en
Feedback
Amhara Prosperity Party/APP2

Amhara Prosperity Party/APP2

Open in Telegram
3 577
Subscribers
+124 hours
+197 days
+1330 days
Posts Archive
ጳጉሜን 2  የማንሰራራት ቀን የማንሠራራት ጉዞ በተጨባጭ ውጤቶች እየተረጋገጠ ያለ ሀገራዊ ሂደት ነው። በብልጽግና ፓርቲ የሚመራዉ የመደመር መንግሥት ፖሊሲዎችና ዕቅዶች፣ ኢትዮጵያ ካላት ዕምቅ አቅም ጋር የሚመጥን የልማትና የብልጽግና መሠረት እየገነባች ነው። ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ እስከ ዘመናዊ የኮሪደር ልማት፤ ከቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ እስከ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም፤ የሀገራችን መነቃቃት በተግባር እየታየ ነው። የግብርና ምርታማነት እየጨመረ፣ የታዳሽ ኃይል አቅማችን እየሰፋ፣ የቱሪዝም መዳረሻዎቻችን እየለሙ፣ ከተሞቻችን እየዘመኑ፣ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አቅማችን እየተጠናከረ ነው። የማዕድን ሀብቶቻችንንም ለልማት በተሻለ ደረጃ ለማዋል የተያዘው አቅጣጫ እየተጠናከረ ነው። ይህ ሁሉ የሚቻለው በመንግሥትና በሕዝብ የተደመረ አቅም ነው። በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በሀገራዊ ምክክር፣ በምርጫና በሌሎች ሀገራዊ ጥሪዎች ላይ የታየው የዜጎች ተሳትፎ የሀገር ብልጽግና የጋራ ጉዳይ መሆኑን ያሳያል። ኢትዮጵያ የጀመረችውን የማንሠራራት ጉዞ በተደመረ አቅም በማፋጠን፣ የዛሬን እመርታ ወደ ዘላቂ ብልጽግና እናሻግራለን። ጳጒሜን 2 ቀን 2018 ዓ.ም   የማንሠራራት ቀን

ጳጉሜን 1 - የእመርታ ቀን፡ ጳጉሜን 1 "የእመርታ ቀን" ሲከበር፣ ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ያሳካቻቸውን ዘርፈ ብዙ የስኬት ጉዞዎችና ለሁለንተናዊ ብልጽግና መሰረት የሆኑ ታላላቅ ምዕራፎችን በማሰብ ነው። በብልጽግና ፓርቲ የሚመራዉ የመደመር መንግሥት ተስፋን ወደ ተግባር፣ ህልምን ወደ እውነታ በመቀየር በተለያዩ የልማት መስኮች የያዘዉን የዕድገት መስመር በግልጽ ያሳየበት ወቅት ላይ እንገኛለን። በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊና በዲፕሎማሲዉ መስክ የተመዘገቡ እምርታዊ ስኬቶች ኢትዮጵያን ወደሚገባት የብልጽግና ከፍታ የሚያሻግሩ መሰረቶች ናቸዉ፡፡ በግብርና እና በምግብ ሉዓላዊነት የተመዘገበዉ እመርታ ትልቅ አብነት ነዉ፡፡ በበጋ መስኖ የተሸፈነው መሬት ከ400 ሺህ ሄክታር ወደ 3 ሚሊዮን ሄክታር በማደጉ ከ100 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ተሰብስቧል። ኢትዮጵያ የበጋ መስኖ በመጠቀም በስንዴ ምርት ላይ ያካሄደችዉ አብዮት ከስንዴ አስመጪነት ወደ አምራችነትና ላኪነት አሸጋግረዋታል፡፡ በዚህ ዘርፍ የተመዘገበዉ እመርታ ሀገራችን የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋጥ የምታደርገዉ ጥረት ተጨባጭ ዉጤት ማምጣቱ የማይቀር መሆኑን የሚያስረግጥ ሀቅ ነዉ፡፡ መላዉን ኢትዮጵያዉያንን በአንድነት በማነሳሳት ለአንድ ታሪካዊ አላማ በህብረት ቆመዉ ዘመን ተሻጋሪ ታሪክ እንዲጽፉ ምክንያት ሆኗል የአረንጓዴ አሻራ፡፡ እኛ ስንደመር የማናሳካዉ ድል አለመኖሩን የተከልናቸዉ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞች ይመሰክራሉ፡፡ በአንድነት የተከልናቸዉ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች የአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም፣ የአፈር ለምነትን የመጠበቅና የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ አህጉራዊ አርአያነት ያለው ስራ ማከናወናችንን ይመሰክራሉ፡፡ በመላዉ ኢትዮጵያውያን የተቀናጀ ህብረት እና የኢኮኖሚ ነፃነት ምልክት የሆነው የህዳሴው ግድብ ተጠናቅቆ የኤሌክትሪክ ሓይል ማምረት መጀመሩ፤ በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች እየተካሄደ ያለዉ የኮሪደር ልማት የከተሞችን ውበት፣ የትራፊክ ፍሰት እና የዜጎችን የመኖሪያ ምቾት ወደ አዲስ ደረጃ ማሸጋገሩና የቱሪዝም ዘርፉን ለማነቃቃት በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትዉልድና በገበታ ለሸገር የተሰሩ የልማት ስራዎች ያስመዘገቡት እመርታ በተምሳሌትነት ከሚጠቀሱ አበይት ስኬቶች መካል ናቸዉ፡፡ ባለፉት የለዉጥ አመታት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የሀገር ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪዎችን በማጠናከርና ለወጣቶች የቴክኖሎጂና አዲስ የስራ እድሎችን በመፍጠር ረገድ ተጨባጭ ውጤት ተመዝግቧል። ጳጉሜን 1 የእመርታ ቀን፣ ያለፉትን ስኬቶች ከማሰብ በላይ ወደፊት ለሚጠብቁን ታላላቅ ሀገራዊ ግቦች አዲስ የቁርጠኝነትና የጋራ ጥረት መንፈስ የምናድስበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው። #prosperity

