Addis Ababa City land Development And Administration Bureau
Open in Telegram
Show more
5 423
Subscribers
+824 hours
+137 days
+10230 days
Posts Archive
+3
ቂርቆስ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር ቅ/ጽ/ቤት በ2018 ላከናወናቸው ሰው ተኮር ተግባራት የገንዘብ ደጋፍ በማድረግ ያገዙ ባለሀብቶችን አመሰገነ።
ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ መጭውን አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግም ከነዚሁ ባለሀብቶች ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ ለአቅመ ደካሞችና ዝቅተኛ ደሞዝ ተከፋይ ሰራተኞቹ ማዕድ አጋርቷል።
ጳጉሜን 05/2018 (መልአ)
ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ከመደበኛ ተግባራቱ በተጓዳኝ ሰው ተኮር ተግባራትን የእቅዱ አካል በማድረግ እንደሚሰራ የገለፁት የቅ/ጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ሙሉነህ ሙሉጌታ ከዚህም ባለሀብቱን በማስተባበር በቀጣይ በክፍለ ከተማው የሚገኙ 6 ጽ/ቤቶች የሚያስገነቡት የበጎነት መንደር አንዱ ነው ብለዋል።
ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በዛሬው ዕለትም እንደ ወትሮው ሁሉ መረዳዳትን ባህል ካደረጉ ባለሀብቶች በተገኘ የገንዘብ እና የአይነት ድጋፍ ከ250 በላይ ለሚሆኑ አቅመ ደካም ወገኖች፣ ለወላጅ አጥ ህፃናትና ዝቅተኛ ደሞዝ ተከፋይ ለሆኑ ሠራተኞቹ መጭውን አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ ማዕድ አጋርቷል።
በከተማ ደረጃ "ዲጂታል የአንድ ማዕከል እና የሞሰብ አገልግሎት ሥርዓትን" በመዘርጋት በ25 ተቋማት ከ150 በላይ አገልግሎቶችን መስጠት መቻሉ ተገለፀ።
ይህ የተገለፀው የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ "የላቀ አገልግሎት አሰጣጥን ለህዝባዊ አመኔታ" በሚል በተዘጋጀ ሰነድ ላይ ባደረገው የውይይት መድረክ ላይ ነው።
ጳጉሜን 05/2018 (መልአ)
***************************
የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ዛሬ የተከበረውን የነገን ቀን አስመልክቶ "የላቀ አገልግሎት አሰጣጥን ለህዝባዊ አመኔታ" በሚል የአገልግሎት አሰጣጥ ውስብስብነትን በመቅረፍ የአስተሳሰብ ለውጥ ማምጣት የሚያስችል ሰነድ ላይ ውይይት አድርጓል
በቀረበው ሰነድ እንደተመላተው በከተማ ደረጃ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት እና የ"ሞሰብ" ሥርዓትን በመዘርጋት በ25 ተቋማት ከ150 በላይ አገልግሎቶችን በመስጠት ከ400 ሺህ በላይ ተገልጋዮችን ማስተናገድ ተችሏል።
በሂደቱ የስነ-ምግባር ክፍተቶች፣ አሰራርን ማብዛትና ብሮክራሲ መከተል፣ የተወሳሰበ የአገልግሎት አሰጣጥ፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ውስንነት እንዲሁም የአመራር ክትትልና ድጋፍ ማነስ እንደ ዋና ዋና ተግዳሮቶች ተለይተዋል።
ክፍተቶችን ለመቅረፍ ድግግሞሾችን በማስወገድ አገልግሎትን ማሳጠር፣ የወረቀት ሥራን በቀነሰ መልኩ ዲጂታላይዜሽንን ማስፋፋት፣ የተቀመጡ የሥራ ደረጃዎችን (ስታንዳርዶች) በመጠቀም አፈጻጸምን መለካት እና ለውጥን በቅንጅት መተግበርም ቁልፍ ስልቶች ሆነው ተቀምጠዋል።
