Wolkite University yeselefiyah channel
የዚህ ግሩፕ ዓለማ 1. ከመንሐጅ ጋር በተያያዘ ያሉ ሙሓደረዎች ፣ምክሮችና ሌላም ጠቃሚ መልዕክቶች በማስተላለፍ ለመመካከር 2.ቻነሉ በተለይም WKU ና አከበቢውን በተመለከተ ከሰለፊዮች ጋ ሀቅን የምንማመርበት አጥማሚዎችን የምነስጠነቅቅበት አወዘጋቢዎችን የምናጋልጥበት ግራ የተጋቡትን የምናመለክትበት ይሆነል በአለሀ ፍቃድ እንሸ አላህ 3 WKUተማሪዎችን የሚመለከት መልእክቶችን ለማስተላለፍ ነው
Show more- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Data loading in progress...
የኡሙ ሐቢባህ ረምላ ቢንት አቢ ሱፍያን (ረዲየላሁ ዐንሃ) አጭር የሕይወት ታሪክ:አል-ኢማም አዝ-ዘሀቢ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) «ሲየር አዕላሚን ኑበላእ» በተሰኘው ኪታባቸው ላይ የኡሙ ሐቢባህ ረምላ ቢንት አቢ ሱፍያን (ረዲየላሁ ዐንሃ) አጭር የሕይወት ታሪክን ሲገልፁ የሚከተለውን አስፍሯል፦ “ሙሉ ስሟ፡ ረምለህ ቢንት አቢ ሱፍያን ሰኽር ቢን ሐቢብ ቢን ኡመየህ ቢን ዐብድ አሽ-ሸምስ ቢን ዐብድ መናፍ ቢን ቁሰይ ትባላለች። ረምላህ (ረዲየላሁ ዐንሃ) ለመልእክተኛውን (ﷺ) የአጎት ልጅ ነች። ከመልእክተኛውን (ﷺ) ሚስቶች ከአጠቃላይ እሷ (ረምለህ) በዝምድና ለመልእክተኛውን (ﷺ) በእጅጉን የቀረበች ነች፤እንዲሁም ከመልእክተኛውን (ﷺ) ሚስቶች ከአጠቃላይ ከፍተኛውን የመህር ድርሻ የወሰደችው እሷ ነች። 400 ዲናር ወይም 4000 ዲርሃም ያክል ወስዳለች። የጋብቻ ስነስርዓቱ የተፈፀመው በሀገረ በሐበሻ (በኢትዮጵያ) ነው። የኢትዮጵያው ንጉስ ነጃሺ ለመህሯ 400 ዲናር ያክል ሰጥቷታል፤ ከዚህ ውጭም ሌሎች ቁሳቁሶችን ሰጥቷል። የረምለህ ቢንት አቢ ሱፍያን (ረዲየላሁ ዐንሃ) የመጀመሪያው ባለቤቷ ዑበይዱሏህ ቢን ጀሕሽ ቢን ሪያብ ቢን አሰዲይ ይባላል። ዑበይዱሏህ እስልምናን ቀይሮ ወደ ክርስትና ገብቷል፤ ሐይማኖቱን ከቀየረ በኃላ ነበር ከዚች ዓለም የተለየው። ለጋብቻ ስነስርዓቷ ዑስማን ኢብኑ አፋን (ረዲየላሁ ዐንሁ በሐበሻ (በኢትዮጵያ) ) ወልይ ሆኖላታል። አባቷ አቡ ሱፍያን ሙስሊም ከመሆኑ በፊት ሊጠይቃት በመጣ ጊዜ፣ በመልእክተኛውን (ﷺ) ፍራሽ እንዳይቀመጥ ከልክለዋለች፤ ምክንያቱም በጊዜው አቡ ሱፍያን ሙሽሪክ ስለነበር ነው።
(ሲየር አዕላሚን-ኑበላእ)አቡ ሱፍያን ለመልእክተኛውን (ﷺ) ያቀረባቸው ሶሥት ጥያቄዎች፡ ዐብዱሏህ ኢብኑ ዐባስ (ረዲየላሁ ዐንሁማ) የሚከተለውን ዘግቧል፦ “ሙስሊሞች አቡ ሱፍያንን በክብር አይመለከቱትም ነበር፤ከሱም ጋር አይቀመጡም፤አቡ ሱፍያን ለአላህ መልእክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብሎ አላቸው፡ "አንቱ የአላህ መልእክተኛ ሆይ! (ﷺ) ሶሥት ነገራቶችን እሺ በሉኝ፤ መልእክተኛውም (ﷺ) እሺ አሉት። ቀጠለና አቡ ሱፍያን እንዲህ አለ፡ “እኔ ዘንድ እጀግ በጣም ውብ (ቆንጆ) የሆነች ሴት አለች፤ ኡሙ ሐቢባህ የአቡ ሱፍያን ልጅ እናም አግቧት።” በመልእክተኛውም (ﷺ) አሺ አሉት። ሙዓዊያን የርሶ ፀሃፊ ያድርጉት፤ በመልእክተኛውም (ﷺ) አሺ አሉት፤ ከዚያም ቀጠለና አቡ ሱፍያን እንዲህ አለ፡ "እኔን የምዕመናን የጦር መሪ ያድርጉኝ፣ከዚህ ቀደም ሙስሊሞችን እንደተፋለምኩ ሁሉ፣ካህዲያኖችን እፋለም ዘንድ።" #መልእክተኛውም (ﷺ) እንዲህ አሉት: "እሺ።" አቡ ዙመይል እንዲህ አለ፡ "አቡ ሱፍያን እነኝህ ሶሥት ጥያቄዎችን ባይጠየቅ ኖሮ፣ባላገኘ ነበር..."
