en
Feedback
Tikvah Economy and Jobs

Tikvah Economy and Jobs

Open in Telegram

የቲክቫህ ኢትዮጵያ ይፋዊ የኢኮኖሚና የስራ መረጃ ቻናል። The official channel for economy, finance, and verified job opportunities. ማስታወቂያ ለማስወጣት ፦ @tikvaheconomy_BOT

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Tikvah Economy and Jobs

Channel Tikvah Economy and Jobs (@tikvaheconomy) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 23 004 subscribers, ranking 5 349 in the Economy & Finance category and 1 499 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 23 004 subscribers.

According to the latest data from 05 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 3 237 over the last 30 days and by 136 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 118.47%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 48.97% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 27 252 views. Within the first day, a publication typically gains 11 266 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 94.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቲክቫህ ኢትዮጵያ ይፋዊ የኢኮኖሚና የስራ መረጃ ቻናል። The official channel for economy, finance, and verified job opportunities. ማስታወቂያ ለማስወጣት ፦ @tikvaheconomy_BOT

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 06 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Economy & Finance category.

23 004
Subscribers
+13624 hours
+3 3367 days
+3 23730 days
Posts Archive
ማመልከቻ ሊንኩ ተስተካክሏል ! የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር 100 አመልካቾችን በአታሼ (Attaché) የሥራ መደብ ለመቅጠር የሥራ ማስታወቂያ አውጥቷል። - የሥራ መደብ፦ አታሼ (Attaché) - የሚቀጠሩ
+1
ማመልከቻ ሊንኩ ተስተካክሏል ! የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር 100 አመልካቾችን በአታሼ (Attaché) የሥራ መደብ ለመቅጠር የሥራ ማስታወቂያ አውጥቷል። - የሥራ መደብ፦ አታሼ (Attaché) - የሚቀጠሩ ሰዎች ብዛት፦ 100 - ደመወዝ፦ ብር 12,566 - የማመልከቻ ጊዜ፦ 7 ተከታታይ የሥራ ቀናት ➡️ ተፈላጊ ችሎታ ፦ በማንኛውም ትምህርት መስክ የመጀመሪያ ዲግሪና 0 ዓመት የስራ ልምድ ምዝገባው በወጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አዲሱ ህንጻ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 401 በአካል በመቅረብ ወይም ከዚህ በታች በተቀመጠው የመመዝገቢያ ሊንክ በመጠቀም መመዝገብ ይቻላል https://forms.gle/R7PmwCNeqEE3EQBN6 @tikvahecocnomy

🏠 100 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያለው የቤት መግዣ ፋይናንስ ተቋም ሊቋቋም መሆኑን ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አሳወቁ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC)
🏠 100 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያለው የቤት መግዣ ፋይናንስ ተቋም ሊቋቋም መሆኑን ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አሳወቁ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) የቤት መግዣ ብድር ፋይናንስን ለማስፋፋት የትብብር ማዕቀፍ ተፈራርመዋል። በ100 ቢሊዮንብር ካፒታል የሚቋቋመው ተቋም IFC እስከ 200 ሚሊዮን ዶላር አስተዋጽኦ ያደርግበታል። ተቋሙ የቤት መግዣ ብድርን በመላ አገሪቱ ለማስፋፋትና የ1.5 ሚሊዮን ተመጣጣኝ ዋጋ ያላቸው ቤቶችን ለመገንባት የተቀመጠውን ግብን ለማሳካት ያግዛል ሲሉ ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል። @tikvahethiopia

የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር 100 አመልካቾችን በአታሼ (Attaché) የሥራ መደብ ለመቅጠር የሥራ ማስታወቂያ አውጥቷል። - የሥራ መደብ፦ አታሼ (Attaché) - የሚቀጠሩ ሰዎች ብዛት፦ 100
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር 100 አመልካቾችን በአታሼ (Attaché) የሥራ መደብ ለመቅጠር የሥራ ማስታወቂያ አውጥቷል። - የሥራ መደብ፦ አታሼ (Attaché) - የሚቀጠሩ ሰዎች ብዛት፦ 100 - ደመወዝ፦ ብር 12,566 - የማመልከቻ ጊዜ፦ 7 ተከታታይ የሥራ ቀናት 👉 ተፈላጊ ችሎታ ፦ በማንኛውም ትምህርት መስክ የመጀመሪያ ዲግሪና 0 ዓመት የስራ ልምድ ምዝገባው በወጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አዲሱ ህንጻ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 401 በአካል በመቅረብ ወይም ከዚህ በታች በተቀመጠው የመመዝገቢያ ሊንክ በመጠቀም መመዝገብ ይቻላል https://forms.gle/R7PmwCNeqEE3EQBN6 @tikvahethiopia

