Addisu Derebe
Open in Telegram
8 649
Subscribers
+424 hours
-77 days
-7830 days
Posts Archive
8 649
የጉባኤ ማጠቃለያ እና የአቋም መግለጫ፡ "የልሂቃን ሚና በአማራ ህልውና"
August 29 እና 30, 2026 በዙም (Zoom) ሲካሄድ የቆየውና በአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ላይ በጥልቀት የመከረው ታላቁ የውይይት ጉባኤ በስኬት ተጠናቋል።
የአማራ ህዝብ ዛሬ ላይ እጅግ ፈታኝ፣ ውስብስብ እና አደገኛ በሆነ የታሪክ ምዕራፍ ላይ ይገኛል። ህዝባችን በየአቅጣጫው የተከፈተበትን የህልውና አደጋ ለመመከት ወደር የለሽ ተጋድሎ እያደረገ ቢሆንም፤ መጠነ ሰፊ ማፈናቀል፣ ግድያ፣ የኢኮኖሚ ውድመት፣ እና ሁለንተናዊ የመዋቅር ማግለል የዕለት ተዕለት እውነታው ሆኗል። ይህ የተደራጀና ዘርፈ ብዙ ጥቃት ህዝባችንን በከፍተኛ የህልውና ስጋት ውስጥ የከተተው ሲሆን፣ የተቀናጀና አገር አቀፍ መፍትሄ ባለመገኘቱ ምክንያት ውድ የሆነ የሰው ህይወትና የንብረት ዋጋ እየከፈለ ይገኛል።
ከዚህ መሪርና አሳሳቢ ነባራዊ ሁኔታ አኳያ፣ እኛ የአማራ ምሁራን እና ልሂቃን ቆም ብለን ራሳችንን ስንገመግም፣ ለህዝባችን የሚመጥንና በታሪክም የሚጠበቅብንን ያህል የበኩላችንን የአመራርና የተግባር ሚና እንዳልተወጣን በግልጽ እናምናለን። በህዝባችን ላይ እየደረሰ ያለውን መከራ ለማስቀረትም ሆነ የህልውና ትግሉን በአስተማማኝ መሰረት ላይ ለማቆም፤ በዕውቀት፣ በስትራቴጂ፣ በዲፕሎማሲ፣ እና ህዝብን በማስተባበር ረገድ የነበረን ተሳትፎ ውስን፣ የተበታተነ እና ወቅቱ የሚጠይቀውን ልክ ያላሟላ እንደነበር ጉባኤው በጽኑ ገምግሟል።
ሆኖም ይህ ጉባኤ የታሪክ ማዕዘን መታጠፊያ ነው። ከእንግዲህ ወዲህ የአማራ ምሁራን ከዳር ቆሞ የመመልከትም ሆነ ተበታትኖ የመጓዝ ምዕራፍ በይፋ አብቅቷል። የህዝባችንን ህልውና ለማስጠበቅ፣ ትግሉን በዕውቀት ለመምራት፣ ጠንካራ አንድነት ለመፍጠር፣ እና ለችግሮቹ ሳይንሳዊና ተግባራዊ መፍትሄዎችን ለማምጣት ከመቼውም ጊዜ በላይ በቁርጠኝነት ተነስተናል። አቅማችንን፣ እውቀታችንን እና ጊዜያችንን አሟጦ በመጠቀም ከህዝባችን ጎን በጽናት ቆመን ኃላፊነታችንን ለመወጣት ቃል ገብተናል።
በዚህ የምስረታ ጉባኤና በቅድመ ጉባኤ በአጠቃላይ ለአንድ ወር የአማራ ልሂቃን ባደረግነው ጥልቅ ውይይት መሰረት ትግሉን ወደ ሚገባው የድል ምዕራፍ ለማሸጋገር ወስነናል፣ ይህንን ቁርጠኝነት ወደ ተግባር ለመቀየር አበይት ኃላፊነቶች የተከፋፈሉ ሲሆን በሚከተሉት ስትራቴጂካዊ ዘርፎች ዙሪያ ጠንካራ ስራዎች እንደሚሰሩ ተገልጿል፦
♦️የህዝባዊ ዲፕሎማሲና አለም አቀፍ ግንኙነት፡ ትግሉን ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ በግልጽ የማስረዳት ስራ።
የአለም አቀፍ ህግና የሰብአዊ መብት፡ በህዝባችን ላይ የሚደርሱ ግፎችን በህግ ማዕቀፍ የመከታተልና ፍትህ የመፈለግ ዘርፍ።
♦️የሽግግር ወቅት እቅድና የፍትህ ስርዓት፡ ለቀጣይ የፖለቲካና የፍትህ መዋቅር አስቀድሞ መዘጋጀት።
የታሪክ፣ ባህልና ማንነት ጥበቃ፡ የህዝባችንን እሴቶች የመንከባከብና የማስቀጠል ስራ።
♦️የኮሙኒኬሽን፣ ሚዲያና የትርክት ግንባታ፡ የተበታተኑ ድምጾችን በማሰባሰብ ጠንካራ ትርክት የመገንባት ዘርፍ።
የትብብር፣ ጥምረትና አጋርነት፡ ከሌሎች ሀይሎች ጋር የሚኖረውን ጤናማ ግንኙነት ማስተዳደር።
♦️የህልውና አቅም ግንባታና መረጃ ትንተና ዘርፍ፡ የህዝቡን የመቋቋም አቅም ማጎልበትና ትክክለኛ የመረጃ ፍሰትን ማረጋገጥ።
♦️የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ፡ ዘላቂ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ፖሊሲዎችን መንደፍ።
♦️የቴክኖሎጂ እና የሳይበር ደህንነት፡ የመረጃ ደህንነትን መጠበቅና በቴክኖሎጂ መታገዝ።
♦️ የዓለም አቀፍ ህግና የሰብአዊ መብቶች ተሟጋችነት ዘርፍ
♦️ የኢኮኖሚ፣ ፋይናንስና የሃብት ማሰባሰብ ዘርፍ በሚል ተቋቁሟል።
"አስተዋይና ብሩህ ህዝብ የማይጠፋ ታሪክ አለው፤ የወደፊት ዕጣ ፈንታውንም እራሱ ይገነባል።" ይህን ታላቅ እውነት ሰንቀን ለጋራ ህልውናችን በአንድነት የምንቆምበት ወሳኝ ሰዓት አሁን ነው። የተጋረጡብንን የህልውና ስጋቶች በተቀናጀ መንገድ ለመመከትና ለህዝባችን የተሻለ ነገን ለመፍጠር፣ መላው ህዝባችን በነዚህ በተዋቀሩት ዘርፎች ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የድርሻውን አዎንታዊ አሻራ እንዲያሳርፍ በአክብሮት ጥሪያችንን እናቀርባለን።
እንተባበር! እንወያይ! እንገንባ!