(ሙስሊም: 2501)۞ عَسَى اللَّهُ أَن يَجْعَلَ بَيْنَكُمْ وَبَيْنَ الَّذِينَ عَادَيْتُم مِّنْهُم مَّوَدَّةً ۚ وَاللَّهُ قَدِيرٌ ۚ وَاللَّهُ غَفُورٌ رَّحِيمٌ በናንተና በእነዚያ ከእነርሱ ጋር በተጣላችሁት ሰዎች መካከል አላህ መፋቀርን ሊያደርግ ይቻላል፡፡ አላህም ቻይ ነው፡፡ አላህም በጣም አዛኝ ነው፡፡
(ሙምተሂነህ:7)ይህንን የቁርኣን አንቀጽ አል-ኢማም አል-ቁርጡቢ (ረሂመሁላህ) በሚከተለው መልኩ ተርጉመውታል፡ “...ይህ ማለት ካህዲያኖች እስልምናን ይቀበላሉ ማለት ነው። ሙስሊሞች መካን ከተቆጣጠሩ በኃላ፣የተወሰኑ ካህዲያኖች ከሙስሊሞች ጋር ተቀላቅለዋል። ለምሳሌ እንደነ አቡ ሱፍያን ቢን ሐርብ፣አል-ሐሪስ ቢን ሒሻም፣ሱሐይል ቢን ዐምር እና ሃኪም ቢን ሂዛም የመሳሰሉ ሰዎች ከሙስሊሞች ጋር ተቀላቅለዋል። እንዲሁም «መወዳ» የሚለው ቃል፡ የአቡ ሱፍያን ልጅ የሆነችው የኡሙ ሐቢባህ እና የመልእክተኛውን (ﷺ) ጋብቻ ነውም ተብሏል... የኡሙ ሐቢባህ ረምላ ቢንት አቢ ሱፍያን (ረዲየላሁ ዐንሃ) የቀድሞው ባለቤቷ፡ ዑበይዱሏህ ቢን ጀሕሽ ይባላል። ሀለቱም ወደ ሐበሻ (ኢትዮጵያ) ተሰደዋል። ይሁንእንጂ የሱ ፍፃሜው የከፋ ነበር፤እስልምናን ለቆ ወጣ፤ወደ ክርስትና ሐይማኖት ገባ። ኡሱ (ዑበይዱሏህ ቢን ጀሕሽ) እሱ የገባበትን ሐይማኖት እንድትገባ ጠይቋት ነበር፤ግን እሷ አሻፈረኝ አለች። በእስልምናም ላይ ፀናች። ባሏ ዑበይዱሏህ ቢን ጀሕሽ በክርስትና ሐይማኖት ሳለ ነው ሕይወቱ ያለፈው። የአላህ መልእክተኛ (ﷺ) የጋብቻ ጥያቄውን ያቀረቡት በንጉሥ ነጃሺ በኩል ነበር...
