en
Feedback
Bible Study Fellowship ✝️

Bible Study Fellowship ✝️

Open in Telegram

“የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ፤...(ቆላ 3፥16)       📖 ተከታይ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት       📖 አንድ ቃል ለአንድ ቀን 📖 መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶች Contact us @Alexsimon19 💌 semonalex03@gmail.com https://t.me/BSF_group @Bible_study_Fellowshp_bot

Show more
353
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
December '23
December '23
+365
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
22 December0
21 December+1
20 December0
19 December0
18 December+1
17 December0
16 December+2
15 December0
14 December+1
13 December0
12 December+1
11 December+4
10 December+1
09 December0
08 December+7
07 December0
06 December+1
Channel Posts
አንድ ጊዜ አንድ ሰው "እንደምናውቀው መልክ ቀና አይደለም፤ የተማርክና የትልቅ ሰው ዘርም አይደለም። ሆኖም ሰው ሁሉ ይከተልሃል፤ ሰው ሊያይህና ሊከተለህ ይፈልጋል። ዓለም ሁሉ እንዲከተልህ ያደረገው ምንድን ነው? በማለት በፌዝና በንቀት መልክ ደጋግሞ ይጠይቀል። ቅዱስ ፍራንሲስኮም ይህንን ሲሰማ በጣም ደስ አለው፤ ዓይኖቹን ወደ ሰማይ አቀና፣ ለረጅም ጊዜ በተመስጦ ከቆየ በኋላ ተንበርክኮ እግዚአብሔርን አመሰገነ። ጥያቄዎን ወዳቀረበለት ወንድም ዘወር ብሎ፦ "ምክንያቱን ማወቅ ትፈልጋለህ? ምክንያቱማ እንዲህ እንዲሆን በልዑል አምላክ ተወስኖአል። ዓይኖቹ መልካሙንና ክፉውን ይመረምራሉ፤ ከኃጢአተኞች መካከል ከእኔ የባሰ ኃጢአተኛ፣ ከትንንሾች መካከልም ከእኔ የባሰ ታናሽ ማግኘት አልቻለም፤ ስለሆነም ይህን ታላቅ ሥራ እንድፈጽም መረጠኝ። የመረጠኝ ከእኔ የባሰ ዋጋ ቢስ ሰው በማጣቱ ነው። ታላላቆችና ስመ ጥር የሆኑትን ለማሳፈር መረጠኝ፤ የዓለምን ጉልበት፣ ውበትና እውቀት ባዶ ለማድረግም እኔን መረጠኝ"። በማለት መልሶለታል። ፦ከቅዱስ ፍራንሲስኮ ሕይወት

2
ተመርጫለሁ የሚል Comment 👇 Am chosen 🤩 @Bible_Study_Fellowshp @Bible_Study_Fellowshp
237
3
Contact us by👉 @Alexsimon19 Join us 👇 https://t.me/Bible_Study_Fellowshp https://t.me/Bible_Study_Fellowshp
Contact us by👉 @Alexsimon19 Join us 👇 https://t.me/Bible_Study_Fellowshp https://t.me/Bible_Study_Fellowshp
1 028
4
ከአዲስ ኪዳን ከወንጌላት መጽሐፍት የቱን ቢያነቡ ይመርጣሉ? ሰኞ በ7/03/16 የሚጀምርነው!
