cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Immigration And Citizenship Service (ICS Ethiopia)

This is the official channel of the FDRE Immigration and Citizenship Services

Show more
Advertising posts
181 136Subscribers
+45224 hours
+3 9697 days
+16 56230 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ደሴ፣ ጅግጅጋ፣ ድሬዳዋ፣ ሆሳዕና፣ ጋምቤላ፣ አዳማ እና ሀዋሳ ቅርንጫፍ ፓስፖርታችሁን የምትወስዱ ደንበኞቻችን ባመለከታችሁበት ኢሚግሬሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በሚያወጣው ኘሮግራም መሰረት በመገኘት ፓስፖርታችሁን መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን ወደ ተቋማችን ስትመጡ ኦንላይን ያመለከታችሁበትን ፕሪንት አውት ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት __ Telegram: https://t.me/ICS_Ethiopia Facebook: https://www.facebook.com/ICSEthiopia Twitter: https://twitter.com/ics_ethiopia TikTok: https://www.tiktok.com/@ics_ethiopia LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/icsethiopia YouTube: https://www.youtube.com/@Ics_Ethiopia Instagram: https://www.instagram.com/icsethiopia/
Show all...
👍 39👎 30
ቋሚ ኮሚቴው፤ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎትን የስራ አፈፃጸም ገመገመ ሚያዚያ 18 ቀን ፣ 2016 ዓ.ም፣ አዲስ አበባ የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የ9 ወራት የስራ አፈጻጸምን ገመገመ። የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ እፀገነት መንግስቱ ቋሚ ኮሚቴው የተቋሙን የስራ እንቅስቃሴን የመስክ ምልከታን ጨምሮ ሲከታተል እንደነበረና የዕቅድ አፈጻፀሙንም መገምገሙን ገልፀዋል። በዚህ ውይይትም በተቋሙ የስራ አፈፃጸም ዙሪያ የሚነሱ ግልጽነት የሚያስፈልጋቸው ጥያቄዎች ቀርበው ማብራሪያ እንደሚሰጥባቸውም ጠቁመዋል። የተቋሙ የ9 ወራት የስራ አፈጻፀም ሪፖርት የቀረበ ሲሆን፤ በተሰራው የሪፎርም ስራ አሰራርን የጣሱ ከፍተኛ አመራሮች ተጠያቂ የማድረግ፣ ለበርካታ ዜጎች አዲስ ፓስፖርት የመስጠትና የማደስ፣ ውዝፍ አገልግሎቶችን የማጠናቀቅ ፣ በህገወጥ መንገድ የሚኖሩ የውጭ ዜጎችን ወደህጋዊ መንገድ የማስገባት፣ አሰራሮችን ለማዘመን ከተለያዮ ባለድርሻና ተባባሪ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት አዳዲስ ቴክኖሎጅዎችን የማልማት እና ስለ ተቋሙ የግንዛቤና የገጽታ ግንባታ ስራዎች በዋናነት መሰራታቸው ተብራርተዋል። በሌላ በኩል የሲቪል ምዝገባን በተጠናከረ መንገድ ለማካሄድ በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ የጸጥታ ችግር መኖር፣ የተቋሙን ተልዕኮ ሊሸከም የሚችል አደረጃጀትና የሰው ሀይል ያለመሟላት፣ አገልግሎቱ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ያለመዘመን፣ ውዝፍ የአዲስ ፓስፖርትና እድሳት ጥያቄዎች መኖራቸው በሪፖርቱ በእጥረት ከተነሱት ውስጥ ተጠቃሽ ናቸው። የተቋሙን የ9 ወራት የዕቅድ አፈጻፀምን አስመልክቶ በቋሚ ኮሚቴው የተዘጋጁ ጥያቄዎች በውይይቱ ተሳታፊ ከሆኑ የምክር ቤት አባላት እና ባለድርሻ አካላት የቀረቡ ሲሆን፤ የተቋሙ አመራሮች በቀረበው ጥያቄ ላይ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በተጨማሪ ቋሚ ኮሚቴው በ9 ወር ሪፖርቱ እና በመስክ ምልከታ ያዮትን ግብረ መልስ በመስጠት በቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችን በማመላከት ውይይቱ ተጠናቋል። ይፋዊ ገጾቻችንን እና ቻናሎቻችንን ብቻ ለታማኝ አገልግሎቶች እና ማስታወቂያዎች ይጠቀሙ። __ Telegram: https://t.me/ICS_Ethiopia Facebook: https://www.facebook.com/ICSEthiopia Twitter: https://twitter.com/ics_ethiopia TikTok: https://www.tiktok.com/@ics_ethiopia LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/icsethiopia YouTube: https://www.youtube.com/@Ics_Ethiopia Instagram: https://www.instagram.com/icsethiopia/
Show all...