ለግቦች ስኬታማት ሠራተኞች አገልጋይነትን መርህ በማድረግ፣ ሙያዊ ሥነ-ምግባርን በመላበስ፣ ዲጂታል ብቃትን በመገንባት እና ቀጣይነት ያለው መሻሻል በማሳየት የህዝብን አመኔታ ከፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው አጽንኦት የተሰጠው ሲሆን አመራሩ የተግባር አርያነትን በማሳየት ግንባር ቀደም ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል ተብሏል።
+7
በከተማ ደረጃ "ዲጂታል የአንድ ማዕከል እና የሞሰብ አገልግሎት ሥርዓትን" በመዘርጋት በ25 ተቋማት ከ150 በላይ አገልግሎቶችን መስጠት መቻሉ ተገለፀ።
ይህ የተገለፀው የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ "የላቀ አገልግሎት አሰጣጥን ለህዝባዊ አመኔታ" በሚል በተዘጋጀ ሰነድ ላይ ባደረገው የውይይት መድረክ ላይ ነው።
ጳጉሜን 05/2018 (መልአ)
***************************
የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ዛሬ የተከበረውን የነገን ቀን አስመልክቶ "የላቀ አገልግሎት አሰጣጥን ለህዝባዊ አመኔታ" በሚል የአገልግሎት አሰጣጥ ውስብስብነትን በመቅረፍ የአስተሳሰብ ለውጥ ማምጣት የሚያስችል ሰነድ ላይ ውይይት አድርጓል
በቀረበው ሰነድ እንደተመላተው በከተማ ደረጃ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት እና የ"ሞሰብ" ሥርዓትን በመዘርጋት በ25 ተቋማት ከ150 በላይ አገልግሎቶችን በመስጠት ከ400 ሺህ በላይ ተገልጋዮችን ማስተናገድ ተችሏል።
በሂደቱ የስነ-ምግባር ክፍተቶች፣ አሰራርን ማብዛትና ብሮክራሲ መከተል፣ የተወሳሰበ የአገልግሎት አሰጣጥ፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ውስንነት እንዲሁም የአመራር ክትትልና ድጋፍ ማነስ እንደ ዋና ዋና ተግዳሮቶች ተለይተዋል።
ክፍተቶችን ለመቅረፍ ድግግሞሾችን በማስወገድ አገልግሎትን ማሳጠር፣ የወረቀት ሥራን በቀነሰ መልኩ ዲጂታላይዜሽንን ማስፋፋት፣ የተቀመጡ የሥራ ደረጃዎችን (ስታንዳርዶች) በመጠቀም አፈጻጸምን መለካት እና ለውጥን በቅንጅት መተግበርም ቁልፍ ስልቶች ሆነው ተቀምጠዋል።
ለግቦች ስኬታማት ሠራተኞች አገልጋይነትን መርህ በማድረግ፣ ሙያዊ ሥነ-ምግባርን በመላበስ፣ ዲጂታል ብቃትን በመገንባት እና ቀጣይነት ያለው መሻሻል በማሳየት የህዝብን አመኔታ ከፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው አጽንኦት የተሰጠው ሲሆን አመራሩ የተግባር አርያነትን በማሳየት ግንባር ቀደም
የነገው ቀን
ሀገራዊ የቴክኖሎጂ ሽግግር
ከወረቀት ወደ ዲጂታል፤ ከተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት! ትናንትን በመማርና በማረም ዛሬን በላቀ ትጋት በመገንባት ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን የዕለት ተዕለት ባህላችን እየሆነ ነው። ንግድና አገልግሎትን ያቀላጥፋል፣ መረጃዎችን ተደራሽ ያደርጋል፣ ዘርፎችንም ያዘምናል! የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያ ኮደሮች ንቅናቄ ወጣቶችን የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፈጣሪ በማድረግ ወደ 7 ሚሊዮን ግባችን እያመራ ሲሆን የዲጂታል አገልግሎት ተደራሽነትና ጥራትን አረጋግጧል። በሀገር በቀል አቅም የበለጸገው የሳይበር ሉዓላዊነታችን ደግሞ የማንቆጣጠራቸው ቴክኖሎጂዎችን ጥገኝነት አላቆ በዲጂታል ኢኮኖሚ በራስ አቅሟ የምትቆም አዲሷ ኢትዮጵያ በታላቅ ምዕራፍ ላይ መሆኗን በኩራት ያበስራል!