የስራ ቅጥር ማስታወቂያ ድርጅታችን ሄነንስ ጋርመንት ኃ/የተ/የግ/ማ (Henens Garment PLC / Jimlazone General Trading) ከዚህ በታች በተጠቀሱት ክፍት የሥራ መደቦች ላይ መስ
የስራ ቅጥር ማስታወቂያ ድርጅታችን ሄነንስ ጋርመንት ኃ/የተ/የግ/ማ (Henens Garment PLC / Jimlazone General Trading) ከዚህ በታች በተጠቀሱት ክፍት የሥራ መደቦች ላይ መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል። 1. የሥራ መደብ፡ ማናጀር 2. የሥራ መደብ፡ ሳምፕል ሰሪ (Sample Maker ) 3. የሥራ መደብ፡ የማርኬቲንግ እና የሽያጭ ባሇሙያ (Marketing and Sales Officer) 4. የሥራ መደብ፡ የልብስ ስፌት ማሽን ኦፕሬተር (Sewing Machine Operator) አድራሻ፡- 📍ቢሾፍቱ - ቃጅማ ድልድይ ከአይቪ ሆቴል አጠገብ, ጅምላዞን ህንፃ ስልክ ቁጥር 📞 0945121314 📞 0913547017 🌐 www.jimlazone.com

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት እንዳስታወቀው፣ የሐምሌ ወር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት 15.3% ደርሷል፤ በሰኔ ወር ከነበረው 13.9% በ1.4 በመቶ ጨምሯል። የምግብ እና አልኮል ያልሆኑ መጠጦች ግ
የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት እንዳስታወቀው፣ የሐምሌ ወር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት 15.3% ደርሷል፤ በሰኔ ወር ከነበረው 13.9% በ1.4 በመቶ ጨምሯል። የምግብ እና አልኮል ያልሆኑ መጠጦች ግሽበት 15.7% ደርሷል። ስኳር 39.4%፣ ስንዴ 21.6%፣ ዘይት 20.34%፣ ፍራፍሬ 19.2% እና የወተት ተዋጽኦና እንቁላል 18.9% ጭማሪ አሳይተዋል። በሌላ በኩል፣ የምግብ ነክ ያልሆኑ ሸቀጦች ግሽበት 14.8% ሆኗል። @tikvaheconomy

Heleph Coffee ሔሌፍ ቡና ከሌሎች የቡና አፍቃሪዎች ጋር ዘና እያሉ ቅዳሜ ከሰዓቶን የሚያሳልፉበት ልዩ ዝግጅት። በባለሞያ የተዘጋጀ ስፔሻሊቲ የሔሌፍ ቡና በተለያዩ አማራጮች ይቀርባል ይቀመሳል
Heleph Coffee ሔሌፍ ቡና ከሌሎች የቡና አፍቃሪዎች ጋር ዘና እያሉ ቅዳሜ ከሰዓቶን የሚያሳልፉበት ልዩ ዝግጅት። በባለሞያ የተዘጋጀ ስፔሻሊቲ የሔሌፍ ቡና በተለያዩ አማራጮች ይቀርባል ይቀመሳል ፣ አዝናኝ የጥያቄና መልስ (Trivia) ውድድሮች፣ አዳዲስ ሰዎችን የሚተዋወቁበት፣ አስደሳች ጨዋታዎች ከበርካታ ሽልማቶሽ ጋር ይኖራሉ። 📅 ቀን እና ሰዓት ቀን፡ ቅዳሜ፣ ነሐሴ 16 ቀን ሰዓት፡ ከቀኑ 8:00 እስከ ምሽቱ 12:00 ሰዓት ቦታ ፦ አዲስ አበባ፣ ቦሌ 📩 እንዴት ማመልከት ይቻላል? @helephcoffee_bot ስም እና ስልክ ቁጥር ምዝገባውን ከአንድ ተጨማሪ ጓደኛ ጋር ማድረግ ይቻላል። ያለው ቦታ ውስን ስለሆነ ቀድመው ለሚመዘገቡት ቅድሚ ያስጣል። መግቢያ በነጻ ! Tikvah X Heleph @tikvaheconomy

