271
Subscribers
No data24 hours
-17 days
-230 days
Data loading in progress...
Similar Channels
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+1
in 0 channels
August '26
+1
in 0 channels
Get PRO
July '260
in 0 channels
Get PRO
June '260
in 0 channels
Get PRO
May '260
in 0 channels
Get PRO
April '260
in 0 channels
Get PRO
March '260
in 0 channels
Get PRO
February '260
in 0 channels
Get PRO
January '260
in 0 channels
Get PRO
December '250
in 0 channels
Get PRO
November '250
in 0 channels
Get PRO
October '250
in 0 channels
Get PRO
September '250
in 0 channels
Get PRO
August '250
in 0 channels
Get PRO
July '250
in 0 channels
Get PRO
June '250
in 0 channels
Get PRO
May '250
in 0 channels
Get PRO
April '250
in 0 channels
Get PRO
March '250
in 0 channels
Get PRO
February '250
in 0 channels
Get PRO
January '250
in 0 channels
Get PRO
December '24
+1
in 0 channels
Get PRO
November '24
+4
in 0 channels
Get PRO
October '24
+3
in 0 channels
Get PRO
September '24
+263
in 0 channels
Get PRO
August '24
+390
in 1 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 08 September | 0 | |||
| 07 September | 0 | |||
| 06 September | 0 | |||
| 05 September | 0 | |||
| 04 September | +1 | |||
| 03 September | 0 | |||
| 02 September | 0 | |||
| 01 September | 0 |
Channel Posts
ትግራይ ክልል ተማሪ ላይመደብ ይችላል
በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ከወታደራዊ እንቅስቃሴ ነፃ እንዲሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር አሰሰሰበ።
ትምህርት ሚኒስቴር በትግራይ ክልል በሚገኙ አራት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መቀሌ፣ አክሱም፣ አዲግራት እና ራያ ዩኒቨርሲቲዎች ግቢ ውስጥ የሚገኙ የጦር ቄስፎች እና ታጣቂዎች በአስቸኳይ እንዲነሱና ግቢዎቹ ከማንኛውም ወታደራዊ እንቅስቃሴ ነፃ እንዲደረጉ ጥብቅ ማሳሰቢያ አስተላለፈ።
ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ለዩኒቨርሲቲዎቹ ፕሬዚዳንቶች በላኩት ደብዳቤ፣ በካምፓሶቹ ውስጥ የወታደራዊ ኃይሎችና የትጥቅ እንቅስቃሴዎች መኖራቸው የተማሪዎችን ደህንነትና ሰላማዊ የመማር-ማስተማር ሂደት አደጋ ላይ እንደሚጥል ገልጸዋል።
ሚኒስቴሩ አክሎም፣ የዩኒቨርሲቲዎቹ ግቢዎች ሙሉ በሙሉ ከወታደራዊ እንቅስቃሴ ነፃ መሆናቸው በበቂ ሁኔታ ካልተረጋገጠ ሚኒስቴሩ ወደ ተቋማቱ ተማሪዎችን እንደማይመድብ አስታውቋል።
በጦርነቱ የተጎዱ እና የቆሰሉ ታጣቂዎች ሰሞኑን ወደ አዲግራት፣አክሱምና መቀሌ ዩኒቨርስቲ ሲገቡ እንደነበር አዩዘሀበሻ መዘገቡ ይታወሳል።
| 2 | 16 አዳዲስ መርከቦች ሊገዙ ነው‼️
የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የውጪና ገቢ ንግድን ለማቀላጠፍ በ83 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር ወጪ 16 አዳዲስ መርከቦችን ለመግዛት ማቀዱን አስታወቀ፡፡
የተቋሙ የዕቅድና ክትትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ስንታየሁ ኃይለማርያም እንደገለፁት፤ ግዥው በቀጣይ አምስት ዓመታት የሚፈፀም ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የስድስት መርከቦች ግዥ ሂደት ተጀምሯል፡፡
ሃገሪቱ አሁን ካሏት 10 መርከቦች በተጨማሪ የሚገዙት እነዚህ አዳዲስ መርከቦች፣ ከ50 ሺህ እስከ 63 ሺህ ቶን የመጫን አቅም ያላቸውና ከቀድሞቹ በእጥፍ የሚበልጡ ግዙፍ መርከቦች ናቸው፡፡
መርከቦቹ ስትራቴጂካዊ ግብዓቶችን በፍጥነት ለማጓጓዝ ጉልህ ድርሻ አላቸው፡፡ ተቋሙ በበጀት ዓመቱ 3 ነጥብ 9 ሚሊዮን ቶን ዕቃ ማጓጓዝ መቻሉና አገሪቱ የባሕር በር ባለቤት የመሆን ሕልሟን ለማሳካት የምታደርገውን ጥረት ታሳቢ ያደረጉ ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑም ተገልጿል፡፡ | 8 |
| 3 | ሰበር ዜና፦ ዶሚኒካን ሪፐብሊክ የ75ኛውን የዓለም ቁንጅና ዘውድ አሸነፈች!
በዓለም ዙሪያ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተመልካቾችን ቀልብ ሲስብ የቆየው የ75ኛው የዓለም ቁንጅና ውድድር (Miss World) ፍጻሜ አግኝቶ የአሸናፊዎች ዝርዝር ይፋ ሆኗል!