491
5
#HolyBible #TheWordOfGOD አንብበው የተገረሙበትን😲 በ Comment ያስቀምጡ👇 ጠቅሞኛል ካሉ Share https://t.me/BSF_group https://t.me/Bible_Study_Fellowshp
1 926
6
🕊🕊የመንፈስ ቅዱስ ሥራ 🕊🕊 መጽሐፍ ቅዱስን ስናነብ ቅዱሳት መጻሕፍት የተጻፉት የእግዚአብሔር መንፈስ ባደረባቸው ሰዎች እንደ ሆነ ክርስቲያኖች እናምናለን፤ (2ጴጥ. 1፥21) የመጽሐፍ ቅዱስ ጸሓፊዎች የዘመኑ ቴክኖሎጂ እንደ ፈጠረው፥ ሰውን ተክቶ እንደሚሠራ ሮቦት አልነበሩም:፡ እግዚአብሔር መልእክቱን እንደ ፈለገ የሚያስተላልፍባቸው የጽሕፈት መኪናም አልነበሩም፡: ጸሓፊዎቹ አስተዋዮችና አዋቂዎች ከመሆናቸውም በላይ፥ መጻሕፍቱን ሲጽፉ የሚያስተላልፏቸው መልእክቶች ነበሯቸው፡፡ ይህን ያደረጉት በእግዚአብሔር መንፈስ ምሪት ስለ ነበር ቅዱሳት መጻሕፍቱ የእግዚአብሔር ማኅተምና ይሁንታ በውስጣቸው ይታያል፤ በመሆኑም ለማስተማር፥ ለመገሠጽ፥ ለማቅናት፥ በጽድቅም መንገድ ለመምከር ሥልጣኑ አላቸው፤ (2ጢሞ: 3፥17) ጳውሎስ መልእክቱን ለቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያን ሲጽፍ ክርስቲያኖች በውስጣቸው የእግዚአብሔር መንፈስ ስላላቸው እግዚአብሔርንና ዕቅዱን የማወቅ ብቃት አላቸው ብሏል፤ (1ቆሮ 2፥10-13)፡፡ እንዲህ ሲባልሞ ክርስቲያኖች ከሆንን በኋላ መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ አያስፈልገንም ማለት አይደለም። በአንጻሩ እግዚአብሔር መጽሐፍ ቅዱስን ለእኛ የሰጠበት ምክንያት፥ በውስጣችን ያደረው መንፈስ ቅዱስ በሕይወታችን የሚፈጽመው ተግባር፥ የሚያከናውነው ታሪክና ሥራ መኖሩን በትምህርቱ አማካይነት ለመግለጽ፥ መጽሐፍ ቅዱስ መጠናት እንደሌለበት ለማሳየት ሳይሆን፥ ትርጐም ያለው መሆኑን ለማስረዳት ነው፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ ቅዱሳት መጻሕፍት እንዲጻፉ ምሪትን የሰጠው ይኸው በውስጣችን ያደረው መንፈስ ቅዱስ ነው። በመሆኑም መንፈስ ቅዱስ፥ ቅዱሳት መጻሕፍት እንዲጻፉ ምሪት የሰጠበትን ሁኔታ መማር ከቻልን፥ ዛሬም መንፈስ ቅዱስ እንዴት በውስጣችን እንደሚሠራ ግንዛቤ ለማግኘት የተመቻች ዕድል አለን፡፡ ስለዚህ ቅዱሳት መጻሕፍት በራሳቸው ኀይል አላቸው፤ ሕያዋንና የሚሠሩ ናቸው (ዕብ 4፥12)፡፡ ሐሳባቸውን ከተገነዘብን፥ ትርኮጐሞቻቸውም እንደዚሁ በሕይወታችን ውስጥ ይሠራሉ። Join our channel 👇 https://t.me/Bible_Study_Fellowshp
1 255
7
🗞ማንኛውም ሰው ሊገነዘበው ይችላል መጽሐፍ ቅዱስን ልዩ የሚያደርገው አስደናቂው ነገር አያሌ ምሁራንና ሊቃውንት ስለ መጽሐፍ ቅዱስ መታወቅ የሚገባውን ሁሉ ማወቅ ሲሳናቸው፥ በአንጻሩ ያልተማሩ ሰዎች ሊገነዘቡት መቻላቸው ነው። ጥንት ቅዱሳት መጻሕፍት በተጻፉበት ጊዜ የነበሩት የመጀመሪያዎቹ አንባቢዎች፥ ዛሬ በከፍተኛ ደረጃ ከተማሩት ሰዎች ጋር ሲመዛዘኑ በትምህርት ደረጃቸው ከፍተኛ እንዳልነበሩ ልናስታውስ ይገባናል:፡ እንዲያውም የአዲስ ኪዳን