ክፍት የሥራ ቦታ የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ፦ - ለኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጽሕፍት አገልግሎት፣ - ለኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም፣ - ለኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ባሉ ክፍት
+6
ክፍት የሥራ ቦታ የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን  ፦ - ለኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጽሕፍት አገልግሎት፣ - ለኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም፣ - ለኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ባሉ ክፍት የስራ መደቦች አመልካቾችን አወዳድሮ ፣በቋሚነት መቅጠር ይፈልጋል፡፡ ማመልከቻ ፦ 1. ለኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጽሕፍት አገልግሎት ሊንከ👇 https://forms.gle/dxgeogAqveHXyyTV7 2. ለኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም 👇 https://forms.gle/Wip8f9qaPduHLvsX9 3. ለኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት 👇 https://forms.gle/rp6LqKDz6HrAikh48 ከወጡት የስራ ዘርፎች መካከል ከ0 ዓመት እስከ 10 ዓመት የስራ ልምድ የተጠየቀባቸው ናቸው። @tikvaheconomy

ወደ ፍርድ ቤት ያመራው ዋጋ ጭማሪ በአዲስ አበባ የሚገኘው British International School (BIS) ወላጆች፣ ትምህርት ቤቱ ለ2026/27 የትምህርት ዘመን ድንገተኛ የክፍያ ጭማሪ ማድረ
+1
ወደ ፍርድ ቤት ያመራው ዋጋ ጭማሪ በአዲስ አበባ የሚገኘው British International School (BIS) ወላጆች፣ ትምህርት ቤቱ ለ2026/27 የትምህርት ዘመን ድንገተኛ የክፍያ ጭማሪ ማድረጉን ተከትሎ ጭማሪውን በመቃወም ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ወስደውታል። ካፒታል ጋዜጣ እንደዘገበው፣ ወላጆቹ ጭማሪው እስከ 36 በመቶ የደረሰ መሆኑንና በቂ ቅድመ ማሳወቂያና ከወላጆች ጋር ተገቢው ምክክር ሳይደረግ እንደተጣለ ገልጸዋል። ጉዳዩ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት እየታየ ነው። አንድ ወላጅ እንደገለጹት፣ የአንድ ልጅ ዓመታዊ ክፍያ ከ2025/26 የትምህርት ዘመን 26 ሺህ ብር ከነበረበት በ2026/27 ከ60 ሺህ ብር በላይ ደርሷል። ሌላ ሦስት ልጆች ያሏቸው ወላጅ እንደገለጹት፣ ጭማሪው እንደ ክፍል ደረጃው ከ25 እስከ 36 በመቶ ይደርሳል፤ ይህም በየሩብ ዓመቱ በአንድ ልጅ ከ11 ሺህ እስከ 12 ሺህ ብር ተጨማሪ ክፍያ እንዲጠየቅ አድርጓል። በፍርድ ቤት ትዕዛዝ መሠረት 15 አባላት ያሉት የወላጆች ኮሚቴ ከትምህርት ቤቱ ጋር ድርድር ቢያደርግም ስምምነት ሳይደረስ ቀርቷል። ወላጆቹ ጭማሪው በሁለት ዓመታት ተከፍሎ እንዲተገበር ሁለት አማራጮች አቅርበዋል፤ አንደኛው ጭማሪውን በድምሩ 20 በመቶ በማድረግ 10 በመቶ በ2026/27 እና 10 በመቶ በ2027/28 እንዲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ የጥሬ ክፍያ ጭማሪው 15 በመቶ ሆኖ በሁለት ዓመታት እንዲተገበር ነበር። ት/ቤቱ ግን ሁለቱንም ሀሳቦች እንደተቃወመ ወላጆቹ ገልጸዋል። የት/ቤቱ አስተዳደር በበኩሉ የክፍያ ለውጡ የሥራ ማስኬጃ ወጪዎች መጨመራቸውንና የትምህርት ጥራቱን ለመጠበቅ አስፈላጊ መሆኑን ለወላጆች እንደገለጸ ተመላክቷል። የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣኑ ጉዳዩን በጽሁፍ መመለሱን እና ት/ቤቱና ወላጆቹ በመግባባት መፍትሔ እንዲያገኙ መምከሩን ለካፒታል ጋዜጣ ገልጿል። ወላጆቹ እንደሚሉት፣ የክፍያ ጭማሪው በትምህርት፣ በመጓጓዣ፣ በምግብና በሌሎች የትምህርት ወጪዎች ላይ እንዲሁም ከኑሮ ውድነት ጋር በተያያዘ የወላጆች/ቤተሰብ ወጪ ጫናን በእጅጉ የሚያከብድ ነው። ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የካፒታል ጋዜጣ ነው። ነሐሴ 3 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvaheconomy

አማራ ባንክ በተለያዩ የሥራ መደቦች ላይ ብቁ የሆኑ ተወዳዳሪዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል። 1. Branch Manager Grade-I 2. Senior Credit Risk Analyst 3. Junior
አማራ ባንክ በተለያዩ የሥራ መደቦች ላይ ብቁ የሆኑ ተወዳዳሪዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል። 1. Branch Manager Grade-I 2. Senior Credit Risk Analyst 3. Junior Property Administration Officer በባንኩ ኦፊሴላዊ ድረገጽ https://vacancy.amharabank.com.et/?csrt=6914453002451074544 ላይ ማመልከት ይቻላል። ⏰ የማመልከቻ ጊዜው እስከ ነሐሴ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. ነው። አማራ ባንክ በማንኛውም የቅጥር ሂደት ክፍያ እንደማይጠይቅ ገልጿል። ስለሆነም ከሐሰተኛ የሥራ ማስታወቂያዎች ይጠንቀቁ። @tikvaheconomy

ክፍት የስራ ቦታ የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ከላይ በምስሉ በተዘረዘሩት ክፍት የስራ መደቦች አመልካቾችን አወዳድሮ ፣በቋሚነት መቅጠር ይፈልጋል፡። አዲስ አበባ ቦሌ መንገድ ፊላሚንጎ አካባቢ በሚገ
+3
ክፍት የስራ ቦታ የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ከላይ በምስሉ በተዘረዘሩት ክፍት የስራ መደቦች አመልካቾችን አወዳድሮ ፣በቋሚነት መቅጠር ይፈልጋል፡። አዲስ አበባ ቦሌ መንገድ ፊላሚንጎ አካባቢ በሚገኘው የኮሚሽኑ ህንጻ 4ኛ ወለል ብቃትና ሰው ሀብት አስተዳደር ሥራ አስፈፃሚ በአካል በመቅረብ መመዝገብ ይቻላል ተብሏል። የስራ ዕድል ማስታወቂያዎችን ለማስወጣት/ ሌሎች መልዕክቶችን ለማስተላለፍ 👉 @tikvaheconomy_BOT ይጠቀሙ። @tikvahecocnomy

#የሥራ_ቅጥር_ዕድል_ጥቆማ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሞዴል ኮሚኒቲ ትምህርት ቤት (AAU-MCS) ለተለያዩ የሥራ መደቦች ፍላጎት ያላቸውና ብቁ የሆኑ ባለሙያዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ ትምህርት ቤቱ ከ2019 የትምህርት ዘመን ጀምሮ ለአንደኛ ደረጃ (ከ1ኛ እስከ 7ኛ ክፍል) ተማሪዎች ከፍተኛ ጥራት ያለው ትምህርት ለመስጠት አቅዷል፡፡ ዝርዝር የሥራ መደቦችና የማመልከቻ ሁኔታ ለማግኘት 👇 https://www.aau.edu.et/announcements/detail?title=Vacancy~Announcement~AAU-MCS ➤ የሥራ መደብ፦ በተለያዩ ሙያዎች ➤ ተፈላጊ ባለሙያዎች ብዛት፦ 70 ➤ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፦ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ዲግሪ (ለተወሰኑ የሥራ መደቦች ዲፕሎማ፣10ኛ እና 12ኛ ክፍል ተጠይቋል፡፡) ➤ የሥራ ቦታ፦ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 5 ኪሎ ➤ የቅጥር ሁኔታ፦ በሙሉ ጊዜ የተገለፁ መስፈርቶችን የምታሟሉ በሙሉ የማመልከቻ ደብዳቤ፣ CV፣ ሙሉ የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውና የማይመለስ ኮፒ እንዲሁም አስፈላጊ ሰርተፊኬቶችን በመያዝ እስከ ሐምሌ 29/2018 ዓ.ም ድረስ በሥራ ቀናት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ የሰው ሃብት ቢሮ በመገኘት ማመልከት ትችላላችሁ ተብሏል፡፡   (ዝርዝር የሥራ መደቦቹ እና መስፈርቶችን ከተያያዘው ፒዲኤፍ ይመልከቱ፡፡) @tikvaheconomy