የአሸናፊዎች ደረጃ፦
1ኛ (የዘውዱ ባለቤት)፦ 🇩🇴 ዶሚኒካን ሪፐብሊክ
2ኛ (1st Runner-Up)፦ 🇪🇸 ስፔን
3ኛ (2nd Runner-Up)፦ 🇲🇾 ማሌዢያ
* የዶሚኒካን ሪፐብሊክ ተወዳዳሪ አስደናቂ ብቃት በማሳየት የዘንድሮውን የዓለም ቁንጅና ዘውድ መደፋት ችላለች!
• የኤርትራዋ ተወዳዳሪ በሕዝብ ድምፅና በጠንካራ ውድድር ወደ ታላቁ Top 6 በመቀላቀል የአፍሪካና የቀጣናችን ኩራት ሆና ውድድሯን አጠናቃለች።
• ኤርትራ እና ደቡብ አፍሪካ ወደ መጨረሻው ዙር አልፈው ድንቅ የውድድር ጊዜን አሳልፈዋል። | 11 |
| 4 | ዜና: #ጣሊያን በ #ዓባይ_ውኃ ዙሪያ #በግብፅና #በኢትዮጵያ መካከል የሚደረግን ውይይት ለማመቻቸት ጥያቄ አቀረበች
ጣሊያን በዓባይ ውኃ ዙሪያ በግብፅና በኢትዮጵያ መካከል የሚደረግ ውይይት ለማመቻቸት ፍላጎት ያሳየች ሲሆን፣ ሁለቱ ሀገራት በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት ፍትሐዊና ዘላቂ በሆነ በድርድር የሚገኝ መፍትሔ ላይ እንዲደርሱ ጥሪ አቀረበች።
የጣሊያን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒዮ ታጃኒ ይህንን ጥያቄ ያቀረቡት በግብፅ ኤል አላሜይን ከግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደላቲ ጋር ከተወያዩ በኋላ በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።
አንቶኒዮ ታጃኒ፣ ሁለቱም ሀገራት ከተስማሙ ሮም ለማሸማገል ወይም ውይይቱን ለማመቻቸት ዝግጁ መሆኗን ገልጸው፣ ጣሊያን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት የረጅም ጊዜ ውዝግቡን ለመፍታት ለሚደረጉ ጥረቶች እንደ አንድ በጎ ግብአት ጠቅሰዋል።
https://addisstandard.com/Amharic/?p=14019 | 13 |
| 5 | የግብር ስወራ የፈጸሙ የመኪና አስመጪዎች ላይ ዕርምጃ መወሰዱን የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ አሳወቀ።
በመኪና አስመጪነት የንግድ ፈቃድ አውጥተው፤ ያስመጧቸውን ተሽከርካሪዎች በራሳቸው መሸጫ ቦታ ከመሸጥ ይልቅ በኮሚሽን ኤጀንቶች አማካኝነት በመሸጥ የግብር ስወራ የፈጸሙ 7 አስመጪዎች ላይ ዕርምጃ መወሰዱን ቢሮ አስታውቋል።
የቢሮው የሕግ ተገዢነት ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ መሐመድ አብዱራህማን፣ " በሕገ-ወጥ የግብር ስወራ ተግባር መሳተፋቸው በጥናት የተረጋገጠባቸው ግለሰቦችና ድርጅቶች ላይ ሱቆችን ማሸግና ጊዜያዊ ፈቃድ እገዳ ተጥሏል " ብለዋል።
" እነዚህ አካላት የአስመጪነት ፈቃዳቸውን ተጠቅመው ራሳቸው ካስመጧቸው ውጪ ከሶስተኛ ወገን ጭምር ተቀብለው በመሸጥ ሕግን ተላልፈው መገኘታቸው ተረጋግጧል " ሲሉም ገልጸዋል።
በተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ቁጥር 1341/2017 መሠረት የንግድ ሥራ በተፈቀደለት ቦታና በተመዘገበው የንግድ ዘርፍ ብቻ መከናወን እንዳለበትም አብራርተዋል።
በዚህም መሠረት የመኪና አስመጪዎች ተሽከርካሪዎችን መሸጥ የሚገባቸው በራሳቸው የንግድ ፈቃድ ባወጡበት መሸጫ ቦታ ብቻ መሆኑ ተጠቁሟል።
በተያያዘም ያገለገሉ መኪኖችን የሚሸጡ የኮሚሽን ኤጀንቶች ከአገለገሉ መኪኖች ውጪ አዲስ መኪና ሲሸጡ ከተገኙ በታክስ አስተዳደር አዋጁ መሠረት የቅጣት ዕርምጃ እንደሚወሰድባቸው ቢሮው አስጠንቅቋል።
ኤጀንቶቹ ያገለገለ መኪና ሲሸጡም መረጃውን ለግብር ሰብሳቢው መሥሪያ ቤት በወቅቱ ማሳወቅ ይጠበቅባቸዋል ተብሏል።
ከሕጋዊ መሥመር ውጪ ተንቀሳቅሰዋል የተባሉት አስመጪዎች አሰራራቸውን አስተካክለው በፍጥነት ወደ ሕጋዊ መሥመር እንዲመለሱ ማሳሰቢያ ተላልፏል።
ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ/ም | 21 |
| 6 | " አደጋው ያጋጠመው የማህበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ ቋንቋ ት/ት ክፍል ህንጻ ላይ ነው "
ዛሬ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ ውስጥ በሚገኘው የማህበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ ቋንቋ ት/ት ክፍል ህንጻ ላይ እስካሁን ባልታወቀ ምክንያት ድንገተኛ የእሳት አደጋ ተከስቶ ነበር።