የዓለም አቀፍ የአማራ ሊህቃን መማክርት ምስረታ ጉባኤ!
ነሐሴ 24 ቀን 2018 ዓ.ም
8 649
የአርበኛ ዘመነ ካሴ መልዕክት‼️
አብይ አህመድና ቡድኑ የመግደል ዘመናቸው ማብቂያ የመጨረሻው ምእራፍ ላይ ይገኛሉ።ይህን የተረዱት እነ አብይና የጋራ መንፈስ የሚጋሩ ልሂቃን ረጅም ጊዜ ወስደው ያዘጋጇቸውን የኢንተርሃሙዬ ቡድኖች ከ"መከላከያው" ጋር አቀናጅተው ማሰማራት ጀምረዋል። በዚህ ወቅት በወለጋና በሸዋ አንዳንድ ቦታዎች የናሙናና የመለማመጃ ጭፍጨፋ እያደረጉ ይገኛሉ።እንደ ሁልጊዜው ሁሉ ዋናው ኢላማቸው የአማራ ህዝብ ቢሆንም፥ የትግራይ ተወላጆች፥ ጉራጌዎች፥ ሲዳማዎች፥ጋሞዎችና ልዩ ልዩ ወገኖችም እያለቁ ነው።አሁን ገና ጅምር ነው። እየመጣ ያለው ነገር ግን እጅግ አስፈሪ ነው።
ውድ ኢትዮጲያውያን ወገኖች ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በጋራ የምንቆምበትና ራሳችን ከእልቂት የምንከላከልበት ቀን ዛሬ ነው። እየመጣ ካለው የእልቂት ዶፍ ማንም የሆነ ጥግ ተከልሎ ማምለጥ አይችልም። ጎረቤቱ ሞቶ እሱ በተአምር መትረፍ የሚችል የሚመስለው ካለ ተሳስቷል።እሳቱ የማያካልለው ቦታና ህዝብ አይኖርም። መትረፍ የምንችለው ከአሁኑ በተግባር አብረን መቆም ስንጀምር ነው። ወለጋና አዲስ አበባ ከፒያሳ አራት ኪሎ ያክል እንኳን አይራራቁም። ሃዋሳ እና ወልቂጤ የአንድ ከተማ ሁለት ቀበሌዎች ያክል ናቸው። ዛሬውኑ አብረን እንቁም።
በዚህ አስከፊ የታሪክ ምእራፍ ውስጥ በነ አብይ አህመድና አንዳንድ ልሂቃን ወገናችን የሆነውን የኦሮሞን ህዝብ ከሌሎች ወንድምና እህት ህዝቦች ለመነጠል የሚደረገው ሙከራ በጣም አደገኛና የበለጠ አውዳሚ ነው። በዚህ ረገድ ወገናችን የኦሮሞ ህዝብም ይህ አውሬ ቡድን ወኪልህ ነኝ ሊለው ሲሞክር ከሌሎች ወገኖቹ ጋር ተባብሮ ወግድ ማለት ይኖርበታል። ይህ ቡድን የትኛውንም ኢትዮጲያዊ ህዝብ አይወክልም፥በሰው ልጆች ታሪክ ከታዩ ሰዎበላ ቡድኖች ሁሉ የከፋው ነው።
ለመሆኑ ህልውናን የመከላከል ጉዳይ የማን ስራ ነው?እያንዳንዱ ዜጋ ህልውናው በራሱ እጅ ነው የሚጠበቀው። ራስን በመከላከል ሂደት ውስጥ አዝማችና ዘማች፥ ተፋላሚና ተመልካች የለም። ነጋዴውም፥ መምህሩም፥ ተማሪውም፥ አርሶ አደሩም፥ ሸምኖ አደሩም፥ ቀድሶ አደሩም፥ ቤተክርስቲያኑም፥ ቤተ መስጊዱም ሁሉም ይመለከታቸዋል። የህልውና ትግል ብዙሃኑ በተመልካችነትና በደጋፊነት የሚታደመው የሁለት ተፋላሚዎች ጨዋታ አይደለም።
ለሌሎች ወገኖች መትረፍ ነፃ አውጭነት ብቻ ሳይሆን የፅድቅም ስራ ነው። ሌላው ይቅር ሰው እንዴት ለራሱ መሆን ያቅተዋል?
'If you can not cross the red sea, just wait and see'እንዲል ባለቅኔና ፈላስፋ ሙሉጌታ ተስፋዬ ባህሩን ተባብረንና ተደማምጠን እንሻገረው ወይንስ ማእበሉን ቆመን እንጠብቀው?ሳንወላውል፥ተደማምጠን፥ ተባብረን እንሻገረው።
በፍርሃት ተፀንሰን፥ በፍርሃት ተወልደን፥ በፍርሃት ውስጥ ኖረን ከነሰቆቃችን መሞት ማብቃት አለበት።
አፋብን እንደ ድርጅት የሚሊዮኖችን ነፍስ ለማትረፍ ሌት ተቀን እየሰራ ነው። በዚህ ረገድ ቡድኑን በፍጥነት ማስወገድ ፍቱን መድሃኒት ነው።ከችግሩ ስፋት፥ ጥልቀትና ፍጥነት አኳያ ግን እያንዳንዱ አማራ እና ኢትዮጲያዊ ወገን በጋራ ራሱን ለመከላከል መዘጋጀት አለበት። ሞት በእያንዳንዳችን ታዛ ተከናንቦ ቆሟል። አሁንም እንንቃ፥ እንነሳ፥ እንደራጅ፥ እንመክት።ያለበለዚያ አለም ጉድ ያያል።
የአለም አቀፉ ማህበረሰብም ከፍተኛ የሞራልና የህግ ሃላፊነት አለበት። አብይ የሚባል ከጥልቁ የፈለቀ ጭራቅን በመንከባከብ የሚረጋገጥ ብሄራዊ ደህንነትና ጥቅም የለም። ኢትዮጲያ ከድጡ ወደ ማጡ ከገባች አለምን የሚያንቁ ጅኒዎች ከየተራራው ስር አፈትልከው በሁሉም አቅጣጫ ይበተናሉ።
ለሰው ልጆች መብትና እኩልነት፥ ለዴሞክራሲ እና ነፃነት የመቆም ወፍራም ተሞክሮ ያላቸው ሃገራት በኢትዮጲያ ጉዳይ ሚፈተኑበትጊዜ አሁን ነው።አለም እየታዘበ ነው።"The arc of the moral universe is long, but it bends towards Justice"
እንንቃ፥ እንተባበር። አብይ እንደ ሮሙ ንጉስ ኔሮ ሀገሩን አቃጥሎ በደስታ ሊዘፍን ተዘጋጅቶ ጨርሷል።
ክፋት ለማንም፥ በጎነት ለሁሉም
አዲስ ትውልድ ፥አዲስ አስተሳሰብ ፥አዲስ ተስፋ!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
ድል ለአማራ ህዝብ!
ድል ለኢትዮጲያ ህዝብ!
አርበኛ ዘመነ ካሴ
ነሃሴ 25/2018 ዓም
8 649
🎯 ንዑስነትና ሰርሳሪነት ተሸንፏል!
በአማራ የህልውና ትግል ታሪክ ውስጥ አዲስና ወሳኝ ምዕራፍ ተከፍቷል። ትውልዱ የውድቀትን ረግረግ በብሔራዊ ንቃቱ ተሻግሮ አሸንፏል። በአጋርነትና በትብብር ጽንሰ-ሀሳብ ላይ የተመሰረተው ይህ ታሪካዊ ተጋድሎአችን፣ ከዚህ ቀደም የፋኖነት ትግላችንን እንደ ሰርሳሪ ተረከዝ ሆኖ ሲያደክመው የቆየውን የክፍፍል ቅኝት ሽሮ አዲስ መስመር እንዲይዝ አስችሎታል።
በዚህም ውስጣዊ የህልውና አደጋችን ዋና መንስኤ የሆነው ንዑስነት ድል ተመቶበታል፤ የድርጅቶች ውህደት የሚፈጥረው እውነተኛ አንድነት አቅማችንን በማባዛት ትግላችን ስትራቴጂካዊ አሸናፊነትን እንዲጎናጸፍ በሚያስችል መልኩ የማይቀለበስ የድል ጎዳና ውስጥ ገብቷል።
በአጋርነትና በጋራ ትብብር ማዕቀፍ ውስጥ ስንቆም፣ የአንድ ህዝብ - አንድ ወጥ ትግል በአንድ ድርጅት እና አመራር ጽናት እና ቁርጠኝነት ለአሸናፊነት እንደሚበቃ ከመቼውም ጊዜ በላይ እውነት ሆኗል። ይህ ድል አዲሱ ትውልድ በጭንቅ ውስጥ ሆኖ አዲስ አስተሳሰብ በመትከል ያስገኘው የትግል ፍሬ ነው። አንድነታችንና አጋርነታችን አዲሱ ተስፋችንና ቀዳሚ አላማ የሆነውን ብሔራዊ ህልውና በክንዳችን የሚረጋገጥበት የእርግጠኝነት ማህተም ሆኗል።
የፋኖ ሰራዊት፣ የሚዲያ አጋሮች እና በሀገር ውስጥ እና በውጭ ትግሉን የሚደግፉ አካላት በተወደደ ጊዜ የተገኘውን ዕድል ወደ ፈጣን የድል እንድርድሪት በመቀየር፣ ጠላት ላይ ጨራሽ ምት ለማሳረፍና ለማስወገድ የሚጠየቀውን ሁሉ ለማድረግ በአጋርነት መንፈስ መዘጋጀት ይገባል።
የመጨረሻው ሰአት አሁን ነው። የአንድነት ዜናውና የአጋርነት ድግሱ የምስራች ብቻ እንዳይደለ እሙን ነው፤ ለፋኖ እና ደጀን የሆነው ህዝባችን የሰልፍ ጥሪ ነውና። የሰልፍ ጥሪው ግላዊ፣ ቡድናዊ እና ሌሎች ትንንሽ ጉዳዮችን የሚበልጥ ነው። አጋርነትንና ትብብርን በሚያጠናክር መልኩ አሉ የሚባሉ ችግሮችንም የምንፈታበት የዕይታ ማዕቀፍ ድርጅታዊ አንድነት በተገኘበት ሂደት እና በፍሬው ውስጥ ተቀምጧል።
በትግል የተሸነፉ ነባር የክፍፍል ዕሳቤ እና አሰላለፍ ላይ ቆመው ከፍሎ ማጉላት እና ከፍሎ ማሳነስ ብሎም ማጥቃት ተራ ስህተት ሳይሆን ራስ ጠልነት መሆኑን በመገንዘብ በግለ ሂስ ከዚህ መንገድ መቆጠብ እና በዚህ መንገድ ያሉትንም መገሰጽ አልፎም ድርጊቱ የጠላትነት መሆኑን አውቆ መታገል ይገባል። ከዚህ ባሻገር ጥያቄን እና ቅያሜን መሪዎቻችን ይህን አንድነት ለማንበር የሄዱበትን መንገድ ተከትለን በአጋርነትና በውይይት እንፍታ፤ በተቀረውም በሚጠበቅብን ሚና እና በቆምንበት አቅጣጫ በኩል ተሰልፈን ተጋድሏችንን በጋራ ለመፈጸም እንትጋ።
ድል ለአማራ የህልውና ትግል! 🎯
መነሾ ፦ ዳዊት መሐሪ
8 649
🎯 የዕውቀት ሠራዊት ለህልውና ትግል፦ የአማራ ልሂቃን መማክርት ምስረታና ታሪካዊ ጠቅላላ ጉባኤ!
