251
Subscribers
-124 hours
-17 days
-130 days
Posts Archive
+9
ነሐሴ 23/2016 ዓ.ም
============
ለምለሚቷ ጉራጌ ዞን ብሎም እንደጋኝ ወረዳ በክረምቱ የስንዴ ክላስተር ደምቃለች።
በጉራጌ ዞን እንደጋኝ ወረዳ በግብርና ልማት በመኸር እርሻ በዊሎና ደ/ፅጌ ቀበሌ በአ/አደር ማሳ በኩታ ገጠም በስንዴ የለማ ማሳ አሁናዊ ገጽታ በፎቶ።
ታታሪዎቹ አ/አደሮቻችን በክረምቱ ተዓምር እየሰሩ ነው።
+8
ነሀሴ 14/2016
የጉራጌ ዞን በሁሉም ወረዳ እና ከተማ አስተዳደር ደረጃ ''ከተረጂነት ወደ ምርታነት'' ልዩ አጀንዳ ግለቱን ጠብቆ መላው የዞኑ ማህበረሰብ ተሳታፊ እየሆነበት ቀጥሏል።
ድህነትና ተረጂነትን ለመላቀቅ ሁሉንም አቅም ማለትም የሰው ሀይል፣ የመሬት ሀብት ፣ የውሀ ሀብት እና ሌሎችንም እምቅ እድሎችን በተገቢው ከተጠቀምን ብልፅግናን በአጭር ጊዜ የማናሳካበት ምክንያት አይኖርም።
እንደ ዞን ፀጋዎቻችንን ወደ ሀብት የመቀየር ትልማችን በእጅጉ ተስፋ ሰጪ ደረጃ ላይም ይገኛል።
በበልግና በመኸር ግብርና ተግባር አፈፃፀማችን፣በሌማት ትሩፋት፣ በወጣቶች እና ሴቶች የስራ እድል ፈጠራ እና በሌሎችም ድህነትን መሻገርያ ኢኒሼቲቮች እየመጣ ያለው ለውጥ ግባችንን ማሳኪያ ጊዜው አጭር መሆኑን ያመላክታል።
ምስል:- ከወረዳ እና ከተማ አስተዳደሮች ፓርቲ ጽ/ቤት
''ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሀገራዊ ሉዐላዊነት''
ነሐሴ 14/2016ዓ.ም
ብልፅግና ፓርቲ ሰው ተኮር መገለጫ በሆነው የበጎነት ተግባር "የነበረብኝን የመኖሪያ ቤት ችግር በመቀረፉ እጅግ ደስ ብሎኛል":-ወ/ሮ ዝፕወድ ቸገነ
ወ/ሮ ዝፕወድ ቸገነ ይባላሉ በእኖር ወረዳ የሻንቃ ቀበሌ ጎርዓ መንደር ነዋሪ ናቸው።
እኚህ እናት በነበረባቸው የመኖሪያ ቤት ችግር ለዓመታት ከጎረቤት ጋር ተጠግተው ይኖሩ እንደነበር ያወሳሉ።ቤት ለመስራት አቅም እንዳልነበራቸውም እንዲሁ።
ይሁንና የአካባቢው በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ከወረዳው መንግስት ጋር በመተባበር ባደረጉላቸው ድጋፍ የቤት ባለቤት መሆናቸውን ይናገራሉ።
"የነበረብኝን የመኖሪያ ቤት ችግር በመቀረፉም እጅግ ደስ ብሎኛል" ይላሉ ወ/ሮ ዝፕወድ።
ይህንን ድጋፍ ላደረጉላቸው የአካባቢው ወጣቶችና የወረዳው መንግስት ወ/ሮ ዝፕወድ ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል፤ መርቀዋልም።
በዚህ መልካም ተግባር ላይ የእኖር ወረዳ የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ አበበ አገዘ፣የወጣቶችና ስፓርት ጽ/ቤት እና የሰራተኛና ማህበራዊ ጉ/ጽ/ቤት ኃላፊዎች እና በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ተገኝቷል ሲል የወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት ዘግቧል።
+6
ሀምሌ 23/2016
ባህላዊ እሴቶቻችን የሀገር ሀብት እና የአንድነታችን መሰረት እንደመሆናቸው ከሀገር አልፎ ለዓለም ማስተዋወቅ ያስፈልጋል።
እነዚህን የሀገር ሀብቶች ተፈጥሯዊ ባህሪያቸው ሳይበረዝ ለትውልድ ማስተላለፍ ቀጣይዋን በሁሉም መስክ የበለፀገች ሀገር ለመገንባት አበርክቶው ከፍ ያለ ነው።
እንደ ሀገር ለባህልና ቱሪዝም ዘርፉ በተሰጠው ትኩረት መሰረት በጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ ዘርፉን ለማጠናከር በርካታ ተግባራቶች እየተከናወኑ ይገኛሉ ።