የብልፅግና ዕሳቤ ሁለንተናዊና ከፍ ያለ ራዕይ ያለው የልማት አቅጣጫ ነዉ ፤ *** የብልፅግና ዕሳቤ የአንድ ዘርፍ ወይም የአንድ ዘመን የልማት አቅጣጫ ብቻ አይደለም። ሁለንተናዊ የሆነ የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካ፣ የማኅበራዊ ልማት፣ የሰላምና ደህንነት እንዲሁም የውጭ ግንኙነት ራዕይን ያካተተ ጥልቅ ዕሳቤ ነዉ፡፡ ሁለንተናዊ ብልፅግና የቁሳዊና የሰብዓዊ ፍላጎቶችን በማጣመር፣ የዜጎችን ኑሮ በማሻሻል እና የሀገርን አቅም በማጎልበት የሚገነባ ልማት ነው። የብዝኃ ዘርፍ ኢኮኖሚን በማጠናከር፣ ግብርናንና ኢንዱስትሪን በማስተሳሰር፣ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የሀገርን ኢኮኖሚ ወደ አምራችነት ማሸጋገር ዋና ትኩረት ነው። የገቢ ምርቶችን በአገር ውስጥ በጥራትና በብዛት መተካት፣ የኤክስፖርት ምርትን ማሳደግ፣ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ማስፋት እና ለዜጎች ዘላቂና አስተማማኝ የሥራ ዕድል መፍጠር የኢኮኖሚያዊ ብልፅግና ዋና መሠረቶች ናቸው። በዚህ መርህ ላይ በመመርኮዝም ዘላቂ፣ ፈጣንና አካታች የኢኮኖሚ ዕድገት በማስመዝገብ የዜጎችን መሠረታዊ ፍላጎት ማሟላት፣ ድህነትን መቅረፍ እና የኑሮ ደረጃን ማሻሻል የብልፅግና ጉዞ ዋና ግቦች ናቸው። ሰላምና ሀገራዊ ሉዓላዊነት ማረጋገጥ የሁለንተናዊ ብልጽግና ዕሳቤ አንዱ አካል ነዉ፡፡ ልማት ያለ ሰላም ዘላቂ አይሆንም። ስለዚህ ሰላምን ማረጋገጥ፣ የሀገርን ሉዓላዊነትና ደህንነት ማስጠበቅ እና የሀገራዊ አንድነትን ማጠናከር የብልፅግና ጉዞ ወሳኝ መሠረቶች ናቸው። የዲሞክራሲ ሥርዓትን ማስፋት፣ የዜጎችን ጥያቄዎች በተገቢው መመለስ፣ የማኅበራዊ ትሥሥርን ማጠናከር እና የጋራ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ የሁለንተናዊ ብልፅግና አካል ነው። የኢትዮጵያን ክብር፣ ጥቅምና ሉዓላዊነት በሚያስጠብቅ መንገድ የውጭ ግንኙነትን ማጠናከር፣ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲን ማስፋት እና የሀገሪቱን ተወዳዳሪነት ማሳደግ የብልፅግና ራዕይ አካል ነው። የብልፅግና ጉዞ በቀስታ የሚሄድ የልማት ጉዞ ሳይሆን፣ መፍጠር፣ መፍጠንና መዝለል በሚሉ የልማት አቅጣጫዎች የተመራ ጥረት ነው። ዓላማውም የኢትዮጵያን የሰው፣ የተፈጥሮና የኢኮኖሚ ሀብቶች በብቃት በማንቀሳቀስ፣ ምርታማነትን በማሳደግና የዜጎችን ተሳትፎ በማጠናከር በአንድ ትውልድ ዕድሜ ውስጥ የበለፀገች፣ ሰላማዊና ተወዳዳሪ ኢትዮጵያን መገንባት ነው። ሁለንተናዊ ብልፅግና ከኢኮኖሚ ዕድገት ባሻገር፣ የዜጎች የተሻለ ኑሮ፣ የሀገር አቅምና የጋራ ተጠቃሚነት ግብ በመሆኑ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቁርጠኝነት መስራት ይኖርባቸዋል፡፡ #prosperity