👍 364👎 101👏 60
ባለፉት ጥቂት ወራት የደንበኞችን ጥያቄ ሙሉ ለሙሉ ለመመለስ ከ1.1 ሚሊዮን በላይ የፓስፖርት ቡክሌት ወደሀገር በማስገባት በ6 ወራት ውስጥ ለአዲስ አበባ 260,371፣ በየአካባቢው ላሉ ቅ/ጽ/ቤቶች 269,358፣ በአስቸኳይ 35,394 እና በውጭ ለሚኖሩ ኢትዬጵያዊያን 81,416 በድምሩ 646,539 ፖስፖርት ታትሞ ማሰራጨት ተችሏል። አሁንም የፓስፖርት ጥያቄዎችን ያለምንም መዘግየት ለደንበኞች ለማድረስ ተግተን እየሰራን ነው። Over the past few months, we’ve taken significant strides to increase our efficiency and customer satisfaction. In just six months, we were able to print and distribute 260,371 passports in Addis Ababa, 269,358 in various regional officies, 35,394 to urgent cases, and 81,416 to Ethiopians residing abroad. The total number of passports printed and distributed during this time is 646,539. We are working hard to continue delivering passport requests to our customers without any delay. __ ይፋዊ ገጾቻችንን እና ቻናሎቻችንን ብቻ ለታማኝ አገልግሎቶች እና ማስታወቂያዎች ይጠቀሙ። TelegramFacebookTwitterTikTokLinkedInYouTubeInstagram
Show all...
👍 1143👎 306👏 190
👍 544👎 190👏 132
በ19/08/2016 ዓ.ም ፓስፓርት የምትወስዱ ደንበኞቻችን በ 7876 አጭር የፅሁፍ መልዕክት የላክን ሲሆን ቅዳሜ ሚያዚያ 19/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00-08፡00 ሰዓት ጎተራ በሚገኘው ኢሚግሬሽን ቢሮ በመገኘት ፓስፖርታችሁን መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን ወደ ተቋማችን ስትመጡ ኦንላይን ያመለከታችሁበትን ፕሪንት አውት ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት We've sent a text message to our customers scheduled for passport collection on April 27, 2024. If you've received a text message from us via 7876, please visit our Gotera Office in Addis Ababa on Sunday, April 21, 2024. Our offices will be open from 9:00 AM to 2:00 PM for passport collection. Remember to bring a printout of your online application form when you visit us. Immigration And Citizenship Service __ Telegram: https://t.me/ICS_Ethiopia Facebook: https://www.facebook.com/ICSEthiopia Twitter: https://twitter.com/ics_ethiopia TikTok: https://www.tiktok.com/@ics_ethiopia LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/icsethiopia YouTube: https://www.youtube.com/@Ics_Ethiopia Instagram: https://www.instagram.com/icsethiopia/
Show all...
👍 327👎 56👏 40
ለክቡራን ደንበኞቻችን ፓስፖርት ደርሷችሁ ለመውሰድ ወደተቋማችን ስትመጡ የተለያዩ ህገወጦች በለሊት መጣችሁ እንድትሰለፉ እና ለአላስፈላጊ ወጭ እንድትዳረጉ የተሳሳተ መረጃ እየሰጡ መሆኑን የተለያዩ ጥቆማዎች እየደረሱን ይገኛሉ፡፡ ስለሆነም በመንግስት ስራ ሰዓት ብቻ ወደተቋማችን በመምጣት መስተናገድ የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን ወደተቋማችን ስትመጡ በስም መነሻ ፊደላችሁ መሰረት የምትስተናገዱ ስለሆነ በለሊት መሰለፍ የማይጠበቅባችሁ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት __ Telegram: https://t.me/ICS_Ethiopia Facebook: https://www.facebook.com/ICSEthiopia Twitter: https://twitter.com/ics_ethiopia TikTok: https://www.tiktok.com/@ics_ethiopia LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/icsethiopia YouTube: https://www.youtube.com/@Ics_Ethiopia Instagram: https://www.instagram.com/icsethiopia/
Show all...