አደጋው በዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ እና በፀጥታ ሀይሎች እና የእሳት አደጋ መከላከል ባለሙያዎች ብርታት በቁጥጥር ስር ሊውል እንደቻለ ከወላይታ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
በአደጋው የደረሰው ጉዳት እና መንስኤ እየተጣራ ይገኛል።
ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ/ም | 20 |
| 7 | በሀሰተኛ ሰነድ ማጭበርበር ወንጀል ተፈርዶባቸው በእስር ላይ የነበሩት ቀሲስ በላይ መኮንን ከእስር መፈታታቸው ተገለጸ።
ቀሲስ በላይ ከ 2 አመት የእስር ቆይታ በኋላ ዛሬ ጠዋት ከእስር ተፈተው በአሁኑ ሰዓት ከቤተሰቦቻቸው ጋር ተቀላቅለዋል።
ግለሰቡ በሐሰተኛ ሰነድ ከአፍሪካ ኅብረት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት 6 ሚሊዮን 50 ሺህ ዶላር ለማውጣት በመሞከራቸው፣ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሦስተኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት የአምስት ዓመት እስራት እና የ10 ሺህ ብር ቅጣት ተፈርዶባቸው የነበረ መሆኑ ይታወሳል።
ከእሳቸው ጋር አብረው ክስ ቀርቦባቸው የነበሩት ሌሎች ሁለት ተከሳሾች ደግሞ እያንዳንዳቸው የአራት ዓመት እስራት እና የ3 ሺህ ብር ቅጣት ተወስኖባቸው እንደነበር አይዘነጋም።
ተከሳሾቹ የወንጀል ሕጉን እና የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ተላልፈዋል በሚል ጥፋተኛ ተብለው ከተፈረደባቸው በኋላ፣ ቀሲስ በላይ ከ 2 አመት የእስር ቆይታ በኋላ ዛሬ በይፋ ከእስር ተለቀዋል።
#ቀሲስበላይመኮንን #ዜና #ፍርድቤት #ፍትህ #BreakingNews #EthiopiaNews #Ethiopia | 22 |
| 8 | ከመንገድ ታፍሰው ቃሊቲ ውሃ ልማት አካባቢ ተይዘው የሚገኙ ዜጎች በተስቦ በሽታ ህይወታቸው እያለፈ መሆኑ ተሰማ- በኢትዮጵያ በተለያዩ ከተሞች በወጣቶች ላይ እየተካሄደ ያለው ህገ-ወጥ አፈሳ እና አስገዳጅ የውትድርና ምልመላ ከፍተኛ ሰብዓዊ፣ ስነ-ልቦናዊ እና የጤና ቀውስ እያስከተለ መሆኑን የህክምና ባለሙያዎች እና የዓይን እማኞች እየተናገሩ ይገኛሉ።መንግስት በመላው ሀገሪቱ በተለይም በአዲስ አበባ፣ አዳማ፣ ባሕር ዳር፣ ዝዋይ (ባቱ) እና እንዲሁም የትግራይ ባለስልጣናት በክልሉ ከተሞች ወጣቶችን ከመንገድ፣ ከእምነት ተቋማት እና ከመኖሪያ መንደሮች በገፍ እያፈሰ ወደ ተለያዩ ጊዜያዊ ማቆያ ስፍራዎች እና ወታደራዊ ካምፖች እያጋዙ እንደሚገኙ በቅርቡ መዘገባችን ይታወሳል።አሁን የደረሰን መረጃ እንደሚጠቁመው በአዲስ አበባ ከተማ ይህ አፈሳ በከፍተኛ ሁኔታ ከተጠናከረባቸው እና ወጣቶች በብዛት ከታሰሩባቸው ስፍራዎች መካከል "ቃሊቲ ውሃ ልማት" የተባለው አካባቢ በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል።በዚህ ስፍራ እጅግ በተጨናነቀ እና አነስተኛ የንጽህና መጠበቂያ እንኳን በሌለበት ሁኔታ በታጎሩ ወጣቶች ላይ የተስቦ በሽታ በመባል የሚታወቀው እና በሰውነት ተባይ አማካኝነት የሚተላለፍ አደገኛ ባክቴሪያዊ በሽታ በከፍተኛ ፍጥነት በመስፋፋቱ ሳቢያ በርካታ ወጣቶች በከባድ ህመም እየተሰቃዩና ህይወታቸው እያለፈ መሆኑን በአዲስ አበባ በሚገኝ አንድ የመንግስት ሆስፒታል ውስጥ የሚሰሩ የህክምና ባለሙያዎች ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።ሀኪሞቹ በሰጡት ምስክርነት መሰረት እና ከመንግስት ሆስፒታሎች በየቀኑ በሚወጣው መረጃ በዚህ የሰውነት ተባይ አምጪ በተስቦ በሽታ በርካታ ወጣቶች በህመም የሚማቅቁ ሲሆን እስካሁን ባለው የተረጋገጠ መረጃ በቃሊቲ ውሃ ልማት አካባቢ በሚገኘው ማቆያ ብቻ ቢያንስ የስድስት ሰዎች ህይወት አልፏል።ይህ በሽታ በአብዛኛው ከፍተኛ የንጽህና ጉድለት ባለባቸው የጅምላ ማቆያ ስፍራዎች የሚከሰት ወረርሽኝ መሆኑ እየታወቀ ይህን እጅግ አሳሳቢ የሆነ የጤና ቀውስ እና የዜጎች ህልፈት ለመንግስት ባለስልጣናት እና ለሚመለከታቸው አካላት ለማሳወቅ ከፍተኛ ጥረት ቢደረግም ሀቁን መቀበል ባለመፈለጋቸው እና ቸልተኝነት በማሳየታቸው ምክንያት ዜጎች ያለምንም በቂ ህክምና በየቀኑ እያለቁ ይገኛሉ በማለት የጤና ባለሙያዎቹ ተናግረዋል።