ምኒሮስ አማራ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት 🟢🟡🔴
Open in Telegram
289
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-530 days
Posts Archive
Repost from N/a
የአስቴ ጎማ ተራራ ክፍለ ጦር ወታደራዊ ቁመናውን ተቋማዊ ሂደትን በተከተለ መልኩ ገምግሞ አሰራሮችን በማዘመን ለሚሰጡ ድርጅታዊ ተልዕኮዎች ራሱን በተሐድሶ አዘጋጀ!!
ጳጉሜ 04/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ መሐመድ ቢሆነኝ ኮር አስቴ ጎማ ተራራ ክፍለ ጦር ተቋማዊና ወታደራዊ ብቃቱን ይበልጥ የሚያጠናክርበትን የተሐድሶ መርሃ-ግብር በደማቅ ሁኔታ ማድረጉን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን አስታወቀ።
በመርሃ-ግብሩ ላይ የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱና፣ የአሳምነው 5ኛ ዕዝ ሰብሳቢ አርበኛ ደሳለኝ ሲያስብሸዋ፣ የዕዙ ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ አማን እሸቱ፣ የዕዙ ፖለቲካ መምሪያ ሃላፊ ዶክተር ታደሰ ገ/ፃድቅ፣ እንዲሁም ሌሎች የዕዝ፣ የኮርና የክፍለ ጦሩ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
ጠላትን እንደ ንብ የሚነድፉት፡ አስቴ ጎማ ተራራ ክፍለ ጦር፤ ህዝቡን ከመጥፋትና ከውርደት ታድጎ ወደ ታሪካዊ የክብር ማማ ለማሸጋገር ራሱን በትግል ሜዳ ያስቀደመ አይበገሬ ጦር ሆኖ ተከስቷል።
ክፍለ ጦሩ ጠላት አካባቢውን በወረረበት የ42 ቀናት ውጊያ ታላቅ የበላይነት በማሳየት፣ ፈተናዎችን በማለፍ፣ የጠላትን ኃይል በማዝረክረክ የቆየ መሆኑ ሲታወቅ፧ የቻለ በእሳት የተፈተነ ስብስብ መሆኑ ተገልጿል። በሂደት ያጋጠሙትን ውስጣዊ ክፍተቶች በመሙላት፣ በአዳዲስ አመራሮችና አደረጃጀቶች ወታደራዊ ቁመናውን በማዘመን ለቀጣይ ግዳጆች በከፍተኛ ዝግጅት ራሱን አድሷል።
በመድረኩ የክብር እንግዳ ሆነው የተገኙት የአሳምነው 5ኛ ዕዝ ዋና መሪ አርበኛ ደሳለኝ ሲያስብሸዋ ባስተላለፉት መልዕክት፦" ይህ ትግል የህዝብ ትግል ነው። በዚህ ቅዱስ በሆነው ትግላችን የጀመርነውን የአማራ ህዝብ ህልውና በማረጋገጥ የኢትዮጵያን የወደፊት መፃኢ እጣፋንታ ለማስተካከል ነው" በመሆኑም ተቋማዊ አሰራርን ጠብቃችሁ በርቱ በማለት ሲቋጩ፤ የዕዙ ዋና ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ አማን እሸቱ በበኩላቸው የወታደራዊ ዝግጅቱን ደረጃ ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው፡ ሁልጊዜም የብቃት ደረጃችሁን በማሻሻል ነገም እንደወትሮው የሁልጊዜ ዝግጅትና ጥንካሬ ይኑራችሁ ሲሉ ደምድመዋል።
በመድረኩ ላይ ከክፍለ ጦሩ አባላት ለተነሱት ጥያቄዎች፦ ከአመራሩ በቂ ማብራሪያና ምላሽ ሲሰጥ፣ ለነበሩ ክፍተቶች በሙሉ በአዲሱ አሠራር እደማይደገሙ ተገልጿል።
በመጨረሻም የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ ባስተላለፉት መልዕክት፦ "የአንድነታችን ውጤት በጠንካራ አላማ እድንወያይና በጋራ እንድናቅድ አድርጎናል" ዕቅዳችንንም በአንድነት እናሳካለን በሚል መልዕክት የዕለቱ መርሀ-ግብር መጠናቀቁን ኮሩ አሳውቋል።
" ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ)ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
https://t.me/abeamoraw
+3
የ7/ለ70 ክፍለ ጦር፤የጦር አበጋዞች በብርቂቶ ቀበሌ ጠላትን ድባቅ በመምታት ታላቅ ድል ተቀዳጁ!!