#DigitalEthiopia2030
Guyyaa Borii
Cehumsa Tekinooloojii Biyyaalessaa waraqatarraa gara dijiitaalaa, fayyadamtummaarraa gara kalaquutti! Kaleessa barachuufi sirreessuun, har’a kutannoo olaanaan ijaaruun tiraanisfoormeeshiniin dijiitaalaa aaddaa keenya hoggayyuu ta’aa jira. Daldalaafi tajaajila ni si’oomsa, walgeettii odeeffannoo ni mirkaneessa, sektaroota ni ammayyoomsa! Sochiin Koodaroota Itoophiyaa miliyoona 5 dargaggoota kalaqxoota artifiishaal intelejensii taasisuudhaan galma keenya miiliyoona 7tti qajeelaa kan jirru yoo ta’u, walgeettiifi qulqullina tajaajila dijiitaalaa mirkaneesseera. Birmadummaan saayiberii humna biyyaalessaatiin gabbate immoo maxxantummaa tekinooloojiiwwan to’achuu hin dandeenyerraa nu baraaree, Itoophiyaan haaraa misooma dijiitaalaatiin humna mataa isheetiin dhaabbattu boqonnaa haaraarra ta'uushee kabajaan ni labsa!
#DigitalEthiopia2030
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር)
የነገው ቀን
ሀገራዊ የቴክኖሎጂ ሽግግር
ከወረቀት ወደ ዲጂታል፤ ከተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት! ትናንትን በመማርና በማረም ዛሬን በላቀ ትጋት በመገንባት ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን የዕለት ተዕለት ባህላችን እየሆነ ነው። ንግድና አገልግሎትን ያቀላጥፋል፣ መረጃዎችን ተደራሽ ያደርጋል፣ ዘርፎችንም ያዘምናል! የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያ ኮደሮች ንቅናቄ ወጣቶችን የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፈጣሪ በማድረግ ወደ 7 ሚሊዮን ግባችን እያመራ ሲሆን የዲጂታል አገልግሎት ተደራሽነትና ጥራትን አረጋግጧል። በሀገር በቀል አቅም የበለጸገው የሳይበር ሉዓላዊነታችን ደግሞ የማንቆጣጠራቸው ቴክኖሎጂዎችን ጥገኝነት አላቆ በዲጂታል ኢኮኖሚ በራስ አቅሟ የምትቆም አዲሷ ኢትዮጵያ በታላቅ ምዕራፍ ላይ መሆኗን በኩራት ያበስራል!
#DigitalEthiopia2030
Guyyaa Borii
Cehumsa Tekinooloojii Biyyaalessaa waraqatarraa gara dijiitaalaa, fayyadamtummaarraa gara kalaquutti! Kaleessa barachuufi sirreessuun, har’a kutannoo olaanaan ijaaruun tiraanisfoormeeshiniin dijiitaalaa aaddaa keenya hoggayyuu ta’aa jira. Daldalaafi tajaajila ni si’oomsa, walgeettii odeeffannoo ni mirkaneessa, sektaroota ni ammayyoomsa! Sochiin Koodaroota Itoophiyaa miliyoona 5 dargaggoota kalaqxoota artifiishaal intelejensii taasisuudhaan galma keenya miiliyoona 7tti qajeelaa kan jirru yoo ta’u, walgeettiifi qulqullina tajaajila dijiitaalaa mirkaneesseera. Birmadummaan saayiberii humna biyyaalessaatiin gabbate immoo maxxantummaa tekinooloojiiwwan to’achuu hin dandeenyerraa nu baraaree, Itoophiyaan haaraa misooma dijiitaalaatiin humna mataa isheetiin dhaabbattu boqonnaa haaraarra ta'uushee kabajaan ni labsa!
