270
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
🛑➡️🛑➡️🛑➡️🛑➡️🛑➡️🛑➡️🛑➡️🛑
የጋራ ጥረት የጋራ ፍሬ ይሰጣል ‼️
➡️ የ2016 ዓ.ም የመጀመሪያው ተርም ውጤት ለወላጆች በመግለፅ ወላጆች በት/ት ጥራትና ስነምግባር ላይ ያላቸው ጉልህ ሚና በመረዳት በዕለቱ ተገኝታችሁ ከት/ቤቱ አስተዳደርና ከመምህራን ጋር በልጃችሁ ውጤትና ባህርይ ላይ በቁርጠኝነት እናግዛለን በርቱ ብላችሁ ስላበረታችሁን ከልብ እናመሰግናለን ።
➡️ ት/ቤቱም የአንደኛ ተርም ውጤት መነሻ በማድረግ ለሁለተኛው ተርም እያንዳንዱ ተማሪ በየት/ት አይነቱ አቅዶ / አቅዳ ውጤቱ/ቷ እንዲያሻሽል/ እንድታሻሽል በሚያደርገው ርብርብ
( የተማሪ - መ/ር - ወላጅ - ት/ቤት ) የአራትዮሽ ዕቅድ በጋራ ባቀድነው ልክ ልጆቻችን በመከታተልና በማገዝ ሀላፊነታችሁ እንድትወጡ አደራ እያልን ስለሰጣችሁን ድጋፍና መልካም ሀሳብ ከልብ እናመሰግናለን ‼️
🛑 ለት /ቤታችን ወላጆች/ አሳዳጊዎች በሙሉ ‼️
የ2016 ዓም የመጀመሪያው ሴሚስተር ውጤት በቀን 05/05/2016 ዓ.ም ( ዕሁድ ) ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ ተማሪዎችና ወላጆቻቸው በተገኙበት ከእያንዳንዱ መ/ራን ጋር በውጤት መሻሻልና በተማሪው ስነ -ምግባር ላይ ለመወያየት ኘሮግራም ስለሚኖረን / open house day ➡️ የት/ቤት እና የወላጆች ግንኙነት ቀን / በዕለቱና በሰዓቱ እንድትገኙ በጥብቅ እናሳስባለን ።
በዚህ ቀን መቅረት በፍፀም የተከለከለ ነው ሌሎች ኘሮግራሞቻችን ለሌላ ጊዜ በመተው በልጆቻችን ውጤትና ባህርይ ላይ በጋራ ለመመካከር ፈቃደኛ ሆነው ባይገኙ ሙሉ ሀላፊነቱ ለወላጅ የሚተው ስለሚሆን
እንዲሁም ዕርስዎ ለልጅዎ አርአያ በመሆን በዕለቱ ልጅዎን ይዘው ይገኙ ‼️
ማሳሰቢያ !!
::::::::::::::::
1. ውይይቱ የሚጀመረው 2:30 በመሆኑ ከ3:00 በኋላ የትኛውም አካል በባለፈው በወላጆች ስምምነት መሰረት የት/ቤቱ ቅጥር ግቢ በር ስለሚዘጋ በሰዓቱ 2:30 ተገኙ
2. በዕለቱ የማይገኝ ተማሪና ወላጅ በፍፁም በሌላ ቀን አናስተናግድም እንዲሁም ተማሪው ሰኞ ት/ቤት ገብቶ መማር አይችልም
3. ከአቅም በላይ የሆነ ችግር የገጠመዎት እንደሆነ ከቀጠሮው በፊት ት/ቤት መጥቶ ማስፈቀድ የወላጆች ሀላፊነት በመሆኑ ከቀጠሮው በኋላ የተፈጠረው ችግር መናገር ተቀባይነት
አይኖረውም ‼️
➡️ በነገው ሀገር ተረካቢ ትውልድ ላይ አዎንታዊ ዘር በጋራ እንዝራ ‼️
የከተማ አቀፍ ሞዴል ፈተና አፈታተን በት/ቤታችን በሰላማዊ መንገድ እየተከናወነ ይገኛል። ተማሪዎች የተማሩትን ት/ት ምን ያህል ደረጃ ላይ እንደሚገኙ እራሳቸውን እንዲያዩበት እና በሀገር አቀፍ ደረጃ የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ላይ በራስ መተማመን የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ታስቦ የተዘጋጀ በመሆኑ ከኩረጃ የፀዳ ትውልድ መፍጠር የት/ቤት ዋነኛ ስራው በመሆኑ የታይም ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ስለ ፈተናው ግንዛቤ ተፈጥሮላቸው ፈተናውን በዚህ መልክ እየተሰጠ መሆኑን ያደረግነው ምልከታ ነው ።
============================
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ቤተሰቦቻችን በሙሉ ‼️
============================
እንኳን ለጌታችን ለመድኀኒታችን ለእየሱስ ክርስቶስ የልደት በአል በሰላም አደረሳችሁ/ አደረሰን::
ይህን የገና በአል የሰላም እና የፍቅር እንዲሁም የአንድነት ያድርግልን::
ለመላው የት/ቤታችን ተማሪዎች ፣ መምህራን ፣ ወላጆች እና ማህበረሰብ በሙሉ ‼️
===========================