በወረዳው የጉራጌ ባህላዊ ቤት በወረዳው መንግስት ወጪ ተገንብቶ ተጠናቋል።
ከዚህ በተጨማሪ የእዣ ወረዳ ባህል ቱሪዝም ፅ/ቤት የማህበረሰቡ እሴት ከሆኑት መካከል የባህል አላባሳት እንዲለበስ ሰፊ ጥረት እያደረገ ይገኛል ።
+9
ሐምሌ 17/2016
በጉራጌ ዞን የ2016ዓ.ም የፓርቲና የመንግስት እቅድ አፈፃፀም በወልቂጤ ከተማ እየተገመገ ይገኛል።
የጉራጌ ዞን ማዕከል አመራሮች በ2016ዓ.ም በፓርቲና በመንግስት የተፈፀሙ ዋና ዋና የፓርቲ እና የንቅናቄ ስራዎች አፈፃፀምን በጥልቀት እየገመገሙ ይገኛል ።
በውይይቱም በዓመቱ በአመራሩ አስተባባሪነት የተፈፀሙ የንቅናቄ ስራዎችን ያሉበት ደረጃ የሚገመገም ሲሆን በሂደቱም በጥንካሬ የተፈፀሙ ጉዳዮችን በማስቀጠል ጉድለቶችን ለማረም ያለመ መድረክ እንደሆነ ተነስቷል።
ያሉ ፀጋዎችን አውቆ ወደሀብት የመቀየር እና ዞኑን የብልፅግና ተምሳሌት የማድረግ ጥቅል ዓላማ ያነገበ መድረክ መሆኑም ተጠቅሷል።
መድረኩም ለተከታታይ ሁለት ቀናት የሚቆይ ሲሆን ለውይይቱ የተዘጋጀው ሰነድ በመቅረብ ላይ ይገኛል።
በእለቱም የጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ክብሩ ፈቀደ ፣ የጉራጌ ዞን ም/አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ፣ የጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አለማየው ገ/መስቀል ፣የጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ አመተረውፍ ሁሴን ጨምሮ የዞን ማዕከል ጠቅላላ አመራሮች ተገኝተዋል።
ዝርዝር መረጃ ይኖረናል።
ሐምሌ 14/2016 ዓ.ም
4ኛዉ ዙር የኬሮድ ታላቁ ሩጫ የማህበረሰባችን አብሮነትን ሰላም ፍቅርን የወንድማማችነትና የእህትማማችነት ያጠናከርንበት መሆኑ የጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ።
4ተኛው ዙር የኮሮድ ታላቁ የጎዳና ላይ ሩጫ በወልቂጤ ከተማ በደማቅ ተካሄዷዋል።
የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አበራ ወንድሙ በኬሮድ ታላቁ ሩጫ ዉድድሩ ተገኝተዉ እንዳሉት የኬሮድ የልማትና የስፖርት ማህበር ለኢትዮጵያ ሰላም እንሩጥ በሚል መሪ ቃል ለ4ኛ ጊዜ በወልቂጤ ከተማ ያካሄደው የ15 ኪሎ ሜትር ሩጫ የማህበረሰባችን አብሮነትን ሰላም ፍቅርን የተሰበከበት የወንድማማችነትና እህትማማችነት እንዲሁም አንድነትን የተጠናከረበት እንደሆነ አብራርተዋል።
የዞኑ ማህበረሰብ በስፓርት ልማት ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንዲሁም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎቹ ከፍተኛ በመሆኑን ለስፖርት ልማቱ ልዩ ትኩርት በመስጠት እየተሰራበት ይገኛል ብለዋል።
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊና ተወዳዳሪ የሆነ የወልቂጤ ከተማ እግር ኳስ ክለብ፣ የወልቂጤ ቅርጫት ኳስ ክለብና የዘቢዳር አትሌቲክስ ክለቦች በማህበረሰቡ ዘንድ ተወዳጅ ቢሆኑም አደረጃጀቶቹንና አሰራሮቹን በማዘመን ህዝባዊ መሰረት በማስያዝ የበለጠ በመጠናከር እንደሚሰራ ተናግረዋል።
በሀገራችን ብቁ አትሌቶችን በማፍራትና ተፎካካሪ በመሆን በአለም አደባባይ ደምቀንና ጎልተን እንድንወጣ የኬሮድ ታላቁ ሩጫ የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ የሚገኝ እንደሆነም አመላክተዉ የኦሎምፒክ ሻምፒዮና ኮማንደር ሰለሞን ባረጋ ፣ሙክታር እድሪስና ሌሎችም በርካታ አትሌቶች ሞዴልና የሀገር ባለዉለታዎቻች ናቸዉ ብለዋል።