#DigitalEthiopia2030
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር)
+4
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የኅብር ቀንን ማዕድ በማጋራት አከበረ፡፡
ጳጉሜን 04/2018 (መልአ)
********
አብሮነትና መደጋገፍን የሚያንጸባርቀው "የኅብር ቀን" የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ከማዕከል እስከ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ሰው ተኮር ተግባራትን ባጎላ መልኩ አክብሯል።
የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በተገባደደው 2018 በጀት ዓመት ከመደበኛ ስራዎቹ ባሻገር ባህልንና እሴትን መሰረት አድርጎ ለሰው ተኮር ተግባራት ቅድሚያ በመስጠት በበዓላት ወቅት ድጋፍ ለሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎች ልዩ ትኩረት መስጠቱን ከቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የተገኘ መረጃ ያመላክታል።
ዛሬም መጭውን አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ ባለሃብቱን በማስተባበር ድጋፍ ለሚሹ 200 የህብረተሰብ ክፍሎች፣ ለወላጅ አልባ ህፃናት እንዲሁም ዝቅተኛ ደመወዝ ለሚከፈላቸው የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ሰራተኞች ማዕድ አጋርቷል።
በመርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የመሬት ዝግጅትና ማስተላለፍ ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የቢሮው ኃላፊ ተወካይ አቶ ፌኑስ ገላና እንደገለጹት፣ ቢሮው ከመደበኛ አገልግሎት አሰጣጡ በተጨማሪ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በአግባቡ በመወጣት አርዓያነት ያለው በጎ ተግባር ማከናወኑን አውስተው
በዚህ በጎ ተግባር ላይ አስተዋጽኦ ያደረጉት ልበቀና ባለሃብቶች አመስግነዋል።
+8
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ጳጉሜን 4 የኅብር ቀንን ማዕድ በማጋራት መርሃ-ግብር አክብሮታል
ጳጉሜን 04/2018 (መልአ)
*************************
የኢትዮጵያን ብዝሃነት፣ አብሮነትና የተቀናጀ ጥረት የሚያንጸባርቀው "የኅብር ቀን" በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ በታላቅ ድምቀት ተከብሯል። ዕለቱ የቢሮው ሰራተኞች እና አመራሮች አብሮነታቸውን አጠናክረው ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ቁርጠኝነታቸውን ያደሱበት ሁነት ሆኗል።
በዓሉን አስመልክቶ የመሬት ዝግጅትና ማስተላለፍ ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የቢሮው ኃላፊ ተወካይ አቶ ፌኑስ ገላና ቢሮው ከመደበኛ አገልግሎት አሰጣጡ በተጨማሪ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በአግባቡ በመወጣት አርዓያነት ያለው በጎ ተግባር ማከናወኑን አውስተዋል።
በዚህ በጎ ተግባር ላይ አስተዋጽኦ ያደረጉትን ልበቀና ባለሃብቶች አመስግነው፤ ቢሮው እንደወትሮው ሁሉ ለአቅመ ደካማ ቤተሰብ ልጆች፣ ለጸጥታ አስከባሪ የፖሊስ አባላት፣ በዘንድሮው ዓመት በጡረታ የተሰናበቱትን ጨምሮ ለተቋሙ ሠራተኞች ልዩ የማዕድ ማጋራት መርሃ-ግብር ስለማካሄዱ ገልፀዋል።
ይህ ማህበራዊ አብሮነትን ያጠናከረና ፍቅርን ያጎላ ሁነት፤ ተቋሙ የዜጎችን ማህበራዊ ደህንነትና ድጋፍ ለማረጋገጥ ያለውን ጥልቅ ሰብአዊ ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየበት እንደሆነም ተገልጿል።
በተመሳሳይ ዜና የንፋስ ስልክ ላፍቶ እና የኮልፌ ቀራንዮ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችም ድጋፍ ለሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎች የበአል አስቤዛን ጨምሮ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድርገዋል፡፡
+9
ዛሬ "በኅብር ቀን" ሀገር በቀል እሴቶቻችንን በተግባር በመጠቀም አብሮነትን፣ መረዳዳትንና ሰው ተኮር ተግባራትን ባህል እያደረግን ማህበራዊ ትስስርን ለማጠናከር በሁሉም ወረዳዎች፣ ክፍለከተሞች እና በማዕከል ለከተማችን ነዋሪዎች ማዕድ አጋርተናል።
ሁልጊዜ እንደምናደርገው ጧሪ ደጋፊ ለሌላቸው፣ ለማህበራዊ ችግር ለተጋለጡ፣ ለአረጋውያን፣ ለአቅመ ደካሞች፣ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ሰራተኞችን ጨምሮ ከለውጡ ዘመን ጀምረን እርስ በእርስ በመረዳዳት ያለው ለሌለው እንዲያካፍል በማድረግ ማዕድ እናጋራለን ።
ዛሬም ክረምቱን ሙሉ እና በበዓላት ስናጋራ እንደነበረው ሁሉ የማዕድ ብቻ ሳይሆን አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ እንኳን አደረሳችሁ በማለት ፍቅራችንን፣ አብሮነታችንን እና አክብሮታችንን ለከተማችን ነዋሪዎች አጋርተናል።
አዲሱን አመት የፍቅር፣ የሰላም፣ በትጋት ሰርተን የምንለወጥበት እንዲሆን እመኛለሁ።
መስጠት አያጎድልም ብለው በከተማችን በሙሉ የምናደርገውን የማዕድ ማጋራት ካላቸው አካፍለው አስተዋፅኦ ላደረጉ ባለሃብቶች፣ ማህበራት፣ ልበቀናዎች ፈጣሪ አምላክ አብዝቶ ይስጣችሁ፤ ከልብ እናመሰግናለን።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
የኅብር ቀን
ኢትዮጵያችን በሀገር በቀል እሴቶቿ፤ የነገውን ብሩህ ተስፋዋን በገዛ እጆቿ እየቀረጸች ትገኛለች!