የ2016 ዓ.ም የመጀመሪያው መንፈቅ አመት የጥያቄና መልስ ውድድር በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ በአየር ጤና ክላስተር ስር ካሉ የግልና የመንግስት ት/ቤቶች የዕርስ በርስ የጥያቄና መልስ ውድድር ከ12ኛ ክፍል ተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ እፀገነት አንዳርጌ ሶስተኛ(3ኛ) በመውጣት እንዲሁም
ከ12ኛ ክፍልማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ተማሪ ቢታንያ ተክለአምላክ (ሶስተኛ) 3ኛ በመውጣት ሲያሸንፉ እንደ ተቋም ታይም 2ኛ ደረጃ 3ኛ በማግኘት የአሸናፊነት ደረጃ በመያዛችን የተሰማንን ደስታ እየገለፅን በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ / ደስ አለን ‼️
ለመላው የት/ቤታችን ተማሪዎች ፣ መምህራን ፣ ወላጆች እና ማህበረሰብ በሙሉ ‼️
የ2016 ዓ.ም የመጀመሪያው መንፈቅ አመት የጥያቄና መልስ ውድድር በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ካሉ የግልና የመንግስት ት/ቤቶች የዕርስ በርስ የጥያቄና መልስ ውድድር ከ9 ት/ቤቶች ከ6ኛ ክፍል አንደኛ በመውጣት እንዲሁም
ከ8ኛ ክፍል 1ኛ በመውጣት በግል በተማሪዎች 1ኛ እና በት/ቤትም 1ኛ በመውጣት በሁለቱም ክፍሎች ሁለት ዋንጫ በማግኘት የአሸናፊነት ደረጃን ይዘን ወረዳ ወክለን ለክፍለ ከተማ በመቅረባችን የተሰማንን ደስታ እየገለፅን በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ / ደስ አለን ‼️
በአዲስ መልክ የተዘጋጀው የክ/ጊዜ ድልድል ከሰኞ (15/04/2016) ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን ‼️
♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️
ለታይም ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች በሙሉ !!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
⏩⏩ ጥብቅ ማሳሰቢያ ‼️
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እንደሚታወቀው ት/ቤታችን የ2016 ዓ.ም አንደኛ ተርም ማጠቃለያ ፈተና እየተሰጠ ይገኛል ።
ፈተናው መምህራን ተማሪዎችን ያበቃል በሚል ጊዜያቸው ሰውተው ያዘጋጁትን ፈተና አንዳንድ ተማሪዎች ተጠቅመን እንደምንጥለው ሶፍት በት/ቤቱ ጥለው ሲወጡ ታዝበናል ። ስለዚህ ከሰኞ ጀምሮ እስከ አርብ የሚሰጡ ፈተናዎች በጥንቃቄ በመያዝ አርብ ሁሉንም የፈተና ወረቀት ይዞ ለት/ቤቱ ገቢ ማድረግ የተማሪዎች ግዴታ የሚሆን ይሆናል ይሄ ሳያደርግ የቀረ የትኛውም ተማሪ ሰኞ ዕለት ውጤት ሲመለስ የፈተናው ወረቀት ይዞ ካልተገኘ 10% ከሚያገኘው ተቀናሽ ስለሚሆን ወላጆች በአግባቡ ልጆቻችሁን እንድትከታተሉ እና የፈተና ወረቀታቸው መያዛቸውን እንድታረጋግጡ በአክብሮት እንገልፃለን ።
♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️
1.👉"የራስህን የህይወት ዕቅድ ካልቀረፅክ፣ ዕጣ ፈንታህ የሚሆነው በሌሎች እቅድ ውስጥ መኖር ይሆናል።"
#ጂም_ሮን
2.👉 "ህይወት በራሷ ፣ ምንም ያልተሳለባት ባዶ የሰዕል ሸራ ነች። ስንፈልግ መከራን፣ ስንፈልግ ሐሴትን የምንስልባት ባዶ ሸራ።"
#ኦሾ
3.👉“ለመጀመር ትልቅ መሆን አይጠበቅብህም ነገር ግን ትልቅ ለመሆን መጀመር አለብህ፡፡"
#ዚግ_ዚግላር
4. 👉“እያንዳንዱ ችግር፣ እያንዳንዱ ውድቀት፣ እያንዳንዱ የልብ ስብራት የእኩል ወይም የላቀ የጥቅም ዘርን በውስጡ ተሸክሟል።”
#ናፖሊዮን_ሂል
5. 👉"በህይወት ያለህን ነገር ከተመለከትክ ሁልጊዜ ብዙ ነገር ይኖርሃል፤ በህይወት የሌለህን ነገር ብትመለከት መቼም አይበቃህም"
#ኦፕራ_ዊንፍሬይ
6. 👉"በሚታይና በሚነካ ነገር ማመን በፍፁም እምነት አይደለም። ባልታየው ማመን ግን አሸናፊነትና መታደል ነው።"
#አብርሀም_ሊንከን
7.👉"እስከ ነጋ፣ እስከ መሸ፣ እስከ ተነፈስን እዚህ ህይወት ውስጥ እስካለን ድረስ ዘገዬ የሚባል ነገር የለም!"