ዉድድሩን ለመታደም ወደ ዞኑ የመጡ የማህበረሰብ ክፍሎች ዞኑ ለማልማት ለኢንቨስትመንት፣ ለመዝናናት፣ ለመጎብኘት ፣ ጥናትና ምርምር ለማድረግ ምቹ ከመሆኑም አልፎ የተለያዩ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቱባ ባህሎቻችንና ዕሴቶቻችን ማለትም ጥንታዊ ገዳማትና አብያተ ክርስቲያናት፣ ታሪካዊ መስጅዶች፣ ሰንሰለታማ ተራሮች፣ ህይቆች፣ ፓርኮችና ዋሻዎች ሌሎችም ዕሴቶች በብዛት ይገኛሉ ብለዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሀላፊ አቶ ዘሪሁን እሸቴ እንዳሉት ስፖርት የሰው ልጆችን አዕምሮ ለማሳደግና በህዝቦች ዘንድ ትስስር የሚፈጥር መሆኑን ገልፀው የኬሮድ የጎዳና ላይ ሩጫ ከውድድር ባለፈ የሰላምና የመቻቻል መድረክ ነው ብለዋል።
በክልሉ በተለያዩ አከባቢዎች ስፖርትን በማስፋፋት ህብረተሰቡ በስፖርት ጤናውን እንዲጠብቅና አምራች ዜጋ እንዲፈጠር በትኩረት እየተሰራ እንደሆነም አብራርተዋል።
የወልቂጤ ከተማ ከንቲባ አቶ እንዳለ ስጦታዉ እንዳሉት በወልቂጤ ከተማ ለ4ተኛ ጊዜ የተዘጋጀው የ15ኪሎ ሜትር የኬሮድ የጎዳና ላይ ሩጫ ዉድድር ሁሉንም ማኅበረሰብ ያሳተፈና ለሀገርችን ተተኪ አትሌቶች ለማፍራት የሚያግዝ እንደሆነም ተናግረዋል።
በርካታ ቁጥር ያላቸዉ ታዋቂና ወጣት አትሌቶች ያሳተፈዉን የኬሮድ ታላቁ ሩጫ የከተማዉን ገጽታ በመቀየር ረገድ ትልቅ አስተዋፆ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል።
በከተማዉ የሚገኙ ወጣቶችና አጠቃላይ ማህበረሰብ እንግዶችን በተገቢዉ ተቀብሎ በማስተናገድ ረገድ ላደረጉት ከፍተኛ አስተዋፆ በከተማ አስተዳድር ስም ምስጋና አቀርባስሁ።
ታላቁ የኬሮድ ሩጫ ዉድድር በከተማዉ መካሄዱ የማህበረሰቡ ባህል እንዲሁም የቱሪዝም ሀብቶች እንዲጎበኙ ያደረገና ሌሎችም እሴቶቻችን የበለጠ ጎልተዉ እንዲተዋወቁ የአንበሳውን ድርሻ እንደሚወጡም ይታወቃል፡፡
አትሌትና አሰልጣኝ ተሰማ አብሽሮ በበኩሉ ኬሮድ አድማሱን እያሰፋ በሌሎችም ዞኖችና ክልሎች የሩጫዉን ዉድድር የሚያስቀጥልም እንደሆነም አስታዉቀዋል።
በዛሬው እለት በድምቀትና በሰላማዊ ሁኔታ የተካሄደው የጎዳና ሩጫ አስተዋጽኦ ላደረጉ ተቋማትና ድርጅቶች እንዲሁም ግለሰዎች መስጋናቸውን አቅርበዋል።
በመጨረሻም የውድድሩ አሸናፊዎችና ሽልማት በ15 ኪሎ ሜትር
በሴቶች
1ኛ መብራት ግደይ (የወርቅ ሜዳሊያና 100 000 ብር )
2 ኛ መቅደስ ሽመልስ ( የብር ሚዳሊያና 50000)
3ኛ ጉተን ሽንቆ (የነሓስ 25000)
@ በወንዶች የ15 ኪሎ ሜትር ሩጫ
1ኛ ጨምቤሳ ደበላ ( የወርቅ ሜዳሊያና 100000ብር)
2ኛ ዘነበ አየለ ( የብር ሜዳሊያና50000) ብር
3ኛ ጃክሳ ታደሰ (የነሀስ ሜዳሊያና 25000) ብር
በማህበረሰብና በፓራሊምክስ ዉድድሮች ከ1ኛ እስክ 3ኛ ለወጡ ወንዶችና ሴት ተወዳዳሪዎች ከ2 ሺህ እስከ 5 ሺህ ብር የገንዘብና የሜዳሊያ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል ሲል የዘገበዉ የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ነዉ።
+6
ሀምሌ 02/2016
በፓርቲያችን ብልፅግና መሪነት ከተረጂነት ወደ ምርታማነት፣ ከልመና ያሉንን ፀጋዎችንና እምቅ አቅሞችን በመጠቀም የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ጉዞ ተስፋ ሰጪ ነው።
