en
Feedback
ኢትዮ ዜና 🇪🇹 Ethio News

ኢትዮ ዜና 🇪🇹 Ethio News

Open in Telegram

እንኳን ወደ ኢትዮ ዜና ( ethio news ) መረጃ ማዕከል ደህና መጣችሁ 🙌 ይህ ቻናል ትከክለኛ መረጃዎችን በሰዓቱ ሚያገኙበት ነው ። for more information 👉 @ashu_online 👉 @S305020SPICE 👉 @Bussnismann 👉 @SPICEFORSUCCESS Share the link our channel 👇 ✍️ https://t.me/ethiozenaAZ

Show more
211
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
በአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ የሚጠይቅ ደብዳቤ ለከንቲባ ጽ/ቤት ማስገባቱን የኢትዮጰያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ ገለጸ፡፡ "ጦርነት ይቁም! ሠላም ይስፈን፣ መከላከያ ሰራዊቱ ባስቸኳይ ወደ ካምፕ ይግባ!" በሚል መሪ ቃል ለህዳር 30 ፣ 2016 ዓ. ም. ታላቅ ህዝባዊ ሠልፍ ለማድረግ ነው ፓርቲው ጥያቄ ያቀረበው፡፡ በዛሬው እለት ህዳር 19 ቀን 2016 ዓ.ም. በሰላማዊ ሰልፉ አስተባባሪዎች በተፈረመ ደብዳቤ፣ ጦርነት እንዲቆም፣ መከላከያ ሠራዊቱ ከዘመተባቸው ክልሎች ወጥቶ ወደ ጦር ካምፑ እንዲመለስና ፖለቲካዊ ውይይቶች እንዲከፈቱ የሚጠይቅ ህዝባዊ የአደባባይ ሠልፍ ለማድረግ እንደሆነ ተሰምቷል፡፡ የኢትዮጰያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ /ኢህአፓ/ እና ሌሎች ዜጎች አስተባባሪነት የተጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ዙሪያ ዛሬ ለአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት፣ የማሣወቂያ ደብዳቤ ማስገባታቸውን ለጣብያችን ገልፀዋል፡፡ ከጣብያችን ጋር ቆይታ የነበራቸው የኢህአፓ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር መጋቢ ብሉይ አብርሃም እንደገለፁት ኢህአፓ እና ሌሎች ሁሉን አቀፍ ሀገር ወዳድ አባላት በመሰባሰብ በጋራ በመሆን ሀገርን የማዳን ሰልፍ መጠራቱን ነግረውናል፡፡ ህዝባዊ ሠልፉ መነሻውን አራት ኪሎ የድላችን ኃውልት አድርጎ በተለያዩ ጎዳናዎችንና አደባባዮችን በማለፍ መዳረሻውን መስቀል አደባባይ አድርጎ የዕለቱን መልዕክት በማስተላለፍ ይጠናቀቃልም ተብሏል። በሠላማዊ ሠልፉ ላይም ከመቶ ሺህ ሰው በላይ  እንደሚጠበቅ የገለፁት አስተባባሪዎቹ፣ ለዚህ የሚሆን የፀጥታና ደህንነት የአዲስ አበባ ፖሊስ ህገ-መንግስታዊ ተልዕኮውን እንዲወጣ ጠይቀዋል፡፡ ሠልፉ በተለይም በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች የጦር ሠራዊቱ ከጦርነት አውድ ውጪ የሚፈፅማቸውን ዘመቻዎችን በማቆም ወደ ጦር ሰፈሩ እንደሚለስ የሚጠይቅ መሆኑንም አስተባባሪዎቹ ለጣብያችን ተናገግረዋል፡፡ ሰላማዊ ሰልፉን ከጠሩት አስተባባሪዎች መካከልም እንደ ናትናኤል መኮንን፣የሺዋስ አሰፋ የመሣሠሉ ፖሊቲከኞችና ሌሎችም ሀገር ወዳዶች የተጠራ ነው መባሉን  ያገኘነው መረጃ ያለመክታል፡፡

የፈረንሳይ ኦሬንጅ ኩባንያ የኢትዮ ቴሌኮምን ድርሻ ከመግዛት ሂደት ራሱን አገለለ!! የፈረንሳይ ኦሬንጅ ኩባንያ የኢትዮ ቴሌኮምን 45 በመቶ ድርሻ ከመግዛት ሂደት ራሱን ማግለሉን አስታወቀ! የኢትዮጵያ
የፈረንሳይ ኦሬንጅ ኩባንያ የኢትዮ ቴሌኮምን ድርሻ ከመግዛት ሂደት ራሱን አገለለ!! የፈረንሳይ ኦሬንጅ ኩባንያ የኢትዮ ቴሌኮምን 45 በመቶ ድርሻ ከመግዛት ሂደት ራሱን ማግለሉን አስታወቀ! የኢትዮጵያ ፋይናንስ ሚንስቴር የኢትዮ ቴሌኮምን የ45 በመቶ ድርሻ ለመሸጥ ዓለም አቀፍ ጨረታ ማውጣቱ ይታወሳል። ይህንን ተከትሎም የፈረንሳዩ ኦሬንጅ እና የተባበሩት አረብ ኢምሬት ቴሌኮም ኩባንያ የሆነው ኢ ኤንድ የተሰኘው ተቋም የኢትዮ ቴሌኮምን የ45 በመቶ ድርሻ ለመግዛት የመወዳደር ፍላጎት እንዳላቸው አሳውቀው ነበር። የፈረንሳይ ኦሬንጅ ኩባንያ በትናንትናው እለት ባወጣው መግለጫ የኢትዮ ቴሌኮምን 45 በመቶ ድርሻ ከመግዛት ሂደት ራሱን ለማግለል መወሰኑን ሬውተርስ ዘግቧል። ኦሬንጅ ከጨረታ ሂደቱ ራሱን ለማግለል የወሰነው ስትራቴጂውን በፍጥነት ለመተግበር አስቻይ ሁኔታ እንደሌል መረዳቱን ተከትሎ እንደሆነም አስታውቋል። የጨረታ ሂደቱን በበላይነት የሚመሩት ኢትዮ ቴሌኮምና የኢትዮጵያ ፋይናንስ ሚኒስቴር በጉዳዩ ላይ እስካን ማብራሪያ አልሰጡም።ኢትዮ ቴሌኮም በፈረንጆቹ በ2018 የመንግስት ልማት ድርጅቶችን በከፊል ወደ ግል ይዞታ ለማዞር በተያዘው እቅድ ውስጥ ከተካተቱ ድርጅቶች አንዱ ነው። ኢትዮጵያ ሙሉ ለሙሉ የመንግስት ድርሻ የሆነው ኢትዮ ቴሌኮምን ለመሸጥ ከወሰነች የቆየች ቢሆንም በሰሜን የሀገሪቱ ክፍል የተከሰተው ጦርነት እንዳዘገየውም ይታወቃል።     

