞችም የተለየ ከሰማያትም ከፍ ከፍ ያለ፥ እንደዚህ ያለ ሊቀ ካህናት ይገባልና፤ ²⁷ እርሱም እንደነዚያ ሊቃነ ካህናት አስቀድሞ ስለ ራሱ ኃጢአት በኋላም ስለ ሕዝቡ ኃጢአት ዕለት ዕለት መሥዋዕትን ሊያቀርብ አያስፈልገውም፤ ራሱን ባቀረበ ጊዜ ይህን አንድ ጊዜ ፈጽሞ አድርጎአልና። ²⁸ ሕጉ ድካም ያላቸውን ሰዎች ሊቀ ካህናት አድርጎ ይሾማልና፤ ከሕግ በኋላ የመጣ የመሐላው ቃል ግን ለዘላለም ፍጹም የሆነውን ልጅ ይሾማል።

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ ከእግዚአብሔር ጋር እንዴት የጠበቀ ግንኙነት ሊኖረን ይችላል? እግዚአብሔር በሰጠው ተስፋ አማካኝነት ከእርሱ ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንዲኖረን፣ ዕድሉን ለእኛ አቅርቧል። የእግዚአብሔር ጥሪ ከእርሱ ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንዲኖረን ነው። ይህ ጥሪ ከምንም ነገር በላይ በእርሱ ላይ ያለንን እምነት የሚፈትን ነው (ያዕቆብ 1፥2-4)። የጠበቀ ግንኙነት ማዕከል ከአንድ ሰው ጋር ቅርብ የሆነ ግንኙነት አለን የምንለው፣ ያንን ሰው የእውነት ስናውቀው እና በዚያም ሰው ደግሞ ስንታወቅ ነው። ብዙ ጊዜ ይህንን ተሞክሮ ለመግለጽ፣ ከስፍራ ጋር የተያያዘ አነጋገር እንጠቀማለን። የቅርብ ጓደኛ የምንለው ሰው፣ ለልባችን ቅርብ የሆነና በጠለቀ መንገድ የሚያውቀን ሰው ነው። ከጓደኛችን ጋር ያለንን የጠበቀ ግንኙነት የሚጎዳ ነገር ከተፈጠረ ደግሞ፣ ልባችን ከዚያ ሰው ይርቃል። ወይም ለልባችን ቅርብ በሆነ መንገድ የማያውቀን ሰው፣ በጠለቀ መንገድ አያውቀንም። ነገር ግን ከሰው ጋር ያለን የጠበቀ ግንኙነት፣ በአንጻራዊ ቦታ ላይ ሳይሆን በግንኙነት ላይ የተመሠረተ ነው። ሁላችንም ከጎናችን ከተቀመጠው ሰው ልባችን ርቆ፣ ስድስት ሺህ ኪሎ ሜትር ርቆ ካለው ሰው ጋር የቀረበ ግንኙነት ሊኖረን ይችላል። ከሌላ ሰው ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንዳለን እንዲሰማን የሚያደርገው ነገር ምንድን ነው? በርግጥ በደንብ ለመቀራረብ አስፈላጊ የሆኑ የተለያዩ ነገሮች ቢኖሩም፣ ለሁሉም የጋራ የሆነው ግን እምነት ነው። ከማናምነው ሰው ጋር የጠበቀ ግንኙነት ሊኖረን አይችልም። እምነት ከሰው ጋር ላለን የጠበቀ ግንኙነት ማዕከል ነው። አንድ ሰውን ባመንነው ቁጥር፣ ይበልጥ ወደ ልባችን እናስጠጋዋለን። እምነታችን በሚሸረሸርበት ልክ ደግሞ፣ ቅርበታችንም በዚያው ልክ ይቀንሳል። ከእግዚአብሔር ጋር ላለን የቀረበ ግንኙነት ማዕከል ይህ ከሌሎች ሰዎች ጋር ባለን ግንኙነት እውነት እንደሆነ ሁሉ፣ ከእግዚአብሔር ጋር ያለን ግንኙነትም እንደዚሁ ነው። ከእግዚአብሔር ጋር አለን ብለን የምናስበው ቅርበት ወይም ርቀት፣ ከእርሱ ጋር ያለንን እውነተኛ ቅርበት አይገልጽም። ቅዱሳት መጻሕፍት፣ እግዚአብሔር ከሚያምኑት ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንዳለው ይናገራሉ። እግዚአብሔርን ይበልጥ ባመነው ቁጥር፣ ይበልጥ እናውቀዋለን። ከእግዚአብሔር የሚያርቀን፣ በእርሱ ላይ ያለንን እምነት የሚሸረሽር ነገር ነው፤ ይኽውም ኅጢአት ነው። ይህንን መረዳት እጅግ አስፈላጊ ነው። እንደ ክርስቲያን ከእግዚአብሔር ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንዲኖረን እንፈልጋለን። ከዘማሪውም ጋር አብረን እንዲህ እንላለን፦ “ለእኔ ግን ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ይሻለኛል” (መዝሙር 73፥28)። የያዕቆብን ምክር እና በምክሩ ውስጥ የሚገኘውን ተስፋ ወራሾች መሆን እንፈልጋለን። “ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ፤ እርሱም ወደ እናንተ ይቀርባል” (ያዕቆብ 4፥8)። ነገር ግን ይህንን ቅርበት በማይፈጥሩ መንገዶች እንፈልገዋለን። የጠበቀ ግንኙነት ከዕውቀት በላይ ነው አንዱ የተለመደው ስሕትተ፣ ወደ እግዚአብሔር መቅረብ የሚቻለው በዕውቀት ክምችት እንደሆነ ማሰብ ነው። በርግጥ ከእግዚአብሔር ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንዲኖረን፣ ስለ እግዚአብሔር ማወቅ ያለብን ዋና ነገሮች አሉ። ኢየሱስ እንዲህ ይላል፦ “እውነትንም ታውቃላችሁ፤ እውነትም ነፃ ያወጣችኋል” (ዮሐንስ 8፥32)። ኢየሱስ ብዙዎች የማያውቁትን እንደሚያመልኩ ይናገራል (ዮሐንስ 4፥22)።    ነገር ግን በቤተ ክርስቲያን ታሪክ፣ እንደ አሁኑ ጊዜ ሥነ መለኮታዊ ዕውቀት ለብዙ ሰዎች የተዳረሰበት ዘመን የለም። የአሜሪካ ቤተ ክርስቲያን የዚህ ዕድል ተጠቃሚ ሆናለች። በመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች፣ በጽሑፎች፣ በሚያንጹ መጻሕፍት፣ በመንፈሳዊ ፊልሞች፣ በመዝሙሮች፣ በዘጋቢ ፊልሞች፣ በተቀዱ ስብከቶች ተሞልታለች። ይህ እጅግ መልካም ነው። ለዚህም ማመስገን አለብን። ነገር ግን አሜሪካ፣ እንደ ሄኖክ አካሄዳቸውን ከእግዚአብሔር ጋር ባደረጉ እና ከእርሱም ጋር የጠበቀ ግንኙነት ባላቸው ሰዎች አልተሞላችም (ዘፍጥረት 5፥24፤ ዕብራውያን 11፥5)። ለምን? ዕውቀት እና እምነት የተለያዩ ነገሮች ናቸው። ለዚህም ነው ኢየሱስ በዘመኑ ለነበሩ፣ የላቀ ዕውቀት ለነበራቸው የሃይማኖት መሪዎች እንዲህ ያለው፦ “በእነርሱ የዘላለም ሕይወትን የምታገኙ እየመሰላችሁ፣ መጻሕፍትን ትመረምራላችሁ፤ እነዚሁ መጻሕፍት ስለ እኔ የሚመሰክሩ ናቸው፤ እናንተ ግን፣ ሕይወት እንዲኖራችሁ ወደ እኔ መምጣት አትፈልጉም” (ዮሐንስ 5፥39-40)። መጽሐፍ ቅዱሳዊ ዕውቀት፣ በእግዚአብሔር ላይ ያለንን እምነት ለመጨመር ስንጠቀመው ከወርቅ ይልቅ የከበረ ይሆናል (መዝሙር 16፥10)። ነገር ግን ይህ ዕውቀት፣ በእግዚአብሔር ላይ ያለንን እምነት ከተካ፣ ትዕቢትን ያመጣል (1ኛ ቆሮንሮስ 8፥1)። ውበት የተላበሱ ሰው ሠራሽ ልምምዶች፣ ከእግዚአብሔር ጋር የጠበቀ ግንኙነት የማያመጡት ለምንድን ነው? ሌላው የተለመደ ስሕተት፣ ከእግዚአብሔር ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንዲኖረን፣ ግላዊና ውበት የተላበሱ ሰው ሠራሽ ልምምዶችን መለማመድ ነው። ይህንን “የሕልም መስክ” አካሄድ ልንለው እንችላለን። ይህ አካሄድ (ትክክለኛውን ስፍራ እና ሁኔታ ማዘጋጀት ከቻልን) እግዚአብሔር “ይመጣል” የሚል ነው። አንዳንዶች ከእግዚአብሔር ጋር ያላቸው ግንኙነት የላቀ እና ሚስጥራዊ እንደሆነ እንዲሰማቸው ከፍ ያሉ የአምልኮ ስፍራዎችን ይመርጣሉ። ሌሎች ደግሞ ውስጣዊ ስሜቶችን ለማነሣሣት የተዘጋጁ መንፈሳዊ ኮንፍረንሶች ላይ ይሳተፋሉ። ሌሎችም ወደ እግዚአብሔር ኃይል መቅረብ፣ ወደ እግዚአብሔር መቅረብ እንደሆነ በማሰብ መንፈሳዊ ሪቫይቫል ያሳድዳሉ። እነዚህ ሁሉ እውነተኛ እምነት ካለን፣ ከእግዚአብሔር ጋር ያለንን ግንኙነት ሊያጠነክሩ ይችላሉ። ነገር ግን አንዳቸውም በራሳቸው ከእግዚአብሔር ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንዲኖረን የማድረግ አቅም የላቸውም። “እግዚአብሔር የሚደነቀው፣ በእምነታችን እንጂ ባስመዘገብነው ድል አይደለም።” እንዲህ ብላችሁ አስቡ፦ በሻማ የታጀበ የራት ግብዣ እና የፍቅር ሙዚቃ፣ በባልና በሚስት መካከል ያለውን ግንኙነት ሊያጠነክር ይችላል። ነገር ግን ይህ ሊሆን የሚችለው በሁለቱም መካከል የጋራ መተማመን እና ፍቅር ካለ ብቻ ነው። በመካከላቸው አለመተማመን ካለ ግን የቦታው ውበት በመካከላቸው ያለውን ክፍተት ሊሞላ አይችልም። የዚህ ብቸኛው አማራጭ፣ እምነትን ወደነበረበት ስፍራ መመለስ ብቻ ነው። ወደ እግዚአብሔር እንዴት እንቅረብ? ወደ እግዚአብሔር የምንቀርብበት እና እርሱም ወደ እኛ የሚቀርብበት ምስጢር በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ በግልጽ ተቀምጦልናል። ወደ  እግዚአብሔር ልንቀርብ የምንችለው በእምነት በኩል፣ በክርስቶስ ወደ እግዚአብሔር ስንጠጋ ብቻ ነው (ዕብራውያን 4፥14-16፣ 7፥25፤ ፊልጵስዩስ 3፥9)። በክርስቶስ ስለምናገኘው “እጅግ ታላቅና ክቡር የሆነውን ተስፋ” እንተማመናለን (2ኛ ጴጥሮስ 1፥4፤ 2ኛ ቆሮንቶስ 1፥20)። እግዚአብሔር የሚደነቀው፣ በእምነታችን እንጂ ባስመዘገብነው ድል አይደለም። እምነታችን በሚጎድልበት ስፍራ እግዚአብሔር በዕውቀታችን ብዛት እና በምናዘጋጀው ውብ ስፍራዎች አይደሰትም።           🔆ሁለም ስለ ኢየሱስ ሁሉም ለኢየሱስ 🔆 ♡ㅤ      ❍ㅤ      ⎙        ⌲ ˡᶦᵏᵉ   ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ    ˢᵃᵛᵉ     ˢʰᵃʳᵉ ◈◈◈◈👇ይ🀄️ላ🀄️ሉን◈◈◈◈◈◈◈    📖  @biblereading7    📖  @biblereading7 ◈◈◈◈◈👆ይ🀄️ላ🀄️ሉን ◈◈◈◈◈◈

ሙሴ ከነአንን እንዲሰልሉ ስንት ሰላዮች ነው የላከው? @biblereading7
Anonymous voting