ይህ በእንዲህ እንዳለ መሠረት ሚዲያን ጨምሮ የተለያዩ የዜና ምንጮች እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት እንዳረጋገጡት በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎችም ይህ አስገዳጅ አፈሳ እና የእስር ዘመቻ ተጠናክሮ ቀጥሏል።ለምሳሌ ያህል በአዳማ ከተማ "ሚዛን" ተብሎ በሚጠራው ትልቅ የፍየል ማቆያ መጋዘን ውስጥ በሺህ የሚቆጠሩ ወጣቶች ታፍነው የሚገኙ ሲሆን አንዳንዶቹን ለማስለቀቅ እስከ ሃያ ሺህ ብር ጉቦ በህገ-ወጥ ደላሎች እና ታጣቂዎች እየተጠየቀ መሆኑ ተጋልጧል።በተመሳሳይ ሁኔታ ነሐሴ 12 ቀን በባሕር ዳር ከተማ ቀበሌ 13 አካባቢ ሰፊ አፈሳ የተካሄደ ሲሆን፣ በባቱ (ዝዋይ) ከተማ ደግሞ ወጣቶች በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ውስጥ መንፈሳዊ መርሀ ግብር ላይ እያሉ ሳይቀር የጸጥታ ሀይሎች ቤተክርስቲያኑን በመክበብ አስገድደው ወስደዋቸዋል።በሌላ በኩል በትግራይ ክልል ሽራሮ እና አካባቢዋ ከሚያዝያ ወር ጀምሮ ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊ ህጻናትን ሳይቀር ያካተተ አስገዳጅ የውትድርና ምልመላ እየተካሄደ መሆኑ ተዘግቧል።ወጣቶቹ በተለያዩ ማቆያ ማዕከላት ውስጥ የታሰሩ ሲሆን ልጆቻቸው የታሰሩባቸው ወላጆች የልጆቻቸውን ሁኔታ ለመጠየቅ ወደ ስፍራው ሲያቀኑ በጸጥታ ሀይሎች ከባድ ድብደባ፣ እንግልት እና ማስፈራሪያ እየተፈጸመባቸው ይገኛል።ይህ አይነቱ ከህግ አግባብ ውጭ የሆነ የጅምላ እስር ቤተሰብን አስተዳዳሪ አሳጥቶ ለከፋ ኢኮኖሚያዊ ችግር ከመዳረጉም በላይ ወጣቶችን በአስከፊ እና ለበሽታ ተጋላጭ በሆነ ሁኔታ ውስጥ ማጎር ለተስቦ እና ለሌሎች ተላላፊ በሽታዎች ወረርሽኝ እጅግ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል።በተጨማሪም በርካታ ወጣቶች ከዚህ አፈሳ ለማምለጥ ሲሉ ትምህርታቸውን እና ስራቸውን አቋርጠው ወደ በረሃ፣ ጫካ እና አጎራባች ሀገራት ህይወታቸውን ለአደጋ አጋልጠው እንዲሰደዱ እያስገደዳቸው እንደሚገኝ መረጃዎች ያሳያሉ።የህክምና ባለሙያዎች እና የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪዎች ይህ በቃሊቲ ውሃ ልማት እና በሌሎችም ማቆያ ማዕከላት የተከሰተው የተስቦ በሽታ ወረርሽኝ ወደ አልታሰበ ሰፊ አደጋ ከማምራቱ በፊት አፋጣኝ የህክምና ጣልቃ ገብነት እንዲደረግ፣ እንዲሁም ህዝቡ እና ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይህን በዜጎች ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍ እና ሰቆቃ ተረድቶ መንግስት ይህን አፈሳ በአስቸኳይ እንዲያቆም ጠንካራ ጫና እንዲፈጥር በአጽንኦት ጥሪያቸውን እያቀረቡ ይገኛሉ።
Via መሠረት ሚድያ
https://t.me/ethio_news367 | 21 |
| 9 | No text... | 20 |
| 10 | የኮይሻ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ፕሮጀክትን ለማጠናቀቅ ተጨማሪ 500 ሚሊዮን ዩሮ እንደሚያስፈልግ ተገለጸ
የኢትዮጵያ ሁለተኛው ትልቁ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ፕሮጀክት የሆነውን የኮይሻ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ፕሮጀክትን ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ ተጨማሪ 500 ሚሊዮን ዩሮ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የተቋሙን የ2018 በጀት ዓመት ዓመታዊ የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት ዓርብ ዕለት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ ተቋማቸው በአጠቃላይ 92 በመቶ የዕቅድ አፈፃፀም ማስመዝገቡን መግለጻቸውን ዘ ሪፖርተር አስነብቧል።
በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ብቻውን የሀገሪቱን አጠቃላይ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት 52 በመቶ ያህሉን ማመንጨት መቻሉ በሪፖርቱ ላይ በዋናነት ተመልክቷል።
@ethio_news367 | 28 |
| 11 | በኢሮብ ወረዳ 35 ሺህ ህዝብ ለከባድ ድርቅ ተጋልጧል።