(አዲሱ ደረበ)
የአማራ ሕዝብ ዛሬ በታሪኩ ፈታኝና አሳሳቢ ወቅት ላይ ይገኛል። የህልውና፣ የደህንነት፣ የሰብአዊ መብትና የባህል መቃወስ አደጋዎች ተደራርበውበት በሚገኙበት በዚህ ወሳኝ ሰዓት፣ ህዝቡን ከወደቀበት አዙሪት ለማውጣት የዕውቀት፣ የጥበብና የባለሙያዎች አስተዋጽኦ ተራ ምርጫ ሳይሆን ፍጹም የህልውና ጉዳይ ሆኗል። በመላው ዓለም የሚገኙ አቅሞችና ባለሙያዎች ተቀናጅተው የሚንቀሳቀሱበት የአማራ ልሂቃን መማክርት መቋቋም ለዚህ ታሪካዊ ጥሪ የተሰጠ ወቅታዊና ትክክለኛ ምላሽ ነው።
ይህ መማክርት የአቅም ስብጥርንና አለማቀፋዊነትን መሠረት በማድረግ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የሚገኙ ምሁራንን ዕውቀት፣ ልምድና ዓለም አቀፍ ትስስር በአንድ ማዕቀፍ ውስጥ አጣምሮ የሚይዝ ነው። የተበታተኑ ጥረቶችን ወደ ማዕከላዊ አውታር በማምጣት፣ የምሁራኑን ድምጽና አቅም በተናጥል ከሚደረግ እንቅስቃሴ አውጥቶ፣ ተቋማዊና ስልታዊ በሆነ መንገድ ለሕዝብ ጥቅም ማዋል አስገዳጅ በመሆኑ ይህ ጉባኤ ታሪካዊ ምዕራፍ ይከፍታል። የሕዝብን ትግል በሳይንሳዊ፣ በስትራቴጂካዊ እና በጥናት ላይ በተመሰረተ መንገድ ለመምራት የሚያስችለው የዕውቀት መሪነት ክፍተት የሚሞላውም በዚህ መልኩ ነው።
የመማክርቱ ዋና ዋና ዓላማዎች የህልውና ትግሉን በዕውቀት መደገፍ፣ የአማራን ሕዝብ የመብት፣ የሰላም እና የህልውና ትግል በጠንካራ ምርምሮች፣ በፖሊሲ ሃሳቦች እና በስትራቴጂያዊ መፍትሄዎች ማገዝ ናቸው። ከዚህም በተጨማሪ በሕዝባችን ላይ የሚደርሰውን ግፍ፣ መፈናቀል እና ስልታዊ ጥቃት በአለም አቀፍ መድረኮች፣ በተቋማት እና በማህበራዊ ሚዲያ በሰነድ አስደግፎ በማቅረብ ፍትህ እንዲሰፍን ማድረግ የትኩረት ማዕከሉ ነው። በመላው ዓለም የተበተኑ የአማራ ምሁራን የሐሳብ ልውውጥ እንዲያደርጉ፣ ልምድ እንዲለዋወጡ እና ለጋራ አላማ እንዲቆሙ የትስስር መድረክ በመፍጠር ምሁራዊ አንድነትና አብሮነትን ይገነባል።
መማክርቱ ከሚያከናውናቸው ዋና ዋና ተግባራት ውስጥ ስትራቴጂካዊ ጥናቶን ሰርቶ፣ የህዝቡን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ቀውሶች የሚተነትኑ ሰነዶችን በማዘጋጀት ለሚመለከታቸው አካላት፣ ድርጅቶች እና መሪዎች አዋጭ የመፍትሄ ሃሳቦችን ያቀርባል። በዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች የውጭ ሀገር ቋንቋዎችን በመጠቀም ዓለም አቀፍ ማህበረሰብን፣ መገናኛ ብዙኃንን እና የሰብአዊ መብት ድርጅቶችን በማነጋገር፣ በዲያስፖራ የሚገኙ ምሁራንን በማቀናጀት የሎቢ እና የዲፕሎማሲ ስራዎችን ያከናውናል።
በተጨማሪም ሕዝቡ ስለወቅታዊው ሁኔታ ትክክለኛውን መረጃ እንዲያገኝ መድረኮችን፣ ሲምፖዚየሞችን እና የሚዲያ ስልጠናዎችን በማዘጋጀት የህዝብ ግንዛቤ ማሳደግና የማስተማር ስራዎችን ይሰራል፤ በባህልና በማንነት ላይ የሚነሱ የተዛቡ ትርክቶችን በምሁራዊ ምርምር ያርማል፣ ያስረዳል። በግፍ ከተፈናቀሉ፣ ጉዳት ከደረሰባቸው እና አቅም ካጡ ወገኖች ጎን በመሰለፍ ሙያዊ፣ ማህበራዊ እና ሰብአዊ ድጋፎችን ያስተባብራል።
ይህ መማክርት ለህልውና ትግሉ የሚያበረክተው ልዩ ጥቅም አለ። የስሜታዊነት እና የዕውቀት ቅንጅት በመፍጠር ትግሉን ከስሜታዊ ምላሽ ይልቅ በሂደት ላይ የተመሰረተ፣ ግልጽ ግብ ያለው እና በሳይንሳዊ ትንተና የሚመራ ያደርገዋል። ምሁራኑ ባላቸው ሙያዊ አቅም፣ እና የዲፕሎማሲ ክህሎት የትግሉን ዓለም አቀፋዊ ተቀባይነት ከፍ ያደርጉታል። አሁን ያለው ትውልድ የሚከፍለውን ዋጋ በባለሙያ ድጋፍ አቀናጅቶ ለመሰነድ፣ ለቀጣዩ ትውልድ ጠንካራ ተቋማዊ መሰረት ይጥላል።
ይህንን ታሪካዊ ተልዕኮ እውን ለማድረግና የዕውቀት ሠራዊቱን በአንድነት ለማሰለፍ ነሐሴ 23 እና ነሐሴ 24 ቀን 2018 ዓ.ም (August 29 & 30, 2026) ከ 1:00 PM እስከ 5:00 PM EST በዙም ስብሰባ (Zoom Meeting) መርሃ-ግብር ታላቁ የልሂቃን መማክርት ምስረታና ጠቅላላ ጉባኤ የሚካሄድ ይሆናል።
ሁላችንም እንገኝ!
