en
Feedback
ልጇ ነው አምላኳ

ልጇ ነው አምላኳ

Open in Telegram

ልጇ ነው አምላኳ ይህ ቻናላችን አላማው ኦርቶዶክሳዊነታችንን ማጠንከር ነው ያላወቅነውን በፅሁፍ በ Video በ Audio በመዝሙር እየተማርን ላላወቁት ሼር በማድረግ በሀይማኖታችን መጠንከር ስለሀይማኖታችን በተጠየቅን ጊዜ መልስ የሚሆኑንትን መማር ማወቅ ነው አላማችን እመቤቴ ምልጇ እና ልመነዋ አይለየን ሁላችንንም በቤቱ ያፅናን ።

Show more
284
Subscribers
No data24 hours
+17 days
No data30 days
Posts Archive
ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ፡ ወሰላም በምድር ለዘሠምሮ ለሰብእ

አእላፋት ዝማሬ 🥰🥰🥰

🔴 ታህሳስ 24 [  ✞ እንኩዋን ለቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞   ] † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። † --------------------------------------------- 🕊 ቅዱስ  ተክለ ሃይማኖት ሐዋርያዊ  🕊 †    ልደት   † - መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ : ጸጋ ዘአብ  ካህኑና  እግዚእ ኃረያ ናቸው:: እርሱ በክህነቱ: እርሷ በደግነቷ: በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ ፍሬን ሰጥቷቸዋል:: - በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ ቢደርስባቸው  ቅዱስ ሚካኤል : ጸጋ ዘአብን ከሞት: እግዚእ ኃረያን ከትድምርተ አረሚ [ ከአረማዊ ጋብቻ ] አድኗቸዋል:: በኋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል:: - አቡነ ተክለ ሃይማኖት የጸነሱት መጋቢት ፳፬, በ፩ ሺህ ፪ መቶ ፮ [1206] (1196) ሲሆን የተወለዱት ታሕሳስ ፳፬ [24] , በ፲፻፯ [1207] (1197) ዓ/ም ነው:: በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል:: ቤታቸውም በበረከት ሞልቷል:: †  ዕድገት  † - የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው " ፍሥሃ_ጽዮን " ይሰኛል:: ይሕንን ስም ይዘው: አባታቸው ጸጋ ዘአብን ተከትለው አድገዋል:: በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን [ብሉያት: ሐዲሳትን] ተምረዋል:: በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል:: ዲቁና ከወቅቱ ዻዻስ አባ ጌርሎስ  ተቀብለዋል:: †  መጠራት  † - አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮን ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ ተሰማ:: የክብር ባለቤት  ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክት እያመሰገኑ በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ:: - የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ: " ከዛሬ ጀምሮ ስምህ ተክለ ሃይማኖት [ ተክለ ሥላሴ ] ይሁን:: አራዊትን ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ:: ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ በግርማ ዐረገ:: ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በኋላሰዓትን አላጠፉም:: ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ:: †   አገልግሎት   † - ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል አገልግሎትን ጀመሩ:: በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ [ ጽላልሽ ] አካባቢ ብቻ በ ፲ ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው አጠመቁ:: ያንጊዜ ኢትዮዽያ ፪ መልክ ነበራት:: ፩. ዮዲት [ ጉዲት ] በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል: ወይም በባዕድ አምልኮ ተጠምዷል:: ፪. ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር:: - ግማሹ ሃገር በጨለመበት ወቅት የደረሱት  ሐዲስ ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ:: ሕዝቡን: መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን [ ጠንቁዋዮችን ] አጥፍተዋል:: †  ገዳማዊ ሕይወት   † - ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል:: እርሳቸው ከሁሉ የተሻሉ ሳሉም በ ፫ ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል:: - እነዚህም በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ለ፲፪ ዓመታት: በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ ገዳም ለ ፯ ዓመታት: በደብረ ዳሞ ከአቡነ ዮሐኒ  ጋር ለ ፯ ዓመታት: በአጠቃላይ ለ፳፮ ዓመታት አገልግለዋል:: - በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ በኋላም ወደ ምድረ ሽዋ ዞረሬ ተመልሰው በአንዲት በዓት ውስጥ ለ ፳፪ ዓመታት ቆመው ጸልየዋል:: በተሰበረ እግራቸውም ፮ ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ ፯ ዓመታት ጸልየዋል:: †  ስድስት ክንፍ   † - ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት መካናት ተባርከዋል:: ጻድቁ ምድረ እሥራኤል  የገቡት በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ ነበር:: - የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሚካኤል  ጋርም ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል:: ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ በኋላ ነው:: ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ እንባቸው ይፈስ ነበር:: - ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም:: በገሃድ :- - በቤተ መቅደስ ብስራቱን - በቤተ ልሔም ልደቱን - በቤተ ዮሴፍ ግዝረቱን - በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን - በቤተ አልዓዛር ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር:: - የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል ወደሆነው  ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ:: በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ  እመቤታችን ድንግል ማርያም ፈጥና ደርሳ ጻድቁን ወደሰማይ አሳረገቻቸው:: †  በዚያም :- - የብርሃን ዐይን ተቀብለው - ፮ ክንፍ አብቅለው - የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው - ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው - ከ፳፬ቱ ካህናተ ሰማይም ተደምረው - ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው - "ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል:: †  ተአምራት   † - የጻድቁ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው:: - ሙት አንስተዋል - ድውያንን ፈውሰዋል - አጋንንትን አሳደዋል - እሳትን ጨብጠዋል - በክንፍ በረዋል - ደመናን ዙፋን አድርገዋል:: - ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን መሥርተዋል:: በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት አብረው ኑረዋል:: በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና:: †   ዕረፍት    † - ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው: አእላፍ ፍሬን አፍርተው: በተወለዱ በ፺፱ [99] ዓመት: ከ ፰ [8] ወር: ከ ፩ [1] ቀናቸው ነሐሴ ፳፬ [24] , በ፲፻፫፮ [1306] [1296] ዓ/ም ዐርፈዋል:: ጌታ: ድንግል ማርያምና ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል:: ፲ ትውልድ የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል:: የፃድቁ በረከታቸው ይደርብን ። ልጇ ነው አምላኳ ልጇ ነው አምላኳ ልጇ ነው አምላኳ ✍ ፳ ፩ ምንቴ ዘማርያም