" በኢትዮጵያ የገበያ መር የውጭ ምንዛሪ ሥርዓት ድህነትን አባብሷል " - የዓለም ባንክ የፖሊሲ ሰነድ የዓለም ባንክ በተያዘው ወር ባወጣው የፖሊሲ ሰነድ፣ በኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሪ ግብይት ሥርዓቱን
+1
" በኢትዮጵያ የገበያ መር የውጭ ምንዛሪ ሥርዓት ድህነትን አባብሷል " - የዓለም ባንክ የፖሊሲ ሰነድ የዓለም ባንክ በተያዘው ወር ባወጣው የፖሊሲ ሰነድ፣ በኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሪ ግብይት ሥርዓቱን ሙሉ በሙሉ በገበያ እንዲመራ መደረጉ ድህነትን ከመቀነስ ይልቅ ማባባሱን ገልጿል። ሰነዱን ያዘጋጁት ከ2019 እስከ 2023 የዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት የነበሩት ዴቪድ ማልፔዝ ሲሆኑ፣ ኢትዮጵያ፣ ግብፅና ናይጄሪያ የተገበሩት ሙሉ በሙሉ ገበያ መር የምንዛሪ ሥርዓት የዝቅተኛ ገቢ ዜጎችን ይበልጥ እንደጎዳና ሀብት ዝቅተኛ ገቢ ካላቸው ዜጎች ወደ ልዩ ተጠቃሚ ቡድኖች እንዲሸጋገር እንዳደረገ ያብራራል። በሰነዱ መሠረት፣ የውጭ ምንዛሪውን በአንድ ጊዜ ለገበያ ከመልቀቅ ይልቅ ብሔራዊ ባንክ ቀስ በቀስ እንዲመራውና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች እንዳይጎዱ ማድረግ ይቻል ነበር። እንዲሁም የዲጂታል ክፍያ አገልግሎት ክፍያዎች እንዲቀንሱና የገንዘብ ዝውውር ፈጣንና ርካሽ እንዲሆን ቢደረግ በድህነት ላይ የሚፈጠረው ጫና ሊቀንስ እንደሚችል ያስረዳል። ሰነዱ በቁጥር የሚያሳየው ለውጥም ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሷል። በግብፅ አንድ ዶላር በ2022 15 ፓውንድ ከነበረ በ2026 ወደ 50 ፓውንድ ከፍ ብሏል፤ በናይጄሪያ በ2023 461 ናይራ የነበረው በ2026 ወደ 1,350 ናይራ ደርሷል፤ በኢትዮጵያም በ2024 56 ብር የነበረው አንድ ዶላር በ2026 ወደ 160 ብር ከፍ ብሏል። ከዚህ ጋር ተያይዞ የዓለም ባንክ ቀደም ሲል ባወጣው መረጃ መሠረት፣ በኢትዮጵያ የድህነት መጠን ከ33 በመቶ ወደ 43 በመቶ በ2025 ከፍ ማለቱን፣ የብር የመግዛት አቅም መዳከሙን፣ የውጭ የፋይናንስ ድጋፍ መቀነሱን እና የአገር ውስጥ የገንዘብ ሥርጭት መቀነሱን ጠቅሷል። ዴቪድ ማልፔዝ በ2019 በኢትዮጵያ ባደረጉት ጉብኝት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር በመነጋገር የውጭ ምንዛሪው በሙሉ ለገበያ እንዳይለቀቅ ማሳሰባቸውን ገልጸው፣ "ነገር ግን ስኬታማ አልነበርንም፤ ምንዛሪው ሙሉ በሙሉ በገበያ እንዲመራ ተደረገ" ብለዋል። በእሳቸው ገለጻ፣ የምንዛሪ ዋጋ መዳከም ጥቅሙ ለጥቂት ልዩ ተጠቃሚዎች ሲሆን፣ ኪሳራው ግን በብር ደመወዝ በሚከፈላቸውና በድህነት ውስጥ በሚኖሩ ዜጎች ላይ ይወድቃል። በሌላ በኩል አይኤምኤፍ ግን በየጊዜው በሚያወጣቸው ሪፖርቶች የኢትዮጵያ የገበያ መር የውጭ ምንዛሪ ሪፎርም የውጭ ምንዛሪ ክምችትን እያሳደገ፣ ኢንቨስትመንትን እየሳበና የኢኮኖሚ ተወዳዳሪነትን እያሻሻለ መሆኑን በመግለጽ ከዚህ ግምገማ የተለየ አቋም ይዟል። #ሪፖርተር @tikvahecocnomy