photo content

"አርቆ ማየት አልቆ መሥራት" የትውልድ ቁጭትን ለትውልድ ልዕልና የማነጽ ትልም --- የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የክልሉን እድገት ለማረጋገጥ እስከ 2042 ዓ.ም የሚዘልቅ የ25 ዓመት ፍኖተ ካርታ እና የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ አዘጋጅቶ በክልል ምክር ቤት ከጸደቀ በኋላ በ2018 በጀት ዓመት ወደ ሙሉ ትግበራ ተገብቷል ። ይህ የሃያ አምስት ዓመቱ የልማት ፍኖተ ካርታ ገዥ እሳቤ በወሳኝ ዘርፎች ትስስር በቴክኖሎጂ እመርታና ኢንዱስትሪያሊዊነት የኢኮኖሚ ተስተካካይነትን በአንድ ትውልድ ማረጋገጥ ነው። ከ25 ዓመታቱ የአሻጋሪ እና የዘላቂ ልማት ዕቅድ የተቀዳ ከ2018 እስከ 2022 ዓ.ም ድረስ ተግባራዊ የሚሆን የአምስት ዓመታት ስትራቴጂክ እቅድ ተዘጋጅቶ በተጠናቀቀው የበጀት አመት ተግባራዊ ስራው ተጀምሯል ። በእቅዱ የትናንት ችግሮችን፣ የዛሬ አሁናዊ ሁኔታዎችን፣ የነገ ተስፋ እና ስጋቶችን ሳይንሳዊ በሆነ ትንታኔ በመለየት የተዘጋጀ ፣ክልሉ ያለውን የሰው ኃይል፣ ካፒታል እና ቴክኖሎጂ አቀናጅቶ በመጠቀም ለአማራ ክልል ዕድገትን እና ዘላቂ ልማትን የሚያጎናጽፍ ፣ ክልሉ ያለውን ጸጋ መሠረት ያደረገ ነው፡፡ በዕቅዱ ክልሉ በስድስት የልማት ቀጣና የተከፋፈለ ሲሆን እነዚህም የጣና የልማት ኮሪደር፣ የደቡብ ምዕራብ አማራ፣ የሰሜን ምዕራብ፣ የተከዜ ኮሪደር፣ የማዕከላዊ አማራ እና የምሥራቅ አማራ ቀጠናዎች ናቸው፡፡ ይህንን ዕቅድ ከሰነድነት ባለፈ መሬት ላይ ወርዶ እንዲተገበር የማስፈጸሚያ ስልቶችም ተዘጋጅተዋል።ልማትን በፍትሐዊነት ማዳረስ፣ ልዩ ፕሮግራሞችን እና ኢኒሼቲቮችን በአግባቡ መጠቀም፣ የማያሠሩ ፖሊሲዎችን እና ስትራቴጂዎችን ማሻሻል፣ የተቋማት አደረጃጀቶችን ማስተካከል፣ ክትትል እና ቁጥጥርን ማጠናከር፣ የተግባቦት ስትራቴጂን በውጤታማነት መጠቀም እና የኅብረተሰብ ተሳትፎን ማረጋገጥ ሥራ አጥነትን ለመቀነስ ለሚሠሩ ሥራዎች የማስፈጸሚያ ስልቶች ሆነው ተግባራዊ መደረግ ተጀምሯል ። የግጭት አዙሪት እና ድኅነት የክልሉ ችግሮች ሆነው በዕቅዱ ተለይተዋል ፤ ይህ ዕቅድም ሁለቱንም ችግሮች እንዲፈታ እና ክልሉን ወደ አዲስ ምዕራፍ እንዲመነጠቅ የሚያደርግ ፣ ዛሬ የዓለም ሀገራት ከደረሱበት ብልጽግና ለማድረስ፣ በቴክኖሎጅ ተወዳዳሪ ለመሆን፣ ደስተኛ ኅብረተሰብን ለመፍጠር ቁልፍ ሚና ያለው ነው። የትውልድ እና የቁጭት ዕቅዱ የአማራ ክልልን በዘላቂነት ከችግር የሚያወጣ፣ ወደ ተሻለ ዕድገት የሚያደርስ ሳይንሳዊ ዘዴን ተከትሎ የክልሉን ሕዝብ ችግሮች ለይቶ ለችግሮቹ መፍትሔ የሚሆኑ እና ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ መንገዶችን በመለየት ለተዘጋጀው ለዚህ የትውልድ እቅድ ተግባራዊነት የመሪዎች ቁርጠኝነት ይጠይቃል ፤ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል የሕልውና ጉዳይ መሆኑን ተረድቶ ርብርብ በማድረግ እቅዱን በመፈጸም ድህነትን ታሪክ ማድረግ ይኖርበታል። ዕቅዱ የሕዝብ እንጅ የአንድ ዘመን ፓርቲ ወይም መንግሥት ባለመሆኑ ሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል ለተፈጻሚነቱ በቅንነት የድርሻውን ማበርከት ይጠበቅባቸዋል ። ይህ የትውልድ እቅድ ትልቅ የመልማት ጸጋ ያለውን ክልሉን መሠረት በማድረግ የወደ ፊት የጋራ ርዕያችንን እና መዳረሻችንን የምንበይንበት ነው። ግጭት እና ድህነት እየተመጋገቡ እና እየተፈራረቁ የሕዝባችን ችግር ሆነው ቆይተዋል፤ ይህ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ እንዲቋጭ በጋራ አመራር በትጋት መሥራት ይጠበቃል። የክልሉ ሕዝብ ካለበት ግጭት እና መከራ የሚወጣበት የታሪክ እጥፋት መሆን አለበት።ሕዝባችን የደህንነት፣ የአብሮነት፣ የማደግ እና መሠረታዊ ፍላጎቶችን ከማሟላትም አልፎ ዓለም የደረሰበትን ቅንጡ አኗኗር መኖር ያሻል፤ ይህንን የሕዝብ ፍላጎት በውል በመረዳት መሥራት ያስፈልጋል። ሕዝቡ በተስተካከለ ሕይዎት እና በተሻሻለ የኑሮ ደረጃ ላይ እንዲደርስ መስዋዕትነት ጭምር እየተከፈለ መሥራትን ባሕል ማድረግ ይኖርብናል ።ጠንካራ የሆነ የተቋማት እና የሥራ አመራር ባሕልን በመላበስ ሕዝብን ማገልገልም ይገባል። በግጭት እና በድህነት አዙሪት ውስጥ መቆየት የማንም ምርጫ ሊሆን አይችልም፤ በመሆኑም የሕዝብን ደህንነት እና የኑሮ ደረጃ የሚያሻሽል አሻጋሪ እቅድ አውጥቶ በጋራ መሥራት ምርጫ ሳይሆን ግዴታ ነው። #amharaprosperityparty ---- 🕊ሰላም ለሁሉም፤ ሁሉም ለሰላም🕊 "የጎርጎራ ቃልኪዳናችን፤ ለዘላቂ ሰላም እና ለሁለንተናዊ ብልጽግናችን" ለወቅታዊ ፣ ትክክለኛና አዳዲስ መረጃዎች የፓርቲያችንን የማህበራዊ ገፆች ይወዳጁ። ትዊተር :- twitter.com/AppAmhara?s=09 ቴሌግራም:- t.me/amharaapp ቲክቶክ፡- tiktok.com/@amharaprosperityparty ዩቲዩብ:- https://www.youtube.com/@amharaapp

photo content

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የጋራ ብልጽግና መሰረት ነዉ! የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ የኢትዮጵያ የልማት ታሪክ ድል ብቻ ሳይሆን የአባይ ውሃ በፍትሃዊ፣ በምክንያታዊና በዘላቂ መርህ ሲተዳደር ለተፋሰሱ ሀገራት የጋራ ብልፅግና መሠረት ሊሆን እንደሚችል ያሳየ ታሪካዊ ምዕራፍ ነው። መላዉ ኢትዮጵያዊያን ተደምረን የመቻል ምልክት የሆነዉን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ለምርቃት እንዲበቃ ያደረግነዉ ብዙ ፈተናዎችን በብልሃት በመሻገር ነዉ፡፡ ኢትዮጵያ የአባይ ዉሃ 86 በመቶ ምንጭ ሆና ሳለ በተሳሳተ ትርክት የሀገራችንን እዉነት ቀምተዉ እንደራሳቸዉ አድርገዉ በዲፕሎማሲዉ፣ በሚዲያዉና በሌሎች መድረኮች እያቀረቡ አለምን ጭምር እያሳሳቱ ለዘመናት የኖሩት ገመናቸዉ በአደባባይ እየተገለጠ የአዞ እንባቸዉ ሳይታበስ፤ እነሱ እየዛቱብን ያልተገባ ስም በአለም አደባባይ እየሰጡን እኛ አላማችን ላይ አተኩረን ተፈጥሯዊ የባለቤትነት መብታችንን በፍትሃዊነት ተጠቅመን አሳክተናል፡፡ የያኔዉ ጩሄት የነበረዉ ህዳሴ ግድብ ከፍታ በጨመረና ዉሃ የመያዝ አቅም በጨመረ ቁጥር ወደ ተፋሰሱ ሀገራት የሚፈሰዉ የዉሃ መጠን በእጅጉ ይቀንሳል የሚል ነዉ፡፡ እዉነቱ ግን ኢትዮጵያ አስቀድማ እንዳለችዉ በግድቡ አስተዳደር ሳቢያ የአባይ ዉሃ ተፈጥሯዊ ፍሰት አንዳች አልቀነሰም፤ ይልቁንም ህዳሴ ከመገንባቱ በፊት በተለይም በዝናብ ወቅት በጎርፍና በደለል ምክንያት ይከሰት የነበረዉን ተፈጥሯዉ አደጋዎች በእጅጉ ቀንሰዋል፡፡ ህዳሴ ግድብ በመሠረታዊ ዓላማው የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ቢሆንም፣ ግድቡ የአባይን የውሃ ፍሰት በመቆጣጠር በዝናብ ወቅት የሚከሰቱ ከፍተኛ ጎርፎችን ለመቀነስና በበጋ ወቅት የተረጋጋ ፍሰት እንዲኖር ያስችላል። ይህም በተለይ ለሱዳን የጎርፍ አደጋን ለመቀነስና የውሃ አቅርቦትን ይበልጥ ያረጋግጣል። ከኢትዮጵያ ደጋማ አካባቢዎች የሚመነጨውና ወደ ታችኛው ተፋሰስ የሚወርደውን ደለል መጠን በመቀነስ፣ የሱዳንና የግብፅ ግድቦች፣ የመስኖ ቦዮችና የውሃ መሠረተ ልማቶች የጥገናና የደለል ማስወገጃ ወጪን ለመቀነስ ያግዛል። በተጨማሪም የውሃ ፍሰት መረጋጋቱ በሱዳን ያሉ የውሃ ኃይል ጣቢያዎች የበለጠ በተረጋጋ ሁኔታ እንዲሰሩ፣ ለመስኖና ለግብርና የሚውል ውሃ በተሻለ ሁኔታ እንዲገኝ እድል ይፈጥራል። ሱዳን ከእነዚህ ጥቅሞች ባሻገር የኤልክትሪክ ሀይል በተመጣጣኝ ዋጋ የምታገኝበትን እድል ፈጥሯል፡፡ የህዳሴ ግድብ ዉሃ ሙሌት ከተጠናቀቀ በኋላ ከጎርፍና ከደለል ጋር ተያይዞ ይከሰቱ የነበሩ ተፈጥሯዊ አደጋዎች እየቀነሱ መሆናቸዉ የአደባባይ እዉነት ነዉ፡፡ የህዳሴ ግድብ ገና የመሰረት ድንጋይ ሲጣል የዉሃ መጠን ፍሰት ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ይፈጠራል መጠኑም ይቀንሳል፣ ግድቦቻችን ዉሃ ይቀንሳሉ፣ መስኖዎቻችንም ይቆማሉ፣ ህልዉናችንም አደጋ ላይ ይወድቃል፤ የሚሉ ክሶች ህዳሴ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቅቆ በፕሮፖጋንዳቸዉ ልክ መሬት ላይ ያለዉ እዉነት መሆኑን የሚያሳይ ማስረጃ እያቀረቡ ሲሞግቱ አይታዩም፤ አንድ ደጋግመዉ የሚደሰኩሯት ነጥብ የቅኝ ግዛት ዘመን ዉል ነዉ፤ ጊዜ ያለፈበት ዉል፡፡ በሀሰት ትርክት የአባይ ዉሃ ብቸኛ ባለቤት እንደሆኑ አስመስለዉ አለምን ሲያወናብዱ የኖሩበትን ልምድ በመጠቀም ጊዜን ወደኋላ ብቻ ነዉ የሚሰራዉ ይሉናል፡፡ ዛሬ አለም በቅኝ ዘመን ላይ አይደለችም፡፡ ብትመኘዉ እንኳን ልትመልሰዉ አትችልም፡፡ የቅኝ ዘመን ዉል በየትኛዉም መመዘኛ በዚህ ዘመን የአለም አቀፍ ህግ ሊሆን አይችልም፡፡ ግብጽ ሰሞኑን በተፈጥሮ ክስተት-ኤል ኒኖ ምክንያት የቀነሰዉን የናይል ዉሃ መጠን ኢትዮጵያ ግድቡን ያስተዳደረችበት መንገድ የፈጠረዉ ችግር ነዉ በማለት የሀገራችንን ስም እያጠለሸች ትገኛለች፡፡ በአጠቃላይ በምስራቅ አፍሪካ በዋናነትም በኢትዮጵያ ይጠበቅ የነበረዉ የዝናብ መጠን በመቀነሱ ምክንያት የአባይ መጋቢ ወንዞች ዉሃ መጠን ቀንሷል፡፡ በዚህም ምክንያት ወደ ግድቡ ይገባ የነበረዉ የዉሃ መጠን ቀንሷል፡፡ በዚህ ኡደትም ከግድቡ ይወጣ የነበረዉ ዉሃ ይቀንሳል፡፡ ለዚህ ማረጋጫ ደግሞ በዚህ ክረምት የማዕከላዊ፣ ሰሜን ምሥራቅ እና ሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ አካባቢዎች የሚያገኙት የዝናብ መጠን ከመደበኛው በታች ሊሆን እንደሚችል በምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) ሥር ያለው 'ክላይሜት ፕሪዲክሽን ኤንድ አፕልኬሽንስ ሴንተር' መረጃ አንዱ ነዉ። ኢትዮጵያ የአባይን ውሃ ለራሷ ልማትና እድገት መጠቀም የማይቀር የመልማት መብቷ ነው፤ ይህንን መብት ስትጠቀም ግን የጎረቤቶቿን ጥቅም ችላ አትልም። ፍትሃዊ አጠቃቀም፣ የጋራ ጥቅም፣ የሳይንስ መረጃ፣ ትብብርና ዘላቂነት የኢትዮጵያ የሁልጊዜ አቋም ነዉ። በዚህ መርህ ላይ በመመርኮዝም የህዳሴ ግድብን ካጠናቀቀች በኋላ በአባይ ወንዝ ላይ ሌሎች ተጨማሪ ግድቦችን ለመገንባት ዉጥናለች፡፡ እቅዷም ለሀገር ሁለንተናዊ እድገት እንዲሁም ለጎረቤት ሀገራት ተጠቃሚነት ልክ እንደ ህዳሴዉ በቁርጠኝነት ይሳካል፡፡ ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ ያላትን ተፈጥሯዊ፣ ታሪካዊና ህጋዊ መብት ተጠቅማ የተፋሰሱን ሀገራት ተጠቃሚነት ባረጋገጠ መንገድ የልማት ተግባራትን በድል ማከናወኗን ትቀጥልበታለች፡፡