መንግስት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ጥያቄን ውድቅ አደረገ! የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በመንግስት የልማት ድርጅቶች ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ ውይይት አድርገዋል። የገንዘብ ሚንስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ
መንግስት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ጥያቄን ውድቅ አደረገ! የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በመንግስት የልማት ድርጅቶች ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ ውይይት አድርገዋል። የገንዘብ ሚንስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ከምክር ቤቱ አባላት በረቂቅ አዋጁ ዙሪያ ላነሷቸው ጥያቄዎች በምክር ቤቱ ተገኝተው ምላሽ ሰጥተዋል።የምክር ቤቱ አባላት ከ60 በላይ ጥያቄዎችን በረቂቅ አዋጁ ዙሪያ ማብራሪያ እንዲሰጧቸው ለሚንስትሩ አቅርበዋል። የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት ከባንኩ ጋር አደረግነው ባሉት ውይይት ባንኩ በሀገሪቱ ያሉ ሰፊ የመልማት አቅም ለመመለስ፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ እንዲመረቱ ድጋፍ ለማድረግ እና ወደ ውጪ ሀገራት የሚላኩ ምርቶችን በስፋት እንዲመረቱ ለማገዝ መቋቋሙን ከግምት ውስጥ እንዲገባለት ጥያቄ አቅርቧል ተብሏል፡፡በመሆኑም የመንግስት የልማት ድርጅት እንደመሆኑ መጠን በየዓመቱ ያገኘውን ትርፍ ለገንዘብ ሚኒስቴር ፈሰስ ከሚያደርገው ላይ ሙሉ ለሙሉ አልያም በከፊል ለራሱ እንዲወስድ እንዲፈቀድለት የምክር ቤቱ አባላት ለገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ በሰጡት ምላሽ መንግስት ልማት ባንክ ከነበረበት ኪሳራ እንዲወጣ ላለፉት 5 ዓመታት የተበላሸ ብድር እንዲስተካከል፣ የበጀት እጥረቱ እንዲፈታ፣ የአሰራር ማሻሻያዎችን ጨምሮ ብዙ ድጋፎችን ሲደርጉ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡ ባንኩ በተደረገለት ድጋፍ መሰረትም ትርፋማ ሆኗል ያሉት አቶ አህመድ ለገንዘብ ሚኒስቴር ፈሰስ የማደርገውን ትርፍ ለራሴ ካልተጠቀምኩ ያሰብኩትን እቅድ ለማሳካት እቸገራለሁ ማለቱ ስህተት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ልማት ባንክ ውጤታማ እንዲሆን መንግስት ድጋፍ ማድረጉን እንደሚቀጥል ነገር ግን አዋጁ ላይ ትርፍ ለራሱ እንዲወስድ የሚፈቅድ አንቀጽ ሊካተት ግን አይገባም ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት በበርበራ ወደብ አጠቃቀም ዙሪያ ከሱማሌላንድ መንግሥት ባለሥልጣናት ጋር አመርቂ ውይይት እያካሄደ መኾኑን ትራንስፖርት ሚንስትር አለሙ ስሜ ትናንት በሚንስትሮች ምክር ቤት የእቅድ
የኢትዮጵያ መንግሥት በበርበራ ወደብ አጠቃቀም ዙሪያ ከሱማሌላንድ መንግሥት ባለሥልጣናት ጋር አመርቂ ውይይት እያካሄደ መኾኑን ትራንስፖርት ሚንስትር አለሙ ስሜ ትናንት በሚንስትሮች ምክር ቤት የእቅድ ግምገማ ላይ መናገራቸውን የመንግሥት ዜና አውታሮች ዘግበዋል። አለሙ፣ ኢትዮጵያ በርበራ ወደብን ለወጪና ገቢ ንግዷ እንድትጠቀም ከሱማሌላንድ መንግሥት ጋር የተጀመረው ንግግር ጥሩ ደረጃ ላይ ደርሷል ማለታቸውን ዘገባዎቹ አመልክተዋል።    

ብሪክስ ለእስራኤልና ፍልስጤም ግጭት ፖለቲካዊ መፍትሄ ይፈልጋል - ፑቲን የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የእስራኤልና ፍልስጤም ግጭት እንዲረግብ ጥሪ አቀረቡ። ፕሬዝዳንቱ የብሪክስ አባል ሀገራት
ብሪክስ ለእስራኤልና ፍልስጤም ግጭት ፖለቲካዊ መፍትሄ ይፈልጋል - ፑቲን የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የእስራኤልና ፍልስጤም ግጭት እንዲረግብ ጥሪ አቀረቡ። ፕሬዝዳንቱ የብሪክስ አባል ሀገራት ጉባኤ በበይነ መረብ ሲካሄድ ባስተላለፉት መልዕክት፥ ለጋዛ ጦርነት ፖለቲካዊ መፍትሄን ለማፈላለግ የብሪክስ አባል ሀገራት ቁልፍ ድርሻ አላቸው ብለዋል። “የጋዛ ውጥረት እንዲረግብና የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረስ አለማቀፉ ማህበረሰብ የተቀናጀ ጥረት ማድረግ አለበት፤ ለእስራኤልና ፍልስጤም ግጭት ፖለቲካዊ መፍትሄ መፈለግ ይኖርበታል፤ ለዚህም የብሪክስ አባል ሀገራት ቁልፍ ሚና አላቸው” ነው ያሉት ፕሬዝዳንት ፑቲን። ፕሬዝዳንት ፑቲን በጋዛ ጉዳይ ላይ ባተኮረው የብሪክስ አባል ሀገራት የበይነ መረብ ውይይት ለመካከለኛው ምስራቅ ቀውስ አሜሪካን ተጠያቂ አድርገዋል። የአሜሪካ የከሸፈ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ቀጠናውን ለትርምስ ዳርጓል ሲሉ የተደመጡት ፑቲን፥ እስራኤል በጋዛ ጦርነቱን እንድታቆም ጠይቀዋል። ባለፈው ወርም እስራኤል በጋዛ የምድር ውጊያ ስትጀምር የጀርመኑ ናዚ በሁለተኛው የአለም ጦርነት በሌኒንግራድ ንጹሃንን ከጨረሰበት ጥቃት ጋር አገናኝተው ማስጠንቀቃቸው አይዘነጋም። ፕሬዝዳንቱ ብሪክስ ለጋዛው ጦርነት ፖለቲካዊ መፍትሄን ለማበጀት ምን አይነት ጥረት እንደሚያደርግ በመልዕክታቸው አላነሱም። በብራዚል፣ ሩሲያ፣ ህንድ፣ ቻይና እና ደቡብ አፍሪካ የተመሰረተው ብሪክስ በነሃሴ ወር ስድስት ተጨማሪ ሀገራትን አባል ለማድረግ መወሰኑ ይታወሳል። ኢትዮጵያ፣ ግብጽ፣ ሳኡዲ አረቢያ፣ አረብ ኤምሬትስ፣ ኢራን እና አርጀንቲና ስብስቡን የሚቀላቀሉ ሀገራት ናቸው።    

Update❗️ "ውይይቱ ያለ ውጤት በዛሬው እለት ተበትናል" በኦነግ ሸኔና በመንግስት መካከል ሲካሄድ የነበረው ድርድር ያለ ውጤት መጠናቀቁ መንግስት አረጋገጠ! የመንግስት ኮሙኒኬሽን ዛሬ በሰጠው መግ
+1
Update❗️ "ውይይቱ ያለ ውጤት በዛሬው እለት ተበትናል" በኦነግ ሸኔና በመንግስት መካከል ሲካሄድ የነበረው ድርድር ያለ ውጤት መጠናቀቁ መንግስት አረጋገጠ! የመንግስት ኮሙኒኬሽን ዛሬ በሰጠው መግለጫ በኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (መንግሥት ሸኔ እያለ የሚጠራው የታጠቀ ኃይል) እና በመንግስት መካከል ሲካሄድ የነበረው ድርድር ያለ ውጤት መጠናቀቁን አስታውቋል። መንግሥት ሸኔ እያለ የሚጠራው የታጠቀ ኃይል እና በመንግስት መካከል ሲካሄድ የነበረው ድርድር ያለ ውጤት መጠናቀቁ የገለፀ ሲሆን ለድርድሩ አለመሳካት ምክንያትን ግን በግልፅ አላስቀመም። ነገር ግን መንግስት በመግለጫው "..ቡድኑ በዚህኛው ዙርም "መንግሥት አዝሎ መንግሥት ያድርገኝ" ከሚል አጉራ ዘለልነት ያለፈ የድርደር ነጥብ ማምጣት አልቻለም። ነገር ግን በኢፌዲሪ መንግሥት በኩል በሀገሪቱ ሰላም ሰፍኖ ኢትዮጵያ ያሉዋትን ጸጋዎች ወደ ተጨባጭ ሀብትና አቅም ቀይራ ብልጽግናዋን ታረጋግጥ ዘንድ ካለው ጉጉት በመነጨ ከግማሽ መንገድ በላይ ተጉዞ ለጉዳዩ እልባት ለመስጠት ሞክሯል፣ ነገርግን የሽብር ቡድኑ በሰላም ጊዜ እንዴት መኖር እንዳለበት ለማሰብ ቸግሮት ታይቷል። በዜጎች ደምና እንግልት መነገዱን መርጧል። በመሆኑም ውይይቱ በዛሬው ዕለት ያለ ውጤት ተበትኗል። ሲል አስታውቋል። መንግሥት "ለሰላማዊ መፍትሔ ያለው አቋም እንደተጠበቀ ሆኖ ሕግና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን የማስከበር ተልዕኮውን አጠናክሮ ይቀጥላል፣ በዚሁ አጋጣሚ ውይይቱ እንዲሳካ ጥረት ሲያደርጉ ለነበሩ አካላት ሁሉ ምስጋና ያቀርባል።" ሲል መግለጫውን አጠናቋል።  

" ያለ ውጤት ተበትኗል " የኢትዮጵያ መንግሥት ከሸኔ (እራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት እያለ ከሚጠራው ታጣቂ ቡድን) ጋር በሁለት ዙር ሲካሄድ የነበረው ንግግር ያለ ውጤት መቋጨቱን አሳውቋል። (የመግ
" ያለ ውጤት ተበትኗል " የኢትዮጵያ መንግሥት ከሸኔ (እራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት እያለ ከሚጠራው ታጣቂ ቡድን) ጋር በሁለት ዙር ሲካሄድ የነበረው ንግግር ያለ ውጤት መቋጨቱን አሳውቋል። (የመግለጫው ሙሉ ይዘት ከላይ ተያይዟል)