ክፍት የስራ ቦታ የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ባለው ክፍት የሥራ ቦታ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ መስፈርቱን የምታሟሉ በኦንላይን ማመልከት ትች
+1
ክፍት የስራ ቦታ የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ባለው ክፍት የሥራ ቦታ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ መስፈርቱን የምታሟሉ በኦንላይን ማመልከት ትችላላችሁ ፦ https://forms.gle/tFmB72pZ7XAGTJy76 @tikvaheconomy

ክፍት የስራ ቦታ የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ባለው ክፍት የሥራ ቦታ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ መስፈርቱን የምታሟሉ በኦንላይን አመልክቱ https:/
+1
ክፍት የስራ ቦታ የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ባለው ክፍት የሥራ ቦታ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ መስፈርቱን የምታሟሉ በኦንላይን አመልክቱ https://forms.gle/mXg8SxMxbVCBN41X8 @tikvaheconomy

ክፍት የስራ ቦታ የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት ባለው ክፍት የሥራ ቦታ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ መስፈርቱን የምታሟሉ በኦንላይን አመልክቱ ht
+3
ክፍት የስራ ቦታ የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት ባለው ክፍት የሥራ ቦታ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ መስፈርቱን የምታሟሉ በኦንላይን አመልክቱ https://forms.gle/PLeWEeRvo3tCUmco6 @tikvaheconomy

ክፍት የስራ ቦታ የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ባለው ክፍት የሥራ ቦታ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ መስፈርቱን የምታሟሉ በኦንላይን አመልክቱ htt
+2
ክፍት የስራ ቦታ የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ባለው ክፍት የሥራ ቦታ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ መስፈርቱን የምታሟሉ በኦንላይን አመልክቱ https://forms.gle/S1KwFgXJAChP7DDi8 @tikvaheconomy

ክፍት የስራ ቦታ የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት ባለው ክፍት የሥራ ቦታ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ መስፈርቱን የምታሟሉ በኦንላይን አመልክቱ፦ http
+2
ክፍት የስራ ቦታ የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት ባለው ክፍት የሥራ ቦታ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ መስፈርቱን የምታሟሉ በኦንላይን አመልክቱ፦ https://forms.gle/SYemTA9r79pUxuY58 @tikvaheconomy

በመርካቶ ሸማተራ 180 የባህል ልብስ ሱቆች መታሸጋቸው 15 ሺህ ያህል ሰዎችን ተጎጂ አድርጓል። እንደ ' አዲስ ፎርቹን ' ዘገባ፣ በአዲስ አበባ መርካቶ የሚገኘው የሸማተራ የባህል ጨርቅና ልብስ ገበ
በመርካቶ ሸማተራ 180 የባህል ልብስ ሱቆች መታሸጋቸው 15 ሺህ ያህል ሰዎችን ተጎጂ አድርጓል። እንደ ' አዲስ ፎርቹን ' ዘገባ፣ በአዲስ አበባ መርካቶ የሚገኘው የሸማተራ የባህል ጨርቅና ልብስ ገበያ በግብር አሰባሰብ ስርዓት ላይ በተነሳ አለመግባባት ምክንያት 180 የንግድ ሱቆች ከታሸጉ ሦስት ሳምንታት አልፈዋል። ይህም በቀጥታና በተዘዋዋሪ 15 ሺህ ያህል ሰዎች የገቢ ምንጫቸውን እንዲያጡ አድርጓል። ነጋዴዎቹ እንደሚናገሩት፣ የፌዴራል መንግሥት የገቢ ግብር ሕጉን ካሻሻለ በኋላ ከቋሚ የግብር ክፍያ ወደ ደረሰኝና ቫት (VAT) ስርዓት እንዲገቡ ተጠይቀዋል። ነገር ግን ጨርቅ ከሸማኔዎች ያለ ደረሰኝ የሚገዙ በመሆናቸው ሥርዓቱን በቀላሉ መተግበር እንደማይችሉ ይከራከራሉ። ባለሥልጣናት በበኩላቸው፣ ነጋዴዎቹ ከሕግ የሚጠይቀውን የገቢ መጠን እያገኙ በመሆኑ ደረሰኝ መስጠትና በVAT መመዝገብ እንዳለባቸው ገልጸዋል። ለዚህም ከስድስት ወራት በላይ ጊዜ መስጠታቸውንና ከተደጋጋሚ ማሳሰቢያ በኋላ ሕጉን ለማስፈጸም ሱቆቹን እንደታሸጉ አስታውቀዋል። የሸማተራ ነጋዴዎች ግን ውይይቱ ሳይጠናቀቅ ሱቆቻቸው መታሸጋቸው ፍትሃዊ እንዳልሆነ ይገልጻሉ። በሱቆቹ መዘጋት ምክንያት የባህል ጨርቅ ሸማኔዎች፣ ልብስ ሰፊዎች፣ ጥልፍ ሠራተኞች ፣ አጓጓዦችና ሌሎች በዘርፉ የተሰማሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ገቢያቸውን አጥተዋል። የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በበኩሉ ነጋዴዎቹ ወደ ሕጋዊ ስርዓቱ እንደገቡ ሱቆቹ እንደሚከፈቱ ገልጿል። የግብር ባለሙያዎችም የVAT ምዝገባው በሕግ የሚጠየቅ ቢሆንም፣ በሸማኔዎችና በነጋዴዎች መካከል ያለውን የደረሰኝ ችግር በውይይትና በተለዋዋጭ መፍትሄ መፍታት እንደሚገባ ያሳስባሉ። ይህ ጉዳይ መንግሥት የግብር ገቢን ለማሳደግ እየወሰደ ካለው ጠንካራ እርምጃ ጋር ተያይዞ የተነሳ ሲሆን፣ የሸማተራ ነጋዴዎች ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ለመውሰድ መዘጋጀታቸው ተገልጿል። አዲስ ፎርቹን የመረጃው ባለቤት ነው። @tikvaheconomy

