በክርስቶስ
በልጁ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው ዮሐንስ ወንጌል 3፥36
Show more781
Subscribers
-124 hours
-47 days
-2330 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
👩💻👩💻 #ስለ_መጽሐፍ_ቅዱስ🧑💻🧑💻
❖ የመጀመሪያው መጽሐፍ ቅዱስ የተፃፈው በእብራይስጥ፣ በአረማይክ እና በኮይኔ ግሪክ ቋንቋዎች ነው።
❖ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ
• 66 መጽሐፍት
• 1,189 ምዕራፎች
• 31,173 አንቀፆች
• 810,697 ቃላት
• 3,566,480 ፊደላት ይገኛሉ።
❖ በጣም ረጅሙ መጽሐፍ- መዝሙረ ዳዊት ሲሆን
• በጣም አጭሩ መጽሐፍ- ሶስተኛ ዮሐንስ
• በጣም ረጅሙ ምዕራፍ- መዝሙረ ዳዊት 119
• አጭሩ ምዕራፍ መዝሙረ ዳዊት 117 ነው።
❖ የመጽሐፍ ቅዱስ አማካይ ስፍራ መዝሙረ ዳዊት 118:8 ነው።
❖በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የብዙ ሰዎች መጠሪያ የሆነው ስም ዘካሪያስ ነው።
❖ ሙሉው መጽሐፍ ቅዱስ እና የትንቢተ ኢሳይያስ መጽሐፍ አስደናቂ መመሳሰል አላቸው።
ይኸውም፦
• መጽሐፍ ቅዱስ #66 መጽሐፍ ሲኖሩት ትንቢተ ኢሳይያስ #66 ምዕራፎች አሉት።
• የመጀመሪያው #39 የመጽሐፍ ቅዱስ መጻሕፍት የሚተርኩት ስለ እስራኤል ህዝብ ነው። እንደዚሁም የመጀመሪያው የትንቢተ ኢሳይያስ #39 ምዕራፎች የሚተርኩት ስለ እስራኤል ህዝቦች ነው።
• የመጨረሻው #27 የመጽሐፍት ቅዱስ መጻህፍት የሚያስተምሩት ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን፤ እንደዚሁም የመጨረሻዎቹ #27 የትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፎች የሚተርኩት ስለ ክርስቶስ መምጣት ነው።
❖ መጽሐፍ ቅዱስ ተፅፎ ያለቀው በ1600 ዓመታት የጊዜ ልዩነት ውስጥ ሲሆን ይህም ከ1500 ዓመተ ዓለም እስከ 100 ዓመተ ምህረት ድረስ ያለውን ዘመን ያጠቃልላል።
❖ መጽሐፍ ቅዱስ በእግዚአብሔር ተልከው ቅዱሳን ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው የጻፉት መጽሐፍ ነው።( 2ጴጥ 1:21)
❖ በመጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ 49 የምግብ ዓይነቶች ተጠቅሰዋል፤ በተለይ "ጨው" #30 ጊዜ ተጠቅሷል።
❖ ከቤት እንሰሳት መካከል ስሟ ያልተጠቀሰ እንሰሳ "ድመት" ብቻ ናት።
ውሻ #14 ጊዜ ተጠቅሷል።
❖ በመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ ውስጥ እራሳቸውን በራሳቸው ያጠፉ ሰዎች ሰባት ሲሆኑ
እነርሱም፦
1. አቤሜሌክ
2. ሳምሶን
3. ሳዖል
4. የሳዖል ወታደር
5. አኪጦፌል
6. ዚምራ
7. ይሁዳ ናቸው።
❖ በመጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ
ስለ ፀሎት 400 ጊዜ
ስለ እምነት 500 ጊዜ
ስለ ገንዘብና ሐብት ደግሞ 2,000 ጊዜ ተፅፏል። መጽሐፍ ቅዱስ ገንዘብን መውደድ የኃጢአት ሁሉ ስር ነው ይለዋል።
❖ መጽሐፍ ቅዱስ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ እንግሊዝኛ የተተረጎመው በ 1388 ዓ.ም ነው።
ምንጭ፦ ቅዱሳን መፅሐፍት
@jjjeesuuss
👍 3
📍እኛ አንተን ከወደድንበት ፍቅር ይልቅ አንተ እኛን የወደድክበት ፍቅር ላይ እርግጠኞች ነን::
”ከክርስቶስ ፍቅር የሚለየን ማን ነው? ችግር ነው ወይስ ሥቃይ፣ ወይስ ስደት፣ ወይስ ራብ፣ ወይስ ዕራቍትነት፣ ወይስ አደጋ፣ ወይስ ሰይፍ?“
ሮሜ 8:35
.