ድል ለአማራ የህልውና ትግል! 🎯
8 649
🎯 የአርበኛ ዘመነ ካሴ መልዕክት አንድምታ!
(አዲሱ ደረበ)
በአማራ ሕዝብ የህልውና ተጋድሎና በኢትዮጵያ ወቅታዊ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ የራስ-አርበኛ ዘመነ ካሴ መልዕክቶች ጥልቅ ፖለቲካዊ፣ ስነ-ልቦናዊና ጂኦ-ስትራቴጂካዊ ርዕዮተ-ዓለምን የሚያመለክቱ የፖለቲካ ኮምፓሶች ናቸው። አርበኛ ዘመነ ካሴ በዚህ መልዕክቱ አማካኝነት ከጠበበ የብሔርተኝነት ቁርሾ የወጣ፣ የነፃነት ትግልን ከስልጡን የፖለቲካ ስትራቴጂ ጋር ያዋሐደ ታላቅ ምሁራዊና ተራማጅ አመራርነቱን በግልጽ አሳይቷል።
የመልዕክቱ የመጀመሪያው ነጥብ የሚያተኩረው በአማራ፣ በትግራይ፣ በኦሮሞ፣ በአፋር፣ በሶማሌ፣ በሲዳማ፣ በጉሙዝና በበርታ ህዝባዊ ኃይሎች መካከል ሊኖር በሚገባው የጋራ ትብብር ላይ ነው። ብዙ ጊዜ በጠባብ ብሔርተኞች አእምሮ ውስጥ ከሌላው ጋር መተባበር የደካማነትና የብቸኝነት መሸሸጊያ እንደሆነ ተደርጎ የሚወሰድ የተሳሳተ ብዥታ አለ። አርበኛው ይህንን አደገኛ አመለካከት በሳይንሳዊ ምልከታ ያፈርሰዋል። እያንዳንዱ ሕዝብ በራሱ እግር መቆም የሚችል፣ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ አቅም ያለው መሆኑን በመቀበል፣ የኃይሎች ትብብር የሚመነጨው ከትብብር ዛሬያዊና ዘላለማዊ ጠቀሜታ እንደሆነ ያስምርበታል።
አገዛዙ ሥልጣኑን ለማራዘም የሚጠቀመው ዋነኛ ስትራቴጂ ሕዝቦችንና ሕዝባዊ ኃይሎችን እርስ በእርስ ማጋጨትና መለያየት በመሆኑ፣ ራስ አርበኛ ዘመነ ካሴ ይህንን የጠላት ወጥመድ በጥበብ በመስበር፣ የሕዝባዊ ኃይሎች የተቀናጀ ትብብር የፋሽስታዊውን ሥርዓት ዕድሜ እንደሚያሳጥርና ዘላቂ የጋራ ሰላም የሚያረጋግጥ ብቸኛው ስልታዊ መንገድ መሆኑን ያስገነዝባል።
ሁለተኛውና የመልዕክቱ እጅግ ከባዱ ጥልቅ መንፈሳዊና ስነ-ልቦናዊ ክፍል ደግሞ የትውልዱን ታሪካዊ ተልዕኮ የቂም ተራራን ማፍረስና የጭራቅ ልብ እንዳይነግሥ መታገል አድርጎ ማስቀመጡ ነው። አርበኛው የእኛን ዘመን ተልዕኮ ሰዎችን መሰብሰብ፣ መቀራረብና ፍቅር ሲል ይገልጸዋል። ሰይፍ ያነሳነው አበባችንን ነጥቀውን ነው የሚለው ገላጭ አገላለጽ፣ የአማራ ፋኖ የጦርነት ፍላጎት ኖሮት ሳይሆን የህልውናው ማስጠበቂያ አስገዳጅ መንገድ ሆኖበት እንደያዘው ያሳያል።
አማራን ከተለያዩ ብሔሮች ጋር የሚያጋጭ ተጨማሪ ጠላት ያለመግዛትና የመከራ ምክንያት ያለመሆን አቋም፣ የላቀ መሪነትና የፖለቲካ ብስለት መታወቂያ ነው። ይልቁንም ይህ ትውልድ የክፋት ሐውልትን ደርምሶ በቦታው የፍቅርና አብሮ የመኖርን ዋርካ ካልተከለ፣ ቀጥሎ የሚመጣው ትውልድ ሙሉ በሙሉ የጭራቅ ልብ የተገጠመለት ይሆናል ሲል ያስቀመጠው ማስጠንቀቂያ እጅግ አስፈሪና ሀቅ ያዘለ ነው። ይህም በበቀል፣ በጽንፈኝነትና በቂም የተሞላ ፖለቲካ የቀጠለ እንደሆነ፣ ሀገሪቱ ሙሉ በሙሉ ወደ አልቦ-መንግሥትና አውሬያዊ አናርኪዝም ውስጥ እንደምትወድቅና መፍትሔው ዛሬውኑ የቂም ተራራን ማፍረስ እንደሆነ የሚያሳይ ጥልቅ የማኅበራዊ ሳይንስ ትንበያ ነው።
በመጨረሻም፣ መልዕክቱ ትግሉ ከውስጥም ሆነ ከውጭ በሚሰነዘሩበት የስም ማጥፋት፣ የነቀፌታና የማንቋሸሽ ዘመቻዎች ፊት ሊኖረው የሚገባውን የጸና አቋም ያመላክታል። ዛሬ በጥላቻና በድንቁርና ተነሳስተው ትግሉን የሚያቋሽሹና የሚያፌዙ ወገኖች፣ ነገ የእውነትና የፍትሕ ድል ሲረጋገጥ ወደ እውነቱ እንደሚመለሱና ያኔም ቢሆን በይቅርታ እንደሚቀበሏቸው ይገልጻል። ለአንድ ስድብ አንድ ጡብ እያስቀመጥን ወደፊት እንቀጥላለን ማለቱ፣ ጥቃቅን ትንኮሳዎች የትግሉን ታላቅ ዓላማና መስመር እንደማያናውጡት ያሳያል።