መልእክተኞች የተላኩላቸው አብዛኛዎቹ ሰዎች ከዚያ በፊት ከቤተ ክርስቲያን ጋር ትውውቅ የሌላቸው ነበሩ: ይሁን እንጂ እነዚያ ሰዎች የተጻፏትን መልእክቶች ሐሳብ ይገነዘቡ ነበር፡፡ ዛሬም አንዳንድ ክርስቲያኖች መጽሐፍ ቅዱስን እንዳይገነዘቡት ከሚያደርጓቸው ምክንያቶች አንዱ መጽሐፍ ቅዱስን በተሳሳተ መንገድ ከማንበባቸው የተነሣ ሲሆን ሌላው ምክንያት ደግሞ የመጽሐፍ ቅዱስ አስተማሪዎች -በተሳሳተ ሁኔታ በማስተማር ተመሳሳይ ስሕተትን ስለሚፈጽሙ ነው። መጽሐፍ ቅዱስን በተሻለ ሁኔታ ለማወቅ እንደ አንባብያንም፥ እንደ አስተማሪም ለረጅም ጊዜ ተተክሎ የቆየውን አጐል ልማድ መለወጥ ያስፈልገናል፡፡
2 276
8
💥 ልዩ መጽሐፍ፥ ግን ደግሞ ቀላል መጽሐፍ ቅዱስን በምናነብበት ጊዜ፥ የምናነበው መጽሐፍ ተራ መጽሐፍ አለመሆኑን ወዲያውት እንገነዘባለን፡፡ ክርስቲያኖች ከሆንን መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈ የእግዚአብሔር ቃል፥ ስለ እግዚአብሔር ማንነት የሚያሳውቀን፥ እግዚአብሔር ለፈጠረው ሕዝብ ምን ምን ተግባራትን እንደ ፈጸመ የሚያስገነዝበን መጽሐፍ መሆኑን ዐውቀን እናነበዋለን:፡ መጽሐፍ ቅዱስ ስዎች ከእግዚአብሔርና ከእርስ በርሳቸው ጋር እንዴት መኖር እንዳለባቸው ያስተምረናል፡፡ - እግዚአብሔር በህልውናው ዘላለማዊ ነው፥ ስለሆነም ማንነቱንና ባሕርዩን በቁሳዊው ዓለም ውስጥ በምናያቸው ነገሮች ልንመዝነው አንችልም፡፡ ሰብአዊ አካል የሌለውን፥ ለዕውቀቱና ለጥበቡ ድንበር የማይደረግለትን፥ ዘላለማዊ ባሕርይ ያለውን አምላክ ሰብአዊ መግለጫ አጥጋቢ ሆኖ ሊገልጸው ከቶ አይችልም፡፡ እንዲህ ሲባልሞ፥ መጽሐፍ ቅዱስ ከእኛ ግንዛቤ በላይ ነው ማለትም አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ውስን የሆነው ዓለም ከሚገልጸው በላይ ታላቅ ቢሆንም፥ ውስን በሆነው ዓለም ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ደግሞ በብዙም ሆነ በጥቂቱ ያውቁታል፡፡ ታዳጊ ልጆች ወላጆቻቸውን የሚያሳስበውን ግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ተግባር አይገነዘቡትም፤ ሆኖም - ከወላጆቻቸው ጋር ባላቸው ግንኙነት ደስተኞች ናቸው፡፡ ወላጆቻቸውም ከልጆቻቸው ጋር ኅብረት ያደርጋሉ፡፡ እኛም ከእግዚአብሔር ጋር ያለንን ኅብረት ስናጠነክር ራሱ ይናገረናል፤ እንድንገነዘበውም ይረዳናል፡፡ ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ ለእኛ ከመጻሕፍት ሁሉ በላይ የላቀ መጽሐፍ፥ የእግዚአብሔር ቃል፥ ነው፤ አስቸጋሪ መጽሐፍም አይደለም፡: እግዚአብሔር ሲናገር፥ ማንኛውም ሰው በሚገባው መንገድ ይናገራል፡፡ ሰዎች መጽሐፍ ቅዱስን እንዳይገነዘቡት ከሚያደርጓቸው ምክንያቶች አንዱ ይህን ሐቅ አለማጤናቸው ነው፡፥ እነርሱ እንደሚገምቱት አንድ መጽሐፍ የእግዚአብሔር ቃል መሆኑን ራሱ ከመሰከረ፥ ትርጐሙ ጥልቅ ስለ ሆነ፥ ሰዎች ሊገባቸው አይችልም ይላሉ፡፡ እንዲያውም አንዳንዶቹ መጽሐፍ ቅዱስ መልእክቱን ቀላል በሆነ ቋንቋ ካቀረበ ክብሩ እንደ ጎደለ ይቄጥሩታል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስን በምናነብበት ጊዜ የሚያቀርባቸውን ታላላቅ እውነቶችና እነዚህን እውነቶች እንዴት እንደሚገልጻቸው ደኅና አድርገን ማስተዋል አለብን፡: ምናልባት ስብአዊ አዕምሯችን የተገለጠውን እውነት ሙሉ ትርገሙን በሚገባ ለመገንዘብ ዐቅም ላይኖረው ይችላል (ለምሳሌ ዘላለማዊውና ያልተፈጠረው የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ፥ ከእግዚአብሔር ፍጥረታት እንደ አንዱ ሆኖ በዚህ ዓለም ውስጥ ተወለደ)፤ ይህ ሁኔታ ስለተገለጠው እውነት እንዳናውቅ ዕንቅፋት ሊሆንብን አይችልም፤ (ይህ- የተገለጠው እውነት - የኢየሱስ ልደት ነው)፡፡ በተመሳሳይ መንገድ ቅዱስና ጻድቅ የሆነው አምላክ አንዴት አድርጎ ኀጢአተኞችን በማጽደቅ ወደ እርሱ እንደሚቀበላቸው ምሥጢሩን ልንገነዘብ አንችልም የሚል ስሜት አለብን፤ የመጽሐፍ ቅዱስ ግን ለዚህ ጥያቄ የሚሰጠው መልስ ትክክል፥ የማያወላውልና ሊገባም የሚችል እውነት ነው፡፡ (ማለትም የኢየሰስ ሞት እግዚአብሔር ይህን እንዲፈጽም አስችሉሎታል)፡፡
1 190
9
@Bible_Study_Fellowshp Bible_Study_Fellowshp Bible_Study_Fellowshp
@Bible_Study_Fellowshp Bible_Study_Fellowshp Bible_Study_Fellowshp
1 665
10
👇JOIN US 👇 @Bible_Study_Fellowshp @Bible_Study_Fellowshp @Bible_Study_Fellowshp @Bible_Study_Fellowshp
👇JOIN US 👇 @Bible_Study_Fellowshp @Bible_Study_Fellowshp @Bible_Study_Fellowshp @Bible_Study_Fellowshp
1 785
11
የአዲስ ኪዳን ካነን የአዲስ ኪዳን መጻህፍት ተጽፈው የወጡት ከ50- 100 ዓ.ም. መካከል እንደሆነ ይታመናል። ሁሉም ተጠቃለው በአንድ ጥራዝ እስኪታወቁ ግን ረዘም ያሉ ዓመታት ወስዶባቸዋል። ከሐዋርያት ዘመን በኋላ በስማቸው አያሌ መጻህፍት ተጽፈው ነበር። ቀደም ሲል የአዲስ ኪዳን መጻህፍት በየአብያተ ክርስቲያኑ እየተነበቡ ይዞሩ ስለነበር፤ ሐሳውያን ትምህርታቸውን ለማስፋፋት አያሌ መጻህፍትን ያወጡ ነበር፡፡ ከዚህም የተነሳ የትክክለኞቹን መጻህፍቶች ዝርዝር ለመወሰን ማከራከሩ አልቀረም፡፡ ለመጨረሻ ጊዜ ውሳኔው የጸናው በ325 ዓ.ም. በኒቅያ ጉባዔና በ397 ዓ.ም. በካርቴጅ ጉባዔ ላይ ነው፡ የካርቴጂ ጉባዔ የመጻህፍቱን አቀማመጥ ቅደም ተከቀልም የወሰነ ነው። 2ኛ ጴጥ. 3፤16 የመሳሰሉት ጥቅሶች እንደሚጠቁሙን የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ከብሉይ ኪዳን መጻህፍት ሥልጣን እኩል መቆጠር የጀመሩት ከሐዋርያት ዘመን ጀምሮ ነው። በጥንት የቤተ ክርስቲያን አባቶች ጽሑፎች ትምህርትና በሌሎች ጸሐፊዎች ዘገባ እንደሚታየው ወንጌላትና መልዕክታት ቀደም ሲል ጀምሮ በአብያተ ክርስቲያናት ሕይውት ሥር መስደዳቸውን እንረዳለን፡፡ (ቅዱሳት መጻሕፍት) የሚለው ስያሜ ቀድሞ ለብሉይ ኪዳን ብቻ የተሰጠ ነበር። (ሮሜ 1፤2) ከ2ኛው መቶ ዓመት በኋላ ግን የአዲስ ኪዳንም መጠሪያ ሆነ፡፡ የመጻሕፍቱ ካነን እንደተወሰነ (የሐዋርያት የሃይማኖት መግለጨ) የሚባለውም ጽሁፍ ወጣ፡፡ ጽሁፉ በሐዋርያት ተጽፎ ሳይሆን ትምህርታቸውንና እምነታቸውን የያዘ አስተዋጸዖ ነው ተብሎ ስለሚታመንና ለአዲስ አማንያን ማስተማሪያ ጠቃሚነት ስላለው በሁሉም ዘንድ ተቀባይነት ሊያገኝ ችሏል። የምዕራፎችና ቁጥሮች መከፋፈል ጥንት አይሁድ ለጥናትና ለንባብ በሚያመች ሁኔታ ብሉይ ኪዳንን ይከፋፈሉ ነበር። ቅዱሳት መጻህፍት ሲጻፋ በምፅራፍና በቁጥር የተከፋፈሉ አልነበሩም፡፡ ስለሆነም የጥንት አባቶች ይህንኑ ዓላማ የተሳካ ለማድረግ ዛሬ እንደምናየው ለጥናትና ለማስታወስ አመቺ በሆነ መንገድ ከፋፍለው አስተላልፈውልናል። በምዕራፎች የከፋፈለልን Stephen Langton  ከ የተባለ የካንተር በሪ ሊቀ ጳጳስ የነበረ ሰው በ13ኛው ክ.ዘ. ላይ ነው፡፡ እንዲሁም Robert Stephanus የተባለ ፈረንሳዊ ሰው በቁጥሮች ከፋፍሎ በ1551 ላይ አሳተመው።
1 432
12
የአዋልድ መጻሕፍት አስቀድሞ በአይሁድ ዘንድ ስለ መጻሕፍቱ ቁጥር ምንም ጥርጥር አልነበረም፡፡ ጌታም ሆነ ሐዋርያት በትምህርታቸው አንዲህ ዐይነት ችግር አላነሱም ነበር። (ማቴ. 21፡42፤ ማር 14፡49፤ ሉቃ. 24፡32፤ ሐሥ. 10፡24፤ 15፡14) እነዚህ መጻሕፍት በጥንቱ የዕብራይስጥ ትርጉም አይገኙም፡፡ ነገር ግን ተበታትነው ይኖሩ በነበሩ የግሪክ ተናጋሪ አይሁድ እንደተጻፈ ይገመታል። መጻህፍቱ የተዛባ የታሪክ አቀራረብ የሐሳብ መቃረንም አላቸው፡፡ እነዚህን መጻህፍት ዛሬም ቢሆን አይሁድ አይቀበሏቸውም፡፡ እነዚህን መጻሕፍት በ363 እ.አ.አ. በሎዶቅያ የተደረገው ጉባዔ አውግዞአቸው ..... አዋልድ (አፖክሪፋ) የተሰወረ ማለት ሲሆን ይህን ስያሜ የሰጣቸው ቅዱስ ጀሮም ነው፡፡ ከሌሎች ቅዱሳት መጻህፍት ጋር በአንድ ጥራዝ ዕድል ያገኙትም በ3ኛው ዓ.ዓ. በሴፕቱጀንት እና በ 420 ዓ.ም. (ቩልጋታ) በሚባለው ላቲን ትርጉም ነው፡፡ ይሁንና የካቶሊካውያን ጉባኤ በ1546 ትሬንት ላይ ባደረገው ስብሰባ ከአዋልድ ሰባቱንና በአሉት ላይ ተጨማሪ ምዕራፎችንና ቁጥሮችን ብቻ ከሌሎች ጋር እንዲቆጠሩ በመወሰኑ በእነሱ ካነን የመጻህፍቱ ቁጥር 73 ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኦድርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ ሌሎች የኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ከሚቀበሏቸው 79 በላይ ሄኖክና ኩፋሌ የሚባሉትን በመጨመር (በሲኖዶስ ውሳኔ ባይሆንም) የምትገለገልባቸው 81 መጻህፍት ናቸው። ከካቶሊካዊት ከሌሎች የምስራቅ ጥንታውያን አብያተ ክርስቲያናትና ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሀዶ ቤተ ክርስቲያን በቀር የፕሮቴስታንት አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ስድሳ ስድስቱን ብቻ ይቀበላሉ፡፡ ፕሮቴስታንቶች ከአዋልድ መፃህፍት መካከል አንዳንዶቹ እንደ መልካም ሃይማኖታዊ ሥነ ጸሁፍ ሊቆጠሩ ቢችሉም ከቅዱሳት መጻህፍት እኩል ሊታዩ አይችሉም በማለት አይቀበሏቸውም።