(ተፍሲር አል-ቁርጡቢከፈርድ ሶላት በኃላ፣ አስራ ሁለት (12) ተጨማሪ የሱንና ሶላቶችን የሰገደ ሰው በጀነት ውስጥ ቤት ያለው ስለመሆኑ፡ ኡሙ ሐቢባህ ረምላ ቢንት አቢ ሱፍያን (ረዲየላሁ ዐንሃ) ከአላህ መልእክተኛ (ﷺ) ይዛ የሚከተለውን ሐዲስ ዘግባለች፦ “ማንኛውም የአላህ ባሪያ ለአላህ ብሎ በየእለቱ 12 የሱንና ረከዓዎችን ከፈርድ ሶላቶች ውጪ ከሰገደ፣አላህ በጀነት ውስጥ ቤትን ይገነባለታል (በጀነት ውስጥ ቤት ይገነባለታል)...እኔ ይህንን ሐዲስ ከአላህ መልእክተኛ (ﷺ) ከሰማው በኃላ፣እነኝህ የሱንና ሶላቶችን ትቼ አላውቅም።”
(ሙስሊም:728)ኡሙ ሐቢባህ ረምላ ቢንት አቢ ሱፍያን (ረዲየላሁ ዐንሃ) በሞት አፋፍ ላይ: እናታችን ዓኢሻህ (ረዲየላሁ ዐንሃ) እንዲህ ትላለች፡ “ኡሙ ሐቢባህ ረምላ ቢንት አቢ ሱፍያን (ረዲየላሁ ዐንሃ) በሞት አፋፍ ላይ ሆና ሳለ ጠራችኝ። እንዲህም ብላ አለችኝ፡ “በኛ መካከል (በነብዩ ﷺ ሚስቶች) የተከሰተው ነገር፤ አላህ እኔንም አንቺንም ምሯል... ከዚያም ዓኢሻህ እንዲህ አልኳት አለች: “አላህኮ ሁሉንም ምሮሻል።” ከዚያም ኡሙ ሐቢባህ ረምላ ቢንት አቢ ሱፍያን (ረዲየላሁ ዐንሃ) እንዲህ አለች፡ “አስደሰትሽኝ አላህ ያስደስትሽ...”
ሲየር አዕላሚን-ኑበላእ፣ከገፅ 218-223 ተቀንጭቦ የተወሰደ)📝 𝐓𝐫𝐚𝐧𝐬𝐥𝐚𝐭𝐞𝐝 𝐁𝐲: 𝐀𝐛𝐮 𝐇𝐚𝐟𝐬𝐚𝐡 (𝐦𝐚𝐲 𝑨𝒍𝒍𝒂𝒉 𝐟𝐨𝐫𝐠𝐢𝐯𝐞 𝐡𝐢𝐬 𝐬𝐢𝐧𝐬 𝐚𝐧𝐝 𝐝𝐞𝐟𝐢𝐜𝐢𝐞𝐧𝐜𝐢𝐞𝐬) @semirEnglish @semirEnglish
✍ አሰላሙ አለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበራካቱሁ በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው ምስጋና በአጠቃላይ ለአላህ የተገባ ነው መልካም ፍፃሜ አላህን ለሚፈሩ ባሮቹ ነው ጠላትነትም የለም ለበዳዮች ቢሆን እንጂ!! የአላህ ውዳሴውና ሰላምታው የነብያትና የመልክተኞች ሁሉ መደምደሚያ በሆኑት ነብያችን ላይ፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረቦቻቸው እንዲሁም የእነርሱን ፋና በመልካ በተከተሉት ላይ ይውረድ!
✍ አሰላሙ አለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበራካቱሁ በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው ምስጋና በአጠቃላይ ለአላህ የተገባ ነው መልካም ፍፃሜ አላህን ለሚፈሩ ባሮቹ ነው ጠላትነትም የለም ለበዳዮች ቢሆን እንጂ!! የአላህ ውዳሴውና ሰላምታው የነብያትና የመልክተኞች ሁሉ መደምደሚያ በሆኑት ነብያችን ላይ፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረቦቻቸው እንዲሁም የእነርሱን ፋና በመልካ በተከተሉት ላይ ይውረድ!
✍ አሰላሙ አለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበራካቱሁ በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው ምስጋና በአጠቃላይ ለአላህ የተገባ ነው መልካም ፍፃሜ አላህን ለሚፈሩ ባሮቹ ነው ጠላትነትም የለም ለበዳዮች ቢሆን እንጂ!! የአላህ ውዳሴውና ሰላምታው የነብያትና የመልክተኞች ሁሉ መደምደሚያ በሆኑት ነብያችን ላይ፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረቦቻቸው እንዲሁም የእነርሱን ፋና በመልካ በተከተሉት ላይ ይውረድ!
Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.