ጳጉሜ 02/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ 7/ለ70 ክፍለ ጦር በኤፌሶን አላላ ክላስተር ቀብርቂቶ በተደረገ ከፍተኛ ተጋድሎ የጠላትን ኃይል አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት ድል ተቀዳጁ።
ለዐቢይ አህመድ አገዛዝ ታማኝ እንደሆነ የሚነገርለት 102ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር ከአጣዬ እና ከሰንበቴ አቅጣጫዎች በመነሳት በፋኖ ላይ ድንገተኛ ከበባ ለማድረግ ብርቂቶ የተከሰተውን ጠላት፤ ቀድመው በመዘጋጀት ስልታዊ የማጥቃት ውጊያ ያደረጉት አናብስቶች ታላቅ ድል አስመዝግበዋል።
በብርቂቶ ቀበሌ በተካሄደው ከባድ ውጊያ የጠላት ኃይል ከፍተኛ ሰብአዊና ቁሳቁሳዊ ውድመት ማስተናገዱን " ጫላ ስዩም" የተባለ አንድ የአገዛዙ አባል እጁን ለፋኖ ከሰጠ በኃላ እንዲሕ ሲል አብራርቷል፤ የአብይ አሕመድ ስርዓት በተሳሳተ ትርክት ከየስራ ቦታችን አፍሶ አምጥቶ፣ ከፋኖጋ በነበረው ውጊያ በጣም በርካታ አባሎቻችን ሙትና ቁስለኛ ሆነውብናል ሲል አረጋግጧል።
ይሕንን ታላቅ ገድል የክፍለ ጦሩ አካል ደመላሽ ሻለቃ ያስመዘገበች ሲሆን፣ ከጠላት የሚከተሉትን ንብረቶች ለክፍለ ጦሩ ገቢ አድርጋለች፦
✔ (2) ጥርጥር ክላሽንኮቭ መሳሪያ
✔ (120) የክላሽኮቭ ተተኳሽ
✔ (3) ወታደራዊ ቦርሳዎች
✔ (2) የውሃ ኮዳዎች
✔ (8) ካዝናዎች
✔ (4) F1 ቦንቦች
በመጨረሻም በዚሕ አውደ ውጊያ ክፉኛ የቆሰሉት የጠላት አባላት ወደ አጣዬና ሰንበቴ ለህክምና በሪፈር እደተላኩና ሌሎች ቀላል ቁስለኞች በአላላ ጤና ጣቢያ እየታከሙ እንደሆነ በውስጥ መረጃዎቹ ማረጋገጡን ገልጿል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ህ/ግንኙነት መምሪያ
የአርበኞች ጦር በተሬ ክላስተር ወደ ዘመናዊ የክፍለ ጦር አደረጃጀት እየተሸጋገረ ነው
ጳጉሜ 01/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ የይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ተሬ ክላስተር የአርበኞች ጦር ሠራዊቱን ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር በጠንካራና ዘመናዊ አደረጃጀት እየሠራ እንደሚገኝ የዕዙ የስምሪት አመራሮች ገለጹ።
የአማራ ሕዝብ ሕልውናውን ለማስከበርና የትውልዱን ነፃነት ለማረጋገጥ አደረጃጀቱን ማዘመን፣ ጠንካራ ተቋም መፍጠርና ቆራጥ አመራር መሰየም ወሳኝ መሆኑን በመገንዘብ የአባት አርበኞች ጦር አደረጃጀቱን በማጠናከር ላይ ይገኛል።
ቀደም ሲል በብርጌድ ደረጃ ተደራጅቶ ሲንቀሳቀስ የቆየው የተሬ ሕዝብ ድሉን ለማፋጠንና ቀጠናውን ለማስተሳሰር ብርጌዶችን ወደ አርበኞች ክፍለ ጦር በማዋሃድ ለመዋቀር ተዘጋጅቷል። በቀጠናው ታላላቅ ወታደራዊ ጀብዶችን ሲያስመዘግቡ የቆዩት ብርጌዶች ጥልቅ ወታደራዊና ፖለቲካዊ ግምገማ በማድረግ ውስጣዊ አንድነታቸውን በመፈተሽና ክፍተቶችን በመሙላት አወቃቀራቸውን በማዘመን ላይ ናቸው።
