en
Feedback
ኢየሱስ

ኢየሱስ

Open in Telegram
311
Subscribers
No data24 hours
-27 days
No data30 days
Posts Archive
በሥጋ መጣ ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ መጣ ማለት በሥጋ ሳይመጣ በፊት ያለ ሥጋ ነበረ፤ ኋላ ግን በሥጋ መጣ ማለት ነው። በሥጋ ሳይመጣ በፊት ያለ ሥጋ ነበረ፤ ቃል ነበረ፤ መለኮት ነበረ። በሥጋ ሲመጣ ደ
በሥጋ መጣ ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ መጣ ማለት በሥጋ ሳይመጣ በፊት ያለ ሥጋ ነበረ፤ ኋላ ግን በሥጋ መጣ ማለት ነው። በሥጋ ሳይመጣ በፊት ያለ ሥጋ ነበረ፤ ቃል ነበረ፤ መለኮት ነበረ። በሥጋ ሲመጣ ደግሞ መለኮትን ሳይተው ሥጋን ጨመረ። ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ ሲመጣ፥ ካለመኖር ወደ መኖር አይደለም የመጣው። ከመኖር ወደ መኖር ነው የመጣው። መለኮት ብቻ ሆኖ ከቀድሞው ለዘላለም መኖር፥ መለኮትም ሰውም ሆኖ በአንድ አካል ከመጣበት ወዲህ ለዘላለም ወደ መኖር ነው የመጣው። ይህንን በሥጋ መምጣቱን የማይቀበል፥ የማያምን፥ የማይታመን ሁሉ፥ ኢየሱስ መለኮት አይደለም፤ ሰው ብቻ ነው፤ የሚል ሁሉ፥ ከእግዚአብሔር አይደለም፤ እርሱ የክርስቶስ ተቃዋሚ መንፈስ ነው። የእግዚአብሔርን መንፈስ በዚህ ታውቃላችሁ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደ መጣ የሚታመን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው፥ ኢየሱስ ክርስቶስም በሥጋ እንደ መጣ የማይታመን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር አይደለም፤ ይህም የክርስቶስ ተቃዋሚው መንፈስ ነው፤ ይህም እንዲመጣ ሰምታችኋል፥ አሁንም እንኳ በዓለም አለ። 1ዮሐ. 4፥2-3 ብዙ አሳቾች ወደ ዓለም ገብተዋልና እነርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደ መጣ የማያምኑ ናቸው፤ ይህ አሳቹና የክርስቶስ ተቃዋሚው ነው። 2ዮሐ. 7 #በዘላለም መንግስት

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ ማቴዎስ 12 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ በዚያን ጊዜ ኢየሱስ በሰንበት ቀን በእርሻ መካከል አለፈ፤ ደቀ መዛሙርቱም ተራቡና እሸት ይቀጥፉ ይበሉም ጀመር። ² ፈሪሳውያንም አይተው፦ እነሆ፥ ደቀ መዛሙርትህ በሰንበት ማድረግ ያልተፈቀደውን ያደርጋሉ አሉት። ³-⁴ እርሱ ግን እንዲህ አላቸው፦ ዳዊትና ከእርሱ ጋር የነበሩት በተራቡ ጊዜ፥ እርሱ ያደረገውን፥ ወደ እግዚአብሔር ቤት እንደ ገባ ካህናትም ብቻ እንጂ እርሱና ከእርሱ ጋር የነበሩት ሊበሉት ያልተፈቀደውን የመሥዋዕቱን ኅብስት እንደ በላ አላነበባችሁምን? ⁵ ካህናትም በሰንበት በመቅደስ ሰንበትን እንዲያረክሱ ኃጢአትም እንዳይሆንባቸው በሕጉ አላነበባችሁምን? ⁶ ነገር ግን እላችኋለሁ፥ ከመቅደስ የሚበልጥ ከዚህ አለ። ⁷ ምሕረትን እወዳለሁ መሥዋዕትንም አይደለም ያለው ምን እንደሆነ ብታውቁስ ኃጢአት የሌለባቸውን ባልኰነናችሁም ነበር። ⁸ የሰው ልጅ የሰንበት ጌታ ነውና።

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ ዮሐንስ 13 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ ኢየሱስም ከፋሲካ በዓል በፊት፥ ከዚህ ዓለም ወደ አብ የሚሄድበት ሰዓት እንደ ደረሰ አውቆ፥ በዚህ ዓለም ያሉትን ወገኖቹን የወደዳቸውን እስከ መጨረሻ ወደዳቸው። ² እራትም ሲበሉ ዲያብሎስ በስምዖን ልጅ በአስቆሮቱ በይሁዳ ልብ አሳልፎ እንዲሰጠው አሳብ ካገባ በኋላ፥ ³ ኢየሱስ አብ ሁሉን በእጁ እንደ ሰጠው ከእግዚአብሔርም እንደ ወጣ ወደ እግዚአብሔርም እንዲሄድ አውቆ፥ ⁴ ከእራት ተነሣ ልብሱንም አኖረ፥ ማበሻም ጨርቅ ወስዶ ታጠቀ፤ ⁵ በኋላም በመታጠቢያው ውኃ ጨመረ፥ የደቀ መዛሙርቱንም እግር ሊያጥብና በታጠቀበትም ማበሻ ጨርቅ ሊያብስ ጀመረ። ⁶ ወደ ስምዖን ጴጥሮስም መጣ፤ እርሱም፦ ጌታ ሆይ፥ አንተ የእኔን እግር ታጥባለህን? አለው። ⁷ ኢየሱስም መልሶ፦ እኔ የማደርገውን አንተ አሁን አታውቅም፥ በኋላ ግን ታስተውለዋለህ አለው። ⁸ ጴጥሮስም፦ የእኔን እግር ለዘላለም አታጥብም አለው። ኢየሱስም፦ ካላጠብሁህ፥ ከእኔ ጋር ዕድል የለህም ብሎ መለሰለት። ⁹ ስምዖን ጴጥሮስም፦ ጌታ ሆይ፥ እጄንና ራሴን ደግሞ እንጂ እግሬን ብቻ አይደለም አለው። ¹⁰ ኢየሱስም፦ የታጠበ እግሩን ከመታጠብ በቀር ሌላ አያስፈልገውም፥ ሁለንተናው ግን ንጹሕ ነው፤ እናንተም ንጹሐን ናችሁ፥ ነገር ግን ሁላችሁ አይደላችሁም አለው። ¹¹ አሳልፎ የሚሰጠውን ያውቅ ነበርና፤ ስለዚህ፦ ሁላችሁ ንጹሐን አይደላችሁም አለው። ¹² እግራቸውንም አጥቦ ልብሱንም አንሥቶ ዳግመኛ ተቀመጠ፥ እንዲህም አላቸው፦ ያደረግሁላችሁን ታስተውላላችሁን? ¹³ እናንተ መምህርና ጌታ ትሉኛላችሁ፤ እንዲሁ ነኝና መልካም ትላላችሁ። ¹⁴ እንግዲህ እኔ ጌታና መምህር ስሆን እግራችሁን ካጠብሁ፥ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ እግራችሁን ትተጣጠቡ ዘንድ ይገባችኋል። ¹⁵ እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁና። ¹⁶ እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ባሪያ ከጌታው አይበልጥም። መልእክተኛም ከላከው አይበልጥም። ¹⁷ ይህን ብታውቁ፥ ብታደርጉትም ብፁዓን ናችሁ። ¹⁸ ስለ ሁላችሁ አልናገርም፤ እኔ የመረጥኋቸውን አውቃለሁ፤ ነገር ግን መጽሐፍ፦ እንጀራዬን የሚበላ በእኔ ላይ ተረከዙን አነሣብኝ ያለው ይፈጸም ዘንድ ነው። ¹⁹ በሆነ ጊዜ እኔ እንደ ሆንሁ ታምኑ ዘንድ፥ ከአሁን ጀምሬ አስቀድሞ ሳይሆን እነግራችኋለሁ። ²⁰ እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ማናቸውን የምልከውን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል። ²¹ ኢየሱስ ይህን ብሎ በመንፈሱ ታወከ መስክሮም፦ እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ከእናንተ አንዱ አሳልፎ ይሰጠኛል አለ። ²² ደቀ መዛሙርቱ ስለ ማን እንደ ተናገረ አመንትተው እርስ በርሳቸው ተያዩ። ²³ ኢየሱስም ይወደው የነበረ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ በኢየሱስ ደረት ላይ ተጠጋ፤ ²⁴ ስለዚህ ስምዖን ጴጥሮስ እርሱን ጠቅሶ፦ ስለማን እንደ ተናገረ ንገረን አለው። ²⁵ እርሱም በኢየሱስ ደረት እንዲህ ተጠግቶ፦ ጌታ ሆይ፥ ማን ነው? አለው። ²⁶ ኢየሱስም፦ እኔ ቍራሽ አጥቅሼ የምሰጠው እርሱ ነው ብሎ መለሰለት። ቍራሽም አጥቅሶ ለአስቆሮቱ ለስምዖን ልጅ ለይሁዳ ሰጠው። ²⁷ ቍራሽም ከተቀበለ በኋላ ያን ጊዜ ሰይጣን ገባበት። እንግዲህ ኢየሱስ፦ የምታደርገውን ቶሎ ብለህ አድርግ አለው። ²⁸ ነገር ግን ከተቀመጡት ስለ ምን ይህን እንዳለው ማንም አላወቀም፤ ²⁹ ይሁዳ ከረጢቱን የያዘ ስለ ሆነ፥ ኢየሱስ፦ ለበዓሉ የሚያስፈልገንን ግዛ፥ ወይም ለድሆች ምጽዋት እንዲሰጥ ያለው ለአንዳንዱ መስሎአቸው ነበርና። ³⁰ እርሱም ቍራሹን ከተቀበለ በኋላ ወዲያው ወጣ፤ ሌሊትም ነበረ። ³¹ ከወጣም በኋላ ኢየሱስ እንዲ አለ፦ አሁን የሰው ልጅ ከበረ እግዚአብሔርም ስለ እርሱ ከበረ፤ ³² እግዚአብሔር ስለ እርሱ የከበረ ከሆነ፥ እግዚአብሔር ደግሞ እርሱን ራሱን ያከብረዋል ወዲያውም ያከብረዋል። ³³ ልጆች ሆይ፥ ገና ጥቂት ጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ፤ ትፈልጉኛላችሁ፤ ለአይሁድም፦ እኔ ወደምሄድበት እናንተ ልትመጡ አይቻላችሁም እንዳልኋቸው፥ አሁን ለእናንተ ደግሞ እላችኋለሁ። ³⁴ እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ፥ እንደ ወደድኋችሁ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ አዲስ ትእዛዝ እሰጣችኋለሁ። ³⁵ እርስ በርሳችሁ ፍቅር ቢኖራችሁ፥ ደቀ መዛሙርቴ እንደ ሆናችሁ ሰዎች ሁሉ በዚህ ያውቃሉ። ³⁶ ስምዖን ጴጥሮስም፦ ጌታ ሆይ፥ ወዴት ትሄዳለህ? አለው። ኢየሱስም፦ ወደምሄድበት አሁን ልትከተለኝ አትችልም፥ ነገር ግን በኋላ ትከተለኛለህ ብሎ መለሰለት። ³⁷ ጴጥሮስም፦ ጌታ ሆይ፥ አሁን ልከተልህ አለመቻሌ ስለ ምንድር ነው? ነፍሴን ስንኳ ስለ አንተ እሰጣለሁ አለው። ³⁸ ኢየሱስም እንዲህ ብሎ መለሰለት፦ ነፍስህን ስለ እኔ ትሰጣለህን? እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሦስት ጊዜ እስክትክደኝ ድረስ ዶሮ አይጮኽም።