ሊቀ_መላእክት_ቅዱስ_ገብርኤል ሠለስቱ ደቂቅን ከእቶን እሳት ውስጥ ያዳነበት አመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ 🙏🙏🙏 #እኔ_በእግዚአብሔር_ፊት_የምቆመው_ገብርኤል_ነኝ (ሉቃ 1፥19) #ይህ_ገብርኤ
ሊቀ_መላእክት_ቅዱስ_ገብርኤል ሠለስቱ ደቂቅን ከእቶን እሳት ውስጥ ያዳነበት አመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ 🙏🙏🙏 #እኔ_በእግዚአብሔር_ፊት_የምቆመው_ገብርኤል_ነኝ (ሉቃ 1፥19) #ይህ_ገብርኤል_ነው በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩ ብርሃን የገለጸና የሰበከ #ይህ_ገብርኤል_ነው ። የነቢያትን ትንቢት የፈጸመ፤ የክርስቶስን ልደት ለድንግል ያበሰረ #ይህ_ገብርኤል_ነው ። ዳንኤልን ከአነብስት ያዳነው #ይህ_ገብርኤል_ነው ። ሠለስቱ ደቂቅን ከእቶን እሳት ያዳናቸው #ይህ_ገብርኤል_ነው ። ወደ ዘካሪያስ የተላከ የዮሐንስ ልደት ያበሰረ #ይህ_ገብርኤል_ነው ። ወደ ዮሴፍና ወደ ኒቆዲሞስ የተላከ #ይህ_ገብርኤል_ነው ። ቂርቆስና ኤናቱ ኢየሉጣን ከእቶን እሳት ያዳናቸው #ይህ_ገብርኤል_ነው ። ሰብአ ሰገልነረ በኮከብ ምልክት የመራቸው #ይህ_ገብርኤል_ነው ። ድንግል ማርያሜና ሕፃኑን ክርስቶስን በምድረ በዳ በስደታቸው የመራ #ይህ_ገብርኤል_ነው ። የብርሃን ወርቅ የተቀዳጀ #ገብርኤል_ነወ ። የአሸናፊና የኀኃይል መልአክ #ገብርኤል_ነው ። ነበልባላዊ ዖፈ ሰማይ #ገብርኤል_ነው ። #የመልአኩ_የቅዱስ_ገብርኤል_ጥበቃና_ረድኤት_አይለየን አሜን #ገብርኤል_ገብርኤል ሲሉ ማማሩ ማማሩ ከእሳት ያወጣል በያዘው #መስቀሉ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል #ሀገራችንን_ይጠብቅልን አሜን አሜን 🙏🙏🙏🙏 #መልካም__በዓል🙏 ልጇ ነው አምላኳ ልጇ ነው አምላኳ ልጇ ነው አምላኳ ✍ ፳ ፩ ምንቴ ዘማርያም

🔴 በዓታ ለማርያም ታኅሣሥ በሦስተኛው ቀን የሚታሰበውና የሚከበረው በዓል ‹‹በዓታ ለማርያም›› በመባል ይታወቃል፡፡ ከእናቷ ከቅድስት ሐና እና ከአባቷ ቅዱስ ኢያቄም በስዕለት የተወለደችው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ዕለት የከበረ እንደመሆኑ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ታከብረዋለች፡፡   በዓት ቃሉ የግእዝ ሲሆን ቤት ማለት ነው፡፡ ደጋጎቹ የእግዚአብሔር ሰዎች ቅዱስ ኢያቄምና ቅድስት ሐና ልጅ አጥተው ለብዙ ዘመናት ከመኖራቸው የተነሣ በኀዘን ፈጣሪያቸውን ሲማጸኑ ቃል በመግባት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሦስት ዓመት ሲሆናት በእግዚአብሔር ቤት ትኖርና ታገለገል ዘንድ በቤተ ክርስቲያን እንድትኖር ስለሰጧት በዓሉም ስያሜውን በዚያ መሠረት አግቷል፡፡  በዚያን ጊዜም በቤተ ክርስቲያን ያገለግል የነበረው ካህኑ ዘካርያስ ስዕለታቸውን አስተውሶ ቅድስት ድንግል ማርያምን ሊቀበላት ሲቀርብ እንደ ፀሐይ የምታበራ ሕፃን ሆና አገኛት፤ በመገረምና በመጨነቅም ከወላጆቿ ጋር ምን ሊመግቧት እንደሚችሉ በመጨነቅ ላይ ሳሉ ሕዝቡ በተሰበሰበበት መካከል መልአኩ ፋኑኤል ኅብስት ሰማያዊ ጽዋዕ ይዞ ከሰማይ ወረደ፡፡ ካህኑ ዘካርያስም ለእርሱ የመጣ መና መስሎት ሲቀረብ ወደ ላይ ተመለሰበት፡፡ በዚያ የተሰበሰቡት ሰዎችም እያንዳንዳቸው ቢሞክሩ በተመሳሳይ መልኩ ተመልሶ ወደ ላይ ራቀባቸው፡፡ ‹‹ምን አልባት ለእንግዶች የመጣ ሀብት እንደሆነ›› ብለው ቅድስት ሐና እና ቅዱስ ኢያቄም እንዲቀርቡ ቢደረግም ለእነርሱም ራቀባቸው፡፡ ካህኑ ዘካርያስም ቅድስት ሐናን ‹‹እግዚአብሔር የሚያደርገውን የሚያውቅ የለምና ልጅቷን ትተሸ ወደዚህ ነይ›› አላት፤ ሆኖም ግን ቅድስት ማርያም እናቷ ትታት ስትሄድ መከተል ጀመረች፤ ምርርም ብላ አለቀሰች፡፡ በዚህም ጊዜ መልአኩ ፋኑኤል ወደ እርሷ ቀርቦ አንድ ክንፉን አንጥፎ አንድ ክንፉን ጋርዶ መገባት፤ ከዚያም በክብር ዐረገ፤ ሊቀ ካህናቱና ሕዝቡም ‹‹የምግቧ ነገር ከተያዘልን በቤት እግዚአብሔር ትኑር›› ብለው ወደ ቤተ መቅደስ አስገቧት፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ሰማያዊ ኅብስትና መጠጥ እየተመገበች  በቤተ መቅደስ  ለ፲፪ ዓመታትም ኖራለች፡፡ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነትና ተራዳኢነት አይለየን፤ በረከቷ ይደርብን፤አሜን!  ልጇ ነው አምላኳ ልጇ ነው አምላኳ ልጇ ነው አምላኳ ✍ ፳ ፩ ምንቴ ዘማርያም