1 335
13
የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ዝርዝር (ካነገ) ካነን “እውነተኛና ትክክለኛ ናቸው” በማለት ቤተ ክርስቲያን እንደ እግዚአብሔር ቃል የተቀበለቻቸው የቅዱሳት መጻሕፍት ዝርዝር ነው። ስለዚህ ቅዱሳት መጻሕፍት ትክክለኛ ናቸው ተብለው በመመረጥ ተቀባይነት አግኝተው ባንድ ጥራዝ የተወሰኑት መጻሕፍት በእንግሊዘኛ ካነን ይባላሉ፡፡ ካነን ማለት በግሪክ መለኪያ፣ ዘንግ (መመዘኛ) ማለት ነው፡፡ እንደምናውቀው የአይሁድ መጽሐፍት እሰከ ዛሬ ብሉይ ኪዳን ብቻ ነው። እነርሱ የተቀበሏቸው መጻሕፍት 39 ብቻ እንደ ሆኑ የታወቀው ታሪክ ጻሕፊያቸው ዮሲፈስ ይገልጻል። ከላይ እንደተገለጠው በአይሁድ ካነን 39ኙ የብሉይ ኪዳን መጻህፍት ብቻ ይገኛሉ፡፡ ካነናቸውም የተወሰነው ከክርስቶስ ልደት በፊት ሲሆን፤ በ400ዎቹ የዝምታ ዓመታት ውስጥ እንደተጻፋ የሚገመቱ ዛሬ “አዋልድ” የምንላቸው መጻሕፍት መባዛትና የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት መፈጠር ስላሳሰባቸው አደገና በ90 ዓ.ም. ገደማ ጉባኤ አድርገው የቀድሞዎቹን አጽንተው አዋልዱን እንዳወገዙ ይተረካል። ይሁንና አዋልዱን በካነናቸው የጨመሩ በስደት የሚኖሩ የነበሩ የአሌክሳንደሪያዎቹ አይሁድ እንጂ ዋኖቹ አይሁድ ተቀብለዋቸው አያውቁም። በዚህም መሠረት የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት 39፤ የአዲስ ኪዳን 27፤ ትክክለኛ የእግዚአብሔር ቃል ናቸው በመባል በፕሮቴስታንት አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ተቀባይነት አግኝተዋል።
455
14
ቅዱሳት መጻሕፍት ወደ እኛ እገዴት ደረሱ? 🤔 ይህ ጽሑፍ የተዘጋጀው ቅዱሳት መጻሕፍትን ማን ጻፋቸው? እንዴት ተጻፋ? መቼ? የት? ለምን? የሚሉትን የቲኦሎጂ ጥያቄዎች ለመመለስ ሳይሆን በመሠረቃዊዎቹ
ቅዱሳት መጻሕፍት ወደ እኛ እገዴት ደረሱ? 🤔 ይህ ጽሑፍ የተዘጋጀው ቅዱሳት መጻሕፍትን ማን ጻፋቸው? እንዴት ተጻፋ? መቼ? የት? ለምን? የሚሉትን የቲኦሎጂ ጥያቄዎች ለመመለስ ሳይሆን በመሠረቃዊዎቹ ቋንቋዎች ከተጻፋ በኋላ ይህን ሁሉ ዘመን አንዴት ኖሩ? ወደ እኛስ አንዴት ደረሱ? የሚሉትን ታሪካዊ ጥያቄዎች ለመመለስ ያህል ነው። በሌላም በኩል የቅዱሳት መጻሕፍት አመጣጥ በጣም ሰፊ ታሪክ በመሆኑ በዚህ አጭር ጸሑፍ በዝርዝር መግለጽ የማይቻል በመሆኑ ለመግቢያ ያሀል ብቻ ባጭር ባጭሩ ተጠቅሷል።
1 367
15