አርበኛ ዘመነ ካሴ ያስቀመጠው የሚስማሮች ብዛትና የጽናት ቀናት ምሳሌያዊ ንጽጽር፣ የመሪውን የስነ-ልቦና ጥንካሬ ፍንትው አድርጎ ያሳያል። በትግል ሂደት ውስጥ የሚሰነዘሩ ስድቦችና ሴራዎች ሁሉ ታጋዩን ከመስመር የሚያስወጡ ሳይሆን፣ ይበልጥ እንዲጸናና የተወረወሩ ጡቦችን በመደራረብ የነፃነት ሕንፃውን እንዲገነባ የሚያደርጉ አዎንታዊ ጉልበቶች እንደሆኑ ያስረዳል፤ ይህም የታላላቅ አብዮታዊ መሪዎች ባህሪ ነው።
በአጠቃላይ፣ የራስ-አርበኛ ዘመነ ካሴ መልዕክት የአማራ ፋኖ ትግል ከጠባብና ከነጠላ አመለካከት ወጥቶ፣ አህጉራዊና አገራዊ ራዕይ ያለው፣ ፍትሕን፣ ትብብርን፣ ይቅርታንና አብሮነትን ያነገበ ስልጡን የነፃነት ንቅናቄ መሆኑን ይመሰክራል። ይህ መልዕክት ለአጋሮች የትብብር ጥሪ፣ ለጠላቶችና ለሴረኞች ማስጠንቀቂያ፣ ለአዲሱ ትውልድ ደግሞ የቁርሾ ሰንሰለትን ሰብሮ ፍቅርን የመትከል ታሪካዊ አደራ ነው።
ድል ለአማራ የህልውና ትግል! 🎯
8 649
አንዳንድ ነገሮች♾️
1)የአማራ ፋኖ ከሌሎች ህዝባዊና ብሄራዊ ሃይሎች ጋር የሚተባበረው ብቻውን መቆም ስለማይችል አይደለም፥ የትግራይ ሃይል ከአማራውና ከኦሮሞው ጋር የሚተባበረው ብቻውን መቆም ስለማይችል አይደለም። አፋሩ ከአማራውም ከኦሮሞውም ከሲዳማውም፥ ከበርታውም ጋር የሚተባበረው ብቻውን መቆም ስለማይችል አይደለም። ኦሮሞው ከጉምዝና ከአማራ ጎን የሚቆመው ብቻውን መቆም ስለማይችል አይደለም።ሶማሊው ከሌሎች ወገኖች ጋር የሚያብረው ብቻውን መቆም ስለማይችል አይደለም።ሁሉም ራሱን ችሉ መቆም ይችላል።እስካሁንም ሁሉም በራሱ መንገድ በገዛ እግሩ ሲጓዝ ነው የመጣውና። እነዚህ ድርጅቶች የሚተባበሩት ብቻቸውን መቆም ስለማይችሉ ሳይሆን ትብብር ዛሬያዊም ዘላለማዊይም ጠቀሜታ ስላለው ነው።ስለዚህ ህዝባዊ ሃይሎች ይተባበራሉ፥ የጋራ ግባቸውን በጋራ ያሳካሉ‼️።
2)የኛ ዘመን ተልእኮ ሰዎችን መሰብሰብ ነው።መቀራረባና ማቀራረብ ነው። ፍቅር ነው።ሰይፍ ያነሳነው አበባችን ነጥቀውን ነው።እኛ በዚህ ሃላፊነት እያለን በግፍ ሊያጠፋን ገፍቶ ካልመጣ በስተቀረ አማራን ከሌላ ህዝብ ጋር አናዋጋውም። መቼም አናደርገውም።ለአማራ ህዝብ ተበድረን ተጨማሪ ጠላቶች አንገዛለትም። ለሌሎች ወገኖችም የመከራ ምክንያት አንሆንም።
ይህ ምኞታችን እንዲሁ ብላሽ አይሆንም ።ሁሌ እንደምንለው በጎ ምኞቶች ዳር የሚያደርስ የራሳቸው እግዜር አላቸው።
ይህ የቂም ተራራን፥ የቁርሾ ጋራን የሚያፈርሰው፥ የመገዳደል እንቧለሌን የሚሰብረው የመጨረሻው ትውልድ ነው። ይህ ደፋርና በጎ ትውልድ ነው።ይህ ትውልድ የክፋት ሃውልትን ደርምሶ በቦታው የፍቅርና አብሮ የመኖርን ዋርካ ካልተከለ በስተቀረ በዚሁ በኛ እድሜ ቀጥሎ የሚመጣው ትውልድ የሰው ሳይሆን ሙሉ በሙሉ "የጭራቅ" ልብ የተገጠመለት ይሆናል።ይመጣል ብለን የምንፈራው መጧል እኮ ብሎ መናገር ይቻላል።ልክ ነው። እየመጣ ያለው ግን በመደበኛ አእምሮ ለማሰብም ይከብዳል።መድሃኒቱ ይህንን የመጨረሻ ጥረት ተጋግዞ ውጤታማ ማድረግ ነው።
3)ዛሬ እኛን ለመዝለፍና አላማችን ለማንቋሸሽ፥ ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ለመሳቅ ብቻ ሲሉ የዋልጌ ማህበር የመሰረቱት ወገኖች ሁሉ አንድ ቀን ወደኛ ይመጣሉ።ይህንን በጎ ምኞታችን ይገዛሉ፥ የራሳቸው ያደርጋሉ። ያኔም ፍፁም ሳይሸማቀቁ፥ በፍፁም ይቅርታ እንቀበላቸዋለን።እስከዛው ድረስ "ለአንድ ስድብ፥ አንድ ጡብ" እያስቀመጥን ወደፊት እንቀጥላለን።
"ሚስማሮችን ቁጠር፥ ብዛታቸው ላለማቆም ወይም እስከመጨረሻው ለመፅናት የወሰንንባቸው ቀናት ጋር እኩል ነው" እንዲል ትልቁ አባታችን።
(ለአንድ አሻጥር፥ አንድ ሚስማር፥ ለአንድ ስድብ አንድ ጡብ‼️)
ክፋት ለማንም በጎነት ለሁሉም
አዲስ ትውልድ ፥አዲስ አስተሳሰብ፥ አዲስ ተስፋ
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
አርበኛ ዘመነ ካሴ!