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ 1ኛ ጴጥሮስ 3 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹-² እንዲሁም፥ እናንተ ሚስቶች ሆይ፥ ከባሎቻችሁ አንዳንዱ ለትምህርት የማይታዘዙ ቢኖሩ፥ በፍርሃት ያለውን ንጹሑን ኑሮአችሁን እየተመለከቱ ያለ ትምህርት በሚስቶቻቸው ኑሮ እንዲገኙ ተገዙላቸው። ³ ለእናንተም ጠጕርን በመሸረብና ወርቅን በማንጠልጠል ወይም ልብስን በመጎናጸፍ በውጭ የሆነ ሽልማት አይሁንላችሁ፥ ⁴ ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋው እጅግ የከበረ የዋህና ዝግተኛ መንፈስ ያለውን የማይጠፋውን ልብስ ለብሶ የተሰወረ የልብ ሰው ይሁንላችሁ። ⁵ እንዲህ በቀድሞ ዘመን በእግዚአብሔር ተስፋ ያደረጉት ቅዱሳት ሴቶች ደግሞ ለባሎቻቸው ሲገዙ ተሸልመው ነበርና፤ ⁶ እንዲሁም ሣራ ለአብርሃም፦ ጌታ ብላ እየጠራችው ታዘዘችለት፤ እናንተም ከሚያስደነግጥ ነገር አንዳች እንኳ ሳትፈሩ መልካም ብታደርጉ ልጆችዋ ናችሁ። ⁷ እንዲሁም፥ እናንተ ባሎች ሆይ፥ ደካማ ፍጥረት ስለ ሆኑ ከሚስቶቻችሁ ጋር በማስተዋል አብራችሁ ኑሩ፤ ጸሎታችሁ እንዳይከለከል አብረው ደግሞ የሕይወትን ጸጋ እንደሚወርሱ አድርጋችሁ አክብሩአቸው። ⁸ በመጨረሻው ሁላችሁ በአንድ ልብ ሁኑ፥ የሌላው መከራ ለእናንተ እንደሚሆን አድርጉ፥ እንደ ወንድሞች ተዋደዱ፥ ርኅሩኆችና ትሑታን ሁኑ፤ ⁹ ክፉን በክፉ ፈንታ ወይም ስድብን በስድብ ፈንታ አትመልሱ በዚህ ፈንታ ባርኩ እንጂ፥ በረከትን ልትወርሱ ለዚህ ተጠርታችኋልና። ¹⁰ ሕይወትን ሊወድ መልካሞችንም ቀኖች ሊያይ የሚፈልግ ሰው፥ መላሱን ከክፉ ከንፈሮቹንም ተንኰልን ከመናገር ይከልክል፤ ¹¹ ከክፉ ፈቀቅ ይበል፥ መልካምንም ያድርግ፥ ሰላምን ይሻ ይከተለውም፤ ¹² የጌታ ዓይኖች ወደ ጻድቃን ናቸውና፥ ጆሮዎቹም ለጸሎታቸው ተከፍተዋል፥ የጌታ ፊት ግን ክፉ ነገርን በሚያደርጉ ላይ ነው። ¹³ በጎንም ለማድረግ ብትቀኑ የሚያስጨንቃችሁ ማን ነው? ¹⁴ ነገር ግን ስለ ጽድቅ እንኳ መከራን ብትቀበሉ ብፁዓን ናችሁ። ማስፈራራታቸውንም አትፍሩ አትናወጡም፥ ¹⁵ ዳሩ ግን ጌታን እርሱም ክርስቶስ በልባችሁ ቀድሱት። በእናንተ ስላለ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቁአችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ፥ ነገር ግን በየዋህነትና በፍርሃት ይሁን። ¹⁶ በክርስቶስ ያለውን መልካሙን ኑሮአችሁን የሚሳደቡ ሰዎች ክፉን እንደምታደርጉ በሚያሙበት ነገር እንዲያፍሩ በጎ ሕሊና ይኑራችሁ። ¹⁷ የእግዚአብሔር ፈቃድ እንዲህ ቢሆን፥ ክፉ ስለ ማድረግ ሳይሆን በጎ ስለ ማድረግ መከራን ብትቀበሉ ይሻላችኋልና። ¹⁸ ክርስቶስ ደግሞ ወደ እግዚአብሔር እንዲያቀርበን እርሱ ጻድቅ ሆኖ ስለ ዓመፀኞች አንድ ጊዜ በኃጢአት ምክንያት ሞቶአልና፤ በሥጋ ሞተ በመንፈስ ግን ሕያው ሆነ፥ ¹⁹ በእርሱም ደግሞ ሄዶ በወኅኒ ለነበሩ ነፍሳት ሰበከላቸው፤ ²⁰ ጥቂቶች ማለት ስምንት ነፍስ በውኃ የዳኑበት መርከብ ሲዘጋጅ፥ የእግዚአብሔር ትዕግሥት በኖኅ ዘመን በቈየ ጊዜ ቀድሞ አልታዘዙም። ²¹ ይህም ውኃ ደግሞ ማለት ጥምቀት ምሳሌው ሆኖ አሁን ያድነናል፥ የሰውነትን እድፍ ማስወገድ አይደለም፥ ለእግዚአብሔር የበጎ ሕሊና ልመና ነው እንጂ፥ ይህም በኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ነው፤ ²² እርሱም መላእክትና ሥልጣናት ኃይላትም ከተገዙለት በኋላ ወደ ሰማይ ሄዶ በእግዚአብሔር ቀኝ አለ።

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ ሮሜ 3 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እንግዲህ የአይሁዳዊ ብልጫው ምንድር ነው? ወይስ የመገረዝ ጥቅሙ ምንድር ነው? በሁሉ ነገር ብዙ ነው። ² አስቀድሞ የእግዚአብሔር ቃላት አደራ ተሰጡአቸው። ታዲያ ምንድር ነው? ³ የማያምኑ ቢኖሩ አለማመናቸው የእግዚአብሔርን ታማኝነት ያስቀራልን? ⁴ እንዲህ አይሁን፤ በቃልህ ትጸድቅ ዘንድ ወደ ፍርድ በገባህም ጊዜ ትረታ ዘንድ ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ ሰው ሁሉ ውሸተኛ ከሆነ እግዚአብሔር እውነተኛ ይሁን። ⁵ ነገር ግን ዓመፃችን የእግዚአብሔርን ጽድቅ የሚያስረዳ ከሆነ ምን እንላለን? ቍጣን የሚያመጣ እግዚአብሔር ዓመፀኛ ነውን? እንደ ሰው ልማድ እላለሁ። ⁶ እንዲህ አይሁን፤ እንዲህ ቢሆን እግዚአብሔር በዓለም እንዴት ይፈርዳል? ⁷ በእኔ ውሸት ግን የእግዚአብሔር እውነት ለክብሩ ከላቀ ስለምን በእኔ ደግሞ እንደ ኃጢአተኛ ገና ይፈርድብኛል? ⁸ ስለ ምንስ መልካም እንዲመጣ ክፉ አናደርግም? እንዲሁ ይሰድቡናልና አንዳንዱም እንዲሁ እንድንል ይናገራሉና። የእነርሱም ፍርድ ቅን ነው። ⁹ እንግዲህ ምን ይሁን? ከእነርሱ እንበልጣለንን? ከቶ አይደለም፤ አይሁድም የግሪክ ሰዎችም ሁሉ ከኃጢአት በታች እንደ ሆኑ አስቀድመን ከሰናቸዋልና፤ ¹⁰ እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፦ ¹¹ ጻድቅ የለም አንድ ስንኳ፤ አስተዋይም የለም፤ እግዚአብሔርንም የሚፈልግ የለም፤ ሁሉ ተሳስተዋል፥ ¹² በአንድነትም የማይጠቅሙ ሆነዋል፤ ቸርነት የሚያደርግ የለም፥ አንድ ስንኳ የለም። ¹³ ጕሮሮአቸው እንደ ተከፈተ መቃብር ነው፥ በመላሳቸውም ሸንግለዋል፤ የእባብ መርዝ ከከንፈሮቻቸው በታች አለ፤ ¹⁴ አፋቸውም እርግማንና መራርነት ሞልቶበታል፤ ¹⁵ እግሮቻቸው ደምን ለማፍሰስ ፈጣኖች ናቸው፤ ¹⁶ ጥፋትና ጉስቁልና በመንገዳቸው ይገኛል፥ ¹⁷-¹⁸ የሰላምንም መንገድ አያውቁም። በዓይኖቻቸው ፊት እግዚአብሔርን መፍራት የለም። ¹⁹ አፍም ሁሉ ይዘጋ ዘንድ ዓለምም ሁሉ ከእግዚአብሔር ፍርድ በታች ይሆን ዘንድ ሕግ የሚናገረው ሁሉ ከሕግ በታች ላሉት እንዲናገር እናውቃለን፤ ²⁰ ይህም የሕግን ሥራ በመሥራት ሥጋ የለበሰ ሁሉ በእርሱ ፊት ስለማይጸድቅ ነው፤ ኃጢአት በሕግ ይታወቃልና። ²¹ አሁን ግን በሕግና በነቢያት የተመሰከረለት የእግዚአብሔር ጽድቅ ያለ ሕግ ተገልጦአል፥ ²² እርሱም፥ ለሚያምኑ ሁሉ የሆነ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ ነው፤ ልዩነት የለምና፤ ²³ ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል፤ ²⁴ በኢየሱስ ክርስቶስም በሆነው ቤዛነት በኩል እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉ። ²⁵ እርሱንም እግዚአብሔር በእምነት የሚገኝ በደሙም የሆነ ማስተስሪያ አድርጎ አቆመው፤ ይህም በፊት የተደረገውን ኃጢአት በእግዚአብሔር ችሎታ ስለ መተው ጽድቁን ያሳይ ዘንድ ነው፥ ²⁶ ራሱም ጻድቅ እንዲሆን በኢየሱስም የሚያምነውን እንዲያጸድቅ አሁን በዚህ ዘመን ጽድቁን ያሳይ ዘንድ ነው። ²⁷ ትምክህት እንግዲህ ወዴት ነው? እርሱ ቀርቶአል። በየትኛው ሕግ ነው? በሥራ ሕግ ነውን? አይደለም፥ በእምነት ሕግ ነው እንጂ። ²⁸ ሰው ያለ ሕግ ሥራ በእምነት እንዲጸድቅ እንቆጥራለንና። ²⁹-³⁰ ወይስ እግዚአብሔር የአይሁድ ብቻ አምላክ ነውን? የአሕዛብስ ደግሞ አምላክ አይደለምን? አዎን፥ የተገረዘን ስለ እምነት ያልተገረዘንም በእምነት የሚያጸድቅ አምላክ አንድ ስለ ሆነ የአሕዛብ ደግሞ አምላክ ነው። ³¹ እንግዲህ ሕግን በእምነት እንሽራለንን? አይደለም፤ ሕግን እናጸናለን እንጂ።