በትግራይ ክልል ምስራቃዊ ዞን የሚገኘው ኢሮብ ወረዳ ከባድ ድርቅ እየተጋፈጠ ሲሆን በአካባቢው የሚኖሩ 35 ሺህ የሚጠጉ ሰዎች ለድርቅ አደጋ መጋለጣቸው ተገልጿል።
በወረዳው የክረምት ዝናብ በበቂ ሁኔታ ባለመዝነቡ የውሃ ጉድጓዶች መድረቃቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል። በውሃ እጥረቱም የቤት እንስሳት መሞት መጀመራቸውን አስረድተዋል።
በወረዳው የሚገኙ ስምንት ቀበሌዎች በከፍተኛ ተራራና ተዳፋት አካባቢዎች መሆናቸው የተጀመረውን የእርዳታ ማዳረስ ስራ ፈታኝ እንዳደረገው ተጠቁሟል።
የአካባቢው አርሶ አደሮች እንደሚሉት፣ ከዚህ በፊት እንደ ዘንድሮ ያለ ከባድ ድርቅ አጋጥሟቸው አያውቅም።
የዝናብ እጥረቱ በማሳ ላይ የተዘራው እህል እንዲደርቅ ከማድረጉም በላይ በክረምት ዝናብ ይሞሉ የነበሩ የውሃ ጉድጓዶች እንዲደርቁ አድርጓል።
የኢሮብ አካባቢ የኢሮብ ብሄረሰብ የሚኖርበት ከትግራይ ምስራቃዊ ዞን ወረዳዎች አንዱ ነው። አካባቢው በ2013 ዓ.ም. በትግራይ ጦርነት ከፍተኛ ጥቃት የደረሰበት ሲሆን እስካሁንም አንዳንድ የቀበሌ ገበሬ ማህበራት በኤርትራ ሰራዊት ቁጥጥር ስር ይገኛሉ።
የድርቁ አደጋ በሰዎችና በእንስሳት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ከማስከተሉ በፊት ለጋሽ ድርጅቶች፣ ባለሀብቶችና ግለሰቦች የእርዳታ እጃቸውን እንዲዘረጉ ወረዳው ቀደም ሲል ጥሪ አቅርቧል።
በዚህ ጥሪ መሰረት አንዳንድ ግለሰቦች የእርዳታ እህል ማቅረብ መጀመራቸው ተገልጿል። ሆኖም የእንስሳት መኖ፣ የሰዎችና የእንስሳት መጠጥ ውሃ አቅርቦት እጥረት አሁንም የድርቁን ተጽዕኖ ለመቀነስ የሚደረገውን ስራ ከባድ እያደረገው እንደሆነ ተጠቁሟል።
የአካባቢው ህዝብ የውሃ፣ የምግብ እና የእንስሳት መኖ አቅርቦት በአስቸኳይ እንዲጠናከር ጥሪ እያቀረበ ነው።
Via ቲክቫህ ኢትዮጵያ | 28 |
| 12 | ምስራቅ ጉራጌ ምን ተከሰተ❓
በምስራቅ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ አጎራባች አካባቢዎች ድንበር ጥሰው የገቡ ታጣቂዎች በፈጸሙት የወረራ ጥቃት በሰው ሕይወትና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሳቸው ተገለጸ።
መነሻቸውን በኦሮሚያ ክልል አጎራባች ወረዳዎች ያደረጉና በስፋት «ሸኔ» በመባል የሚጠሩ ከባድ የቡድን መሣሪያ የታጠቁ ታጣቂዎች፣ ከነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት ጀምሮ በሶዶ ወረዳ ድንበር ጥሰው በመግባት ጥቃት መክፈታቸው ተስምቷል።
በወረዳው በሚገኙት ሱተን፣ ጢያ እና ኧሽከዲየ በተባሉ ከተሞች እንዲሁም በዙሪያው ባሉ የገጠር ቀበሌዎች በተከፈተው በዚህ ጥቃት፡
* የመኖሪያ ቤቶችና የንግድ ሱቆች በእሳት ተቃጥለዋል፤
* ከፍተኛ የንብረት ዘረፋና ውድመት ተፈጽሟል።
በጥቃቱ ሳቢያ እናቶች፣ ሕፃናትና አረጋውያን ለከፍተኛ የሕይወት አደጋ የተጋለጡ ሲሆን፣ ሱተን ከተማን በተደረገው ውጊያ የጉራጌ ዞን ፖሊስ አባላት ሕይወታቸው ማለፉ ተረጋግጧል።
ከዚህ በተጨማሪ፣ የአካባቢው ነዋሪዎች አካባቢያቸውን ለመከላከል ባደረጉት ተጋድሎ ጥቃቱን ለማስቆም ሲታገሉ የነበሩ ነዋሪዎች ሕይወት አልፏል።
የአካባቢው ነዋሪዎች እንደሚያስረዱት፣ ከአካባቢው የተመከቱት ታጣቂዎች አሁን ላይ በታሪካዊው ቆንዳልቲ ገዳም ዙሪያ ከባድ መሣሪያዎችን በመያዝ እንደገና በመከማቸት ላይ ይገኛሉ። | 29 |
| 13 | የሐምሌ ወር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ወደ 15.3 በመቶ ከፍ ማለቱን የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት ይፋ አድርጓል።
• የስኳር ዋጋ ብቻውን 39 በመቶ በላይ ጭማሪ ማሳየቱን ሪፖርቱ አመልክቷል።
የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት ይፋ ባደረገው ወርሃዊ የዋጋ ግሽበት መረጃ በሐምሌ 2018 ዓ.ም የተመዘገበው አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት 15.3 በመቶ በመድረስ ካለፉት ወራት አንጻር ከፍተኛ ጭማሪ አሳይቷል።
ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወር ማለትም ከሐምሌ 2017 ዓ.ም (13.7 በመቶ) ጋር ሲነጻጸር ጎልቶ የሚታይ ልዩነት ያለው ነው።