በዚህ የግንባታ መርሃ ግብር ላይ ከፍተኛ የድርጅት አመራሮች፣የቀጣናው ስምሪት አካል የዕዝ ከፍተኛ አመራሮች እና የኮር አመራሮች የተገኙ ሲሆን፤ የአፋብን ተቀዳሚ ም/ል ሊቀመንበር አርበኛ መከታው ማሞ ድርጅቱ ወጥ አሰራሮችን በመተግበር ለማይቀረው የነፃነት ጉዞ መዋቅሮቹን እያጠናከረ መሆኑን ገልጸዋል።በዚህም ሁሉም በየደረጃው ለትግሉ የሚጠበቅበትን አበርክቶ በማድረግ ሁልጊዜም ንቁና ቆራጥ ተሳትፎ ማድረግ እንዳለበት አሳስበዋል።
በዚህም መሐመድ ስንዴው ብርጌድ እና ታደለ ወርቁ ብርጌድ አመራሮቻቸውን በማዋሃድ አንድ ታላቅ ክፍለ ጦር እንዲመሰርቱ አቅጣጫ ተቀምጧል።
ለአዲሱ አርበኞች ክፍለ ጦር በውጊያ ሜዳ ብቃታቸው የተመሰከረላቸው ቆራጥ መሪዎች የተሰየሙ ሲሆን፣ በተደራጀ ሁኔታ ወደ ሥራ በመግባት የሕዝቡን ሰቆቃ ለመታደግ መዘጋጀታቸው ተገልጿል።
"ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!"
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!"
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
+3
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መንዝ አውራጃ እና የመንዝ ጓሳ ማህበረሰብ ጥበቃ ታሪካዊ ቦታ !!
መንዝ አውራጃ ታሪካዊቷ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት እምብርት፣ የኢትዮጵያ ነገሥታት መነሻ እና በከፍታማ ተራራማ ምድሯ፣በቅዝቃዜው አየሯ እና በጥንታዊ ሥልጣኔዋ የምትታወቀው መንዝ፤ የነጋሢ፣ የሰፋ እልፍኝና የትግል ምድር ናት። የሰው ልጅ ከተፈጥሮ ጋር ተጣጥሞና ተከባብሮ መኖር እንደሚችል ትልቅ ማሳያ የሆነችው ይህች ምድር፣ በውስጧ ልዩ የተፈጥሮ ሀብት አቅፋ ይዛለች።
የመንዝ ጓሳ እና የጓሳ ኮሙኒቲ ሎጅ (Guassa Community Lodge)
በመንዝ አውራጃ የሚገኘው የመንዝ ጓሳ ጥበቃ ቦታ፣ ከ400 ዓመታት በላይ ያስቆጠረና የሀገር በቀል የተፈጥሮ ጥበቃ ሥርዓት የሚከተል የሚመራ ድቅ ተፈጥሮ ቦታ ነው።
ይህ አካባቢ፦ ልዩ የዱር አራዊት ቤት፦ ብርቅዬው የኢትዮጵያ ቀይ ቀበሮ (Ethiopian Wolf)፣ ጭላዳ ባቡን (Gelada Baboon) እና የዐለት አጋዘን (Klipspringer) በነጻነት የሚቦርቁበት ገነት ነው።
• የጓሳ ሎጅ (Guassa Lodge)፦ የአካባቢው ማህበረሰብ የሚመራውና የሚጠቀምበት ውብ ማረፊያ ሲሆን፣ ከዘመናዊ የቱሪዝም አገልግሎት ጋር ባህላዊ ውበትን አዋህዶ የያዘ ነው። ሎጁን የሚጎበኙ እንግዶች የመንዝን ቀዝቃዛ አየር፣ በጭጋግ የተሸፈኑ አናት አናቶችና የተንጣለለውን የጓሳ ሳር ሜዳ እየተመለከቱ የተለየ ሰላምና እረፍት ያገኛሉ።
• የእግር መንገድና ተፈጥሮ፦ በፈረስ ወይም በእግር ተጓዞ የመንዝን አስደናቂ ተፈጥሮና የታችኛውን የስምጥ ሸለቆ (Rift Valley) እይታ ከመስኮት እንደሚታይ ስዕል ለማየት ተወዳዳሪ የሌለው ስፍራ ነው።
መንዝ ታሪክን፣ ባህልንና ተፈጥሮን በአንድ ላይ አጣጥሞ ለመለማመድ የሚመረጥ የኢትዮጵያ ድንቅ ቅርስ ናት።
✍️✍️ ፊታውራሪ አዶናይ አበበ !!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ዕዞች የ2019 ዓ/ም የትምህርት ዘመን መደበኛ የመማር ማስተማር ሥራ በይፋ እንዲጀመር ጥሪ አቅርበዋል!!
ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም።