photo content

ጠንካራ ኅብረ ብሔራዊነት ፤ ለዘላቂ አብሮነት! የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ አፈጣጠር የብዝኃነት ማሳያ ነው። ልዩ ልዩ ሕዝቦቿና ባህሎቻቸው፣ ያሸበረቀ መልክዓ ምድሯ፣ ማራኪው ሥነ-ምኅዳሯና ብዝኃ-ሕይወቷ ብሎም ጣፋጭ የባህል ምግቦቿ በሙሉ የሚነግሩን አንድ ትልቅ የተፈጥሮ እውነት ቢኖር የሀገራችን የውበቷም ሆነ የጥንካሬዋ ምስጢር ኅብራዊነቷ መሆኑን ነው። ኅብረ ብሔራዊነት የኢትዮጵያ የተፈጥሮ ጸጋ እና ደማቅ መልክ ነው። እኛ ኢትዮጵያውያን የልዩ ልዩ እምነቶች፣ የውብ ባህሎች፣ የቋንቋዎች፣ የጥንታዊ ሥልጣኔዎች፣ የረጅም ታሪክና የቅርሶች ባለቤት የሆንን በብዝኃነት ያሸበረቅን ኅብራዊ ሕዝቦች ነን። ብዝኃነታችን የውበታችንና የጥንካሬያችን ምንጭ ሲሆን የጋራ ዕጣ ፈንታችን ደግሞ እንደ ድርና ማግ የተሳሰረና የተጋመደ ነው። በዘመናት የአብሮነት ጉዟችን ጣፋጩንም ሆነ መራራውን ጊዜ በአብሮነት የተጋራን የማይበጠስ ጠንካራ ማኅበራዊ ትስስር ያለን ነፃና ኩሩ ሕዝቦች ነን። ኢትዮጵያ በዘመናት መካከል ከየትኛውም ማዕበልና መናወጥ ተጠብቃ ለዘላለም ጸንታ የምትኖረው ኅብረ ብሔራዊነትን እና አንድነትን ነጣጥሎ በማየት አይደለም። ይልቁንም የብዝኃነት ውበትንና መብትን ከጋራ ሀገራዊ ፍቅር ጋር አዋሕዶ ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን እንደ ጽኑ ዓምድ ከፍ አድርጎ በማጽናት ብቻ ነው። ይህንኑ ሀገራዊ ጸጋ ወደ ፖለቲካዊ አቅም በመቀየር ሀገርን እየመራ የሚገኘው ብልፅግና ፓርቲያችን እውነተኛ ኅብረ ብሔራዊነትን ዋነኛ መለያ ቀለሙ አድርጎ እየሠራ ይገኛል፡፡ ብልፅግናዊነት ማለት ብዝኃነትን ያቀፈ ተግባራዊ ኅብራዊነት ማለት ነው፡፡ በዚህም መሠረት ፓርቲያችን የተዛቡ ትርክቶችን በማረም ፍትሐዊነትና ሐቅ ወደ ትክክለኛ ስፍራቸው እንዲመለሱ እንዲሁም የሕዝቦች መልካም ፈቃድ፣ እኩልነትና አብሮነት በአስተሳሰብም በተግባርም እንዲጎመራ በጽኑ ቁርጠኝነት እየሠራ ይገኛል። ስለሆነም ለኅብረ ብሔራዊ አንድነታችን ሰርክ ዘብ እንቁም ፤ አብረንም እንትጋ። ጠንካራ ኅብረ ብሔራዊነት፤ ለዘላቂ አብሮነት! ~•~•~•~• 🕊ሰላም ለሁሉም፤ ሁሉም ለሰላም🕊 #amharaprosperityparty