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ #የእግዚአብሔርን_የጦር_መሣሪያ_ልበሱ (2) እንደ ሐዋርያው ጳውሎስ 7 የእግዚአብሔር የጦር መሣሪያዎችን እናገኛለን፤ እነሱም የሚከተሉት ናቸው። (ኤፌሶን 6፤ 14-17 አ.መ.ት ይመልከቱ) ❶ እውነት (እውነትን እንደ ዝናር ታጠቁ) ሰይጣን የውሸት አባት ነው፤ (ዮሐ 8:44)። የእርሱን ውሸት ሊረታ የምችለው እውነት ብቻ ነው። ወሸት የጥፋት መንገድ ሲሆን፤ እውነት (ኢየሱስ) የሕይወት መንገድ ነው። ❷ ጽድቅ (ጽድቅን እንደ ደረት ጥሩር ልብሱ) የክርስቶስን ጽድቅ እንደተቀበልን፤ እንደ ጻድቃን የጽድቅን የደረት ጥሩር መልበስ ይገባናል። በዚህ የምንመላለስ እንደሆነ ሰይጣን በእኛ ላይ እድልፈንታ የለውም። "ጽድቅን እንደ ጥሩር አጠለቀ፤ የድነትን ቊር በራሱ ላይ ደፋ፤ የበቀልንም ልብስ ለበሰ፤ መጐናጸፊያ እንደሚደረብም ቅናትን ደረበ"[ኢሳ 59:17 አ.መ.ት]። ❸ የሰላም ወንጌል (የሰላም የምስራች ቃል በእግሮቻችሁ አጥልቃችሁ በመዘጋጀት ቁሙ) የክርስቶስን ወንጌል ሳንታክት ለሌሎች ለማድረስ ይዘን መሮጥ ያስፈልገናል። የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ ለምንድን የእግዚአብሔር ኀይል ነውና። ❹ እምነት (የእምነት ጋሻ) በእግዚአብሔር ያለን እምነት እንደ ጋሻ ተቆጥሮአል። ጋሻችንን ወደላይ በምናነሳበት ጊዜ በእግዚአብሔር ኀይል ፍጹም መተማመን ይኖረናል። ❺ መዳን (የደኅንነት ራስ ቁር ነው) "ጽድቅን እንደ ጥሩር አጠለቀ፤ የድነትን ቊር በራሱ ላይ ደፋ፤ የበቀልንም ልብስ ለበሰ፤ መጐናጸፊያ እንደሚደረብም ቅናትን ደረበ"[ኢሳይያስ 59:17 አ.መ.ት]። ከብረት በተሠራው የራስ ቁር ወታደሩ ራሱን ይከላከልበታል፤ ጠላቱም ሊገድለው አይችልም። በዚሁ አይነት የደኅንነት ራስ ቁር ሰይጣን መንፈሳዊ ሕይወታችንን እንዳይገድል ይከላከልልናል። ❻ የመንፈስ ሰይፍ /የእግዚአብሔር ቃል ነው፤  እስካሁን ያየናቸው 5ቱ መሣሪያዎች የሚያገለግሉት ለመከላከያ መሆናቸውን አንዘንጋ፤ ይሄ 6ኛው ክፍል ግን የመንፈስ ሰይፍ ሰይጣንን የሚንዋጋበት የማጥቂያ መሣሪያ ነው። ❼ ጸሎት (ዘወትር በመንፈስ ጸልዩ)። "በሁሉ ዐይነት ጸሎትና ልመና፣ በማንኛውም ሁኔታ በመንፈስ ጸልዩ፤ ይህንም በማሰብ ንቁ፤ ስለ ቅዱሳንም ሁሉ በትጋት ልመና አቅርቡ"[ኤፌሶን 6:18 አ.መ.ት]። ዶ/ር ሰብስቤ [ሰቢ]

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ ኢሳይያስ 59 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁵ እውነትም ታጥቶአል፥ ከክፋትም የራቀ ሰው ለብዝበዛ ሆኖአል። እግዚአብሔርም አየ ፍርድም ስለሌለ ተከፋ። ¹⁶ ሰውም እንደሌለ አየ፥ ወደ እርሱ የሚማልድ እንደሌለ ተረዳ ተደነቀም፤ ስለዚህ የገዛ ክንዱ መድኃኒት አመጣለት፥ ጽድቁም አገዘው። ¹⁷ ጽድቅንም እንደ ጥሩር ለበሰ፥ በራሱም ላይ የማዳንን ራስ ቍር አደረገ፤ የበቀልንም ልብስ ለበሰ፥ በቅንዓትም መጐናጸፊያ ተጐናጸፈ። ¹⁸ እንደ ሥራቸው መጠን እንዲሁ ቍጣን ለባላጋራዎቹ፥ ፍዳንም ለጠላቶቹ ይከፍላል፤ ለደሴቶችም ፍዳቸውን ይከፍላል። ¹⁹ እርሱ የእግዚአብሔር ነፋስ እንደሚነዳው እንደ ጐርፍ ፈሳሽ ይመጣልና በምዕራብ ያሉት የእግዚአብሔርን ስም፥ በፀሐይ መውጫም ያሉት ክብሩን ይፈራሉ። ²⁰ ለጽዮን ታዳጊ ይመጣል፥ በያዕቆብም ዘንድ ከኃጢአት ለሚርቁ፥ ይላል እግዚአብሔር። ²¹ ከእነርሱ ጋር ያለው ቃል ኪዳኔ ይህ ነው ይላል እግዚአብሔር፤ በአንተ ላይ ያለው መንፈሴ በአፍህም ውስጥ ያደረግሁት ቃሌ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘላለም ድረስ ከአፍህ ከዘርህም አፍ ከዘር ዘርህም አፍ አያልፍም፥ ይላል እግዚአብሔር።

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ አንድ ክርስቲያን በመዳኑ እርግጠኛ መሆኑን መናገር ትዕብተኝነት ነውን? በእኛው ወንጌላዊያን አማኞች ዘንድ ብዙውን ጊዜ በመዝሙርም በስብከትም መሃል ድነትን ከወደፊቱ 'ገጽታው' ይልቅ በአሁናዊ 'ገጽታው' ላይ ትኩረት ያደርጋል። ስለዚህም "ድኝያለሁ" ፣ "ጸድቅያለሁ" ፣ "ተቀድሽያለሁ" ፣ "ታጥብያለሁ" ፣ "ኩኔነ የለብኝም"፣ " አሁን እንኳን ብሞት ቀጥ ብዬ ወደ መንግሥተ ሰማይ እንደምገባ እርግጠኛ ነኝ" እና ተመሳሳይ ሐሳብ ያላቸው ገለጻዎች ይዘወተራሉ። ይኽም ብዙውን ጊዜ በሌሎቹ ቤተ-እምነቶች ዘንድ እንደ ትዕብተኝነት እና እንደ አጉል ትምክህት ይወሰዳል። በእኛውም ሕብረት ውስጥ "አሁን ብትሞት ወዴት እንደምትሄድ ታውቃለህን?" ተብሎ ቢጠየቅ የአንዳንዶቹ መልስ "አላውቅም" ፣ "ያኔ ስሞት/ስደርስ አረጋግጠዋለሁ" ፣ "ጌታ ያውቃል" በሚሉ በጥርጣሬ የተሞሉ ምላሾች ይደመጣሉ። አንድ ክርስቲያን በድነቱ እርግጠኛ ሆና አሁን ብሞት መዳረሻዬ መንግሥት ሰማይ ነው ብሎ ቢመልስ ይህ ሰው ትዕብተኛ ነውን? መጽሐፍ ቅዱሳችን በተለይም አዲሱ ኪዳን ስለ ድነት በቂ አስተምህሮ አለው። በአዲሱ ኪዳን ድነት አስተምህሮም(New testament soteriology) ድነትን ምንጠባበቀው ተስፋ ብቻ አድርጎ ሳይሆን አሁናዊ እውነትም(ገጽታም) እንዳለው በግልጽ ያስተምራል። ከነዚህም ጥቅቶችን በገረፍታ ለማሰስ ብንሞክር:- "በጸጋው ድናችኋልና" ኤፌ 2:5 "ጸጋው በእምነት አድኖአችኃልና" ኤፌ 2:8 ሐዋርያው ጳውሎስ ለኤፌሶን ቅዱሳን(በክርስቶስ ላሉት) ሲናገር "ድናችኋልና" በማለት ባለፈ ጊዜ በተፈጸመ አሁናዊ እርግጠኝነትን ያንጸባርቃል፤ ስለዚህም  ከኤፌሶን ሰዎች መካከል አንዱ "ድኝያለሁ" ቢል ትዕብት አይሆንበትም። "ድኝያለሁ" ማለቱ ራሱን ከፍ የሚያደርግበት የትዕብት ቃል አለመሆኑን ሐዋርያው ጳውሎስ "ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም" በማለት አዳኙን ለማወደስ እንጂ የዳነውን ሰው ልብ ለማሳበጥ እንዳይደለ "ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም" ይላል። ሌላው:- " እግዚአብሔርም የዘላለምን ሕይወት እንደ ሰጠን ይህም ሕይወት በልጁ እንዳለ ምስክሩ ይህ ነው። ልጁ ያለው ሕይወት አለው፤ የእግዚአብሔር ልጅ የሌለው ሕይወት የለውም።" 1ዮሐ 5:11-12 ሐዋርያው ዮሐንስ አጽኖትን ሲሰጥ፤ እግዚአብሔር የዘላለም ሕይወትን ሰጠን ይህም ሕይወት በልጁ ነው ያለው ስለዚህም ልጁ ያለው የዘላለም ሕይወት አለው ይላል፤ "ልጁ አለኝ" ብሎ የሚያምን "የዘላለም ሕይወት አለኝ" ለማለት ማፈር የለበትም ምክንያቱም የዘላለም ሕይወት በልጁ ነውና፤ "ኢየሱስ(ልጁ) አለኝ" ብሎ መናገር ትዕብት እንዳደለ ሁሉ በልጁ ያለው "የዘላለም ሕይወት አለኝ" ማለትም ትዕብት አይደለም። ምክንያቱም የዘላለም ሕይወትን በራሱ ሳይሆን በልጁ ስላገኘ።“በልጁ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ በልጁ የማያምን ግን የእግዚአብሔር ቍጣ በእርሱ ላይ ይኖራል እንጂ ሕይወትን አያይም።” ዮሐ 3፥36 ስለዚህም አንድ በኢየሱስ ክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ ያመነ ዳግምም የተወለደ ሰው"የዘላለም ሕይወት አለኝ/ ድኝያለሁ" ማለቱ ትዕብት ሳይሆን የቃሉን እውነት ማንጸባረቅ ነው። ባዳነውም ጌታ ላይ በመተማመን በቃሉም የተገለጠውን እውነት ተቀብሎ ማረፍ ነው። እንዲሁም ደግሞ ስለመዳን እርግጠኛ አለመሆን እና "ያኔ ስሞት/ስደርስ አረጋግጠዋለሁ" ፣ "ጌታ ያውቃል" ማለትም ትህትና አይደለም።