👍 1009👎 178👏 161
👍 1032👎 300👏 281
በ13/08/2016 ዓ.ም ፓስፓርት የምትወስዱ ደንበኞቻችን በ 7876 አጭር የፅሁፍ መልዕክት የላክን ሲሆን እሁድ ሚያዚያ 13/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00-06፡30 ሰዓት ጎተራ በሚገኘው ኢሚግሬሽን ቢሮ በመገኘት ፓስፖርታችሁን መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን ወደ ተቋማችን ስትመጡ ኦንላይን ያመለከታችሁበትን ፕሪንት አውት ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት We've sent a text message to our customers scheduled for passport collection on April 21, 2024. If you've received a text message from us via 7876, please visit our Gotera Office in Addis Ababa on Sunday, April 21, 2024. Our offices will be open from 9:00 AM to 12:30 AM for passport collection. Remember to bring a printout of your online application form when you visit us. Immigration And Citizenship Service __ Telegram: https://t.me/ICS_Ethiopia Facebook: https://www.facebook.com/ICSEthiopia Twitter: https://twitter.com/ics_ethiopia TikTok: https://www.tiktok.com/@ics_ethiopia LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/icsethiopia YouTube: https://www.youtube.com/@Ics_Ethiopia Instagram: https://www.instagram.com/icsethiopia/
Show all...
👍 476👎 72👏 66
በጅዳና አከባቢዋ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ከጉዞ ሰነድና ፓስፖርት ጋር ተያይዞ ያለባቸውን ችግር ለመቅረፍ ያለመ ውይይት ተካሄደ በኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት የተመራ ልዑክ በጅዳና አከባቢዋ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ከጉዞ ሰነድና ፓስፖርት ጋር ተያይዞ ያለባቸውን ችግር ለመፍታት ያለመ ውይይት ከተለያዩ ግዛቶች ከተውጣጡ የኢትዮጵያ ኮሚዩኒቲ አመራሮች ጋር አካሂዷል። በውይይቱም በጅዳ የኢፌዲሪ ቆንስል የሚሸፍናቸው ሰባት የተለያዩ ግዛቶች የተውጣጡ የኢትዮጵያ ዜጎች ተወካዮች ተሳትፈዋል። በዚህ ወቅትም ዜጎች ከፓስፖርትና ህጋዊ ሰነዶች ጋር በተያያዘ እያጋጠማቸው ያለውን ችግር በሚመለከት በጅዳ በኢትዮጵያ ቆንስል ጀነራልና በኮሚኒቲ ተወካዮች አማካኝነት በዝርዝር ቀርቦ ውይይት ተካሂዶባቸዋል። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተሯ ከዜጎቹ ጋር የነበረው ውይይት ያለውን ችግር በተጨባጭ ለመገንዘብ የረዳ መሆኑን በመጠቆም መንግስት ለዜጎች ጉዳይ ቅድሚያ የሚሰጥ በመሆኑ የተነሱ ችግሮችን በዘላቂነት ለመቅረፍ ተቋማቸው እየተገበረ ያለውን የሪፎርም ስራ አብራርተተዋል። ከፓስፖርት እድሳት ጋር ተያይዞ ያለውን ችግር ለመቅረፍ በተሰጠው ልዩ ትኩረት ከዚህ ቀደም ህጋዊ ሰነድ ኖሯቸው ላመለከቱ ዜጎች የእድሳት አገልግሎት መሰጠቱን ያስታወሱት ዋና ዳይሬክተሯ፣ በቀጣይ የዜግነት ማጣራት ስራ በተለየ ትኩረትና ጥንቃቄ መሰራት እንዳለበት ተናግረው ለዚህም የኮሚዩኒቲ አመራር ህገወጥ ደላሎችን በማጋለጥ፣ ዜጎች በህጋዊ መንገድ ብቻ እንዲስተናገዱ ህብረተሰቡን በማንቃት ረገድ ከተቋሙ ጋር በትብብር እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል። ከጉዞ ሰነድ ጋር በተያያዘ ያለ ችግርን ለመቅረፍ አሁን ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ ቢመጣም ካለው ፍላጎት ጋር የተጣጣመ ባለመሆኑ አቅርቦቱን የማሻሻል ስራ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። በዋና ዳይሬክተሯ የተመራው የልዑካን በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንሱል ጀነራል ከሆኑት ክቡር አምባሳደር ሙሉጌታ ከሊል ጋር በመሆን ወደ አገራቸው ለመመለስ የተለዩ ዜጎችን በእስር ቤት በመገኘት መጎብኘትና ማነጋገር ችሏል። __ Telegram: https://t.me/ICS_Ethiopia Facebook: https://www.facebook.com/ICSEthiopia Twitter: https://twitter.com/ics_ethiopia TikTok: https://www.tiktok.com/@ics_ethiopia LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/icsethiopia YouTube: https://www.youtube.com/@Ics_Ethiopia Instagram: https://www.instagram.com/icsethiopia/
Show all...
Immigration And Citizenship Service (ICS Ethiopia)

This is the official channel of the FDRE Immigration and Citizenship Services

👍 348👎 39👏 29