ትምህርት ለአንድ ሀገር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ እድገት ወሳኝ መሠረት መሆኑ በውል የሚታወቅ ሲሆን፤ ሀገራችን ከገጠማት ውስብስብ ችግር እና የጸጥታ ስጋት አንጻርም ጭምር የትምህርትን አስፈላጊነት ከግምት ውስጥ በማስገባት የ2019 ዓ/ም የትምህርት ዘመን በወቅቱ እና በአግባቡ እንዲጀመር የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ዕዞች ጥሪ አስተላልፈዋል።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ባስቀመጠው አጠቃላይ አቅጣጫ መሠረት፦
፩. አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው 5ኛ ዕዝ (በማኅበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አስታወሰኝ ላቀ በኩል) እንደገለጸው፤ ትምህርት ሰላም እና መረጋጋት ቢፈልግም፣ ከሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ አኳያ በስጋት ውስጥ ሆነንም ቢሆን የ2019 ዓ/ም የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራ በወቅቱ እንዲጀመር አቅጣጫ ተቀምጧል። በመሆኑም በየደረጃው ያሉ የፋኖ አመራሮች፣ ወላጆች፣ መምህራን፣ ርዕሰ መምህራን እና የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል።
፪. አፋብን ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ ለሁሉም ኮሮች ባስተላለፈው ጥሪ፣ ድርጅታችን ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት መደበኛ ትምህርት እንዲጀመር አሳስቧል። ለዚህም ስኬት አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት እንዲደረግ አሳስቦ፣ ሁሉም ኮሮች ትምህርት እንዲጀምሩ ጥሪ አቅርበዋል።
፫. አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ (በማኅበራዊ ጉዳይ መመሪያ ኃላፊ አርበኛ ብዙአየሁ ወንድምነው አማካኝነት) በሰጠው መግለጫ፣ ድርጅቱ ያስቀመጠውን አቅጣጫ መሠረት በማድረግ በዕዙ ሥር የሚገኙ ሁሉም ኮሮች አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አድርገው ትምህርት እንዲያስጀምሩ አሳስቧል። ሙሉው ሕዝብ፣ መምህራን፣ የተማሪ ወላጆች እና ባለድርሻ አካላት አስፈላጊውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ ተላልፏል።
፬. አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ጠቅላይ ግዛት ምኒልክ 1ኛ ዕዝ በሰጠው ማሳሰቢያ፣ የ2019 ዓ/ም የትምህርት መርሐ ግብር እውን እንዲሆን በቁጥጥራቸው ሥር በሚገኙ አካባቢዎች የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ወደ ሥራ እንዲገቡና የምዝገባ ሥራዎች እንዲጀመሩ አሳስቧል፤ ለዚህም አስፈላጊው ትብብር እንዲደረግ ጥሪ አቅርቧል።