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ ኢሳይያስ 53 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ የሰማነውን ነገር ማን አምኖአል? የእግዚአብሔርስ ክንድ ለማን ተገልጦአል? ² በፊቱ እንደ ቡቃያ ከደረቅም መሬት እንደ ሥር አድጎአል፤ መልክና ውበት የለውም፥ ባየነውም ጊዜ እንወድደው ዘንድ ደም ግባት የለውም። ³ የተናቀ ከሰውም የተጠላ፥ የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው፤ ሰውም ፊቱን እንደሚሰውርበት የተናቀ ነው፥ እኛም አላከበርነውም። ⁴ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው። ⁵ እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን። ⁶ እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ። ⁷ ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም። ⁸ በማስጨነቅና በፍርድ ተወሰደ፤ ስለ ሕዝቤ ኃጢአት ተመትቶ ከሕያዋን ምድር እንደ ተወገደ ከትውልዱ ማን አስተዋለ? ⁹ ከክፉዎችም ጋር መቃብሩን አደረጉ፥ ከባለጠጎችም ጋር በሞቱ፤ ሆኖም ግፍን አላደረገም ነበር፥ በአፉም ተንኮል አልተገኘበትም ነበር። ¹⁰ እግዚአብሔርም በደዌ ያደቅቀው ዘንድ ፈቀደ፤ ነፍሱን ስለ ኃጢአት መሥዋዕት ካደረገ በኋላ ዘሩን ያያል፥ ዕድሜውም ይረዝማል፥ የእግዚአብሔርም ፈቃድ በእጁ ይከናወናል። ¹¹ ከነፍሱ ድካም ብርሃን ያያል ደስም ይለዋል፤ ጻድቅ ባሪያዬም በእውቀቱ ብዙ ሰዎችን ያጸድቃል፥ ኃጢአታቸውን ይሸከማል። ¹² ስለዚህም እርሱ ብዙዎችን ይወርሳል፥ ከኃያላንም ጋር ምርኮን ይከፋፈላል፤ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቶአልና፥ ከዓመፀኞችም ጋር ተቈጥሮአልና እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ፥ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ።

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ የጠራ፣ የጠለቀና የተዘጋጀ የነገረ መለኮት ትምህርቱ ጠቅሞታል፡፡ በተጨማሪም፡- ዘመን ዘለቅ ስጦታ የሆኑ መጽሐፍ ቅዱስን፣ ወንጌልን፣ ጸጋን፣ ሕግን … በተሻለ  ሁኔታ ቤተክርስቲያንን ለመርዳት  ሕያው  አስተምህሮዎችን በጽሑፍ ያስተላለፈልን ነገረ መለኮትን በመማሩ ነበር፡፡  ስለዚህ የዛሬ የነገረ መለኮት ምሁራኖቻችን ከማርቲን ሉተር ተማሩ።  እንማር፡፡ አንታበይ፡፡ ትሁታን እንሁን፡፡ በተማርነው የነገረ መለኮት ዕውቀታችን በቤተክረስቲያን የተሻለ ደሞዝ፣ የተሻለ ወንበር፣ ስም፣ ሹመት፣ ዝና … ለማግኘት ሳይሆን ቀይጥነትን፣ ዓለማዊነትን፣ ሥጋዊነትን … በቀጥታ በፍቅርና በቃሉ በመግጠም ቤተ ክርስቲያንን  ለማደስ እንነሳ፡፡ ተሐድሶ፣ ተሐድሶ፣ ተሐድሶ ። ቀኑ የካቲት 18/ 1546  ማርቲ ሉተር  በሞት አልጋ ላይ ሰዎች ከበውት እያለ ...እግዚአብሔር አንዲያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና" ደግሞም ነፍሴን በእጆችህ አኖራለሁ.." በማለታ የእምነት ጀግናው ወደቀጣዩ ዓለም በድል ተሻገረ። 🔥 ማርቲን ሉተር ሚስቱ ካቲ ሞታ የአስክሬን ሳጥኗ እንደተዘጋ- "ምስማሩ ገብቶ ዘጋው❗️በአዲሱ ቀን እንደገና ትነሣለች❗️"(wa.tr. 5:189) እንዳለው እርሱም አንድ ቀን እንደገና ይነሣል❗️ ተባረኩ።  አመሰግናለሁ፡፡  ሼር ወንጌላዊ ጸጋአብ በቀለ

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ 1ኛ ቆሮንቶስ 8 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁴ እንግዲህ ለጣዖት የተሠዋውን ሥጋ ስለ መብላት፥ ጣዖት ሁሉ በዓለም ከንቱ እንደ ሆነ ከአንዱም በቀር ማንም አምላክ እንደሌለ እናውቃለን። ⁵ መቼም ብዙ አማልክትና ብዙ ጌቶች አሉ፤ ነገር ግን በሰማይ ሆነ በምድርም ሆነ አማልክት የተባሉ ምንም ቢኖሩ፥ ⁶ ለእኛስ ነገር ሁሉ ከእርሱ የሆነ እኛም ለእርሱ የሆንን አንድ አምላክ አብ አለን፥ ነገር ሁሉም በእርሱ በኩል የሆነ እኛም በእርሱ በኩል የሆንን አንድ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አለን።