በአማራ ክልል በመከላከያ ሠራዊት እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በቀጠለው የትጥቅ ውጊያ ምክንያት በሰው አልባ አውሮፕላን ወይም ድሮኖች የሚደርሱት ጥቃቶች አሳሳቢ መሆናቸውን የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን አስታወቀ።  ጥቅምት 26 በዋደራ ወረዳ በአንድ ትምህርት ቤት ላይ የተፈጸመ የድሮን ጥቃት ሦስት መምህራንን ጨምሮ 7 ሰዎች፣ ጥቅምት 29 በምሥራቅ ጎጃም ዞን ዋብር ከተማ በመነሃሪያ ላይ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት 13 ሰዎች መገደላቸውን የገለፀው የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን መግለጫ በክልሉም ይሁን በሌሎች አካባቢዎች የቀጠሉ ያላቸው የመብት ጥሰቶችና የዘፈቀደ እሥሮች አሳሳቢነታቸው መጨመሩን አመልክቷል። የመንግሥታቱ ድርጅት ዘገባ ይዘት ምን ይመስላል? የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በአማራ ክልል ግጭት ውስጥ ያሉት አካላት ሕገ ወጥ ካላቸው ጥቃቶች እንዲቆጠቡ እና በጦርነቱ ምንም ተሳትፎ የሌላቸው ሰላማዊ ሰዎችን ደህንነታቸውን እንዲጠብቁ ባወጣው መግለጫ ጠይቋል። በተለይ በሰሜን ምዕራብ አማራ እና ሌሎችም የሀገሪቱ አካባቢዎች የዘፈቀደ እሥራትን ጨምሮ ቀጥሏል ያለው "የሰብአዊ መብት ረገጣ እና የመብት ጥሰት በእጅጉ አሳሳቢ ነው" ሲል አስታውቋል።የድርጅቱ የሰብአዊ መብት ጽ/ ቤት በሰው አልባ አውሮፕላኖች ወይም ድሮኖች እና ሌሎች ጥቃቶች በዚሁ ክልል አስከፊ ጉዳት እየደረሰ መሆኑን ጠቅሷል።በመንግስት ኃይሎች እየተወሰደ ባለው የድሮን ጥቃት ዋደራ ወረዳ የሚገኘኝ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ላይ ሦስት መምህራንን ጨምሮ ሰባት ሰዎች ስለመገደላቸው መግለጫው ያትታል።    

የየመን አማጺ የእስራኤል መርከብን እንዳገቱ ገለጸ! ሃማስ በእስራኤል ላይ ድንገተኛ እና ያለተጠበቀ ጥቃት መሰንዘሩን ተከትሎ የተቀሰቀሰው ጦርነት ከተጀመረ 43ኛ ቀኑን ይዟል።እስራኤልም ራሴን ለመከላከል በሚል የአጸፋ እርምጃ ለመውሰድ ጋዛ ላይ ድብደባ ከጀመረች 43 ቀናት የተቆጠሩ ሲሆን፤ በእስራኤል ጦርና በሃማስ ታጣቂዎች መካከል የተቀከቀሰው ጦርነት እንደቀጠለ ይገኛል። በርካታ ሀገራት እስራኤል የጀመረችውን ጥቃት እንድታቆም ግፊት በማድረግ ላይ ቢሆኑም በጋዛ ላይ እየደረሰ ያለው ጥቃት አሁንም እንደቀጠለ ነው።ለሀማስ ወግኖ በእስራኤል እና አሜሪካ ላይ ጥቃት በማድረስ ላይ ያለው የየመኑ አማጺ ቡድን ሁቲ ንብረትነቱ የእስራኤል የሆነ መርከብ መያዙን አስታውቋል፡፡ አማጺ ቡድኑ በቀይ ባህር ወደብ ላይ ሰራሁት ባለው ወታደራዊ ዘመቻ የእስራኤል መርከብን በቁጥጥር ስር እንዳዋለ ገልጿል፡፡መርከቡን በየመን ወደብ ዳርቻ ላይ እንዳስቀመጠው የገለጸው ይህ አማጺ ቡድን ከእስራኤል ጋር የተያያዙ ማናቸውም እንቅስቃሴዎች ላይ እርምጃ መውሰዱን እንደሚቀጥልም አስታውቋል፡፡ የቡድኑ ወታደራዊ ቃል አቀባይ ያህያ ሳሪ በሰጡት መግለጫ እስራኤል በፍልስጤማዊያን ላይ የጀመረችውን ጦርነት ካላቆመ ጥቃቱን እንደሚቀጥልበትም ገልጿል፡፡ማንኛውም ሀገር እና ተቋም ከእስራኤል ጋር እንዳይሰራ ሲል ያስጠነቀቀው የሁቲ አማጺያን በቀይ ባህር እና አካባቢው እርምጃ መውሰዱን እንደሚቀጥልም አስታውቋል፡፡ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በጽህፈት ቤታቸው በኩል ባወጡት መግለጫ ኢራን ዓለም አቀፉን የባህር ትራንስፖርት እያስተጓጎለች ነው ሲል ከሷል፡፡ጽህፈት ቤቱ አክሎም ኢራን ለሁቲ አማጺያን ድጋፍ በማድረግ የብሪታንያ ንብረት የሆነ መርከብ በጃፓናዊያን እየተንቀሳቀሰች እያለ ተጠልፋለችም ብሏል፡፡በዚች መርከብ ላይ አብረው የነበሩ 25 ሰዎች በታጣቂዎቹ ተይዘዋል ያለው ጽህፈት ቤቱ ዩክሬናዊያን፣ ቡልጋሪያ፣ ፊሊፒንስ እና ሜክሲኮ ዜግነት ያላቸው ዜጎች ከመያዛቸው ውጪ አንድም እስራኤላዊያን በመርከቧ ላይ እንዳልተሳፈሩም ገልጿል፡፡ [Al ain]