አገልግሎቱ ባወጣው ሪፖርት መሠረት፣ የምግብና አልኮል ያልሆኑ መጠጦች ዋጋ 15.7 በመቶ የጨመረ ሲሆን፣ ለዚህ በዋነኝነት አስተዋጽኦ ያደረጉት ደግሞ ፦
• ስጋ በ21.6%፣
• ስኳር በ39.4% ፣
• ዘይት በ20.34%፣
• ፍራፍሬ በ19.2%፣
• የወተት ተዋጽኦዎች እንቁላል በ18.9% እና አትክልት በ13.6% ጭማሪ አሳይተዋል።
በሪፖርቱ መሰረት የስኳር ዋጋ ብቻውን ከፍተኛውን 39 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።
የምግብ ነክ ያልሆኑ ሸቀጦችና ግሽበትም በሐምሌ ወር ወደ 14.8 በመቶ ደርሷል።
ከእነዚህ መካከል ፦
- ምግብ ቤቶች፣ ሆቴሎች እና ትራንስፖርት 15.6 በመቶ፣
- አልኮል መጠጦች እና ትምባሆ 16.0 በመቶ፣
- ሌሎች ዕቃዎችና አገልግሎቶች 19.3% ጭማሪ ያሳዩ ሲሆን፣ ኮሙኒኬሽን ብቻ በአንጻራዊነት ዝቅተኛ ማለትም 8.0 በመቶ ጭማሪ በማሳየት ተለይቷል።
ተቋሙ ይፋ አድርጎት በነበረው የሰኔ 2018 ዓ.ም ሪፖርት አጠቃላይ ግሽበቱ 13.9 በመቶ ደርሶ እንደነበር የሚያመላክት ሲሆን ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወር ማለትም ከሰኔ 2017 ዓ.ም (13.9%) ጋር ተመሳሳይ ደረጃ ላይ ነበር።
ከዚያም ቀደም ብሎ በግንቦት 2018 ዓ.ም የተመዘገበው አጠቃላይ ግሽበት 13.4 የነበረ ሲሆን ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወር ማለትም ከግንቦት 2017 ዓ.ም (14.4%) ጋር ሲነጻጸር የተወሰነ መሻሻል የታየበት ወር ነበር።
የተቋሙ የሦስት ወራት ሪፖርት እንደሚያሳየው አጠቃላይ የዋጋ ግሽበቱ ከግንቦት እስከ ሐምሌ ወር ባለው ጊዜ ውስጥ ብቻ በ1.9 መቶኛ ነጥብ ከፍ ብሏል፤ ከ13.4 በመቶ ተነስቶ በሐምሌ ወር 15.3% ደርሷል።
በተለይም የምግብ ነክ ያልሆኑ ሸቀጦችና አገልግሎቶች ዋጋ ከ12.2 በመቶ ወደ 14.8 በመቶ በመድረስ ጎልቶ የሚታይ ጭማሪ ማሳየቱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከተቋሙ ሪፖርት ተመልክቷል።
Via ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ/ም | 25 |
| 14 | No text... | 20 |
| 15 | የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ሀገር አቀፍ የምክክር ጉባኤ ላይ የቀረቡ ምክረ ሃሳቦችን አተገባበር የሚከታተል “ገለልተኛ እና ህጋዊ” አካል አንዲቋቋም ጥያቄ አቀረበ። የፌደራል መንግስት ምክረ ሃሳቦቹን ለመተግበር “ከተገቢው በላይ ጊዜ እንዳይወስድ” እና አፈጻጸሙን “በፍጥነት” እንዲከናወን እንዲያደርግም ፓርቲው አሳስቧል።
ኢዜማ ማሳሰቢያውን እና ጥያቄውን ያቀረበው፤ ለ38 ቀናት ሲካሄድ የቆየውን ባለፈው ሳምንት መጨረሻ የተጠናቀቀውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤን አስመልክቶ ዛሬ ረቡዕ ነሐሴ 20፤ 2018 በሰጠው መግለጫ ነው። ፓርቲው በዚሁ መግለጫው ሀገራዊ የምክክር ሀሳቡ “ከተጠነሰሰበት ቀን” ጀምሮ “በከፍተኛ ሀገራዊ ኃላፊነት፣ በንቃት እና በሙሉ ቁርጠኝነት ሲሳተፍ መቆየቱን” አስታውቋል።
አራት ሺህ ሰዎች በተሳተፉበት ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ላይም፤ ፓርቲው በመሪው አቶ እዮብ መሳፍንት፣ በሌሎች አመራሮቹ እና አባላቱ ተወክሏል። የጉባኤ ሂደቱን “ረጅም” እና “እልህ አስጨራሽ” ሲል በዛሬው መግለጫው የጠራው ኢዜማ፤ በምክክሩ ወቅት “በርካታ ስልታዊ ማነቆዎች” እና “አሰራርን ያላከበሩ ችግሮች” እንዳጋጠሙት አመልክቷል።
ፓርቲው ለዚህ በማሳያነት የጠቀሰው በጉባኤው “በኤክስፐርትነት” እና “በአስተባባሪነት” በተመደቡ የተወሰኑ ግለሰቦች ተፈጽሟል ያለውን የአሰራር ችግር ነው። ግለሰቦቹ በምክክሩ ሂደት ወቅት “ግልጽ ወገንተኛነት” እና “የተዛባ አካሄድ” ያንጸባርቁ ነበር ሲል ኢዜማ በዛሬው መግለጫው ወንጅሏል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
🔴ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2026/18613/ | 18 |
| 16 | " ተማሪዎች ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው ውጤታቸው ማየት ይችላሉ " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት የሚገለጽባቸው አድራሻዎች ይፋ ሆነዋል።