በመርካቶ ሸማተራ 180 የባህል ልብስ ሱቆች መታሸጋቸው 15 ሺህ ያህል ሰዎችን ተጎጂ አድርጓል። በአዲስ አበባ መርካቶ የሚገኘው የሸማተራ የባህል ጨርቅና ልብስ ገበያ በግብር አሰባሰብ ስርዓት ላይ በ
በመርካቶ ሸማተራ 180 የባህል ልብስ ሱቆች መታሸጋቸው 15 ሺህ ያህል ሰዎችን ተጎጂ አድርጓል። በአዲስ አበባ መርካቶ የሚገኘው የሸማተራ የባህል ጨርቅና ልብስ ገበያ በግብር አሰባሰብ ስርዓት ላይ በተነሳ አለመግባባት ምክንያት 180 የንግድ ሱቆች ከታሸጉ ሦስት ሳምንታት አልፈዋል። ይህም በቀጥታና በተዘዋዋሪ 15 ሺህ ያህል ሰዎች የኑሮ ምንጫቸውን እንዲያጡ አድርጓል። ነጋዴዎቹ እንደሚናገሩት፣ የፌዴራል መንግሥት የገቢ ግብር ሕጉን ካሻሻለ በኋላ ከቋሚ የግብር ክፍያ ወደ ደረሰኝና ቫት (VAT) ስርዓት እንዲገቡ ተጠይቀዋል። ነገር ግን ጨርቅ ከሸማኔዎች ያለ ደረሰኝ የሚገዙ በመሆናቸው ሥርዓቱን በቀላሉ መተግበር እንደማይችሉ ይከራከራሉ። ባለሥልጣናት በበኩላቸው፣ ነጋዴዎቹ ከሕግ የሚጠይቀውን የገቢ መጠን እያገኙ በመሆኑ ደረሰኝ መስጠትና በVAT መመዝገብ እንዳለባቸው ገልጸዋል። ለዚህም ከስድስት ወራት በላይ ጊዜ መስጠታቸውንና ከተደጋጋሚ ማሳሰቢያ በኋላ ሕጉን ለማስፈጸም ሱቆቹን እንደታሸጉ አስታውቀዋል። የሸማተራ ነጋዴዎች ግን ውይይቱ ሳይጠናቀቅ ሱቆቻቸው መታሸጋቸው ፍትሃዊ እንዳልሆነ ይገልጻሉ። በሱቆቹ መዘጋት ምክንያት የባህል ጨርቅ ሸማኔዎች፣ ልብስ ሰፊዎች፣ ጥልፍ ሠራተኞች፣ ብረት ሠራተኞች፣ አጓጓዦችና ሌሎች በዘርፉ የተሰማሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ገቢያቸውን አጥተዋል። የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በበኩሉ ነጋዴዎቹ ወደ ሕጋዊ ስርዓቱ እንደገቡ ሱቆቹ እንደሚከፈቱ ገልጿል። የግብር ባለሙያዎችም የVAT ምዝገባው በሕግ የሚጠየቅ ቢሆንም፣ በሸማኔዎችና በነጋዴዎች መካከል ያለውን የደረሰኝ ችግር በውይይትና በተለዋዋጭ መፍትሄ መፍታት እንደሚገባ ያሳስባሉ። ይህ ጉዳይ መንግሥት የግብር ገቢን ለማሳደግ እየወሰደ ካለው ጠንካራ እርምጃ ጋር ተያይዞ የተነሳ ሲሆን፣ የሸማተራ ነጋዴዎች ውሳኔውን በፍርድ ቤት ለመቃወም መዘጋጀታቸው ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ (GBE) የቀድሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተስፋዬ ቦሩን፣ በተደጋጋሚ የተፈጸሙ የቁጥጥር ደንብ ጥሰቶችን በመጥቀስ፣ በማንኛውም በኢትዮጵያ በሚሠራ የፋ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ (GBE) የቀድሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተስፋዬ ቦሩን፣ በተደጋጋሚ የተፈጸሙ የቁጥጥር ደንብ ጥሰቶችን በመጥቀስ፣ በማንኛውም በኢትዮጵያ በሚሠራ የፋይናንስ ተቋም ውስጥ የቦርድ አባል፣ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወይም ከፍተኛ አመራር ኃላፊነት እንዳይይዙ ለ5 ዓመታት አግዷል። ብሔራዊ ባንኩ ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በላከው ደብዳቤ፣ በግሎባል ባንክ ላይ ባደረገው ልዩ የቁጥጥር ምርመራ መሠረት አቶ ተስፋዬ ከሥራ መነሳታቸውን ገልጿል። ምርመራው የባንኩን የኮርፖሬት አስተዳደር፣ የብድርና የክሬዲት አስተዳደር፣ የሰው ኃይል አመራር፣ የውጭ ምንዛሬ አሠራር እና አጠቃላይ የፋይናንስ አስተዳደርን መገምገሙን አመልክቷል። እንደ ብሔራዊ ባንኩ ገለጻ፣ በምርመራው ወቅት በርካታ የቁጥጥር መመሪያዎችና የባንኩ የውስጥ አሠራር ደንቦች መጣሳቸው በመረጋገጡ የባንኩን ጤናማ አሠራር እንደጎዳ ተገልጿል። ግኝቶቹም ከባንኩ ቦርድና ከከፍተኛ አመራሮች ጋር ተወያይተው በተለዩት ችግሮች ላይ መግባባት መደረሱን ብሔራዊ ባንኩ ገልጿል። ባንኩ በበኩሉ የማስተካከያ ዕቅድ ቢያቀርብም፣ የተገኙት ጥሰቶች ክብደት እና አቶ ተስፋዬ ከዚህ ቀደም በግንቦት 2013 እና በኅዳር 2017 ዓ.ም የተሰጧቸው የጽሑፍ ማስጠንቀቂያዎች በመኖራቸው፣ የበለጠ ጠንካራ እርምጃ መውሰድ አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን አስታውቋል። በዚህም መሠረት፣ ከሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ከግሎባል ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚነት መነሳታቸውን እና ከዚያው ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 5 ዓመታት በማንኛውም የፋይናንስ ተቋም ውስጥ የቦርድ አባል፣ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወይም ከፍተኛ አመራር ኃላፊነት እንዳይይዙ ውሳኔ መተላለፉን ገልጿል። ይህ የብሔራዊ ባንክ እርምጃ የግሎባል ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ አቶ ተስፋዬን ከሥራ ካሰናበተ በኋላ የተወሰደ መሆኑ ተገልጿል። በጉዳዩ ላይ የአቶ ተስፋዬ ቦሩ፣ የግሎባል ባንክ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ዮሴፍ ጌታቸው እና የብሔራዊ ባንክ የባንክ ቁጥጥር ኃላፊ ፍሬዘር አያሌው አስተያየት ለማግኘት የተደረገው ጥረት ውጤታማ እንዳልሆነ ተገልጿል። #Capital @tikvaheconomy