በትውልድ ቅብብሎሽ ያገኘናቸውን ድንቅ የሀገር በቀል እሴቶቻችንን በማጎልበት እና በመደመር ፍልስፍና በመመራት፣ ለጽኑ ኅብረብሔራዊ አንድነታችን የማይናወጥ መሠረት ጥለናል። ታሪካዊውን ሀገራዊ ምክክር የመጀመር የታሪክ እጥፋት ተነስተን፣ የሁሉም ዜጎቻችንን ሕይወት ከሚለውጡ ሰው-ተኮር የኮሪደር ልማታችን፣ የበጎ ፈቃድ ስራዎቻችን እንዲሁም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃግብርን በተግባር እውን እስከማድረግ ድረስ፤ ሁላችንም በአንድነት ስንቆም የጋራ ትርክቶቻችን ወደ ጋራ ስኬት እንደሚያሻግሩን በተግባር አሳይተናል።
እኛ የምንገነባው አካታች የሆነች፣ በኢኮኖሚ ራሷን የቻለች፣ የአብሮነትና መረዳዳት ባህል የጎለበተባት ጠንካራ ሀገር ብቻ ሳይሆን የሁሉንም ኢትዮጵያውያን የጋራ ታላቅነትና እምቅ አቅም በተግባር እያረጋገጥን እንገኛለን። በአንድነት ወደ ብልጽግና ጉዟችን እንቀጥላለን።
አንድ ህዝብ፣ ታላቅ ሀገር ኢትዮጵያ!
#EthiopiaPrevails
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
አዲስ አበባ የአየር ንብረት አደጋዎችን በመቋቋም በዓለም 2ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ የምሥራች አበሰረች
ዓለም አቀፉ የጂኦስፓሻል አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ተቋም አልፋጂኦ (AlphaGeo) የዓለም ታላላቅ 72 ከተሞችን የአየር ንብረት አደጋ የመቋቋም አቅም (Climate Resilience) አመላካች ይፋ አድርጓል።
በዚህ አዲሱ ዓለም አቀፍ ደረጃ መሠረት መዲናችን አዲስ አበባ ከዓለም አቀፍ ከተሞች ሁሉ በ2ኛ ደረጃ ላይ በመቀመጥ አስደናቂ ስኬት አስመዝግባለች።
ጥናቱ የከተሞችን ዝግጁነት የለካው ከተፈጥሮ አደጋዎች ተጋላጭነት ነጻ በመሆናቸው ብቻ ሳይሆን አደጋዎችን የመከላከል፣ የማላመድ እና የመቋቋም አቅማቸውን መሠረት በማድረግ ነው።
በዚህ መሠረት የአሜሪካዋ ቺካጎ ከተማ በ1ኛ ደረጃ ላይ ስትቀመጥ፣ አዲስ አበባ ደግሞ እንደ ሜልቦርን፣ ባርሴሎና እና ፓሪስ ያሉ ታላላቅ የዓለም ከተሞችን በልጣ በዓለም 2ኛ ተስፋ ሰጪ እና ጽኑዕ ከተማ በመሆን ተመዝግባለች።
ይህ ታሪካዊ ውጤት በአዲስ አበባ ከተማ በመከናወን ላይ ያሉ የኮሪደር ልማት ሥራዎች፣ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር፣ የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ዘመናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታዎች ለከተማዋ አደጋዎችን የመቋቋም አቅም ያበረከቱትን ታላቅ አስተዋጽኦ በተግባር ያረጋገጠ ነው።
ጥናቱ እንደሚያመላክተው፣ ብዙኃኑ የደቡብ እስያ ከተሞች ለአየር ንብረት አደጋ ከፍተኛ ተጋላጭ ሆነው ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ወድቀዋል።
በዚህ ወቅት ታዲያ አዲስ አበባ ያስመዘገበችው ይህ የላቀ ደረጃ ሀገራችን ኢትዮጵያ በአካባቢ ጥበቃ እና ዘላቂ የከተሞች ልማት ላይ የምታደርገው ጥረት ፍሬ ማፍራቱን የሚያሳይ ነው።
መዲናችን ለነዋሪዎቿ ምቹ እና ደኅንነቷ የተጠበቀ የጽናት ተምሳሌት መሆኗን እየኖሩባት ላሉት ሁሉ የየቀን እውነት ቢሆንም አሁን ደግሞ ለዓለም ሁሉ የታወጀ ታላቅ ብስራት ነው።
“የተናበበ ተግባር ለውጤት“ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና አሰተዳድር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ።
ጳጉሜን 3 2018 (መልአ)