የኦሮሚያ ክልል ከአንድ ሺህ  በላይ ሃኪሞችን  ለመቅጠር  ቢፈልግም ተቀጣሪ  በማጣቱ  መሰረዙን አስታወቀ፡፡ የኦሮሚያ  ክልል ጤና ቢሮ 1ሺህ 1መቶ ሀኪሞችን ለመቅጠር  ባለፈዉ ዓመት ሰኔ ወር  2015 ዓ.ም ማስታወቂያ ቢያወጣም ተቀጣሪዎችን ባለማግኘቱ በጀቱን ወደ ሌላ ዘረፍ  ማዛወሩን አስታዉቋል፡፡ የቢሮዉ ምክትል ሃላፊ ዶ/ር ጉሻ በለኮ በሰኔ 2015 ላይ 1ሺህ 1መቶ ሀኪሞችን ለመቅጠር ማስታወቂያ የወጣ ቢሆንም ተቀጣሪዎችን ባለማግኘቱ  ቢሮዉ በጀቱን ለሌላ ጉዳይ ማዋሉን ተናግረዋል፡፡ለ2 ወራት ያክል ማስታወቂያዉን ክፍት ባደርግም ገበያ ላይ ተቀጣሪዎችን አላገኘሁም ብሏል ቢሮዉ፡፡ በየአንዳንዱ ጤና ተቋም ሀኪሞች መኖር ስላለባቸዉ ያንን ለማሟላት ማስታወቂያ ብናወጣም ሀኪሞችን ባለማግኘታችን በምትኩ  የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎችን፣ አዋላጆችን እና ነርሶችን ለመቅጠር ተገደናል ነዉ ያሉት፡፡ ከዚህ በፊት ለመላዉ ኦሮሚያ አገልግሎት የሚሰጡ የጤና ባለሙያዎች ቁጥር 72ሺህ ነበር ያሉት ሃላፊዉ አሁን ላይ ቁጥሩ ወደ 85ሺህ ከፍ ማለቱን ተናግረዋል፡፡በተቻለን አቅም ማስታወቂያ አዉጥተን ገበያ ላይ የነበሩትን ለመዉሰድ ሞክረናል ነገር ግን አሁንም የሀኪሞች ዕጥረት አለ ብለዋል፡፡ ማስታወቂያዉን አይተዉ የመጡትን እንቀጥራለን ፤ካልመጡ ግን ገበያዉ ላይ የሰዉ ሃይል እንደሌለ ነዉ የሚቆጠረዉ ሲሉ ተናግረዋል፡፡ሃላፊዉ በተጨማሪም ባለፈዉ ዓመት ሃኪሞችን ለመቅጠር ባወጣነዉ ማስታወቂያ ሀኪሞችን ማግኘት ስላልቻልን ወደ 7 መቶ አከባቢ የሚሆኑ የተለያዩ ባለሙያዎችን ቀጥረናል ሲሉም ነግረዉናል፡፡ Via Ethio FM

ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ ከጀርመን መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያዩ! ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከ"G20 Compact with Africa (CWA)” ጉባኤ አስቀድሞ
ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ ከጀርመን መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያዩ! ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከ"G20 Compact with Africa (CWA)” ጉባኤ አስቀድሞ ከጀርመን መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል። ውይይታቸውም ሁለቱ ወገኖች በጋራ ትብብር መስኮች፣ በሀገር ውስጥ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆኑን ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ያገኘዉ መረጃ ያመላክታል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና የጀርመኑ መራሄ መንግስት በዚህ አመት መጀመሪያ የጀርመኑ መራሄ መንግስት ኢትዮጵያን በጎበኙበት ወቅት መገናኘታቸውም ይታወሳል።

" 65 ቢሊዮን ብር የት እንደገባ አይታወቅም " - አምባሳደር ሱሌማን ደደፎ በቀድሞ አጠራሩ የኢትዮጵያ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) በአዲሱ አወቃቀር ኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ላይ የሒሳብ ምርመራ አገልግሎት ኮርፖሬሽን ባደረገው የሒሳብ ኦዲት ምርመራ፣ 65 ቢሊዮን ብር የት እንደደረሰ እንደማይታወቅ ተገለጸ፡፡ በአገሪቱ ከሚገኙ ትልልቅ ድርጅቶች መካከል አንዱ የነበረው ሜቴክ ከተመሠረተ ከ2002 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ 2012 ዓ.ም. ድረስ የነበረው የሒሳብ ኦዲት ከተሠራ በኋላ ከፍተኛ ኪሳራ መገኘቱን የግሩፑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው የተሾሙት ሱሌማን ደደፎ (አምባሳደር) ለሪፖርተር ጋዜጣ ተናግረዋል። " የሒሳብ ምርመራ አገልግሎት ኮርፖሬሽን በሠራው ሪፖርት መሠረት 65 ቢሊዮን ብር የት እንደደረሰ ስለማይታወቅ፣ የኦዲት ሪፖርቱን መሠረት በማድረግ መንግሥት እንዲሽረው (Write off) ተጠይቆ ውሳኔ አግኝቷል " ብለዋል፡፡ በዚህም መሠረት የተገኘው የኪሳራ ገንዘብ በዕዳ እንዳይመዘገብ መንግሥት ሽሮታል (Writeoff) ሲሉ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገልጸዋል፡፡ በኦዲት የተገኘው ገንዘብ ምንም ሥራ ላይ ያልዋለና በወቅቱ የነበሩ አመራሮች ተከፋፍለው የወሰዱት በመሆኑ በዚህ ተቋም አማካይነት የአንድ ህዳሴ ግድብ መሥሪያ ብር መዘረፉን ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ለውጥ ከተደረገ በኋላ ወታደራዊ ምርቶች ለብቻ እንዲሆኑ በመክፈል እንደ አዲስ የተዋቀረው ግሩፑ፣ የደረሰበትን ሀብትና ዕዳውን የመለየትና ጥፋቶችን በመመርመር በሕግ የሚገዛ አገራዊ ተቋም ለማድረግ እየተሠራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የቀድሞው ሜቴክ ከተመሠረተበት ጀምሮ እስካሁን ያለውን አጠቃላይ ሒሳብ ኦዲት መደረግ የተጀመረ መሆኑን፣ እስከ 2012 ዓ.ም. ድረስ ያለውን በማጠናቀቅ ከ2012 ዓ.ም. በኋላ ያለው በሒደት ላይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በኦዲት ሪፖርቱ ግኝት መሠረት ከኪሳራው በተጨማሪ፣ በሀብት ደረጃ የተመዘገቡት እንዲሸጡ በማድረግ ለግሩፑ ገቢ እንዲሆን እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡ በዚህም መሠረት በአሁኑ ወቅት ያለ አገልግሎት የተቀመጡ 5 ቤቶችን ወደ ገንዘብ ለመቀየር በቅርቡ ለሽያጭ እንደሚቀርቡ ገልጸዋል፡፡ " የቀድሞ የድርጅቱ አመራሮች የዝርፊያ ሥልት አሁንም ድረስ በተለያዩ መንገዶች እየቀጠለ በመሆኑ፣ ከኪሳራ እንዳይላቀቅ ማነቆ እየሆነ ነው " ብለዋል፡፡ በቅርቡ ይፋ የተደረገው የፓወር ኢኪዩፕመንት ፋብሪካ ውስጥ የሚገኙ ስምንት አመራሮች #ከብረት_ስርቆት ጋር በተገናኘ መያዛቸው አንዱ ማሳያ መሆኑን፣ ሌሎች አመራሮችም ቀስ በቀስ ተጠያቂ እንደሚደረጉ አሳውቀዋል። መረጃው የሪፖረተር ጋዜጣ ነው።