ሳምንታዊ መልዕክት ኢትዮጵያ አሸንፋለች! ኢትዮጵያ ታላቅ የፖለቲካ ምዕራፍ ያበሰረውን ሀገራዊ ምክክር ጉባኤን በድል አጠናቃለች። ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ለዓመታት ያካሄደው ሰፊ የምክክር ሂደት በአራት ሺህ ተመካካሪዎች በስምንት መሠረታዊ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ በመመካከር ተጠናቋል። በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግሥት የሀገራችንን የቆየ የፖለቲካ ስብራቶችን በኃይልና በግጭት ሳይሆን መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ በማሳተፍ በሀሳብ፣ በውይይትና በምክክር ለመፍታት የወሰነው ውሳኔ ትልቅ ፍሬ አፍርቷል። ከአራት ዓመታት በፊት በአዋጅ ቁጥር 1265/2021 የተቋቋመው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፥ ከቀበሌ ጀምሮ እስከ ዲያስፖራ ድረስ በሰፊ የህዝብ ተሳትፎ አጀንዳዎችን ሰብስቦ፣ የሀገራችንን መሠረታዊ ጥያቄዎች ወደ ሀገራዊ ውይይት መድረክ አምጥቷል። ይህ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን የወከሉ አራት ቁልፍ ባለድርሻ አካላትን በአጠቃላይ 4 ሺህ ተሳታፊዎችን፣ ከ150 በላይ አማካሪዎችንና 8 ባለ 500 ተመካካሪ ንዑስ ቡድኖችን ያሳተፈ ሰፊ የምክክር ሂደት ሆኗል። ሂደቱም ኮሚሽኑ በመረጠው የምክክር ስነ ዘዴ አላማውን ማሳካት ችሏል። ኋላቀር የጠብመንጃ ፖለቲካ መንገድም ያከተመለት አካሄድ መሆኑን በግልጽ መስክሯል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በሀገራዊ ምክክሩ መክፈቻ ላይ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ባህል በተመለከተ “ፖለቲካችን በጠንካራ ቃላት ይጀምርና በጠንካራ እርምጃ ይጠናቀቃል፤ ይህ ክፍተት አንድ ጊዜና ለሁልጊዜ መቆም አለበት” የሚል ጥሪ አቅርበዋል። ይህ ማለት የፖለቲካ ባህላችንን ከግጭት ወደ ውይይት፣ ከኃይል ወደ ሀሳብ፣ ከመሸነፍና ከማሸነፍ የዜሮ ድምር አስተሳሰብ ወደ የጋራ መፍትሔ እና መግባባት ማሸጋገር ነው። በዚህ ዕሳቤ ላይ የፀኑ ኢትዮጵያዊያን ለሀገራቸው ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት ለምክክር በቀረቡ አጀንዳዎች ዙሪያ የመፍትሔ ሀሳቦችን አፍልቀዋል። በሰለጠነ መንገድ በጠረጴዛ ዙሪያ የመነጋገር የመከራከር የመደማመጥ የመፍትሔ መንገዶችን የመጠቆም ባህል አዳብረዋል። የመደመር ፍልስፍናም ልዩነትን በመካድ ሳይሆን ልዩነትን በመቀበል፣ መደማመጥን በማስፋት፣ እኔነትን ወደ እኛነት በማሸጋገር የጋራ እውነትና የጋራ መፍትሄ መፈለግን ያስቀድማል። በዚህ መንፈስ የተካሄደው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሀገራችንን የፖለቲካ ባህል ለመቀየር ትልቅ መሠረት ጥሏል። ላለፉት 40 ቀናት የተመከረባቸው የሀገረ-መንግሥት ግንባታ፣ የመንግሥት አወቃቀርና የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፌዴራል ከተሞች ጉዳይ፣ የሃይማኖት ጉዳዮች፣ ተቋማዊ ግንባታና የሕግ የበላይነት፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች፣ ፀረ-ሙስናና መልካም አስተዳደር እንዲሁም ሰላም ግንባታን ያካተቱ ስምንቱ መሰረታዊ አጀንዳዎች የሀገራችንን የዛሬ ችግሮች ብቻ ሳይሆን፣ የነገ ትውልድ የሚገነባባቸውን የፖለቲካ፣ የማኅበራዊ ሰላም፣ የተቋማትና የኢኮኖሚ መሠረቶች የያዙ ናቸው። በመሆኑም የሀገራዊ ምክክሩ ድል አሁናዊ አጀንዳ ብቻ ሳይሆን ለነገ ኢትዮጵያ የተጣለ መሠረት ጭምር ነው። የምክክሩ መጠናቀቅ ምክረ ሀሳቦቹን ወደ ተግባር የማዋል አዲስ ምዕራፍ መጀመሪያ ስለሆነ የሁሉም ኢትዮጵያዊን፣ ባለድርሻ አካላት፣ የፖለቲካ ኃይሎችና ተቋማት ቀጣይ ተሳትፎ ይጠበቃል ለዚህም በቁርጠኝነት ልንተጋ ይገባል። #prosperity

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የኢትዮጵያን የፖለቲካ ባህል ከተቃርኖ እና ከጥላቻ ወደ ይቅርታ፣ ስክነት እና መረጋጋት ያሸጋገረ ታሪካዊ ክስተት መሆኑን የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ አስታወቁ። ፕሬዚ
+2
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የኢትዮጵያን የፖለቲካ ባህል ከተቃርኖ እና ከጥላቻ ወደ ይቅርታ፣ ስክነት እና መረጋጋት ያሸጋገረ ታሪካዊ ክስተት መሆኑን የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ አስታወቁ። ፕሬዚዳንቱ የምክክር መድረኩ በስኬት መጠናቀቁን አስመልክተው ባስተላለፉት ጠንካራ መልዕክት፤ ሀገራዊ ምክክርን የዘመናዊት ኢትዮጵያ ግንባታ ማዕዘን ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ በታሪካችን ታይቶ የማይታወቅ ደፋር ውሳኔ መሆኑን አብራርተዋል። ይህ መድረክ ተፎካካሪ ሀሳቦች በስሜታዊነት ሳይሆን በከፍተኛ መከባበር ተንሸራሽረው የተሻለ ሀሳብ የሚወጣበትን ዕድል የፈጠረ መሆኑንም አጽንዖት ሰጥተውበታል። ይህን ታሪካዊ የለውጥ ሀሳብ ወደ ተግባር በመቀየር ላሳዩት ጽኑ ቁርጠኝነት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የላቀ አድናቆታቸውን ገልጸዋል፡፡ ለሂደቱ ሕጋዊ ማዕቀፍ ላጸደቀው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፕሬዚዳንቱ ምስጋና አቅርበዋል። በምክክር መድረኩ ላይ ተሳትፈው ለመጪው ትውልድ የሚሻገር ብሩህ ታሪካዊ አሻራ ላኖሩ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባገዳዎች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች እና የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮችም ጥልቅ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ የምክክር መርሆዎችን በማውጣት እና አጀንዳዎችን በማሰባሰብ ግልጽነት የተላበሰ መድረክ በማዘጋጀት ላከናወነው ስኬታማ ሥራ ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ፣ እንዲሁም ይህ ታሪካዊ ውይይት በሰላም እንዲጠናቀቅ ሌሊት እና ቀን ለተጉት የመከላከያ ሠራዊት እና መላው የጸጥታ ኃይሎች ልዩ እውቅና እና ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ #prosperity