💥ስለ መጽሐፍ ቅዱስ አስደናቂ እውነታዎች 🔸መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው በሦስት ቋንቋዎች ማለትም በዕብራይስጥ፣ በአረማይክ እና አዲስ ኪዳን በግሪክ ነው። 🔸 መጽሐፍ ቅዱስ በታሪክ ውስጥ ከ5 ቢሊዮን በላይ ቅጂዎች የተሸጠ መጽሐፍ ነው። 🔸 ሙሉው መጽሐፍ ቅዱስ ወደ 700 የተለያዩ ቋንቋዎች ተተርጉሟል አዲስ ኪዳን በ1,548 ቋንቋዎች! 🔸 መላው የኪንግ ጀምስ መጽሐፍ ቅዱስ 788,258 ቃላት እና 1,189 ምዕራፎች አሉት። 🔸 በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በአጠቃላይ 31,173 ቁጥሮች (እንደ ትርጉሙ) 23,214 ቁጥሮች በብሉይ ኪዳን ይገኛሉ። 7959 ቁጥሮች በአዲስ ኪዳን ውስጥ አሉ። 🔸 በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በአጠቃላይ 185 መዝሙሮች 🔸 የመጽሐፍ ቅዱስ ረጅሙ ምዕራፍ መዝሙር 119 ሲሆን 176 ቁጥሮች አሉት። 🔸 የመጽሐፍ ቅዱስ ረጅሙ ቁጥር በአስቴር 8:9 ላይ ይገኛል። 🔸 በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በጣም አጭሩ ምዕራፍ መዝሙር 117 ሲሆን 2 ቁጥሮች አሉት። 🔸 በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በጣም አጭር የሆነው መጽሐፍ 3ኛ ዮሐንስ በድምሩ 219 ቃላት። በብሉይ ኪዳን፣ አጭር የሆነው መጽሐፍ የአብድዩ እጅግ አስደናቂ በሆነ 440 ቃላት። 🔸 በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በጣም አጭሩ ጥቅስ ዮሐንስ 11፡35 ነው፣ እሱም “ኢየሱስ አለቀሰ” ይላል። 🔸 በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ረጅሙ ቃል በኢሳይያስ 8፡1 እና 8፡3 ላይ የሚገኘው “ማህርሻላልሃሽባዝ” ነው። የዕብራይስጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም "ምርኮ ፈጠነ , ብዝበዛ ቸኮለ ነው." 🔸 የመጽሐፍ ቅዱስ ትክክለኛው ማእከል የሆነው ጥቅስ መዝሙረ ዳዊት 118፡8 🔸 በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የአምላክን ስም ፈጽሞ ያልተናገረው ብቸኛው መጽሐፍ የአስቴር መጽሐፍ ነው። በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ያሉት ሁሉም መጻሕፍት እግዚአብሔርን ይጠቅሳሉ። 🔸 ሙሴ የመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት የሆነው ፔንታቱክ(ኦሪት) በመባል የሚታወቁትን የመጀመሪያዎቹን አምስት የመጽሐፍ ቅዱስ መጻሕፍት ጻፈ። 🔸 ብዙ ሊቃውንት ኢዮብ በ1500 ዓ.ዓ. አካባቢ ባልታወቀ እስራኤላዊ የተጻፈው የመጽሐፍ ቅዱስ ጥንታዊ መጽሐፍ እንደሆነ ይስማማሉ። 🔸 የአዲስ ኪዳን 14 መጻሕፍትን (ከግማሹ በላይ) የጻፈው ሐዋርያው ​​ጳውሎስ። 🔸 እንዳንፈራ የሚነግሩን በአጠቃላይ 365 ጥቅሶች አሉ! በዓመቱ ውስጥ ለእያንዳንዱ ቀን አንድ! 🔸 በ40 ደራሲዎች፣ መጽሐፍ ቅዱስ በ3 አህጉራት ተጽፏል! • እስያ • አፍሪካ • አውሮፓ 🔸 በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመጨረሻው መጨረሻ ቃል በመፅሐፍ ውስጥ "አሜን" ነው ራዕይ(22:21). አሜን ማለት "እንዲህ ይሁን" ማለት ነው። @Bible_Study_Fellowshp @Bible_Study_Fellowshp
2 109
16
No text...