ሕገወጥ መታወቂያ ይዘው የሚገኙ የውጭ ዜጎች ቁጥር በአሳሳቢ ሆኔታ እየጨመረ እንደሚገኝ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አስታወቀ። አዲስ ፓስፖርት ለማግኘትም ይሁን ለማደስ አመልክተው ለረጅም ጊዜ
ሕገወጥ መታወቂያ ይዘው የሚገኙ የውጭ ዜጎች ቁጥር በአሳሳቢ ሆኔታ እየጨመረ እንደሚገኝ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አስታወቀ። አዲስ ፓስፖርት ለማግኘትም ይሁን ለማደስ አመልክተው ለረጅም ጊዜ ወረፋ በመጠበቅ ላይ የሚገኙ ወደ 200 ሺህ የሚደርሱ አመልካቾች እስከ ታህሣስ መጨረሻ ፓስፖርት እንዲያገኙ ለማድረግ ጥረት ላይ መሆኑንም ገልጿል። ከፓስፓርት እድሳትም ይሁን አሰጣጥ ጋር ተያይዞ በሌብነትና ሙስና ውስጥ የተዘፈቁ ሕዝብን ያማረሩ ያላቸውን 38 የተቋሙን ሰራተኞችን እና 15 ደላሎችን መያዙን የገለፀው ተቋሙ ሕገወጥ መታወቂያ ይዘው የሚገኙ የውጭ ዜጎች ቁጥርም በአሳሳቢ ሆኔታ እየጨመረ እንደሚገኝ አስታውቋል። የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ለኢትዮጵያውያን የሚሰጠው የፓስፖርት አገልግሎት ዜጎች በቀላሉ የማያገኙት እና ለከፍተኛ እንግልት የሚዳረጉባቸው የሥራ መስኮች ውስጥ አንደኛው ሲሆን በመሥሪያ ቤቱ ሠራተኞችም ይሁን በደላሎች ከፍተኛ እጅ መንሻ እየተጠየቀ ከሚፈልገው ጉዞ ሲደናቀፍ ይታያል።ለተቋሙ በቅርቡ ተሹመው በዋና ዳይሬክተርነት እያገለገሉ ያሉት ሰላማዊት ዳዊት መሥሪያ ቤቱ በርካታ የሌብነት ኔትዎርክ ያለበት ፣ ደላሎች በስፋት በውጭም በውስጥም የተንሰራፉበት፣ በርካታ ሰዎች በዚህ ችግር ውስጥ ወድቀው የተግኙበት ስለመሆኑ ከዚህ በፊት ገልፀው ነበር።  "ቀውስ" ሲሉ የጠቀሱት እና የዜጎች ፓስፓርት የማግኘት መብት ችግር አሁን በስፋት እየታተመ እየገባ ባለው ፓስፖርት እየተቃለለ መሆኑን ፣ ወረፋ እየጠበቀ ያለው ወደ ሁለት መቶ ሺህ ፓስፖርት አመልካችም እስከ ታህሳሥ መጨረሻ እንዲያገኝ ጥረት ላይ መሆናቸውን ዛሬ ተናግረዋል።

