en
Feedback
Kasuen Tech

Kasuen Tech

Open in Telegram

Tech insight

Show more
924
Subscribers
No data24 hours
-67 days
-2730 days
Posts Archive
የ10 ኣመት ህፃን ልጅ ነው ኪሱ ላይ ጥቂት ሳንቲሞችን ይዞ አንድ አነስተኛ ካፌ ቤት ጎራ አለ ሰው ጥቅ ብሏል ከህፃንነቱ የተነሳ ማንም ትኩረት አልሰጠውም ትንንሽ አይኖቹን ከርተት ከርተት አድርጎ አንድ ክፍት ወንበር አገኘና ሄዶ ቁጭ አለ .)- ምን ፈለክ...... አስተናጋጁዋ በቁጣ እና በንቀት (- እ....እእ....እ ...... አይስክሬም .እ..አለ ?? . ፦ ብርይዘሃል?...... ገልመጥ አድርጋ ጠየቀችው ህፃኑም ስንት ነው አላት ፦ 1 ብር ከ25 ሳንቲም ነው ስትለው ወድያው ኪሦቹ ውስጥ ያለውን ሳንቲሞች አውጥቶ መቁጠር ጀመረ አንድ ብር ከ ሃያ አምሥት ሳንቲም ነው የያዘው አስተናጋጇም ፦ "ቶሎ በል ባክህ ሌላ ስንት ምታዘዘው ሰው አለ አተ ሳንቲም ትቆጥራለህ" ብላ አመናጨቀችው ህፃኑም ሳንቲሞቹን ቆጥሮ ፦ " እሺ ኬክ ስንት ነው አላት ??.. ፦ " አንድ ብር" በቁጣ... ፦ " በቃ ኬክ  ስጪኝ ብሎ እጆቹን ዘርግቶ ሣንቲሞቹን ሰጣት ስትቆጥረውእንድ ብር ነው ኬኩን ውርውር አድርጋለት ሄደች ህፃኑም በልቶ ጨርሶ ወጣ አስተናጋጅዋም የበላበትን እቃ ለማንሳት እቃውን ስታነሳ ከ ሠህኑ ሾር ሃያ አምስት ሣንቲም አስቀምጦላት ነበር ስታይ ደነግጠች ወድያው እንባዋ ዱብ ዱብ ማለት ጀመረ ሥቅሥቅ ብላ አለቀሰች የሚወደውን እና የሚፈልገውን አይስክሬም ብር ከሃያ አምስት ሣንቲም ከፍሎ ከበላ ለአስተናጋጁዋ እሚሰጣት ነገር ስላነበረው ያልፈለገውን ኬክ በአንድ ብር በልቶ 25 ሳንቲሟን ለሡ ቲፕ አስቀምጦላት ሄደ ትንሹ ልጅ ትንሹዋን ነፍስያውን አሸንፎ ክብርን እዝነትንም መስጠትን በትህትና ላላስተናገደችዋ አስተናጋጅ አስተማራት። ለምታውቋቸው ሰዎች ሁሉ ሟር በማረግ ተባበሩ 🙏              👌👌@fkrlovelove

"እኔ አሁን በህይወቴ ላለው ሁሉም ነገር 100% ኃላፊነት ወስዳለሁ። አሁን ለምትኖረው ህይወት ደረጃ፣ ጥራት፣ ተጠያቂ የሆነ አንድ ሰው ብቻ አለ። እሱም ራስህ ነህ። እኛ ኢትዮጵያዊያን በተለይ በሌላ አካል ላይ የማሳበብ ውቅራችን ጠንካራ ይመስለኛል። ሌላ ሃገር ልጅ አደናቅፎት ሲወድቅ ከወላጆቹ  የሚወራው ቃል 'ተነስ።  አይተህ መሄድ ነበረብህ ' የሚል እና ልጆች ለውድቀታቸው ኃላፊነት እንዲወስዱ የሚገራ ነው። የእኛ አስተዳደግ ሲታይ ግን እንቅፋት መታኝ ብለን የምናለቃቅስ እና  የወላጆቻች እጅ ላይ ምራቅ ተፍተን ድንጋይ የተመታልን የድሮ ህጻናት የዛሬ እጅ ቀሳሪ አዋቂዎች ያደረገን ነው። ለመሆኑ ሰፈር ውስጥ እየተንጎራደደ ጠብቆ የሰውን እግር የመታ ድንጋይ አይታችሁ ታውቃላችሁ ወይ? አርፎ በተቀመጠበት በእግራችን ካልቾ ያልነው እኛ እንጂ። ግን ዛሬም ሰዎች እንቅፋት መታኝ እንጂ እንቅፋቱን መታሁት ሲሉ አይሰማም። በእኛ አለም ውጫዊ አካል ለውድቀታችን ተጠያቂ ነው። "በግልህ ኃላፊነት ልትወስድ ይገባል። ሁኔታዎቹን፣ ወቅቱን፣ ወይም የንፋሱን አቅጣጫ መቀየር አትችልም። ነገር ግን እራስህን መቀየር ትችላለህ"  ጂም ሮን ያ የሚሆነው ግን ኃላፊነት ስትወስድ ነው። ቃል ህይወት ነው። ሃሳብን ያቀናል፣ ስሜትን ይፈጥራል ፣ ከዛም ተግባርን ያስጀምራል ስለዚህም ሃሳቡን ከገዛን ከልብ እንዲህ እንበል "እኔ አሁን በህይወቴ ላለው ሁሉም ነገር 100% ኃላፊነት እወስዳለሁ !" @fkrlovelove