በአጠቃላይ የአፋብን ዕዞች ባስተላለፏቸው መልእክቶች፤ ትውልድን ለማዳን፣ አስተሳሰብን ለመገንባት እና ትናንትን በአዲስ ተስፋ ለመተካት ትምህርት ቤቶች መደበኛ አገልግሎታቸውን እንዲጀምሩና መላው የህብረተሰብ ክፍል አስፈላጊውን እገዛና ትብብር እንዲያደርግ አጽንኦት ተሰጥቷል።
— የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ(አፋብን) ወታደራዊ ቃል አቀባይ
https://t.me/abeamoraw
https://t.me/abeamoraw
https://t.me/abeamoraw
" የአያቶቻችንን እርስትና ማንነት እንድናስመልስ" ራስ መከታው ማሞ ከበራራ ክፍለጦር ጋር በነበረው ቆይታ የተናገረው !!
ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ
ቀን፦ ነሐሴ 06 ቀን 2018 ዓ.ም
በንጹሐን ወጣቶች ላይ የሚፈጸመውን የግፍ ግድያ፣ ወታደራዊ የግዳጅ አፈሳ እና የአዲስ አበባን የፖለቲካ ሴራ አስመልክቶ ከአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የተሰጠ መግለጫ
የአማራ ህዝብ የተደቀነበትን የህልውና አደጋ ለመመከት እና ተፈጥሮአዊ ወይም ሰብአዊ መብቱን ለማስከበር የሚያደርገው ፍትሃዊ ትግል በከፍተኛ ህዝባዊ ደጋፊነት ወደፊት እየገሰገሰ ይገኛል። ነገር ግን የስርዓቱ አስፈጻሚዎች ትግሉን ማቆም ሲሳናቸው በንጹሐን ወላጆች እና ወጣቶች ላይ የሚያደርሱትን የግፍ እርምጃ እና የሽብር ተግባር አጠናክረው ቀጥለውበታል።
በመሆኑም አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ወቅታዊ እና አስቸኳይ የፖለቲካ እና ወታደራዊ ሁኔታዎችን አስመልክቶ የሚከተለውን የአቋም መግለጫ አውጥቷል፦
1. በንጹሐን ወጣቶች ላይ በአገዛዙ ብልፅግና የተፈጸመውን አሰቃቂ የእብሪት ግድያ ( መረሸንን) በተመለከተ:- በቀን 04/12/2018 ዓ.ም በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ከተሳፈሩበት የሕዝብ ማጓጓዣ መኪና ላይ “ፋኖ ናችሁ” በሚል መላ ምት እና ውንጀላ ተገደው እንዲወርዱ ከተደረጉ በኋላ በማንነታቸው ብቻ በአሰቃቂ ሁኔታ የተረሸኑትን የሶስት ንጹሐን አማራ ወጣቶች ግድያ እዛችን በጽኑ ያወግዛል።
1ኛ. ወጣት ተመስገን ጌታቸው
2ኛ. ወጣት ይታገሱ አሰግደው
3ኛ. ወጣት ግዛው ግርማ
ፋኖነት የአማራ ህዝብ የታሪካዊ እሴቱ፣ የጀግንነቱ እና የህልውናው መገለጫ እንጂ ንጹሐን ዜጎችን ያለ ህግ አሰራር የሚያስገድል "ወንጀል" ወይም ኮድ አይደለም። በህዝብ ማጓጓዣ ላይ የሚጓዙ ንጹሐን ዜጎችን በማንነታቸው ብቻ ተለይቶ መረሸን የስርዓቱን አረመኔነት እና የሞራል ውድቀት ወይም መፍረስን የሚያሳይ ግልጽ የጦር ወንጀል ነው።
2. የግዳጅ ወታደራዊ አፈሳ እና የከተሞች ወታደራዊ ከበባን አስመልክቶ :-
በአሁኑ ወቅት በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ሁሉም ከተሞች ማለትም በአዲስ አበባ፣ በናዝሬት ፣ በደብረዘይት ፣ ደብረብርሃንን ጨምሮ በሁሉም አውራጃዎች ስር ባሉ ወረዳዎች ይህ አረመኔ ስርዓት ሰፊ ወታደራዊ የግዳጅ አፈሳ ጀምሯል። ወጣቶችን ከመንገድ፣ ከስራ ቦታ እና ከሙያ መስካቸው እያፈሰ የአማራን ህዝብ እየጨፈጨፈ ያለ ፀረ -ህዝብ እና ፀረ- አንድነት የሆነው አገዛዝ በግዳጅ ከተሸናፊነት ለማያድነው ጉዞ ወጣቶችን ወደ ጦርነት ማግዳ በመክተት ላይ ይገኛል።