በመለየት ረገድ የሰከነ፣

መጽሐፍ ቅዱስ ሲናገር፦ "እግዚአብሔር፤  ወደዚህ ወደ ትሑት፥ መንፈሱም ወደ ተሰበረ፥ በቃሌም ወደሚንቀጠቀጥ ሰው እመለከታለሁ" ("ኢሳ.66:2) ይላል። በቃሉ ብርሃን መገለጥ የሚሆነው እግዚአብሔር ስመለከተን፣ ዘንበል ሲልልን፣ የልብ ዓይኖች ሲበሩና ሓልዎቱ ስከበን ነው። የነገረ መለኮት ፕሮፌሰር የነበረው ማርቲን ሉተር እንደ ሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ሥርዓትና አስተምህሮ  በሥራ ለመጽደቅ እየታገለና እያስተማረ ብዙ ዘመን ቆየ፡፡  በዚህ ህዴት መዝሙረ ዳዊትን፣ ሮሜን፣ ገላቲያን፣ የዕብራውያን መጻሕፍት፣ በጥልቀት ሲያጠና ሲያስተምር ስለ እምነቱና ስለ ካቶሊክ እስተምህሮ ትልቅ ጥያቄ በውስጡ እንደተፈጠረ ይናገራል፡፡ የመዳኑ ጥያቄ እያለ የሮማ  የካቶሊክ ቤተክርስቲያን በልቡ እርስ በርስ ሰጋጩ ተሰማው፡፡ ከዚህም የተነሣ  "መዝሙረ ዳዊት፣ ገላትያ፣ ሮሜ፣ የዕብራውያን መጽሐፎችና የሮማን ካቶሊክ አስተምህሮ ሁለቱም በአንድ ጊዜ እውነት መሆን አይችሉም" በሚለው ድምዳሜ ላይ ደረሰ፡፡   ከዚያም ሮሜ. 1፡17 ሲያጠና እግዚአብሔር በተለየ ሁኔታ ዓይኖቹን አበራለት፡፡ በዚህ ድንቅ መገለጥና ግኘት መጽሐፍ ቅዱስን በጥልቀት ለማጥናት የነገረ መለኮት እውቀት እንደጠቀመው ለማንም ግልጽ ነው፡፡ ስለ እግዚአብሔር ለማወቅ መማርና ማንበብ ሲሆን እግዚአብሔርን ለማወቅ ግን መለኮታዊ መገለጥ ይጠይቃል፡፡ ያ ከሰማይ እንጂ ከነገረ መለኮት ትምህርት ቤት ወይንም   መጻሕፍት አይገኝም፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ በገማሊያል እግር ሥር ቁጭ ብሎ መማሩ፣ የብሉይ ኪዳን ሊቅ ፈረሳዊ መሆኑ በሐዋ.9 ክርስቶስ እስኪገለጥለት ድረስ ዕውቀት ቢኖረውም መንፈሳዊ ዓይኖቹ አያዩም ነበር። ኢየሱስንም በሕይወቱ አያውቅም ነበር፡፡  ማርቲን ሉተርም እንደዚሁ ነበር፡፡  ሉተር እግዚአብሔር በመንፈስ ቅዱስ ዓይኖቹን እንዳበራለት ሲናገር፡- "በራሴ መረዳት ወይም በጥንካሬ በጌታዬ በኢየሱስ ክርስቶስ ለማመን ወይም ወደ እርሱ ለመምጣት እንደማልችል፡ ይልቁኑ መንፈስ ቅዱስ በወንጌል እንደጠራኝ በስጦታዎችም እንዳበራልኝ፡ እንደቀደሰኝ፣ በእውነተኛ እምነት እንደሚጠብቀኝ አምናለሁ፡፡" ብሎዋል፡፡ (የቤ/ክ አዳሹ የሉተር ታሪክ 2011 ዓም ገጽ 213 ) ✍️ ማርቲን ሉተር በዘመኑ ስለነበሩ ቄሳውስት  ሲናገር፦ ኢየሱስ በዘመኑ የአይሁድ የሃይማኖት መሪ የነበሩ ጻሐፊት ፈረሳውያንን "የተሰወረ መቃብር የሚምሱ" (ሉቃ 11:44) መንግሥተ ሰማያትን በሰው ፊት የሚዘጉ (ማቴ:5: 20)  እንዳለው  ማርቲን ሉተር ወንጌል እንደበራለት የሮም ካቶሊክ የቄሳውስቱና ርእሰ ሊቀነ ጳጳሱቱን ኑፋቄ፣ ኢመጽሐፍ ቅዱሳዊ ወግ፣  የሥነ ምግባር ቀውስና አደገኛ አካሄድ በአደባባይ ቃሉ ላይ ቆሞ ይቃም ጀመር፡፡ ስለ ቄሳውስቱም  ሲናገር፡- "አቤት እነዚህ አሳፋር ሆዳሞችና የሆድ አገልጋዮች፣ የነፍሳት ጠባቂዎች ቄሶች ከመሆን ይልቅ የአሳማ መንጋ ወይንም የውሾች ጠባቂዎች ቢሆኑ ይመጥናቸዋል" ይል ነበር፡፡ (የቤ/ክ አዳሹ የሉተር ታሪክ 2011 ዓም ገጽ 214 )፡፡ ስለ ሮም ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሲናገር፡- "ቀደሚ ሲል ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ የክርስቶስ ተወካይ ነው ብያለሁ፤ አሁን ግን ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ የክርስቶስ ተቃዋሚና የዲያብሎስ ሐዋርያ እላለሁ፡፡  ... ጳጳሱ የክርስቶስን ሥልጣን ዘርፈዋል። ስለዚህ ሥጋ የለበሰ የክርስቶስ ተቃዋሚ ናቸው" (WA Br. 2:389) በማለት በግልጽ ተቃውሞውን አሰምቷል። ዛሬ ከለባው፣ ከአጭበርባሪው በወንጌል ስም  ከውሃ፣ ከዘይትና እራፍ ጨርቅ ሻጩ፣ በድንቅና ተአምራት ስም የመብለትና የአሮጊቶችን መቀነት ከሚፈቱ፣ ሌላ ወንጌል ከሚሰብኩት  ጋር በጓዳ ኪዳን ገብተን በአደባባይ ተሐድሶ፣ ተሓድሶ ...የሚል የውሸት ሙዝሙራችንን ማርቲን ሉተር ምን ይለን ይሆን❓ ✍️ ማርቲን ሉተር በዘመኑ ስላመጣው ተጽዕኖ ራሱ ሲናገር፡-- "በመጀመሪያ ደረጃ የሮማ ካቶሊካውያንን በገዛ መጽሐፋቸው በተለይም በቅዱሳት መጻሕፍት ሞግቻቸዋለሁ፤ …. ሁለተኛ የትኛውም ጉባኤ ሊነካው ያልፈለገውን ሁከትና ጸያፍ የነበረውን የስርየት ጽሑፍ ሽያጭ አስቆምኩ፡፡ በሶስተኛ ደረጃ፡- ሃይማኖታዊ ጉዞንና የጣዖት መሠዊያዎችን ከሞላ ጎደል እቀርቻለሁ፡፡ …. በሌላ በኩል በእነዚህ ጊዜያት በዐሥራ አምስት ዓመት ወንድና ሴት ልጆች ከእነርሱ ከቀደሙት ከፍተኛ ደረጃ ላይ የነበሩ ምሁራንና አስተማሪዎች ያወቁ ከነበረው በበለጠ ስለ ክርስትና አስተምህሮ እስኪያውቁ ድረስ ስለ እግዚአብሔር ጸጋ አብዝቼ አስትምሬአለሁ፡፡"የቤ/ክ አዳሹ የሉተር ታሪክ 2011 ዓም ገጽ 215 )፡፡ ብሎዋል ተሐድሶ፡- ከውሸት ጋር በመጋባት፣ ውሸትና እውነትን፣ ብርሃንና ጨለማን በማቻቻል፣ ደግሞ በማመቻመች፣ ከሁሉ ጋር በመወዳጀትና ሰውና እግዚአብሔርን አንድ ላይ ለማስደሰት በመጣሪ  ሳይሆን እውነትን ይዞ ውሸትን በመጋፈጥና በመግጠም፣ በቃሉ ላይ በመቆም ብቻ እውን ይሆናል፡፡ የሉተር  ግልጽነት፣ አቋም፣ እምነት፣ ዱካ፣ ድፍረት፣ ... የሚያስተምረን ይህ ነው፡፡ እውነተኛ ተሐድሶ በጸሎትና በመዝሙር ብቻም አይመጣም፡፡ በቃሉ ላይ በመቆም ቤቱን ባጨናነቁ ኑፈቄ፣ ንግድ፣ የተሳሳተ የጸጋ ስጦታ አጠቃቀምና የሥነ ምግባር ቀውስ ላይ  በግልጽ  መንፈሳዊ ጦርነትን  መክፈት የግድ ይላል፡፡  መጽሐፍ ቅዱስ "ጸልዩ" ወይንም "እወቁ"  ብቻ ሳይሆን "መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደል"(1ጢሞ.6፡12) "በእምነት ተቃወሙት"(1ጴጥ.5፡9)፣ የጨለማን ሥራ ግለጡት (ኤፌ.5፡11) በእግዚአብሔርም እውቀት ላይ የሚነሣውን ክፍ ያለውን ነገረ ሁሉ አፍርሱ (2ቆሮ.10፡5) ጸንታችሁ ቁሙ(ገላ/5፡1) … ብሎም እንዳዘዘን  አንዘንጋ፡፡ ✍️ የማርቲን ሉተር መወገዝና የፕሮቴስታንት ልደት በመጨረሻም ማርቲን ሉተር እ.ኤ.አ ኖቨምበር 31/1517 95 የተሐድሶ ነጥቦችን ከቃሉ በማውጣት በዊተንበርግ ቤተክርስቲያን በር በመለጠፍ ቀይ መስመር በአደባባይ አሳየ፡፡ በቤተ ክርስቲያን በሞሉ አደገኛ ኑፋቄ  ትምህርቶች፣ ልማዶችና በጳጳሳት ሊቅ የአኗኗር ዜይቤ ላይ ገሃዳዊ መንፈሳዊ ጦርነት ከፈተ፡፡ ታላቅ መንፈሳዊ ፍንዳታ በዓለም ላይ ሆነ፡፡ ወንጌል ለአንድ ሺ ዓመታት ከተያዘበት ዋሻ በኃይልና በድል ወጣ፡፡  በዚህም ማርቲን ሉተር አምስቱ "Solas - ብቻዎች"፡-  1. ድነት በእግዚአብሔር ቃል ብቻ፣2.  ድነት በጸጋ ብቻ፣ 3. ድነት በእምነት ብቻ፣ 3. ድነት በኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ 5. ድነት ለእግዚአብሔር ክብር ብቻ በማለቱ ተወልዶ፣ አድጎ፣ ተምሮ፣ ለአገልግሎት ከተሾመበት  ከሮማ   ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ተባረረ፡፡  በዚህም ፕሮቴስታንት(የሐሰት ተቃዋሚ) የተባሉ  አብያተ ክርስቲያናት በዓለማችን ተወለዱ፡፡ ዛሬ 1.5 ቢሊዮን ፕሮቴስታንቶች በዓለማችን ላይ እንዳሉ መረጃዎች ቢጠቁሙም ከሉተር ዘመን በላይ ተሐድሶ በሚያስፈልጋቸው ብዙ ግሳግስ እንደተሞሉ ይነገራል፡፡    ❗️ማጠቃለያ የዶ/ር ማርቲን ሉተር ነገረ መለኮትን ተምሮ ማስተማር የጀመረው በሕይወቱ ክርስቶስን ከማወቁ በፊት እንደሆነ ተመልከተናል፡፡ የሉተር፡- ጥልቅ የነገረ መለኮት ምልከታዎች ለአገልግሎቱ ስኬትና ለቤተክርስቲያን ተሐድሶ እግዚአብሔር ተጠቅሞበታል፡፡ የነገረ መለኮት ጥልቅ እውቀቱን፣ ራሱን ዝቅ አድርጎ በትህትናና በፍቅር በእግዚአብሔር እጅ በማድረጉ ለዘመናት የፈረሰውን ድልድይ ገንቢ አድርጎ እግዚአብሔር በኃይል ተጠቅሞበታል፡፡ ማርቲን ሉተር በቃሉና በመንፈሱ በመደገፍ ገለባን ከፍሬው፣ ብርሃንን ከጨለማ፣ የአጋንንትን፣ የሥጋን፣ የመንፈስ ሥራዎችን በመለየት ረገድ የሰከነ፤

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ 2ኛ ቆሮ 4 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ ስለዚህ ምክንያት ምሕረት እንደ ተሰጠን መጠን ይህ አገልግሎት ስላለን አንታክትም። ² ነገር ግን የሚያሳፍረውን ስውር ነገር ጥለናልና በተንኮል አንመላለስም የእግዚአብሔርንም ቃል በውሸት አንቀላቅልም፤ እውነትን በመግለጥ ግን በእግዚአብሔር ፊት ለሰው ሕሊና ሁሉ ራሳችንን እናመሰግናለን። ³ ወንጌላችን የተከደነ ቢሆን እንኳ የተከደነባቸው ለሚጠፉ ነው። ⁴ ለእነርሱም የእግዚአብሔር ምሳሌ የሆነ የክርስቶስ የክብሩ ወንጌል ብርሃን እንዳያበራላቸው፥ የዚህ ዓለም አምላክ የማያምኑትን አሳብ አሳወረ። ⁵ ክርስቶስ ኢየሱስን ጌታ እንደ ሆነ እንጂ ራሳችንን አንሰብክምና፥ ስለ ኢየሱስም ራሳችንን ለእናንተ ባሪያዎች እናደርጋለን። ⁶ በክርስቶስ ፊት የእግዚአብሔርን የክብሩን እውቀት ብርሃን እንዲሰጥ በልባችን ውስጥ የበራ፦ በጨለማ ብርሃን ይብራ ያለ እግዚአብሔር ነውና። ⁷ ነገር ግን የኃይሉ ታላቅነት ከእግዚአብሔር እንጂ ከእኛ እንዳይሆን ይህ መዝገብ በሸክላ ዕቃ ውስጥ አለን፤ ⁸ በሁሉ እንገፋለን እንጂ አንጨነቅም፤ እናመነታለን እንጂ ተስፋ አንቆርጥም፤ ⁹ እንሰደዳለን እንጂ አንጣልም፤ እንወድቃለን እንጂ አንጠፋም፤ ¹⁰ የኢየሱስ ሕይወት ደግሞ በሥጋችን ይገለጥ ዘንድ ሁልጊዜ የኢየሱስን መሞት በሥጋችን ተሸክመን እንዞራለን። ¹¹ የኢየሱስ ሕይወት ደግሞ በሚሞት ሥጋችን ይገለጥ ዘንድ እኛ ሕያዋን የሆንን ከኢየሱስ የተነሣ ዘወትር ለሞት አልፈን እንሰጣለንና። ¹² ስለዚህ ሞቱ በእኛ ሕይወቱም በእናንተ ይሠራል። ¹³ ነገር ግን፦ አመንሁ ስለዚህም ተናገርሁ ተብሎ እንደ ተጻፈ ያው አንዱ የእምነት መንፈስ ስላለን፥ እኛ ደግሞ እናምናለን ስለዚህም እንናገራለን፤ ¹⁴ ጌታን ኢየሱስን ያስነሣው እኛን ደግሞ ከኢየሱስ ጋር እንዲያስነሣን ከእናንተም ጋር እንዲያቀርበን እናውቃለንና። ¹⁵ በብዙዎች በኩል የተትረፈረፈው ጸጋ ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋናን ያበዛ ዘንድ፥ ሁሉ ስለ እናንተ ነውና። ¹⁶ ስለዚህም አንታክትም፥ ነገር ግን የውጭው ሰውነታችን ቢጠፋ እንኳ የውስጡ ሰውነታችን ዕለት ዕለት ይታደሳል። ¹⁷-¹⁸ የማይታየውን እንጂ የሚታየውን ባንመለከት፥ ቀላል የሆነ የጊዜው መከራችን የክብርን የዘላለም ብዛት ከሁሉ መጠን ይልቅ ያደርግልናልና፤ የሚታየው የጊዜው ነውና፥ የማይታየው ግን የዘላለም ነው።