ነሃሴ 21/2018
8 649
ይልቁን ለአማራ ሕዝብ ሕልውና ሲዋደቁ መስዋዕት የሆኑ ጀግኖችን ልጆችና ቤተሰቦች ጠይቁ። ልጆቻቸውን አስተምሩ፤ ቤቶቻቸውን ገንቡ።
ይኸው ነው!
8 649
🎯 ፍትሐዊው ባለ ሚዛን!
(አዲሱ ደረበ)
የአማራ ሕዝብ ሁሌም ቢሆን ፍትሐዊ፣ ባለሚዛንና ሥርዓት አዋቂ ሕዝብ ነው። ለመንግሥት፣ ለሕግና ለመንግሥታዊ አሠራር ያለው ቀናኢነትና አክብሮት ለዘመናት የጸና ቢሆንም፣ ይህ በጎ እሴቱ ግን ግፍና ጭቆና በእርሱና በወገኖቹ ላይ ሲጫኑ እጁን አጣጥፎ እንዲቀመጥ አድርጎት አያውቅም። ዛሬማ ይልቁን በአማራዊ ማንነቱ ላይ የህልውና አደጋና የዘር ማጥፋት ጥቃት ተደቅኖበት እንዴት ዝም ይላል? ወትሮም ቢሆን ኢ-ፍትሐዊነትንና ጥቃትን እምቢ ለማለትና ለመፋለም ቦዝኖ የሚያውቅ ሕዝብ አይደለም!
እውነቱ አሁን እንደሚታየው ነው፤ እንኳን አሁን መላው አማራ በየአቅጣጫው አለሁ ብሎ በአንድነት ተሰልፎ ይቅርና፣ ወትሮም ቢሆን በየትኛውም አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ በአጥቢያው ተደራጅቶ ግፈኞችንና ወራሪዎችን ለመታገል አንዲት ሰከንድ የማያመነታ ብርቱና ኩሩ ሕዝብ ነው። የታሪክ መዝገብ ለዚህ ሕያው ምስክር ነው፤ የፋሽስት ጣሊያንን እብሪትና ወረራ፤ ዘመናዊ የጦር መሣሪያና የመርዝ ጋዝ ሳይበግረው ዱር ቤቴ ብሎ ተፋልሟቸዋል። በቀደሙት ስርአቶች ሁሉ የመሬት ግብር ጭቆና በበረታበት ወቅትም፣ የማይከሰሱና የማይጠየቁ የሚመስሉትን መሳፍንቶች አልገብርም ብሎ በመሬት ግብር እምቢተኝነት አንቀጥቅጧቸዋል።
በአህጉር ደረጃ ገናና ስምና ግዙፍ የጦር ግንባር የነበረውን የደርግን መራር ግፍና ቀይ ሽብር የመታገልና የመቋቋም ታሪካዊ ውርስ ያለው ነው፤ ለዚህም የጀግኖች ምድር አቸፈር፣ በለሳና ሰቆጣ ሕያው ምስክሮች ናቸው። እንዲሁም የወያኔ ኢሕአዴግን ዘረኛ አገዛዝ ከዘረኝነት፣ ከጠባብነትና ከመድሎ እንዲወጣ ያለ ምንም ፍርሃትና ተሸማቃቂነት በአደባባይ የተጋፈጠውና የታገለው ይኸው ሕዝብ ነው።
ዛሬማ መደራጀት፣ መቀራረብና በጋራ የአማራነት ጉዳይ ላይ በጋራ መሰለፍን ዘመኑም፣ የታሪክ አጋጣሚውም ፈቅዶለታል! ትናንት የፋሽስት ጣሊያን የመርዝ ጋዝ ያልበተነውና ያላበረከከው ሕዝብ፣ ዛሬ በፋሽስቱ አብይ አሕመድ ድሮን በፍጹም አይንበረከክም። የደርግን አሰቃቂ ቀይ ሽብር በጽናት የተሻገረው አቅሙ፣ በዛሬው ገዢ ቡድን የዘር ማጥ*ፋት ዘመቻ አይፈታም። የወያኔ የትጥቅ ማስፈታት አዋጅና በሐውልት ማቆም አንገት አስደፊነት ተግባር ያልተሰበረው ወኔ፣ በዛሬው የብአዴንና የአገዛዙ ሱሪ የማስፈታት ዘመቻ ከቶ ድል አይደረግም።
ጥቅሙን፣ ጉዳቱንና ክብሩን አሳምሮ የሚያውቅ፣ ፍትሐዊ ባለሚዛን የሆነው የአማራ ሕዝብ—ትናንት ጅራፍ እያጮኸ ያልተሰማውን አጠቃላይ ብሶቱን፣ ዛሬ በእውነተኛው የፋኖ ክንድና በጥይት አረር እየታገለ፣ መብቱንና ሕልውናውን እያስከበረ ይገኛል። ከትናንት እስከ ዛሬ ባልተለወጠው የገዢዎች ክፋት፣ ሴራና የወገናችን መራር አኗኗር ውስጥ አንድ ቋሚና የማይናወጥ ትልቅ እሴት አለ፤ እርሱም የአማራ ሕዝብ እምቢ ባይነትና የማይበገር ወኔ ነው!
ድል ለአማራ የህልውና ትግል! 🎯
8 649
መሐል አዲስ አበባ ሆኜ ከአገዛዙ ጋር እንዲህ ስተናነቅ የብአዴን ከዳሚ የነበሩ ግለሰቦች ዛሬ ላይ አማራነትን ሊያስተምሩኝ ሲዳዱ እንደማየት ያለ ነውር የለም!
ብቻችንን ነበርን ፤ አሁን እልፍ ሆነናል!
ይኸው ነው!
8 649
🎯 የአማራነት ጽኑ አለት አርበኛ ስለሺ ከበደ!