የየካ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በተጠናቀቀው የስራ ዘመን ለልማት ተነሺዎች ከ2.5 ቢሊዮን ብር በላይ የካሳ ክፍያ መፈጸሙን አስታወቀ።
ጳጉሜን 3/2018 (መልአ)
*******************
በመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ የየካ ክፍለ ከተማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በተጠናቀቀው 2018 በጀት ዓመት በኮሪደርና ወንዝ ዳርቻ ልማት ምክንያት ከመኖሪያ አካባቢያቸው ለተነሱ የግልና የቀበሌ ቤት የልማት ተነሺዎች ከ2.5 ቢሊየን ብር በላይ የካሳ ክፍያ መፈፀሙን አስታውቋል ።
ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ባካሄደው የ2018 የስራ ዘመን አፈፃፀምና የ2019 እቅድ ዝግጅት ላይ በመከረበት ወቅት የካሳ ክፍያው የዜጎችን መብት በማክበር ተገቢውን ምትክ በመስጠት መፈፀሙን የቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቢሆነኝ አበጋዝ ገልፀዋል።
የመልሶ ማልማት ሥራው ከተማዋን ለነዋሪዎች ጽዱ፣ አረንጓዴ እና ለኑሮ ተስማሚ ከማድረግ ባሻገር የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴውን ለማስፋፋት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለውም አክለዋል ።
የአርሶ አደሩን የረጅም ጊዜ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመፍታት በተሰራው ስራም በክፍለ ከተማው ለሚገኙ 781 አርሶ አደሮች የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ተዘጋጅቶ የተሰራጨ ሲሆን ልዩ የገቢ አሰባሰብ ንቅናቄ በማዘጋጀትም ከሊዝና ይዞታ አገልግሎቶች ከ674 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ መገኙቱን ከቀረበው የአፈፃፀም ሪፖርት ለማወቅ ተችሏል ።
በሁሉም ዘርፍ ለተገኘው ውጤት የቴክኖሎጂ አጠቃቀሙ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱን የገለፁት አቶ ቢሆነኝ በተያያዘው በጀት አገልግሎት አሰጣጥን ሙሉ ለሙሉ በሲስተም ለማስደገፍ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
በዚሁ መድረክ በበጀት ዓመቱ የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ሰራተኞች እና ለቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ስራ መቃናት አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለድርሻ ተቋማት የእውቅና ሰርተፍኬት የተበረከተ ሲሆን መጪውን አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግም ለዝቅተኛ ደመወዝ ተከፋይ ሰራተኞች ማዕድ ተጋርቷል።
የየካ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በተጠናቀቀው የስራ ዘመን ለልማት ተነሺዎች ከ2.5 ቢሊዮን ብር በላይ የካሳ ክፍያ መፈጸሙን አስታወቀ።
ጳጉሜን 3/2018 (መልአ)
*******************
በመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ የየካ ክፍለ ከተማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በተጠናቀቀው 2018 በጀት ዓመት በኮሪደርና ወንዝ ዳርቻ ልማት ምክንያት ከመኖሪያ አካባቢያቸው ለተነሱ የግልና የቀበሌ ቤት የልማት ተነሺዎች ከ2.5 ቢሊየን ብር በላይ የካሳ ክፍያ መፈፀሙን አስታውቋል ።
ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ባካሄደው የ2018 የስራ ዘመን አፈፃፀምና የ2019 እቅድ ዝግጅት ላይ በመከረበት ወቅት የካሳ ክፍያው የዜጎችን መብት በማክበር ተገቢውን ምትክ በመስጠት መፈፀሙን የቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቢሆነኝ አበጋዝ ገልፀዋል።
የመልሶ ማልማት ሥራው ከተማዋን ለነዋሪዎች ጽዱ፣ አረንጓዴ እና ለኑሮ ተስማሚ ከማድረግ ባሻገር የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴውን ለማስፋፋት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለውም አክለዋል ።
የአርሶ አደሩን የረጅም ጊዜ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመፍታት በተሰራው ስራም በክፍለ ከተማው ለሚገኙ 781 አርሶ አደሮች የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ተዘጋጅቶ የተሰራጨ ሲሆን ልዩ የገቢ አሰባሰብ ንቅናቄ በማዘጋጀትም ከሊዝና ይዞታ አገልግሎቶች ከ674 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ መገኙቱን ከቀረበው የአፈፃፀም ሪፖርት ለማወቅ ተችሏል ።
በሁሉም ዘርፍ ለተገኘው ውጤት የቴክኖሎጂ አጠቃቀሙ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱን የገለፁት አቶ ቢሆነኝ በተያያዘው በጀት አገልግሎት አሰጣጥን ሙሉ ለሙሉ በሲስተም ለማስደገፍ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
በዚሁ መድረክ በበጀት ዓመቱ የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ሰራተኞች እና ለቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ስራ መቃናት አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለድርሻ ተቋማት የእውቅና ሰርተፍኬት የተበረከተ ሲሆን መጪውን አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግም ለዝቅተኛ ደመወዝ ተከፋይ ሰራተኞች ማዕድ ተጋርቷል።
+5
ጳጉሜ 3 "የፅናት ቀን" በአዲስ አበባ ከተማ መሬት ነክ ተቋማት በተለያዩ ኩነቶች ተክብሯል፡፡
ጳጉሜ 3 2018 (መልአ)
*********************
ወረሃ ጳጉሜ የኢትዮጵያ ብቸኛ ወር ናት ።አምስት ቀኖች ያሉት የዘንድሮ ጳጉሜ ዛሬ 3ኛ ቀኑን ይዟል ጳጉሜ 3 "የፅናት ቀን" የሚል ስያሜም ተሰጥቶታል
አራቱ መሬት ነክ ተቋማት አመራርና ሰራተኞችም ዕለቱን ለሀገረ-መንግሥቱ ዘላቂነትና ሉዓላዊነት ለተከፈለው የጀግኖች መስዋዕትነት በማሰብና ክብር በመስጠት ፣አገራዊ ፅናት ለሕዝብ ሰላምና ለሁለንተናዊ እድገት መሠረት መሆኑን በማጎላት አክብረውታል።
የተቋማት ትስስርና ጥንካሬ ፣ የህዝብ አንድነት፣ኃላፊነትና ተሳትፎ ለሀገር ትልቅ መሰረት ነው።
ፅናት አልሸነፍ ባይነት፣በችግር ውስጥ ተስፋን መጠበቅና የተጀመረን ሁለንተናዊ ለውጥ በጥንካሬ ማስቀጠል ነው በማለትም የየተቋማቱ አመራርና ሰራተኞች በመጭው አዲስ ዓመት ከወትሮ በላቀ የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመቅረፍ በቅንነትና በታማኝነት ያለስስት በእውቀት በሙሉ አቅም ለማገልግል ቃል ገብተዋል።
ጳጉሜን 3/2018 ዓ.ም
የፅናት ቀን ፤-ለኢትዮጲያ ማንሰራራት መሰረት የሆነዉ ፅናታችን የሉዓላዊነታችን መሰረት ነው!