በ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን (Link) በመጠቀም ማየት የሚችሉ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
በተያያዘም ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልግ https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በማቅረብ ምላሹንም በተመሳሳይ ማስፈንጠሪያ በኩል መከታተል የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ ገልጿል።
ውጤት የሚገለጽባቸው ማስፈንጠሪያዎች፡-
- በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et
- ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram
- አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms
ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም | 21 |
| 17 | የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ አልተደረገም።
የተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት መለቀቁን በመግለጽ ተማሪዎችና ወላጀችን የሚያደናግር ሀሰተኛ መረጃ እያሰራጩ ይገኛሉ።
እስካሁን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት፣ የፈተናው ውጤት ይፋ ስለመደረጉ በይፋ አላሳወቀም።
ትክክለኛ የተረጋገጡ መረጃዎች ከትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ብቻ የሚገኙ በመሆኑ ተማሪዎች እና ወላጆች ሀሰተኛ መረጃዎችን ከሚያሰራጩ የተለያዩ አካላትና ገጾች ትጠነቀቁ ዘንድ ቲክቫህ ኢትዮጵያ መልዕክት ያስተላልፋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በ2018 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ዙሪያ መግለጫ በሰጡበት ወቅት የፈተናው ውጤት ሰኞ ወይም እስከ ማክሰኞ ከሰዓት ይፋ ይደረጋል ማለታቸው ይታወሳል።
ውጤት ሰኞ ዕለት ይፋ ያልተደረገ ሲሆን እስከ ማክሰኞ ከሰዓት ይፋ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።
የፈተናው ውጤት ይፋ ሲደረግ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ብቻ በይፋ የሚያሳውቅ ሲሆን እንዴት ማየት እንደሚቻልም ተቋሙ ገለጻ ያወጣል። እኛም ተከታትለን የምናቀርብ ይሆናል። | 21 |
| 18 | የ2018 ዓ.ም. የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ዋና ዋና መረጃዎች‼️
📊 የማለፊያ ውጤት
• 70,544 ተማሪዎች ፈተናውን አልፈዋል።
• ይህም 12.8% የማለፊያ ምጣኔ ነው።
• 565 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ ማሳለፍ አልቻሉም።
🏫 100% ያሳለፉ ትምህርት ቤቶች
• አምና — 62
• ዘንድሮ — 88
➡️ በዚህ ዓመት 26 ትምህርት ቤቶች ጨምረዋል።
💻 በፈተና አሰጣጥ ዘዴ
• በኦንላይን የተፈተኑ — 18.37% አልፈዋል።
• በወረቀት የተፈተኑ — 4.2% አልፈዋል።
🏆 የክልሎች የማለፊያ ምጣኔ
🥇 አዲስ አበባ — 32.4%
🥈 ሀረሪ — 22.76%
🥉 አማራ — 15%
• ድሬዳዋ — 11.92%
• ትግራይ — 11.2%
• ጉምዝ — 10.53%
• ደቡብ — 9.2%
• ሶማሌ — 9%
• ሲዳማ — 6.95%
• ጉምዝ — 6.1%
• ደቡብ ኢትዮጵያ — 4.2%
• 3.74% — የክልሉ ስም አልተጠቀሰም።
🎯 ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ
• 591/600 — ተፈጥሮ ሳይንስ፣ ወንድ — ኦዳ ትምህርት ቤት
• 583/600 — ተፈጥሮ ሳይንስ፣ ሴት — አገው ምድር ትምህርት ቤት
• 576.25/600 — ማህበራዊ ሳይንስ፣ ወንድ — ዶዶላ ኢፋ ቦሩ ትምህርት ቤት
• 569/600 — ማህበራዊ ሳይንስ፣ ሴት
📌 በአጠቃላይ፦ የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የማለፊያ ምጣኔ 12.8% ሲሆን፣ አዲስ አበባ 32.4% በማስመዝገብ ከፍተኛውን የክልል ደረጃ ይዟል። በተጨማሪም 100% ያሳለፉ ትምህርት ቤቶች ከ62 ወደ 88 ከፍ ብለዋል። | 28 |