የንጹሃንን ጉዳት ለመቀነስ ያደረግነው ጥረት "ስኬታማ አልሆነም"- ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታኔያሁ በጋዛ በሚደረገው ጦርነት የንጹሃንን ጉዳት ለመቀነስ ያደረ
የንጹሃንን ጉዳት ለመቀነስ ያደረግነው ጥረት "ስኬታማ አልሆነም"- ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታኔያሁ በጋዛ በሚደረገው ጦርነት የንጹሃንን ጉዳት ለመቀነስ ያደረጉት ጥረት ስኬታማ አለመሆኑን ተናግረዋል። በጋዛ ጦርነት እያካሄዱ ያሉት የእስራኤል ወታደሮች በአል ሽፋ ሆስፒታል ውስጥ ሀማስ ይጠቀምበት የነበረ ክፍል ማግኘታቸውን ገልጸዋል። ጦሩ በሆስፒታሉ ስር ወደሚገኝ ዋሻ ያስገባል ያለውን መግቢያመሰ በቪዲዮ አሳይቷል። ከዚህ በተጨማረም ጦሩ በሆስፒታሉ ግቢ ውስጥ ብዙ መሳሪያ የተጫነበት መኪና አግኝታለሁ ብሏል። ነገረግን ሀማስ በትናንትናው እለት ባወጣው መግለጫ ቡድኑ አልሽፋ ሆስፒታልን ለወታደራዊ አላማ ተጠቅሞበታል የሚለው "የሀስት ትርክት" ነው ብሏል። ባለፈው ጥቅምት ወር ሀማስ የእስራኤልን ድንበር በመጣስ 1200 እስራኤላውያንን መግደሉን ተከትሎ እስራኤል መጠነሰፊ የሆነ የአጸፋ ምላሽ እየሰጠች ትገኛለች።የጋዛ የጤና ባለስልጣናት እንደሚናገሩት በእስራኤል ጥቃት እስካሁን ከ11ሺ በላይ ፍልስጤማውያን ተገድለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ኔናንያሁ ከአሜሪካው ቴሌቪዥን ሲቢኤስ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እስራአል የንጹሃንን ጉዳት ለመቀነስ ያደረገችው ጥረት አለመሳካቱን ገልጸዋል።"የትኛውም የንጹሃን ግድያ ዘግናኝ ነው። ንጹሃንን እንዳይጎዱ ጥንቃቄ አድርገን ነበር። ነገርግን ሀማስ ለአደጋ እንዲጋለጡ አደረጋቸው።"ኔታንያሁ ንጹሃን እንዳይጎዱ"በራሪ ወረቀት በትነናል፤ በእጅ ስልካቸው ደውለናል፤ በዚህም ብዙዎች ሸሽተዋል" ብለዋል።

#MoH የህክምና ስፔሻሊቲ ስልጠና ምዝገባ ተጀመረ። የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በ2016 የትምህርት ዘመን በ21 የህክምና ስፔሻሊቲ ፕሮግራሞች አመልካቾችን ተቀብሎ እ
+1
#MoH የህክምና ስፔሻሊቲ ስልጠና ምዝገባ ተጀመረ። የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በ2016 የትምህርት ዘመን በ21 የህክምና ስፔሻሊቲ ፕሮግራሞች አመልካቾችን ተቀብሎ እንደሚያሰለጥን አሳውቋል። ሚኒስቴሩ ፤ የብሔራዊ የህክምና ስፔሻሊቲ ስልጠና /ERMP/ መግቢያ ፈተና በመስጠት አወዳድሮ እንደሚያሰለጥን የገለፀ ሲሆን የህክምና ዶክትሬት ዲግሪ ያላቸውና የስፔሻሊቲ ስልጠና መውሰድ የሚፈልጉ ምዝገባ ማድረግ እንደሚችሉ ገልጿል። ምዝገባው ከዛሬ ህዳር 06 ቀን 2016 ዓ /ም የሚጀምር ሲሆን ህዳር 20 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚያበቃ አሳውቋል። አመልካቾች የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ድረ-ገፅ www.moh.gov.et/ermp ላይ በመግባትና ለመሰልጠን በሚፈልጉት የስፔሻሊቲ ትምህርት ላይ በመመዝገብ መወዳደር እንደሚችሉ ተገልጿል። ተመዝጋቢዎች ምዝገባውን ከመጀመራቸው በፊት ዝርዝር መረጃዎችንና መመሪያዎችን በዚህ ይመልከቱ ተብሏል👇 https://www.moh.gov.et/site/initiatives-4-col/ermp

ዩኤሴኤይድ በኢትዮጵያ የሚያደርገውን የምግብ ርዳታ እንደሚቀጥል አስታወቀ! የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (ዩኤሴኤይድ)፣ ለኢትዮጵያ የሚሰጠውን የምግብ ርዳታ፣ ከአምስት ወራት መቋረጥ በኋላ በ
ዩኤሴኤይድ በኢትዮጵያ የሚያደርገውን የምግብ ርዳታ እንደሚቀጥል አስታወቀ! የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (ዩኤሴኤይድ)፣ ለኢትዮጵያ የሚሰጠውን የምግብ ርዳታ፣ ከአምስት ወራት መቋረጥ በኋላ በመጪው የፈረንጆች ወር እንደሚቀጥል አስታውቋል። ርዳታው ተቋርጦ የነበረው ለተረጂዎች መዳረስ የነበረበት ምግብ በአካባቢ ባለሥልጣናት እውቅና ጭምር ለገበያ ቀርቧል በሚል ነበር። ዩኤሴኤይድ ባለፈው ወር አንድ ሚሊዮን ለሚሆኑና በኢትዮጵያ ለሚገኙ ፍልሰተኞች ርዳታ መስጠቱን ቀጥሎ ነበር። ይህም መንግስት ምግብ ለፍልሰተኞች በማዳረስ ሥራ ውስጥ እንደማይገባ ስምምነት ላይ ከተደረሰ በኋላ መሆኑን የአሶስዬትድ ፕረስ ዘገባ አመልክቷል። የድርጅቱ ቃል አቀባይ ጀሲካ ጀኒንግስ ትናንት እንደገለጹት፣ ርዳታው እንዲቀጥል የተደረገው የተረጂዎችን ምዝገባ እና የታደለው እህል መድረሱን ማረጋገጥ በተመለከተ አዲስ የተሻሻለ አሠራር መዘርጋቱን ተከትሎ ነው። Via VoA