#ዳግማዊት_ክፍለ
8. 👉"በህይወት ውስጥ ትልቁ ክብር ያለመውደቅ ሳይሆን በወደቅን ቁጥር መነሳት ላይ ነው።
#ኔልሰን_ማንደላ
9. 👉“ደስተኛ የሆነ ሕይወት ለመኖር ከፈለግክ ከሁኔታና ከሰዎች ጋር ሳይሆን ከአላማና እቅድህ ጋር ተጣበቅ።”
#አልበርት_አንስታይን
10.👉“ለመማር ፈቃደኛ ካልሆንክ ማንም ሊረዳህ አይችልም፣ ለመማር ፈቃደኛ ከሆንክ ማንም ሊያስቆምህ አይችልም”
#ዚግ_ዚግለር
መልካም ቀን🙏🙏🙏🙏
ምንጭ 👉👉👉ሶሻል ሚዲያ
Repost from Time Secondary school official channel
ከ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ወላጆች ጋር በተማሪዎች ውጤትና ባህርይ ፣ እያደረጉት ስላለው የፈተና ዝግጅት ፣ ስለ ተማሪዎች ትምህርት ፍላጎት እና በቀጣይ በወላጅ ፣ በመምህራን ፣ በተማሪዎች እና በት/ቤቱ የሚጠበቁ ተግባራቶች ጉዳይ ሰፊ ውይይት ተደርጎ በት/ቤቱ እና በተገኙ ወላጆች መግባባት በመፍጠር የጋራ ውጤት ለማምጣት በሀላፊነትና በቁርጠኝነት ለመወጣት በጋራ መቆም አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑን በመረዳት ውይይቱ በተሳካ ሁኔታ እንድናደርግ በውይይቱ ለተሳተፋችሁ ተማሪዎች ፣ መምህራንና ወላጆች/አሳዳጊዎች እንዲሁም ሀሳባችሁን ላካፈላችሁ መምህራን ፣ ወላጆችና ተማሪዎች በት/ቤቱ ስም እናመሰግናለን ‼️
ማሳሰቢያ !!
♦️♦️♦️♦️
ዛሬ ወላጅ ያላመጣችሁ ተማሪዎች ሰኞ ፈተና መፈተን የምትችሉት ከፈተና በፊት ከጠዋቱ 1:45 - 2:25 ድረስ ተማሪዎች ከወላጆቻቸው ጋር ቁጭ ብለው በውጤታቸውና ስነ ምግባር ጉዳይ በጋራ ተወያይቶ ከስምምነት ስንደርስ ብቻ ስለሆነ ተማሪዎች ይህንን ዕድል ሳትጠቀሙ ብትቀሩ ት/ቤቱ ተጠያቂ እንደማይሆን በተደጋጋሚ እንደገለፅነው ፈተና የማትፈተኑ መሆኑን እንገልፃለን ።
⏩ ወላጆች ት/ቤቱ በልጆቻችሁ መማር ማስተማርና ስነ ምግባር ጉዳይ ሲጠራችሁ ት/ቤት መገኘት ግዴታችሁ መሆኑን በመገንዘብ በዕለቱና በተጠቀሰው ሰዓት ብቻ እንድትነኙ በአክብሮት እንገልፃለን ‼️