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ ራእይ 5 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ በዙፋኑ ላይም በተቀመጠው በቀኝ እጁ ላይ በውስጥና በኋላ የተጻፈበት በሰባትም ማኅተም የተዘጋ መጽሐፍን አየሁ። ² ብርቱም መልአክ፦ መጽሐፉን ይዘረጋ ዘንድ ማኅተሞቹንም ይፈታ ዘንድ የሚገባው ማን ነው? ብሎ በታላቅ ድምፅ ሲያውጅ አየሁ። ³ በሰማይም ቢሆን በምድርም ላይ ቢሆን ከምድርም በታች ቢሆን መጽሐፉን ሊዘረጋ ወይም ሊመለከተው ማንም አልተቻለውም። ⁴ መጽሐፉን ሊዘረጋ ወይም ሊመለከተው የሚገባው ማንም ስላልተገኘ እጅግ አለቀስሁ። ⁵ ከሽማግሌዎቹም አንዱ፦ አታልቅስ፤ እነሆ፥ ከይሁዳ ነገድ የሆነው አንበሳ እርሱም የዳዊት ሥር መጽሐፉን ይዘረጋ ዘንድ ሰባቱንም ማኅተም ይፈታ ዘንድ ድል ነሥቶአል አለኝ። ⁶ በዙፋኑና በአራቱ እንስሶች መካከልም በሽማግሌዎችም መካከል እንደ ታረደ በግ ቆሞ አየሁ፥ ሰባትም ቀንዶችና ሰባት ዓይኖች ነበሩት እነርሱም ወደ ምድር ሁሉ የተላኩ የእግዚአብሔር መናፍስት ናቸው። ⁷ መጥቶም በዙፋን ላይ ከተቀመጠ ከዚያ ከቀኝ እጁ መጽሐፉን ወሰደው። ⁸ መጽሐፉንም በወሰደ ጊዜ አራቱ እንስሶችና ሀያ አራቱ ሽማግሌዎች በበጉ ፊት ወደቁ፥ እያንዳንዳቸውም በገናንና የቅዱሳን ጸሎት የሆነ ዕጣን የሞላበትን የወርቅ ዕቃ ያዙ። ⁹-¹⁰ መጽሐፉን ትወስድ ዘንድ ማኅተሞቹንም ትፈታ ዘንድ ይገባሃል፥ ታርደሃልና፥ በደምህም ለእግዚአብሔር ከነገድ ሁሉ ከቋንቋም ሁሉ ከወገንም ሁሉ ከሕዝብም ሁሉ ሰዎችን ዋጅተህ ለአምላካችን መንግሥትና ካህናት ይሆኑ ዘንድ አደረግሃቸው፥ በምድርም ላይ ይነግሣሉ እያሉ አዲስን ቅኔ ይዘምራሉ። ¹¹ አየሁም፥ በዙፋኑም በእንስሶቹም በሽማግሌዎቹም ዙሪያ የብዙ መላእክትን ድምፅ ሰማሁ፤ ቍጥራቸውም አእላፋት ጊዜ አእላፋትና ሺህ ጊዜ ሺህ ነበር፥ ¹² በታላቅም ድምፅ፦ የታረደው በግ ኃይልና ባለ ጠግነት ጥበብም ብርታትም ክብርም ምስጋናም በረከትም ሊቀበል ይገባዋል አሉ። ¹³ በሰማይና በምድርም ከምድርም በታች በባሕርም ላይ ያለ ፍጥረት ሁሉ በእነርሱም ውስጥ ያለ ሁሉ፦ በረከትና ክብር ምስጋናም ኃይልም ከዘላለም እስከ ዘላለም በዙፋኑ ላይ ለተቀመጠው፥ ለበጉም ይሁን ሲሉ ሰማሁ። ¹⁴ አራቱም እንስሶች፦ አሜን አሉ፥ ሽማግሌዎቹም ወድቀው ሰገዱ።

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ ዕብራውያን 11 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹³ እነዚህ ሁሉ አምነው ሞቱ፥ የተሰጣቸውን የተስፋ ቃል አላገኙምና፤ ዳሩ ግን ከሩቅ ሆነው አዩትና ተሳለሙት፥ በምድሪቱም እንግዶችና መጻተኞች እንዲሆኑ ታመኑ። ¹⁴ እንዲህ የሚሉት ለእነርሱ የሚሆነውን አገር እንዲፈልጉ ያመለክታሉና። ¹⁵ ያን የወጡበትን አገር አስበው ቢሆኑ፥ ሊመለሱ ጊዜ በሆነላቸው ነበር፤ ¹⁶ አሁን ግን የሚበልጠውን እርሱም ሰማያዊ አገር ይናፍቃሉ። ስለዚህ እግዚአብሔር አምላካቸው ተብሎ ሊጠራ በእነርሱ አያፍርም፥ ከተማን አዘጋጅቶላቸዋልና።