በጉራጌ ዞን እኖር ወረዳ በወጣቶች የለማ የበቆሎ ማሳ።
#ከተረጂነት ወደ ምርታማነት
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት
የፌስቡክ ገፃችን https://www.facebook.com/gurageprosperityparty
የቴሌግራም ገፃችን https://t.me/gurageprospcomm
ኢሜይል gurageprosperity@gmail.com
ቲክቶክ ገፃችን https://www.tiktok.com/@guragezoneprosperity?_t=8nlQI86taon&_r=1
ዩቲዩብ ገፃችንhttps://www.youtube.com/@Guragezoneprosperityparty
whatsup ገፃችን https://whatsapp.com/channel/0029VagiC1MLCoX7dKrchh0Y
#የጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት
+9
ሰኔ 28/2016
የብልፅግና ትሩፋቶች በጉራጌ ዞን‼
''ጀምሮ መጨረስ የብልፅግና ፓርቲ መለያ ባህሪ ነው''
ከ24 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የተገነባው የጌታ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት እና ከ20 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የእዣ ወረዳ የፋይንስ ፅ/ቤት ህንፃ ግንባታዎች ተጠናቀው ርክብክብ ተደረጓል።
ፕሮጀክቶቹ በመጠናቀቃቸው በወረዳዎቹ የቢሮ እጥረቶችን በመቅረፍ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን የሚሻሽሉ ናቸው።
''በህብር ወደ ብልፅግና''
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት
የፌስቡክ ገፃችን https://www.facebook.com/gurageprosperityparty
የቴሌግራም ገፃችን https://t.me/gurageprospcomm
ኢሜይል gurageprosperity@gmail.com
ቲክቶክ ገፃችን https://www.tiktok.com/@guragezoneprosperity?_t=8nlQI86taon&_r=1
ዩቲዩብ ገፃችን https://www.youtube.com/@Guragezoneprosperityparty
whatsup ገፃችን https://whatsapp.com/channel/0029VagiC1MLCoX7dKrchh0Y
#የጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት
+8
ሰኔ 28/2016
በእንደጋኝ ወረዳ የተቀናጀ ግብርና ለቤተሰብ ብልፅግና በሚል የ5-10-25 የዶሮ መንደር ምስረታና ልማት ጅማሮ ስራዎች
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት
የፌስቡክ ገፃችን https://www.facebook.com/gurageprosperityparty
የቴሌግራም ገፃችን https://t.me/gurageprospcomm
ኢሜይል gurageprosperity@gmail.com
ቲክቶክ ገፃችን https://www.tiktok.com/@guragezoneprosperity?_t=8nlQI86taon&_r=1
ዩቲዩብ ገፃችንhttps://www.youtube.com/@Guragezoneprosperityparty
whatsup ገፃችን https://whatsapp.com/channel/0029VagiC1MLCoX7dKrchh0Y
#የጉራጌዞንብልፅግናፓርቲጽ/ቤት