(አዲሱ ደረበ)
በትግል አውድማ ላይ ከሁሉ በላይ የሚያስደንቀኝና ልቤን የሚነካው፣ ስማቸው በየሚዲያው በጉልህ ሳይጻፍ ነገር ግን በላብ፣ በደምና በአጥንታቸው ትልቅ ታሪክ የሚሠሩ ጥንቅቅ ያሉ እውነተኛ ጀግኖች መኖራቸው ነው። አርበኛ ስለሺ ከበደ ለእኔ ተራ የትግል አጋር አይደለም፤ አብሬው መራራውን የትግል ጽዋ የተቀበልኩት፣ በርካታ ዋጋዎችን የከፈልንበትና ወንድምነቱን በተግባር ያረጋገጠልኝ የቁርጥ ቀን ጀግናዬ ነው።
የስለሺ የአማራነት ተጋድሎ የትናንት እና የዛሬ ትኩስ ታሪክ አይደለም። በወያኔ የጨለማ ዘመን አማራነትን ቀና ለማድረግና የሕዝባችንን ክብር ለማስጠበቅ ሲታገል፣ በአስፓልት ላይ እስከመጎተትና እስከ ከባድ ግርፋት ድረስ አሰቃቂ እንግልቶችን አስተናግዷል። ወጣትነቱን ሙሉ በሙሉ ለአማራነት ለመገበር ወደ ኤርትራ በረሃ ወርዶ፣ በአዴሃን ውስጥ ከአባልነት እስከ አመራርነት ድረስ በጽናት ታግሏል። ወደ ሀገር ቤት ከተመለሰ በኋላም ቢሆን፣ እንደ አንዳንዶቹ አጋጣሚ ጠባቂዎች በብአዴን የጥቅም ድርጎ ሳይደለልና ሳይሸጥ፣ ስለ አማራነት መራራውን መንገድ መርጦ ተንከራቷል፤ በሰኔ 15ቱ አሰቃቂ ሁነትም በእስር መማቀቁ የታወቀ ነው።
ከእስር በኋላ ከእኔ ጋር በአካል ተገናኝተን፣ ከብዙ ጥልቅ ምክክሮች በኋላ በጋራ በፈጠርነው የህቡዕ አደረጃጀት የጠላትንና የብአዴንን ጉሮሮ ያነቀ፣ በርካታ አስደናቂ ጀብዱዎች የተፈጸሙበት ትልቅ ምዕራፍ ነበር። የእርሱ እምቅ አቅምና የአማራነት ቁጭት በእውነት ልዩ ነው። ወታደራዊና ፖለቲካዊ እውቀቱን ከቁጭት ጋር አዋህዶ የያዘ ጀግና ጠበብት ነው ስለሺ። ክንዱ አይዝልም፤ እኔ ራሱ አንዳንዴ በብዙ ውጣ ውረድ ደከም ያልኩ ሲመስለው፣ ያለመሰልቸት በሞራልና በትግል ወኔ በመወትወትና በማነቃቃት ወንድምነቱን በተግባር አሳይቶኛል። ያቀደውን ነገር መሬት ላይ አውርዶ በተግባር ሳይፈጽም እረፍት የሚባል ነገር አያውቅም።
የጎጃምን ምድር ብትመለከቱ፣ እርሱ ያልረገጠው አንድም የገጠር ቀበሌ የለም። ከአባይ ሸለቆ እስከ ሶማ፣ ከየጁቤ ኮርክ እስከ ቡሬ ቁጭ፣ ከሞጣ እስከ ደንበጫ፣ ከዳንግላ እስከ መተከልና አቸፈር ድረስ በእግሩ አዳርሶ በርካቶችን አሰልጥኗል፣ አስታጥቋል፣ ለአብዮት አብቅቷል። በግል ጥረቱ ብቻ ከ85 በላይ ክላሽንኮቭ ጠመንጃዎችን በገንዘቡ እየገዛ ወገኖቹን ታጣቂ ያደረገ ልባም ነው። በሕዳር 2016 ዓ.ም በዳንግላ ወረዳ፣ ጫራ ላይ ከ1170 በላይ ብቃት ያላቸውን ፋኖዎች አሰልጥኖ፣ ከተከታታይ ንቅናቄዎች በኋላ ዛሬ የምንኮራበት የሰከነና የጸና መደበኛ የፋኖ ጦር እንዲኖረን ያደረገው ይኸው አርበኛ ነው። የታዋቂው የቢትወደድ መንገሻ ጀምበሬ ብርጌድ ዋና አዋላጅም እርሱ ነው።
ከሁሉም በላይ ደግሞ በጠላት ሴራና በእነ ሰማ ጥሩነህ ይቀነቀን የነበረውን እኩይ የአገው ሸንጎ አጀንዳ የበጣጠሰበትና ያከሸፈበት ጀግንነቱ ሁሌም ያስደምመኛል። የጎጃም አገው ምድርንና ጃዊ መተከልን ከብአዴን እኩይ ሴራ አላቆ፣ ወደ አማራነት ትግል ማዕበል አዋህዶ ያስገባቸው የቁርጥ ቀን አርበኛ ነው።
ከአዲስ አበባ እስከ ደብረ ማርቆስና ባሕር ዳር ድረስ የባንዳዎችን አንገት የሚያስደፋ፣ የቴዎድሮስ ዕዝን አንድነት ለመገንባት ሌት ተቀን የደከመና ለዛሬው ሕዝባዊ ተጋድሎም በፊተኝነት የቆመ የሕዝብ አለት ነው።
እውነት ለመናገር፣ የነዚህን መሰል ጀግኖች ተጋድሎ ስመለከት አሁንም እጅግ ይደንቀኛል። ጀግናን መፍጠር ብቻ ሳይሆን፣ የተፈጠሩ ጀግኖችን መጠበቅና መንከባከብም ልምዳችን ሊሆን ይገባል፤ ምክንያቱም ያለ መሪና ያለ መስዋዕትነት የሚመጣ ድል የለምና!
አርበኛ ስለሺ ከበደ በርታልኝ አንበሳው!
ድል ለአማራ የህልውና ትግል! 🎯
8 649
+3
እናንተ የዐማራ ህያው ጀግናቻቸን ሆይ ፦ የተሰዋችሁለትን አላማ ከግብ እናደርሳለን!
ደመቀ የተባለው ገረድ ደማችሁን ረግጦ ለዘረ-ፈጁ ስርአት በመገበር የተሰዋችሁለትን ህዝብ እየፈጀ መሆኑን ብታዩ ምን ይሰማችሁ ይሆን?
በአማራ ልብ ውስጥ ለዘለአለም ታትማችሁ ትኖራላችሁ!