ይህ ህገ-ወጥ አፈሳ የስርዓቱን ውድቀት የሚያፋጥን እንጂ ህዝባዊ ትግሉን የሚያስቆም አይደለም። በመሆኑም በነዚህ ከተሞች የምትገኙ የአማራ ወጣቶች ለገዢው ቡድን የመሳሪያ ማኖሪያ ከመሆን ይልቅ፣ የህዝባችሁን ህልውና ለማስከበር በግንባር ቀደምትነት እየታገለ የሚገኘውን አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝን እንድትቀላቀሉ ጥሪ እናስተላልፋለን።
3. የአዲስ አበባ ህልውና እና የፖለቲካ ደባ :-
የአማራን ህዝብ "ወደ ዋና ከተማህ አዲስ አበባ አትገባም" ሲል የቆየው የገዢው ቡድን ፖለቲካዊ መዋቅር፣ ዛሬም በአዲስ ማጭበርበሪያ የከተማዋን ነዋሪዎች እና ተወላጆች ከመንግስታዊ እና ኢኮኖሚያዊ መዋቅር በማግለል ላይ ይገኛል።
ከተማዋን ሙሉ በሙሉ ለመዋጥ እና የስነ-ሕዝብ (demographic) ስብጥርን ለመቀየር የሚደረገው የተቀናጀ ሴራ፣ መብታቸውን የሚጠይቁና የሚሟገቱ ሰዎችን በማሰር፣ በማሳደድ እና በማስፈራራት አደገኛ ደባውን እያከናወነ ይገኛል። ይህ የሀገርን ጥቅም ለመሸጥ እና ለመቀራመት የሚደረግ እቅድ የመላው ኢትዮጵያውያን ስጋት ነው።
4. አጽንኦት የሚሰጠው የትግል አቅጣጫና ጥሪ
• ለአማራ ወጣቶች፦ የግፍ ሰለባ ከመሆን እና በግዳጅ አፈሳ ወደማታምኑበት እቅድ ከመነዳት ይልቅ ህልውናችሁን እና የህዝባችሁን ክብር ለማስከበር የፋኖን ትግል ተቀላቀሉ።
• ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች እና መላው ኢትዮጵያውያን፦ በከተማችሁ እና በሀገራችሁ ላይ እየተፈጸመ ያለውን ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖ በጋራ እንድትታገሉ፣ የፋኖን ህዝባዊ የህልውና ትግል በገንዘብ፣ በሀሳብ እና በፅናት እንድትደግፉ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
• ለስርዓቱ የፀጥታ መዋቅር/የደህንነት አባላት፦ ህዝብን ጨፍጫፊ እና ሀገር አፍራሽ ለሆነው አገዛዝ መሳሪያ ከመሆን ተቆጥባችሁ ወደ ህዝባችሁ ጎን እንድትቆሙ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ እንሰጣለን።
''ክብር ለትግሉ ሰማዕታት''
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ
ነሐሴ 06 ቀን 2018 ዓ.ም
+2
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ከተሞች፦ አዲስ አበባና ናዝሬትን ጨምሮ በአጣዬ፣ ሸዋሮቢት፣ ደብረብርሃን፣ መሀልሜዳ፣ ሞላሌ፣ ዓለም ከተማ፣ ደብረሲና፣ አረርቲና መተሀራ ከተሞች ተሸናፊው የብልፅግና ስርዓት ወጣቶችን እያፈሰ ነው። ደርግን ከውድቀት ያላዳነ ወታደራዊ አፈሳ መዋቅራዊ መበስበስ አጋጥሞት ከተሸነፈ የከረመውን ብልፅግናን ከወድቀት አያድነውም። ወጣቶች ራሳችሁን ከብልፅግና አፈሳ ሰውራችሁ የአማራ የህልውና ትግልን በህዝባዊ ድጋፍ ከፍ ወዳለ እድገት ያሸጋገረውን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ፋኖን እድትቀላቀሉ ስል መልዕክት አስተላልፋለሁ።
ኢንጂነር አዶናይ አበበ
ድል ለአማራ !!