" የተደፈረችው ቅድስት ቤተክርስቲያን ናት " - ብፁዕነታቸው ድርጊቱ የተፈፀመው ህዳር 1 ቀን ምሽት ላይ ነው። መልአከ መንክራት ቆሞስ አባ ኤርምያስ ገ/ጻድቅ የቦሌ ቡልቡላ ምስካበ ቅዱሳን አቡነ ሳ
+1
" የተደፈረችው ቅድስት ቤተክርስቲያን ናት " - ብፁዕነታቸው ድርጊቱ የተፈፀመው ህዳር 1 ቀን ምሽት ላይ ነው። መልአከ መንክራት ቆሞስ አባ ኤርምያስ ገ/ጻድቅ የቦሌ ቡልቡላ ምስካበ ቅዱሳን አቡነ ሳሙኤል ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ ሲሆኑ በደብሩ ለሁለት ቀን በተዘጋጀው ጉባኤ ላይ ኅዳር 1 ምሽት ጉባኤው ተጠናቆ ምዕመናን ሲባርኩ " ማንነቱ ባልታወቀ " ግለሰብ በጥይት ተመተዋል። በኃላም ወደ ላንሴት አጠቃላይ ሆስፒታል ገብተዋል። በአሁን ሰዓትም በህክምና ክትትል ላይ ናቸው። ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተፈፀመው ድርጊት " የተደፈረችው ቅድስት ቤተክርስቲያን ናት " ብለዋል። ብፁዕነታቸውን ይህን ያሉት መልአከ መንክራት ቆሞስ አባ ኤርምያስ ገ/ጻድቅ በሆስፒታል ተገኝተው ከጎበኙ በኃላ ነው። ሀገረ ስብከቱ ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር እንደሚነጋገር የገለፁት ብፁዕነታቸእ " ለአገልጋዮች ነገ ዋስትና እንዲኖራቸው መሠራት አለበት " ሲሉ አስገንዝበዋል። በተፈጸመው ድርጊት የተደፈረችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ናትም ብለዋል ብፁዕነታቸው። ጉዳዩን በተመለከተ እስካሁን በፖሊስ በኩል የተሰጠ ማብራሪያ የለም።

#MoE ትምህርት ሚኒስቴር 6 የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሬሜዲያል ተማሪዎችን እንደማያስተናግዱ አሳወቀ። በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስደው በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የ
+1
#MoE ትምህርት ሚኒስቴር 6 የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሬሜዲያል ተማሪዎችን እንደማያስተናግዱ አሳወቀ። በ2015 ዓ.ም  የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስደው በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሪሚዲያል ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል የማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም ምርጫቸውን በየትምህርት ቤታቸው በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ ህዳር 12/2016 ዓ.ም ድረስ እንዲያስተካክሉ ተብሏል። ሚኒስቴሩ፦ 1. አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 2. አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ 3. አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ 4. ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ 5. አርሲ ዩኒቨርሲቲ 6. ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ፕሮግራም #የማያስተናግዱ መሆኑን አሳውቋል።

#StockMarket ኢትዮጵያ ውስጥ በቅርቡ የ ' ስቶክ ማርኬት ' ስራ እንደሚጀመር ተገለፀ። ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በቅርቡ በኢትዮጵያ የሚጀምረውን የ ' ስቶክ ማርኬት ' ለመደገፍ ከወዲሁ እን
+1
#StockMarket ኢትዮጵያ ውስጥ በቅርቡ የ ' ስቶክ ማርኬት ' ስራ እንደሚጀመር ተገለፀ። ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በቅርቡ በኢትዮጵያ የሚጀምረውን የ ' ስቶክ ማርኬት ' ለመደገፍ ከወዲሁ እንዲዘጋጅ ጥሪ አቅርበዋል። ስቶክ ማርኬት በከፍተኛ ደረጃ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ይደግፋል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ " በጣም ብዙ ሰው ሃሳብ አለው ገንዘብ የለውም፤ ጥቂት ሰዎች ደግሞ ገንዘብ አላቸው ሃሳብ የላቸውም ፤ ጥቂቶች ደግሞ ገንዘብ አላቸው ሃሳብም ገብቷቸዋል ተቋም የላቸውም ፤ ስቶክ ማርኬት ማለት ገንዘብ ያለውን ሃሳብ ያለውንና ተቋምን የሚያገናኝ ምርጥ ሀሳብ ማለት ነው " ሲሉ አስረድተዋል። " ለአብነት ፦ - በአረብ ሀገራት ያሉ እህቶች ' ስቶክ ማርኬት ' ውስጥ ሼር ገዝተው እዛ እየሰሩ ኢንቨስት ማድረግ እንደሚችሉ ፤ - አርሶ አደሮችም ከስቶክ ማርኬት ሼር ገዝተው እያረሱ ኢንቨስት ማድረግ ይችላሉ ፤ - ዲያስፖራዎችም ወደ ሀገር ሲመለሱ ምንም የሌላቸው እንዳይሆኑ ከወዲሁ ዋና ዋና ኩባንያዎች ላይ ኢንቨስት ማድረግ ይችላሉ " ሲሉ ተናግረዋል። ዶ/ር ዐቢይ ፤ ቴሌኮሚኒኬሽን በቅርቡ የተወሰነ ፐርሰንት ለህዝቡ እንደሚሸጥ አሳውቀዋል። በሂደት ቴሌን፣ አየር መንገድን የህዝብ ተቋማት የማድረግ ስራ እንደሚሰራ አመልክተዋል። " እኛ ሂልተንንም፣ ጊዮንንም፣ አየር መንገድንም፣ ቴሌኮምን ይዘን አንዘልቀውም " ያሉ ሲሆን እነዚህ ኩባንያዎች ላይ ብዙዎች ኢንቨስት እንዲያደርጉበት ካደረግን የተሻለ እድገት ሊያመጡ ይችላሉ፤ ለኢትዮጵያ እድገትም እገዛ ያደርጋል ሲሉ ተናግረዋል። ለዚህም ተግባራዊነት ምክር ቤቱ ከወዲሁ ድጋፍ ለማድረግ እንዲዘጋጅ ጠይቀዋል።