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ መጽሐፍ ቅዱስ ተሰወሮበት የነበረው የመጽሐፍ ቅዱስ                   ኘሮፌስር  ማርቲን ሉተር ❗️          ✍️ የሉተር ልደት፣ ትምህርትና የገዳም ሕይወት የኘሮቴስታን ተሐድሶ አባት የተባሉ ጀርመናዊው ዶ/ር ማርቲን ሉተር የተወለደው በኖቨምበር 10/1483 ነበር፡፡ እ.ኤ.አ በ1501 በላቲን ሥነ ጽሑፍና በፍልስፍና ከኤርፍርት ዩኒቨርሲቲ ፣ በማስተርስ ዲግሪ የተመረቀው ገና በለጋ ዕደሜው ነበር፡፡  እ.ኤ.አ በ1507 በሮማን ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ካህን ሆኖ  ተሾመ፡፡ ማርቲን ሉተር ብሩህ አዕምሮ የተቸረው ወጣት፣ ብዙ የፍልስፍና ሥራዎችን ያጠናና የቤተክርስቲያንም ካህን ቢሆንም ወንገል ያልገባው  "በሞት፣ በመለኮታዊ ፍርድና በገሃነም ፍርሃት" ይሰቃይ እንደነበር ታሪኩ ያወሳል። ከዚያም የሞት ፍርሃት ለማምለጥ ሁሉን እርግፍ አደርጎ በመተው መነኩሴ ሆኖ በኤርፎርት የቅዱስ ኦገስትን  ገዳም ገባ፡፡ ከተሰማው የነፍስ ፍርሃት ለማምለጥ ዕለት ዕለት በኑዛዜ፣ በብርቱ ጾምና ጸሎት፣ ሥጋውን በመጨቆንና በመልካም ሥራ ለመጽደቅ ይታገል ነበር፡፡ ውስጡ ግን እረፍት አልነበረውም (Here I Stand: a Life of Martin Luther. New York: Penguin, 1995, 40–42.)፡፡ መናኝ ሆኖ ለነፍሱ ጩኼት በገዳም እየታገለ  በነበረበት በዚያን ወቅት ከዊተንበርግ ዩኒቨርስቲ በbiblical studies ሁለት ዲግሪ ከዚያም የዶከትረት ዲግሪ አግኝቶ በዊተንበርግ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮት ፕሮፌሰር ሆኖ ያስተምር እንደነበር ታሪክ ይመስክራል   (James L. Schaaf, Philadelphia: Fortress Press, 1985–93, p. 93):: ሉተር ስለዚያ ጊዜ በሕይወቱ ስለነበረው ጨለማና ባዶነት ሲናገር፡-  "I lost touch with Christ the Savior and Comforter, and made of him the jailer and hangman of my poor soul." (Luther The Reformer. Minneapolis: Augsburg Fortress Publishing House, 1986, 79. ብሏል፡፡ የፍልስፍና፣ የቋንቋና የነገረ መለኮት ፕሮፌሰር መሆኑ በልቡ ከተፈጠረው ቀውስና ባዶነት አልታደገውም፡፡ ስለ እግዚአብሔር ማወቅ እግዚአብሔርን በሕይወት ማወቅ አይደለምና፡፡ ማርቲን ሉተር  የነገረ መለኮት ዶ/ር ቢሆንም  በኢየስሱ ክርስቶስ የቤዛነት ሥራ  ላመኑት ሁሉ  ቃሉ "አባ አባት ብለን የምንጮኽበትን የልጅነት መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ እንደገና ለፍርሃት የባርነትን መንፈስ አልተቀበላችሁምና" (ሮሜ.8:15) የሚለው ቃል አልበራለትም ነበር። ደግሞም "ፍጹም ፍቅር ፍርሃትን አውጥቶ ይጥላል እንጂ በፍቅር ፍርሃት የለም፥ ፍርሃት ቅጣት አለውና፤ የሚፈራም ሰው ፍቅሩ ፍጹም አይደለም"(1ዮሐ.4:18)  አልተገነዘበሞ ነበር። ✍️ ዛሬም  በነገረ መለኮት ዕውቀት መጥቀው ክርስቶስ   አልባ  ልቦች ብዙዎች ዛሬም እንደ ኢየሱስ ዘመን አይሁዶች ከኢየሱስ  ይልቅ ስለ አየሱስ በሚናገሩት መጻሕፍት ላይ ልባቸው ወድቆዋል።  መንፈሳዊ መጻሐፍት መልካም ናቸው የአዕምሮ ዕውቀት ብቻ ሆነውብን ክርስቶን በሕይወታችን ካልገለጡ  ግን አድካሚ ሸክም ናቸው። ለዚህ ነበር ኢየስሱስ በቶራ የሕግ መጻሕፍት ዕውቀት ተደግፈው እርሱን ለገፉት ለአይሁድ የነገረ መለኮት አዋቂዎች- "እናንተ በመጻሕፍት የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ይመስላችኋልና እነርሱን ትመረምራላችሁ፤ እነርሱም ስለ እኔ የሚመሰክሩ ናቸው፤ ነገር ግን ሕይወት እንዲሆንላችሁ ወደ እኔ ልትመጡ አትወዱም። "(ዮሐ.5: 39-40) ችግራቸው መጽሐፉን ያነበንቡታል እንጂ አያምኑበትም። ዛሬም ችግሩ ተመሳሳይ ነው። አንድ ሰው በሕይወቱ ክርስቶስን የግል ብቸኛ አዳኙ አድርጎ አምኖ ተቀብሎ ሳያርፍ የነገረ- መለኮትን  ሊቅ፣ ቀማር፣ መምህር መሆን እንደምችል የሉተር ሕይወት ትልቅ ምሳሌ ነው።  ዛሬም ጌታን በሕይወታቸው የማያውቁ ወይም የማያሳዩ በነገረ መለኮት እውቀታቸው፣ የመቀመርና የመተንተን ችሎታቸው እጅግ የላቁ፣ ያልታረመ ሕይወት ይዘው የሰዎችን ሰብከትና ትምህርት ለማረም የበረቱ፣ የቃሉ ሊህቃኖች በአብያተ ክርስቲያናት፣ በዓለማችን ዕውቅ ሰሜነሪዎችና የቲኦሎጂ ትምህርት ቤቶች  እጅግ ብዙ ናቸው፡፡ እውቀታቸው መልካም ነው፤ ሕይወታቸው ግን  ዕውቀታቸውን አይመስልም፡፡ ሲያገለግሉ አይታዩም ሲተቹ አይደክሙም፡፡ በእውቀት የገነቡትን በሕይወት ያፈርሳሉ፡፡ በዘመናችን ይህ አንዱና ትልቁ የቤተክርስቲያን ፈተና ሆኖዋል። ብዙዎቻችን ነገረ መለኮት  የተማረ፣ በአመክንዮ የሰላ አዕምሮና አንደበት እንጂ ጨውና ብርሃን ሆነን  ከሩቅ የሚስብ ሕይወት የለንም፡፡  አዕምሮአችንን አራሚ፣   መርማሪ፣ ጠያቂና መላሽ ብቻ አድርጎ የሠራ የነገረ መለኮት  ትምህርት የወንጌል ሰባኪ፣ አስተማሪ፣ መስካሪና  በሕይወታችን ክርስቶስን ለዓለም ካልገለጠ ተምረናል ለማለት ካልሆነ በቀር ዋጋ የለውም። ✍️ ከአዕምሮ እብጠት የተሰበረ ልብ ይቅደም❗️ ልቡ በጌታ ፍቅር የተነካና የተሰበረ ሰው በአዕምሮ ዕውቀት መታበይ አይችልም። መስቀልና መታበየ አብረው አይሄዱምና።  የጠራ፣ ክርስቶስ ተኮር፣ ለተግባራዊ አገልግሎት አጋዥ፣ በመንፈስ ቅዱስ ሙላትና ምሪት የተደገፈ የነገረ መለኮት ትምህርት ለቤተክርስቲያን አማራጭ የለሌው መለኮታዊ ስጦታና አቅም ነው።  በዓለም ላይ ያለው ሊብራል(ለቀቅተኛነት) አመለካከት ብዙ የነገረ መለኮት መምህራንን፣ ተማሪዎችንና ትምህርት ቤቶችን እየመታ ንዝረቱ በቤተክርስቲያን መድረክም ላይ በገሃድ እየተሰማ ነው። በወሳኝ ጉዳዮችና ጥያቄዎች ዙርያ ማመቻመች፣ በአንድ ጊዜ ሁሉን ማስደሰት መሞከር፣  መቀየጥ ...የሊብራል አመለካከት ተጽዕኖዎች ናቸው። ከ40 ዓመታት በላይ በዓለማችን እውቅ የነገረ መለኮት ትምህርት ቤት ያስተማሩ ፕሮፌሰር ኢግሁን አች. ፔትርሶን  "Subversive Spirituality 1994" በሚል መጽሐፋቸው፡- "የሰሚኔሪ ትምህርት አደገኛ ነው፡፡ ብዙዎች በመማሪያ ክፍልና በቤተመጻሕፍት ክፍል ውስጥ እምነታቸውን አጥተዋል" ብለዋል፡፡ ይህ እጅግ ያስደነግጣል፡፡   ቤተክርስቲያን ቃሉን  ተምረው መጥተው ያስተምሩኛል ብላ ወደ ሰሜነሪ  የላከቻቸው ተማሪዎች እምነታቸው ጥለው ዲግሪ ይዘው ሲመጡ❓ እኚህ እውቅ የዘርፉ ፕሮፌሰር የነገረ-መለኮት ትምህርት እያጣጣሉ ወይንም እየተቃወሙ ሳይሆን አዎንታዊ ጥቅሙ ብቻ ሳይሆን አሉታዊ ተጽዕኖውንም ለማሳየት ፈለገው ነው፡፡ ይህም ነገረ-መለኮት እንዳይበረዝ ተግተን መጠበቅ፤ ደግሞም መማርና ማስተማር ብቻውን የሰውን ሕይወት እንደማይለውጥ በግልጽ ያሳያል፡፡ እውቀት ጥሩ ነው፤ ከሕይወት ጋር ካልሄደ ዋጋ የለም፡፡ ሚዛናዊ መሆን ያሻል፡፡ ማርቲን ሉተር በእውነት የነገረ መለኮት ትምህርት መማር ማለት ምን እንደሆነ ሲናገር፡- "አንድ ሰው የሥነ መለኮት ዐዋቂ የሚያደርገው ማወቁ፣ ማንበቡ፣ ወይንም ማመዛዘኑ ሳይሆን መኖሩ፣ እንዲያው መኖሩ ሳይሆን ለራሱ መሞቱና በሕይወቱ ሌላውን መኮነኑ ነው" (WA 2:28b) ብለዋል፡፡ በአጭሩ ከዕውቀት፣ ከማንበብ፣ ከማመዛዘንና ከመተንተን ችሎታ ይልቅ ነገረ መለኮት መማራችንን በሕይወት፣ ለራሳችን ምኞትና ፈቃድ በመሞትና ሌላው ምሳሌ በሚሆን ሕይወት መግለጥ ነው ይለናል፡፡ ወገኖቼ፡- እኛ ምን እንመስላለን? በተለይ ነገረ መለኮትን የመማር ዕድል ያገኘን ሰዎች? ✍️   ለማርቲን ሉተር የእግዚአብሔር በቃሉ መገለጥ❗️ <<ይቀጥላል >>