በአፋብን ሸዋ ጠቅለይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ አምደ ጽዮን ኮር አካል የሆነው ከራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦር 1ኛ እና 3ኛ ሻለቆች ጋር ባተካሔደው መድረክ ላይ ወቅታዊ የፖለቲካ ጉዳዮችን በተመለከተ የተሳካ ውይይትና የፖለቲካ የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራም ተደርጓል !! ክፍለጦሩ...
"ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
https://t.me/mekesuabጀግናው የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር በብልፅግናው አየር ወለድ ሰራዊት ላይ ባካሄደው የተቀናጀ ኦፕሬሽን ድል መቀዳጀቱን አስታወቀ!
ነሐሴ 01/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዓምደ ጽዮን ኮር አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር፣ እራሱን "101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር" ብሎ በሚጠራው የአገዛዙ ሰራዊት ላይ ትላንት ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 1:00 ሰዓት ባደረገው የተቀናጀ ወታደራዊ ኦፕሬሽን አኩሪ ድል መጎናፀፉን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል አስታወቀ።
የአገዛዙ ኃይል መነሻውን ከመርሐቤቴ አውራጃ ሬማ ከተማ በማድረግ፣ የህዝብ አለኝታ የሆነውን የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ሰራዊት ለማጥቃት ወደ መጅት እና ቢራባ ቀበሌዎች እንቅስቃሴ አድርጎ ለማጥቃት ቢሞክርም የክፍለ ጦሩ የጦር ጠበብቶች በወታደራዊ ስልት የጠላትን ኃይል ወዳዘጋጁለት የውጊያ ቀጠና በስቦ መምታት ስልት፡ በወታደራዊ የበላይነት የሬማ ዙሪያ አካባቢዎችን በወቅቱ በቁጥጥር ስር በማስገባት ጠላት ወደ ኋላ እንዳይመለስ መንገድ በመዝጋት በተከናወነው በዚህ የተሳካ ኦፕሬሽን፣ የአገዛዙ ኃይል ከፍተኛ ወታደራዊና ቁሳዊ ኪሳራ አስተናግዷል።
በዜሮ መስዋዕትነት በተጠናቀቀው በዚህ ልዩ ኦፕሬሽን የተገኙ ዋና ዋና ውጤቶች፦
➠ የተደመሰሰ የጠላት ኃይል፡ 09
➠ የቆሰለ የጠላት ኃይል፡ ከ14 በላይ
እንዳቀደው ያልተሳካለት ጠላት ከፋኖ በደረሰበት ሽንፈት የተበሳጨው ወደ መጣበት ሲመለስ እንደለመደው ንፁሀንን የበቀል እርምጃ፡ የብስጭት ማብረጃ እያለ ንፁሀን ወገኖች ከፍተኛ ድብደባ የተፈፀመባቸው ሲሆን የመጅት ቀበሌ የ8 ዓመት ታዳጊ ህፃን ቶፋው ጋሻው የተባለች እንስት በጥይት ተመታ መቁሰሏን የአይን እማኞች ተናግረዋል።
ሽንፈቱን የተከናነበው ጠላት የቆሰሉት አባላቱን ለሕክምና በሬማ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና በሬማ ከተማ ጤና ጣቢያ የመጀመሪያ ደረጃ ህክምና እየተደረገላቸው ሲሆን፣ ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው አባላቱን ዛሬ ነሐሴ 01/2018 ዓ.ም ከንጋቱ 12:30 ላይ ወደ መርሐቤቴ ዓለም ከተማ እናት ሆስፒታል መዛወራቸውን የኮሩ መረጃዎች አረጋግጠዋል።
"ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
የንስር ሻለቃ የትግል ዝግጁነቱን ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋገረ ልዩ የተሀድሶና የፖለቲካ ንቃተ-ህሊና መድረክ ተካሔደ!!
ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ተወርዋሪው የንስር ሻለቃ፣ ህዝባዊ ትግሉን በተሻለ ስትራቴጂያዊ ዝግጁነትና ወታደራዊ ዲስፕሊን ለማጠናከር ያለመ ልዩ የተሀድሶና የፖለቲካ ንቃተ-ህሊና ማሳደጊያ መድረክ በታላቅ ድምቀት አካሂደዋል።
በዓላማ ፅናትና በወታደራዊ ስትራቴጂ ዝግጁነት የታነፀው ይህ መድረክ የአማራ ህዝብ እያካሄደ ባለው ፍትሃዊ የህልውና ተጋድሎ ውስጥ የኃይል ሚዛኑን ሙሉ በሙሉ ወደ ድል ለመቀየር ያለሙ ቁልፍ ውሳኔዎች የተበሰሩበት ሆኖ አልፏል።
በመድረኩ ላይ የአፋብን ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር አርበኛ መከታው ማሞ፣ የአፋብን መካናይዝድ ጦር መምሪያ ሃላፊ አርበኛ አብረሃም ኩራባቸውን ጨምሮ የዕዙ ከፍተኛ ወታደራዊና ፖለቲካዊ አመራሮች፣ የንስር ሻለቃ መሪዎች እንዲሁም በክብር እንግድነት የተገኙት የአፄ አምደፂዎን ኮር አመራሮች ተሳትፈዋል።
የመድረኩ ዋና ዋና ዓላማዎች
~ የአመራርና የሻለቃውን ወታደራዊ ብቃት ማሳደግ፡
~የተሀድሶ መድረኩ የወታደራዊ ስልቶች ማሻሻያዎች
~ የግዳጅ አፈፃፀም ግምገማዎችንና የወደፊት ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎችን በጥልቀት በመገምገም የትግል ዝግጁነቱን ወደ ላቀ ደረጃ ተማሻገር
~ርዕዮተ-ዓለማዊና ፖለቲካዊ አንድነትን ማጠናከር
~የትግሉን ፖለቲካዊ ግቦች ማስረፅ የሠራዊቱንና የአመራሩን የእርስ በእርስ ውህደትና የዓላማ አንድነት የበለጠ ለማጠናከር
~የጋራ ትብብርና አድነትን ማጠናከር
እንደ ስማቸው ሁሉ በከፍታ ላይ በመብረር የጠላትን እንቅስቃሴ ከሩቅ የሚቃኙትና የመመታት አቅማቸው ከፍተኛ የሆነው የንስር ሻለቃ አባላት በዚህ የፖለቲካና የውጊያ ተሀድሶ ይበልጥ ታድሰውና ተዘጋጅተው ለተጨማሪ ግዳጅ መቅረባቸው ተገልጿል።
ይህ የተሀድሶ መድረክ አመራርና አባላት የህዝባቸውን ነፃነት፣ ክብርና ህልውና ለማረጋገጥ የሚያደርጉትን ተጋድሎ እስከ አሸናፊነት ለመምራት ያላቸውን የማይናወጥ ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጡበት ሆኗል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