497
Subscribers
No data24 hours
-127 days
-1430 days
Posts Archive
ዝርዝራችሁ የተጠቀሰው ሁሉ
ከዚህ በፍት በወጣው ማስታወቂያ የፋይዳ መታወቂያችሁን ኮፒ አድርጋችሁ ለስራ ክፍላችን እንዲታመጡ መጠየቃችን የሚታወቅ ሲሆን፣ ነገር ግን እስካሁን ያላቀረባችሁ በመሆኑ እስከ ዓርብ ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንዲታቀርቡ በጥብቅ እናሳውቃለን።
ከብቃት ና የሰው ሀብት ስራ አስፈጻሚ
29/11/2018
ማስታወቂያ
ለሚኒስቴር መ/ቤታችን ሠራተኞች በሙሉ
የመ/ቤታችን ሶሻል ኮሚቴ ለሁሉም ሠራተኞች ስኳር ለማምጣት ፕሮግራም የያዙ በመሆኑ የአንድ ኪሎ ዋጋ 175 ብር ሲሆን አንድ ሰው 3 ኪሎ መውሰድ የሚችል በመሆኑ በየስራ ክፍል ተሰብስቦ ከነዝርዝሩ ብሩን ለወ/ሮ አያልነሽ እንዲትሰጡ እናሳውቃለን።
ኮሚቴው
ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም እንደ ሀገር በአንድ ጀምበር # 800 ሚሊዮን ችግኞችን # ለመትከል መንግስት ፕሮግራም መያዙን አሳውቀውናል።
ስለሆነም ሁሉም የሚኒስቴር መ/ቤታችን ሠራተኞች በዚህ ታሪካዊ ተግባር ላይ እንዲንሳተፍ መ/ቤታችን ዝግጅቱን ያጠናቀቄ በመሆኑ ሰኞ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12:30 ላይ በዋናው መ/ቤት በመገኘት በተዘጋጀው ትራንስፖርት በጋራ ችግኝ ተከላው ቦታ እንዲንሄድ እናሳውቃለን።
የብቃት እና የሰው ሀብት አስተዳደር ሥራ አስፈፃሚ
ቀን 21/11/2018
ማስታወቂያ
የሚኒስቴር መ/ቤታችን ባልደረባ የሆኑት የወ/ሮ አበባ ተረፈ እናት ስላረፉ ቀብራቸው ዛሬ ከቀኑ 8:00 ሆለታ ወልመራ ሚካኤል የሚፈፀም መሆኑን እንገልጻለን።
ስልካቸውም 0900310304
የአቶ አረጋ አድስ የሀውልት ምረቃ እና የ40 ቀን መታሰቢያ ላይ ሁሉም ሠራተኞች እንዲትገኙ የተላለፈ ጥሪ ነው።
ቀን 12/11/2018
ማስታወቂያ
ከዚህ በፊት ነፃ የጤና ምርመራ ለማድረግ የተመዘገባችሁ ሴት ሰራተኞች ማክሰኞ በ 14/11/2018 ጳውሎስ ሆስፒታል ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በመገኘት ምርመራ እንድታደርጉ እናሳውቃለን።
የሰቶችና ማ/ጉዳዮች ስራ አስፈፃሚ
ቀን 04/11/2018
ማስታወቂያ
ለሚኒስተር መ/ቤታችን ሠራተኞቾ
ነጌ ሐምሌ 05 ቀን 2018 የምክክር ኮምሽን ያዘጋጀው ሩጫ ስላለ መሳተፍ የሚትፈልጉ ከጠዋቱ 12:30--1:00 ቢሮ በመገኘት ትሸርት በመውሰድ እነንዲትሳተፉ ተጋብዛችሃል።።
ወ7ሮ አመሐወርቅ ሕዝቀልን ማነጋገር ይቻሊል።
ቀን 29/10/2018
ማስታወቂያ
የሚኒስቴር መ/ቤታችን ባልደረባ የሆኑት አቶ አያለው ቦጋለ እህታቸው ከዚህ አለም ድካም ማረፋቸውን የተረዱ ስለሆነ መድረስ የሚትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
ቤታቸው ገርጂ መብራት ሀይል ወረቀት ፋብሪካ አካባቢ ነው።
የብቃት እና የሰው ሀብት አስተ/ሥራ አስፈፃሚ
ቀን 29/10/2018 ዓ. ም
ማስታወቂያ
ለሁሉም ሠራተኞች በሙሉ
ዛሬ ሰኔ 29/10/2018 ዓ.ም ከ7:00 ሰዓት ጀምሮ ሞጆ ደረቅ ወደብ ጉብኝት ስላለ
በተጠቀሰው ቀን እና ሰዓት ዋና ቢሮ እንዲትገኙና በተዘጋጀው ትራንስፖርት እንዲትሄዱ እናሳስባለን።
አዘጋጆች