የኢትዮጵያ ብቸኛ ወር የሆነችው የጳጉሜ ወር በከተማ አስተዳደሩ በተለያዩ ሀገራዊ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል።
ጳጉሜ 3 "የፅናት ቀን" በአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ፤- የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀነራል አስራት ዴኔሮ ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ምክትልና የፀጥታ ኦፕሬሽን ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ደንድርን ጨምሮ ከፍተኛ የፖሊስ እና የደንብ ማስከበር አመራሮች የፀጥታ አካላት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በተለያዩ መርሀ ግብሮች ተክብሯል፡፡
የፀናች ሀገር መሠረት የተቋማት ጥንካሬ ብቻ ሳይሆን፣ የህዝብ አንድነት፣ኃላፊነትና ተሳትፎ ሲሆን ፅናት በፈተና ጊዜ አለመሸነፍ፣በችግር ውስጥ ተስፋን መጠበቅና የተጀመረን የለውጥ ጉዞ በጥራት እስከ መጨረሻ መፈፀምና ማስፈጸም ነው።
የዛሬ ፈተና የነገ ድል መሠረት በመሆኑ በጋራ በመተጋገዝ፣ በትዕግስትና በቁርጠኝነት ችግሮችን በመሻገር የተሻለ ነገን መገንባት እንችላለን።
የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀነራል አስራት ዴኔሮ በመርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው እንደተናገሩት የአዲስ አመት መሸጋገሪያ የሆነችው የጳጉሜ ወር ቀናት በተለያዩ ሀገራዊ ድሎችን በሚዘክሩ ስያሜዎች እየተከበሩ እንደሚገኙ ጠቁመዉ ቀደምት አባቶቻችን በአንድነት ቆመው የፀናች ሀገርን እንዳስረከቡን ሁሉ የአሁኑ ትውልድም ሀገርን በሚያፀኑ የልማትና የለውጥ ስራዎች በአንድነት በመቆም የሀገርን ፅናት ማረጋገጥና ማስቀጠል ይገባል ሲሉ ገልፀዋል፡፡
ጀነራሉ አክለውም በዱር በገደሉ ሀገርን ለማፅናት መስዋትነት እየከፈሉ ለሚገኙ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ታላቅ አክብሮት ሰጥተው ኢትዮጲያ በጀግኖች ልጆቿ ታፍራና ተከብራ ትኖራለች ብለዋል።
አቶ ተስፋዬ ደንድር የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ /ምክትልና የፀጥታ ኦፕሬሽን ዘርፍ ኃላፊ በበኩላቸዉ ኢትዮጲያውያን ለጋራ ዓላማ በጋራና በፅናት የሚኖሩ ህዝቦች መሆናቸውንና ለዚህም የአድዋ ድል ግንባር ቀደም ተጠቃሽ መሆኑን አንስተው አሁን ላይ ታላቁን የህዳሴ ግድብን ጨምሮ ሀገር እንድንታሰራራና ወደ ብልፅግና ማማ እንድትሄድ የለውጡ መንግስት ከመጣ ጀምሮ ውጤታማ ስራዎች በመስራት የጋራ ድምር ዉጤት እየተመዘገበ ይገኛል ብለዋል።
ኃላፊው አክለውም እንደ ሀገር የተገኙ ውጤቶችን ለማስቀጠል ውስጣዊ አንድነታችንን በማጠናከር፤ የይቻላል መንፈስን በማጎልበት፤ድህነትንና ተረጅነትን ታሪክ በማድረግ ኢትዮጲያን አፅንተን እናሻግር ሲሉም መልእክታቸዉን አስተላልፈዋል፡፡
በመርሐግብሩ የፌደራል ፖሊስ ፣ የአዲስ አበባ ፖላስ ፣ የደንብ ማስከበርና የእሳትና አደጋ አባላት የተለያዩ ትርኢቶችና ሀገርና የሚዘክሩ ሁነቶች ተካሂደዋል።