ኢትዮጵያ መርከብ ናት፤ ሰዎች የሚሰቃዩት ግን መርከቡን አፍርሰው ጀልባ በመስራት ነው፤ ጀልባ ባህር አያቋርጥርም ፤ መርከብ ግን ባህር ያቋርጣል፤ ትልቁን ሩቅ የሚወስድህን አፍርሰህ ትንንሹን ብትሰራ
ኢትዮጵያ መርከብ ናት፤ ሰዎች የሚሰቃዩት ግን መርከቡን አፍርሰው ጀልባ በመስራት ነው፤ ጀልባ ባህር አያቋርጥርም ፤ መርከብ ግን ባህር ያቋርጣል፤ ትልቁን ሩቅ የሚወስድህን አፍርሰህ ትንንሹን ብትሰራ ሰፈር ትቀራለህ እንጂ አትሻገርም። - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) #prosperity

ዘላቂ ብሔራዊ መግባባት ላይ መድረስ👇 https://youtu.be/v6pxHb-Oahw?si=73NCRj7WKZYoQvGT

ወጣትነት ነገን ዛሬ የመገንባት አቅም፣ የሀገር ተረካቢነት መሰረት ነው! ወጣትነት የነገ ዕጣፈንታ የሚፃፍበት ወሳኝ የዕድሜ ክልል ነው፡፡ የወጣትነት ጊዜያቸውን በአግባቡ የተጠቀሙ ሁሉ በየተሰማሩበት ከስኬት ጫፍ መድረሳቸው አይቀሬ ጉዳይ ነው፡፡ በላቀ መታተር እና ትጋት ህይወታቸውን የሚለውጡ ወጣቶች ከቤተሰባቸውም ባሻገር የሀገር አለኝታዎች ናቸው። ወጣቶች የነገዋ ኢትዮጵያ ተረካቢ ናቸው፤ ነገን ዛሬ በመገንባቱ ሂደትም ሚናቸው የማይተካ ነው፡፡ ወጣቶች በእውቀት ተገንብተው፣ በመልካም ስነ ምግባር ተቀርፀው ሀገር መረከብ የሚያስችል አቅም እንዲያጎለብቱ ምቹ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል። በትምህርት ተደራሽነት ላይ በተደረገው ውጤታማ ርብርብ ለአብነትም በከተማችን በርካታ የማስፋፊያ እና የአዳዲስ ትምህርት ቤቶች ግንባታ ተከናውነዋል። ሁሉም ዜጋ የመማር መብቱ እንዲረጋገጥም የተማሪዎች ምገባ ፕሮግራም ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ ወጣቶች በአካል እንዲዳብሩ፣ አብሮነታቸውን እንዲያጠናክሩ ፣ አቅሙና ዝንባሌው ያላቸውም በተለያዩ የስፖርት መስኮች ሀገራችንን ማስጠራት እንዲችሉም የስፖርት ማዘውተሪያዎችን በየሰፈሩ ማስፋፋት ተችሏል፡፡ አስፋልት ላይ በመጫዎት ለተለያዩ አደጋዎች ሲጋለጡ የቆዩ፣ የውስጥ ክህሎታቸውን ማሳየት የሚችሉባቸውን አጋጣሚዎች ማግኘት ያልቻሉ ወጣቶች፣ አሁን ላይ ደረጃቸውን ጠብቀው በየአካባቢው በተገነቡ የስፖርት ማዘውተሪያዎች የሚገለገሉበት ሰፊ ዕድል ተፈጥሯል፡፡ ከተማችንን ውብ አበባ ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት የወጣቶችን የፈጠራ አቅምም እያሳደጉ በመሆናቸው በኪነ ጥበብ ዘርፍ ያላቸውን እምቅ ተሰጥዖ ማዳበር ችለዋል፡፡ በተፈጠሩት ምቹ ሁኔታዎች ሰርከስን ጨምሮ በተለያዩ ስፖርታዊ ውድድሮች ኢትዮጵያን ወክለው በዓለም አቀፍ መድረኮች የሚካፈሉ ታዳጊዎችና ወጣቶች ቁጥርም ከምንጊዜውም በላይ እየተበራከተ ይገኛል፡፡ የከተማችንን ተምሳሌትነት ለማጠናከርና ለማስፋት የሚደረገው ያልተቋረጠ ርብርብ በስራ ዕድል ፈጠራው እና በሌሎችም የወጣቶችን ፍትሀዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ መሆኑን መገንዘብ ይቻላል፡፡ በከተማችን እየተገነቡ የሚገኙ የዘላቂ ልማት ፅኑ መሰረቶች ወጣቶች ነገ የሚረከቧት ብቻም ሳትሆን ዛሬ የሚኖሩባት ኢትዮጵያ በአንፀባራቂና በተስፋ ሰጪ ዕድገት ውስጥ እንድትገኝ አስችለዋል። በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት #prosperity