▷ @jjjeesuuss◁
▷ @jjjeesuuss◁
❤ 1
ደስታ የራቀህ፣ የተጎሳቆልህ፣ ያፈገፈግህ፣ የተሸነፍክ ክርስቲያን ወዳጄ ዕድለኛ ነህ
እግዚአብሔር (አባካኙን ልጁን እንደሚወድ አባት) ይወድሃል። ወደ እግዚአብሔር ፊትህን መልስ፣ ልቡ አንተን ይናፍቃል። ያለፈውን ሁሉ ይረሳል።
__Martyn Lloyd-Jones
@jjjeesuuss
❤ 1
{~ ይቅርታዬ🙏~}
አልበደልሁም አልል በደሌን አውቃለሁ ፣
ቃሉን እረስቼ ሥስት ተይዥያለሁ
ውዴ ጋር ያመጡኝ ውሸት አይደል ክሴ ፣
ስጋዬስ ይወገር ምን ይዋጣት ነፍሴ
ከሚል ቃል በስተቀር አፌ አልተናገረም ፣
ይቅርታም ፈልጎ ቃሌ አለመነም
እማር ይሆን ብዬ ላፍታም አላሰብኩም ፣
ለዚህ ሁሉ በደል ምህረት አልጠበቅኩም ።
ግን ከከሳሾቼ ጫጫታ የኔን ዝም ማለት ሰምቶ፣
ክሴን ከመዝገብ አጣፋው ዳግም ህይወት ለኔ ሽቶ
ይቅርታዬ ተነሺ አለኝ ጉድፍ ልብሴን አጸዳድቶ ፣
አዲስ ቃልኪዳን አስጋበኝ ምንዝር መሆኔን እረስቶ
ባጎነበሰው ጀርባዬ ወጋሪ ድንጋይ ስጠብቅ ፣
በፍቅሩ ወግርት ወገረኝ አንገት ደፍቼ እንዳልማቅቅ
ኃጢአት ያልሰራ ይውገራት ሲል ከሳሾቼ ሁሉ ጠፉ፣
ልውገርሽ ያለ አንድ የለም ብዙ በደል ስላቀፉ
ግን አንድ ንፁህ ነበረ በኃጢአት በደል ያለደፈ፣
እንኳንስ እኔን ልወግረኝ ለኔ ጥፋት ተገረፈ
ልፍረድብሽ አላለኝም ፍርዴን ራሱ ተቀበለ፣
ለኃጢአቴ ኃጢአት ሆኖ በመስቀል ላይ ለኔ ዋለ
ዋጋዬን ራሱ ከፈለ ሲሰቀል እርቃኑ ታየ፣
እኔን ሲወድ እየሱሴ እኔን ሆኖ ተሰቃየ
ብቻ የኃጢአቴን ፅዋ ጠጣ ሞቴን ሞተ በፈንታዬ፣
ልጅነትን ሊለግሰኝ እየሱስ ሆነኝ ይቅርታዬ።
@jjjeesuuss
ኢየሱስ ፍፁም ሰው ነው ፍፁም አምላክ ነው::
ግማሽ ሰው ግማሽ አምላክ የለንም
🙅♀🙅♀🙅♀🙅♀🙅♀🙅♀🙅♀🙅♀🙅♀🙅♀
@jjjeesuuss
👍 2