395
17
....ከላይ የቀጠለ የጻሐፊዎቹ ብዛት የብሉይ ኪዳን 40፤ የአዲስ ኪዳን 8 ያህል ነው፡፡ መጸሐፍቱ የተጻፋበት ዘመን ብሉይ ኪዳን ከ1400-400 ዓ.ዓ. ሲሆን አዲስ ኪዳን ከ45-96 ዓ.ም. ባሉት ዓመታት ውስጥ ነው።ደራሲዎቹ ነቢያትን፣ ነገሥታትን፣ ካህናትን፣ ገጣሚዎችን፣ ሐዋርያትን እና የታሪክ ጸሐፍትን ያካትታሉ። ይህን በሚያህል የተራራቀ ዘመን መካከል በማይተዋወቁ ስዎች ተጽፈው አንድ ዓላማና መልአክት መያዛቸው መጸሐፍ ቅዱስን አውነተኛ ከሚያደርጉት ማስረጃዎች አንዱ ነው፡፡
406
18
፨ መጽሃፍ ቅዱስ ምንድነው? መጽሐፍ ቅዱስ የሚለው ቃል ከግሪኩ ቢብልያ ማለትም "መጸሐፍት" ከሚለው ቃል የተገኝ ነው። ይህ ስም ቀስ በቀስ እየተለመደ መጥቶ በተለይ ከ2ኛው መቶ ዓመት ወዲህ ቋሚ የቅ
፨ መጽሃፍ ቅዱስ ምንድነው? መጽሐፍ ቅዱስ የሚለው ቃል ከግሪኩ ቢብልያ ማለትም "መጸሐፍት" ከሚለው ቃል የተገኝ ነው። ይህ ስም ቀስ በቀስ እየተለመደ መጥቶ በተለይ ከ2ኛው መቶ ዓመት ወዲህ ቋሚ የቅዱሳት መጻሕፍት መጠሪያ ሆነ። “መጸሐፍ ቅዱስ” ስንል በአግዚአብሔር ዕቅድ ትውልድ ሁሉ እንዲመራበት በመጸሐፍ ስፍሮ የተላለፈልን የእግዚአብሔር ቃል ማለታችን ነው። (ሮሜ 14፡4፣ 1 ቆሮ 10፡6-11፣ 1 ጢሞ 3፡14-15) በዚህ ዓይነት ብሉይና ሐዲስ ተብለው የሚጠሩትን ቅዱሳት መጻሕፍት ባንድ ላይ “መጽሐፍ ቅዱስ” እንላቸዋለን”። በሌሎች የሃይማኖት ክፍሎችም "ቅዱሳት" ተብለው የሚጠሩ መጻሕፍት አሉ። ለክርስቲያኖች ግን አንድ ብቻ እውነተኛ “ቅዱስ” የሕይወት መጸሐፍ አለ። እርግጥ ነው መጽሐፍ ቅዱስ “የተሳሳተ መጽሐፍ ነው” በማለት በኢአማንያን ብዙ ነቀፋና ጥርጥር የተሰነዘረበት አስከ ዛሬም የሚስነዘርበት መጽሐፍ ነው። ይሁንና መጽሐፍ ቅዱስ እውነተኛና ትክክለኛ መጽሐፍ ለመሆኑ ዘመናዊ ሳይንስ እንኳ እየመስከረለት ነው። በተለይም በየጊዜው የሚገኙ የአርኪኦሎጂ ታሪካዊ ማስረጃዎች ዋና ምስክር ሆነዋል። መጽሐፍ ቅዱስ በእግዚአብሔር መንፈስ የተጻፈ ሕያው ቃል ነው፤ (ት.ኤር 35፡21፤ ት.ሕዝ 1፡3፤ 2ጢሞ 3፡16-17፤ 2 ጴጥ 1፡21) በዚህ ዓይነት ምንም ጸሐፊዎቹ ከሰው ያልተለዩ ባይሆንም መንፈስ ቅዱስ በሰጣቸው መገለጥ እየተመሩ መጸሐፍትን ጽፈዋል። • መጽሐፍ ቅዱስ በሁለት ዋና ዋና ክፍሎች የተከፈለ ነው፡ ብሉይ ኪዳን እና አዲስ ኪዳን። ብሉይ ኪዳን ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በፊት የተጻፉ 39 መጻሕፍትን ሲይዝ በአዲስ ኪዳን ደግሞ ከሞቱና ከተነሣ በኋላ የተጻፉ 27 መጻሕፍትን ይዟል።
661