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ መዝሙር 42 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ፥ አቤቱ፥ እንዲሁ ነፍሴ ወደ አንተ ትናፍቃለች። ² ነፍሴ ወደ ሕያው አምላክ ተጠማች፤ መቼ እደርሳለሁ? የአምላክንስ ፊት መቼ አያለሁ? ³ ዘወትር፦ አምላክህ ወዴት ነው? ሲሉኝ እንባዬ በቀንና በሌሊት ምግብ ሆነኝ። ⁴ ይህን ሳስብ ነፍሴ በእኔ ውስጥ ፈሰሰች፥ ወደ እግዚአብሔር ቤት ወደ ምስጋና መኖሪያ ስፍራ እገባለሁና፤ በዓል የሚያደርጉ ሰዎች የደስታና ምስጋና ቃል አሰሙ። ⁵ ነፍሴ ሆይ፥ ለምን ታዝኛለሽ? ለምንስ ታውኪኛለሽ? የፊቴን መድኃኒት አምላኬን አመሰግነው ዘንድ በእግዚአብሔር ታመኚ። ⁶ አምላኬ ሆይ፥ ነፍሴ በእኔ ውስጥ ታወከች፤ ስለዚህ በዮርዳኖስ ምድር በአርሞንኤምም በታናሹ ተራራ አስብሃለሁ። ⁷ በፍዋፍዋቴህ ድምፅ ቀላይ ቀላይን ትጠራታለች፤ ማዕበልህና ሞገድህ ሁሉ በላዬ አለፈ። ⁸ እግዚአብሔር በቀን ቸርነቱን ያዝዛል፥ በሌሊትም ዝማሬው በእኔ ዘንድ ይሆናል፤ የእኔ ስእለት ለሕይወቴ አምላክ ነው። ⁹ እግዚአብሔርን፦ አንተ መጠጊያዬ ነህ፤ ለምን ረሳኸኝ? ጠላቶቼ ሲያስጨንቁኝ ለምን አዝኜ እመላለሳለሁ? እለዋለሁ። ¹⁰ ጠላቶቼ ሁልጊዜ፦ አምላክህ ወዴት ነው? ባሉኝ ጊዜ አጥንቶቼን እየቀለጣጠሙ ሰደቡኝ። ¹¹ ነፍሴ ሆይ፥ ለምን ታዝኛለሽ? ለምንስ ታውኪኛለሽ? የፊቴን መድኃኒት አምላኬን አመሰግነው ዘንድ በእግዚአብሔር ታመኚ።

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ #በክርስቶስ_ያገኘነው_ጽድቅ (2) ጽድቅ ለዕብራውያን አንድ ሰው በስነምግባር ፍፁም መሆኑን የሚያሳይበት ሀሳብ አይደለም። ነገር ግን ሕግን በመተላለፍ ጥፋተኛ አይደለህምና /አይደለምሽምና/ በሕግና በመንግሥት ፊት ፃድቅ ነህ /ነሽ/ ማለት ነው። እኔ ክርስቶስ ወደ ምድር ወርዶ በከፈለልኝ ዋጋ ጽድቅን አግኝቻለሁ፤ ያዋጣውት፥ የደከምኩት ምንም ነገር የለም። ክርስቶስ ስለኔ ሕግን ፈፅሟል፤ ሕግ በእግዚአብሔር ፍቅር ፍጻመ አግኝቷል። #እኔ_በእርሱ_ሆኘ_አሁን_ኩነኔ_የለብኝም_ጸድቅያለሁ!! ኩነኔ ለመስበክም ለማስተማርም ጊዜ የለኝም። በክርስቶስ የጸደቀ ከኩነኔ ላይታረቅ ተለያይቷል። "እንግዲህ በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን ኵነኔ የለባቸውም" (ሮሜ 8:1)። "ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፣ አዲስ ሆኖአል" (2ኛ ቆሮንቶስ 5:17 አ.መ.ት)። 🙆 ይሄን ጽድቅ መፅሐፍ ቅዱስ እንደዚህ ይለዋል፤ #ስጦታ_ነው!! "በአንዱም በደል ሞት በአንዱ በኩል ከነገሠ፥ ይልቁን የጸጋን ብዛትና የጽድቅን ስጦታ ብዛት የሚቀበሉ በአንዱ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በሕይወት ይነግሣሉ" (ሮሜ 5:17)። #በጸጋ_ነው!! "በኢየሱስ ክርስቶስም በሆነው ቤዛነት በኩል እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉ" (ሮሜ 3:24)። #በእምነት_ብቻ_የሚገኝ_ነው!! "የዓለምም ወራሽ እንዲሆን ለአብርሃምና ለዘሩ የተሰጠው የተስፋ ቃል በእምነት ጽድቅ ነው እንጂ በሕግ አይደለም" (ሮሜ 4:13)። #በእግዚአብሔር_የተቆጠረልን_ጽድቅ_ነው!! "ለእግዚአብሔርም ክብር እየሰጠ፥ የሰጠውንም ተስፋ ደግሞ ሊፈጽም እንዲችል አጥብቆ እየተረዳ፥ በእምነት በረታ እንጂ በአለማመን ምክንያት በእግዚአብሔር ተስፋ ቃል አልተጠራጠረም። ስለዚህ ደግሞ ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት" (ሮሜ 4:20-21)። #በክርስቶስ_ነው!! "ነገር ግን፡ የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ ተብሎ እንደ ተጻፈው ይሆን ዘንድ፥ ከእግዚአብሔር ዘንድ ጥበብና ጽድቅ ቅድስናም ቤዛነትም በተደረገልን በክርስቶስ ኢየሱስ የሆናችሁ ከእርሱ ነው።" (1ቆሮ 1:30-31) #በክርስቶስ_የሚያሚኑ_ሁሉ_የሚፀድቁበት_ጽድቅ_ነው_ይላል። "የሚያምኑ ሁሉ ይጸድቁ ዘንድ ክርስቶስ የሕግ ፍጻሜ ነውና" (ሮሜ 10:4)። #ሕግን_በመፈጸም_የማይገኝ ጽድቅ ነው ይለዋል!! "የሚያምኑ ሁሉ ይጸድቁ ዘንድ ክርስቶስ የሕግ ፍጻሜ ነውና። ይህም የሕግን ሥራ በመሥራት ሥጋ የለበሰ ሁሉ በእርሱ ፊት ስለማይጸድቅ ነው፤ ኃጢአት በሕግ ይታወቃልና። አሁን ግን በሕግና በነቢያት የተመሰከረለት የእግዚአብሔር ጽድቅ ያለ ሕግ ተገልጦአል፥(ሮሜ 3:20-21) 👉 ታዲያ ሕግ ለምን ተሰጠ? ስንል ... ❶ ሃጥያትን ለመግለጥ “ይህም የሕግን ሥራ በመሥራት ሥጋ የለበሰ ሁሉ በእርሱ ፊት ስለማይጸድቅ ነው፤ ኃጢአት በሕግ ይታወቃልና” (ሮሜ 3፥20)። [ሮሜ 7፤ 7-9፤ ገላ 3:19-21፤ 1ኛ ቆሮ 15:55-56 ይመልከቱ] ❷ አፍም ሁሉ ይዘጋ ዘንድ፤ (ኢዮ 5:16፤ ሕዝ 16:63) “አፍም ሁሉ ይዘጋ ዘንድ ዓለምም ሁሉ ከእግዚአብሔር ፍርድ በታች ይሆን ዘንድ ሕግ የሚናገረው ሁሉ ከሕግ በታች ላሉት እንዲናገር እናውቃለን፤” (ሮሜ 3፥19) ❸ ወደ ክርስቶስ የሚያመጣ ሞግዚት ስለሆነ፤(ገላ 4:1-2) "እምነትም ሳይመጣ ሊገለጥ ላለው እምነት ተዘግተን ከሕግ በታች እንጠበቅ ነበር። እንደዚህ በእምነት እንጸድቅ ዘንድ ሕግ ወደ ክርስቶስ የሚያመጣ ሞግዚታችን ሆኖአል፤ እምነት ግን መጥቶአልና ከእንግዲህ ወዲህ ከሞግዚት በታች አይደለንም" (ገላትያ 3፤ 23-25)። ❹ የጽድቅን መለኪያ ለማስቀመጥ፤ “በዓይናችሁ ፊት ዛሬ እንደማኖራት እንደዚህች ሕግ ሁሉ ጽድቅ የሆነች ሥርዓትና ፍርድ ያለው ታላቅ ሕዝብ ማን ነው?” (ዘዳግም 4፥8)፤ [ዘሌ 11:44-45፤ ሮሜ 7:12-14] ❺ መሲሁ የሚመጣበትን ዘር ለመጠበቅ፤ “ሐማም ንጉሡን አርጤክስስን፦ አንድ ሕዝብ በአሕዛብ መካከል በመንግሥትህ አገሮች ሁሉ ተበትነዋል፤ ሕጋቸውም ከሕዝቡ ሁሉ ሕግ የተለየ ነው፥ የንጉሡንም ሕግ አይጠብቁም፤ ንጉሡም ይተዋቸው ዘንድ አይገባውም” (አስቴር 3፥8)። ❻ የክርስቶስ ጥላ ስለሆነ፤ (ቆላ 2:16-18) "ሕጉ ሊመጣ ያለው የበጎ ነገር እውነተኛ አምሳል ሳይሆን የነገር ጥላ አለውና፥ ስለዚህም በየዓመቱ ዘወትር በሚያቀርቡት በዚያ መሥዋዕት የሚቀርቡትን ሊፈጽም ከቶ አይችልም። እንደዚህማ ባይሆን፥ የሚያመልኩት አንድ ጊዜ ነጽተው ከዚያ በኋላ በሕሊናቸው ኃጢአትን ስላላወቁ ማቅረብን በተዉ አልነበረምን?" (ዕብራውያን 10፤ 1-2) ❼ እንዲገድል እና እንዲኮንን፤ (2ኛ ቆሮ 3:9) "ዳሩ ግን የእስራኤል ልጆች ስለዚያ ስለ ተሻረው ስለ ፊቱ ክብር የሙሴን ፊት ትኩር ብለው መመልከት እስኪሳናቸው ድረስ፥ ያ በፊደላት በድንጋዮች ላይ የተቀረጸ የሞት አገልግሎት በክብር ከሆነ፥" የኵነኔ አገልግሎት ክብር ከሆነ፥ ይልቅ የጽድቅ አገልግሎት በክብር አብዝቶ ይበልጣልና" (2ኛ ቆሮ 3፤7&9)። ❽ ሰው እራሱን ማዳን እንደማይችል ለማሳየት። “ይህም የሕግን ሥራ በመሥራት ሥጋ የለበሰ ሁሉ በእርሱ ፊት ስለማይጸድቅ ነው፤ ኃጢአት በሕግ ይታወቃልና” (ሮሜ 3፥20)። (ኢዮ 25:4፤ መዝ 103:3-4) ዶ/ር ሰብስቤ [ሰቢ]