| 19 | የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ባለበት እንዲቀጥል ምክረ ሐሳብ ቀረበ
#Ethiopia: -የሥራ ቋንቋዎች ከ13 ወደ አምስት እንዲጠጋጉ ተደርጓል
-"አጃንዳ አጣጣሚዎች ቡድን ምርጫ ቅሬታ የሚፈጥር ነው"
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ
በ500 ቡድን ተመካካሪዎች መግባባት ላይ የተደረሰባቸውን ምክረሐሳቦች ለማጣጣም የተቋቋመው 15 አባላት ያሉት ቡድን፣ ሁለት ምክረሐሳቦች ቀርበውለት የነበረውን የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ጉዳይ ወደ አንድ በማምጣት፣ አሁን ያለው የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ባለበት ይቀጥል የሚል ምክረሐሳብ ማቅረቡ ተገለጸ
የቁጫ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲን ወክለው በምክክሩ እየተሳተፉ የሚገኙት አቶ ገነነ ገደቡ፣ እሳቸው እየተመካከሩ በሚገኙበት የአገር ግንባታ አጀንዳ ሥር የሚገኘው ብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ ጉዳይ፣ በ500 ደረጃ በነበረው ውይይት ያለው ይቀጥል አልያ ዓርማው ይቀየር በሚሉ ሁለት ምክረሐሳቦች ከመግባባት ተደርሶ እንደነበር አስታውሰው፣ በ500 ቡድን መግባባት ላይ የተደረሰባቸውን ምክረሐሳቦች በሚያጣጥመው 120 አባላት ባሉት ቡድን ታይቶ መምጣቱንና ቃለጉባዔው ሲነበብ ግን ወደ አንድ እንዲጠጋጋ መደረጉን ለሪፖርተር ተናግረዋል።
በዚህም አሁን ያለው ባለበት ይቀጥል የሚለው አንድ ወጥ ምክረሐሳብ ሆኖ መቅረቡን፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሕዝብ መዝሙርም ባለበት እንዲቀጥል መባሉንና ይህም የሆነው በስፋት ተመሳሳይ ሐሳብ በመቅረቡ ምክንያት መሆኑ እንደተገለጸላቸው አስረድተዋል።
ቃለ ጉባዔ ሲነበብ በዚህ አጀንዳ ሥር የነበሩ ንዑስ አጀንዳዎች፣ ለአብነት የማንነት ጉዳዮች ለሚመለከታቸው በሚል ወደ ሌሎች አጀንዳዎች እንዲገቡ፣ ከሌሎች አጀንዳዎችም ወደዚህ አጀንዳ ሥር እንዲመጡ የተደረጉ ...
🔗 ተጨማሪ ያንብቡ: https://ethiopianreporter.com/159239/ | 28 |
| 20 | በድርቅ 16 ሰው😥‼️
በጠለምት ወረዳ በተከሰተ ድርቅ የ16 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የመረው ቀበሌ አስተዳዳሪ ገለፁ‼️‼️
👉ከ17000 በላይ የቤት እንስሳት ሞተዋል።
በሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ መረው ቀበሌ በተከሰተው በረታች ድርቅ ሳቢያ የ16 ሰዎች ሕይወት ማለፉንና በመቶዎች የሚቆጠሩ የቤተሰብ አባላት ለስደት መዳረጋቸውን የመረው ቀበሌ ዋና አስተዳዳሪ ጥላሁን ገብረሚካኤል ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል።
እንደ አስተዳዳሪው ገለጻ፣ በአካባቢው ከመጋቢት ወር ጀምሮ ምንም ዓይነት ዝናብ በመጥፋቱ አርሶ አደሩ የዘራው እህል ሳይበቅል ቀርቷል። በዚህም ምክንያት በአካባቢው የምግብ እጥረትና ረሃብ በመከሰቱ፣ የሰው ሕይወት ከማለፉ ባሻገር የቁም እንስሳትም በሙሉ ማለቃቸውን አክለዋል፡፡
በተጨማሪም ድርቁ ያስከተለው የረሃብን ሁኔታ መቋቋም የተሳናቸው 488 አባወራዎች ከአካባቢው ለቅቀው ወደ ምዕራብ ትግራይ መሰደዳቸውን ጥላሁን አስረድተዋል።
ችግሩን በተመለከተ እስከ ክልል ድረስ አቤቱታ መቅረቡን የጠቆሙት አስተዳዳሪው፣ ከየቀበሌው የተመደቡ አካላት የሞቱ ሰዎችን፣ የተሰደዱ አባወራዎችን እና ያለቁ እንስሳትን ቁጥር መዝግበው ለሚመለከተው አካል ቢያሳውቁም እስካሁን ምንም ዓይነት ምላሽ አለመገኘቱን ገልጸዋል።
ከዚህ ቀደም ከመንግሥት የተደረገው ድጋፍ ለአቅመ ደካሞች ብቻ የተሰጠ የሴፍቲኔት እርዳታ እንደነበርም አክለው ጠቁመዋል።
እየከፋ የመጣውን የረሃብ አደጋ ተከትሎ የአካባቢው ነዋሪዎች የድንገተኛ እርዳታ ጥያቄ በማንሳት ሰልፍ መውጣታቸውን የገለጹት ጥላሁን፤ አሁንም አስቸኳይ ድጋፍ ካልቀረበ የአካባቢው ሕዝብ በረሃብ የሚያልቅበት አጋጣሚ ሰፊ በመሆኑ የሚመለከታቸው አካላት በፍጥነት እንዲደርሱላቸው ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
ሼር አድርጉት❗️❗️። | 33 |