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ መዝሙር 63 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ አምላኬ፥ አምላኬ፥ ወደ አንተ እገሠግሣለሁ፤ ነፍሴ አንተን ተጠማች፥ ሥጋዬ አንተን እንዴት ናፈቀች እንጨትና ውኃ በሌለበት በምድረ በዳ። ² ኃይልህንና ክብርህን አይ ዘንድ እንዲሁ በመቅደስ ውስጥ ተመለከትሁህ። ³ ምሕረትህ ከሕይወት ይሻላልና ከንፈሮቼ ያመሰግኑሃል። ⁴ እንዲህ በሕይወቴ ዘመን አመሰግንሃለሁ፥ በአንተም ስም እጆቼን አነሣለሁ። ⁵ ነፍሴ በቅቤና በስብ እንደሚጠግቡ ትጠግባለች፥ ከንፈሮቼም ስምህን በደስታ ያመሰግናሉ። ⁶ በመኝታዬም አስብሃለሁ፥ በማለዳም እናገርልሃለሁ፤ ⁷ ረዳቴ ሆነኸኛልና፥ በክንፎችህም ጥላ ደስ ይለኛልና። ⁸ ነፍሴ በኋላህ ተከታተለች፥ እኔንም ቀኝህ ተቀበለችኝ። ⁹ እነርሱ ግን ነፍሴን ለከንቱ ፈለጓት፤ ወደ ምድር ጥልቅ ይገባሉ። ¹⁰ ለሰይፍ እጅ አልፈው ይሰጣሉ፥ የቀበሮም እድል ፈንታ ይሆናሉ። ¹¹ ንጉሥ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለዋል፤ በእርሱ የሚምል ሁሉ ይከብራል፥ ሐሰትን የሚናገር አፍ ይዘጋልና።

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ #በክርስቶስ_ያገኘነው_ጽድቅ  (1) ጽድቅ በእኛ ትጋትና ሥራ ያልተገኘ በክርስቶስ ሥራ በማመነናችን ብቻ የተሰጠን ስጦታ መሆኑ መዘንጋት የለበትም። መዳናችን እንኳን በልጁ በኢየሱስ ሞትና ትንሣኤ በማመን እንጂ በእግዚአብሔር ፊት አሳማኝ ሥራ ሰርተን አይደለም። ጽድቅ መልካም ሥራ በመስራት የምናገኘው ሳይሆን እግዚአብሔር በልጁ በክርስቶስ ሰርቶ ለእኛ የቆጠረልን ድንቅ ሥጦታ ነው። "እኛ በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንድንሆን፣ ኀጢአት የሌለበትን እርሱን እግዚአብሔር ስለ እኛ ኀጢአት አደረገው"(2ኛ ቆሮንቶስ 5:21 አ.መ.ት)። ጽድቅ (RIGHTEOUSNESS) በዕብራይስጥ TSEDEQ ማለት ሲሆን ትክክል (Right) ወይም ትክክለኛነት (Equity) ማለት ነው። በእግዚአብሔር ፊት የእኛ ጽድቅ ወይም ትክክለኝነት በእኛ ምትክ ክርስቶስ በመስቀል ላይ የሠራው ሥራ ነው። በክርስቶስ ጻድቅ የተባልነው የእርሱ ሥራ ለእኛ ተቆጥሮልን እንጂ አንዳች በጎ ነገር አስቆጥረን አይደለም። ጻድቃን ተደርገን እንጂ ለጽድቃችን ምንም አስተዋጽኦ አድርገን አይደለም። ያገኘነው ጽድቅ ምንም የእኛ አስተዋጽኦ የሌለበት በማመን ብቻ በክርስቶስ ሥራ ለእኛ የተቆጠረልን ነው። ➮ ሰው የተባለ ሁሉ ከአዳም ጀምሮ በእግዚአብሔር ፊት ትክክልና ትክክለኛ የሚያሰኘውን ሥራ መፈጸም ባለመቻሉ እግዚአብሔር በክርስቶስ አማካኝነት በገዛ ክንዱ በሰው ልጆች ምትክ ትክክል የሆነውን ሥራ ሰርቶ ለእኛ ቆጠረልን። “ሰውም እንደሌለ አየ፥ ወደ እርሱ የሚማልድ እንደሌለ ተረዳ ተደነቀም፤ ስለዚህ የገዛ ክንዱ መድኃኒት አመጣለት፥ ጽድቁም አገዘው” (ኢሳይያስ 59፥16)። ጽድቅ ማለት ያለምንም ኩነኔ፥ ያለምንም ሃፍረት፥ ያለምንም ፍርሃት እና ጭንቀት፥ ያለምንም መሸማቀቅ በእግዚአብሔር ፊት የመቆም መብት ማግኘት ማለት ነው። እሱም በክርስቶስ ሥራ ያገኘነው በእግዚአብሔር ፊት የመቆም ሙሉ መብታችን ነው። #ጽድቀ_ክርስቶስን_በማመን_ብቻ_ያገኘሁት_ነው የሥራዬ ወይም የድካሜ ውጤት አይደለም። "በወንጌል የእግዚአብሔር ጽድቅ ተገልጦአልና፤ ጽድቁም ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ በእምነት የሆነ ነው፣ “ጻድቅ በእምነት ይኖራል” ተብሎ እንደ ተጻፈው"(ሮሜ 1:17 አ.መ.ት)። ፅድቅ በእግዚአብሔር በአባታችን ፊት ቀርቦ የመናገርና መልስ የመቀበልን መብት ማግኘት ነው። 👉 እኔ እግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ በተሰራልኝ ሥራ እንዲሁ በሥራው ጸድቂያለሁ። ጻድቅ ትክክል ተብሎ አዋጅ የታወጀለት፤ በፍርድ ፊት ቆሞ "ንፁህ ነህ ነቀፋ የለብህም" ተብሎ በአዋጅ የተመሠከረለት ሰው ማለት ነው። አንድ ሰው በእግዚአብሔር ፊት ትክክል ስለመሆኑ የተነገረለት ማለት ነው። ጻድቅ እንደሆነ የታወጀለት እንዲሁም ፍርድ ቤት ቀርቦ በዳኛ ንፁህ ነህ ተብሎ አዋጅ የወጣለት ሰው ማለት ነው። የክርስቶስ ትክክለኝነት ለኔ ተቀጥሮልኝ ጻድቅ ተብያለሁ። ይሄ ሁሉ የሆነው በክርስቶስ ስራና ሥራ ብቻ ነው። #ጽድቃችን_እግዚአብሔር_ነውና። "በእርሱም ዘመን ይሁዳ ይድናል፤ እስራኤልም በሰላም ይኖራል፤ የሚጠራበትም ስም፣ ‘እግዚአብሔር ጽድቃችን’ የሚል ነው"(ት. ኤር 23:6 ፤ ት. ኤር 33:16 አ.መ.ት)። ይሄ የኢሳይያስ ትንቢት በክርስቶስ አሁን አምነው ባሉት ተፈጽሟል፤ ጽድቃችን ከእግዚአብሔርና እግዚአብሔር ነው። ጽድቅ ለመልካም ባህሪ ወይም ሥራ የሚሰጥ ሽልማት አይደለም። "ይህ የእግዚአብሔር ጽድቅ ኢየሱስ ክርስቶስን በማመን የሚገኝ ጽድቅ ነው"(ሮሜ 3:22 አ.መ.ት)። #ጽድቀ_በክርስቶስ_ኢየሱስ_የሆንኩት_ነገር_ነው፤ በክርስቶስ ማን እንደሆንን፥ ምን እንደሆንን ካላወቅን የፅድቅና የአሸናፊነት ሕይወት መኖር አንችልም፤ ምክንያቱም ሰይጣንና በሽታ አለቃችን ይሆናል። #አሜሪካዊው_ጆናታን_ኤድዋርድ_እንዲህ_ብሎ_ነበር "በራስህ ጽድቅ የሚትታመንበት ምንም አይነት ምክንያት ካለ በክርስቶስ አንተን ወይም አንቺን ለማዳን እግዚአብሔር ያዘጋጀው መንገድ ሁሉ ከንቱ ልፋት ነው ማለት ነው" ብሏል። ፅድቅ የበጎ ሥራችን ውጤት አይደለም፤ ክርስቶስን በማመን የሚገኝ የእግዚአብሔር ቸርነት /ሥጦታ ነው። "አንድ ሰው ሥራ ከሠራ ደመወዙ እንደ ስጦታ ሳይሆን እንደ ተገቢ ዋጋው ይቈጠርለታል።  ነገር ግን ለማይሠራው፣ ኃጥኡን ሰው ጻድቅ በሚያደርግ በእግዚአብሔር ለሚያምን ሰው፣ እምነቱ ጽድቅ ሆኖ ይቈጠርለታል" (ሮሜ 4:4-5 አ.መ.ት)። ምንጭ።፦ ዶ/ር ሰብስቤ [ሰቢ]

#የቃሉን_ወተት_ተመኙ ሮሜ 14 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ በእምነት የደከመውንም ተቀበሉት፥ በአሳቡም ላይ አትፍረዱ። ² ሁሉን ይበላ ዘንድ እንደ ተፈቀደለት የሚያምን አለ፥ ደካማው ግን አትክልት ይበላል። ³ የሚበላ የማይበላውን አይናቀው የማይበላውም በሚበላው አይፍረድ፥ እግዚአብሔር ተቀብሎታልና። ⁴ አንተ በሌላው ሎሌ የምትፈርድ ማን ነህ? እርሱ ቢቆም ወይም ቢወድቅ ለገዛ ጌታው ነው፤ ነገር ግን እግዚአብሔር ሊያቆመው ይችላልና ይቆማል። ⁵ ይህ ሰው አንድ ቀን ከሌላ ቀን እንዲሻል ያስባል፥ ያ ግን ቀን ሁሉ አንድ እንደ ሆነ ያስባል፤ እያንዳንዱ በገዛ አእምሮው አጥብቆ ይረዳ። ⁶ ቀንን የሚያከብር ለጌታ ብሎ ያከብራል፤ የሚበላም እግዚአብሔርን ያመሰግናልና ለጌታ ብሎ ይበላል፤ የማይበላም ለጌታ ብሎ አይበላም እግዚአብሔርንም ያመሰግናል። ⁷ ከእኛ አንድ ስንኳ ለራሱ የሚኖር የለምና፥ ለራሱም የሚሞት የለም፤ ⁸ በሕይወት ሆነን ብንኖር ለጌታ እንኖራለንና፥ ብንሞትም ለጌታ እንሞታለን። እንግዲህ በሕይወት ሆነን ብንኖር ወይም ብንሞት የጌታ ነን። ⁹ ስለዚህ ነገር ሙታንንም ሕያዋንንም ይገዛ ዘንድ ክርስቶስ ሞቶአልና ሕያውም ሆኖአልና። ¹⁰ አንተም በወንድምህ ላይ ስለ ምን ትፈርዳለህ? ወይስ አንተ ደግሞ ወንድምህን ስለ ምን ትንቃለህ? ሁላችን በክርስቶስ ፍርድ ወንበር ፊት እንቆማለንና። ¹¹ እኔ ሕያው ነኝ፥ ይላል ጌታ፥ ጉልበት ሁሉ ለእኔ ይንበረከካል መላስም ሁሉ እግዚአብሔርን ያመሰግናል ተብሎ ተጽፎአልና። ¹² እንግዲያስ እያንዳንዳችን ስለ ራሳችን ለእግዚአብሔር መልስ እንሰጣለን።