#በከባድ_ጊዜ_እንዴት_ተስፋ_ይደረጋል ? ከባድ ጊዜያት ማንንም ሰው ተስፋ መቁረጥ እንዲሰማው ያደርጋሉ። ነገር ግን ካመንን ቀና እና ጠንካራ እምነት ካለን በጣም ፈታኝ ጊዜያቶችንም መጋፈጥ እንችላለን። ነገሮች እንዳሰቡት ሳይሆኑ ሲቀር እናዝናለን ወይም ከፈታኝ ሁኔታ መውጣት ይከብደናል ፤ አሉታዊ መዘዞችን ማሰብ እንቸገራለን። አሉታዊ በሆነ መንገድ ባሰብን ቁጥር አስቸጋሪ እየሆነ ይመጣል። በየትኛውም ፈታኝ ጊዜ ዘላለም ቢመስልም ተስፋ ይኑርህ !! ምንም ነገር ለዘላለም አይቆይም ፤ ከባድ የሆኑ ቀናት እንኳን ያልፋሉ። ዝም ብለህ መጸለይህን ፣ ማመንህን እና እምነትህን ቀጥል፤ ያንን ለማሸነፍ አቅም ይሰጥሃል። 👇👇👇👇👇👇👇 🌾 @fkrlovelove 🌾

የ10 ኣመት ህፃን ልጅ ነው ኪሱ ላይ ጥቂት ሳንቲሞችን ይዞ አንድ አነስተኛ ካፌ ቤት ጎራ አለ ሰው ጥቅ ብሏል ከህፃንነቱ የተነሳ ማንም ትኩረት አልሰጠውም ትንንሽ አይኖቹን ከርተት ከርተት አድርጎ አንድ ክፍት ወንበር አገኘና ሄዶ ቁጭ አለ .)- ምን ፈለክ...... አስተናጋጁዋ በቁጣ እና በንቀት (- እ....እእ....እ ...... አይስክሬም .እ..አለ ?? . ፦ ብርይዘሃል?...... ገልመጥ አድርጋ ጠየቀችው ህፃኑም ስንት ነው አላት ፦ 1 ብር ከ25 ሳንቲም ነው ስትለው ወድያው ኪሦቹ ውስጥ ያለውን ሳንቲሞች አውጥቶ መቁጠር ጀመረ አንድ ብር ከ ሃያ አምሥት ሳንቲም ነው የያዘው አስተናጋጇም ፦ "ቶሎ በል ባክህ ሌላ ስንት ምታዘዘው ሰው አለ አተ ሳንቲም ትቆጥራለህ" ብላ አመናጨቀችው ህፃኑም ሳንቲሞቹን ቆጥሮ ፦ " እሺ ኬክ ስንት ነው አላት ??.. ፦ " አንድ ብር" በቁጣ... ፦ " በቃ ኬክ  ስጪኝ ብሎ እጆቹን ዘርግቶ ሣንቲሞቹን ሰጣት ስትቆጥረውእንድ ብር ነው ኬኩን ውርውር አድርጋለት ሄደች ህፃኑም በልቶ ጨርሶ ወጣ አስተናጋጅዋም የበላበትን እቃ ለማንሳት እቃውን ስታነሳ ከ ሠህኑ ሾር ሃያ አምስት ሣንቲም አስቀምጦላት ነበር ስታይ ደነግጠች ወድያው እንባዋ ዱብ ዱብ ማለት ጀመረ ሥቅሥቅ ብላ አለቀሰች የሚወደውን እና የሚፈልገውን አይስክሬም ብር ከሃያ አምስት ሣንቲም ከፍሎ ከበላ ለአስተናጋጁዋ እሚሰጣት ነገር ስላነበረው ያልፈለገውን ኬክ በአንድ ብር በልቶ 25 ሳንቲሟን ለሡ ቲፕ አስቀምጦላት ሄደ ትንሹ ልጅ ትንሹዋን ነፍስያውን አሸንፎ ክብርን እዝነትንም መስጠትን በትህትና ላላስተናገደችዋ አስተናጋጅ አስተማራት። ለምታውቋቸው ሰዎች ሁሉ ሟር በማረግ ተባበሩ 🙏              👌👌@fkrlovelove

📖ኢንፌርኖ ✍🏾ዳን ብራውን ትርጉም:- አበበ ወርቅ የምዕራቡ ዓለም አፍሪካን የማጥፋት ድብቅ ሴራ "ኢንፈርኖ" በ 2013 የታተመው የዳን ብራውን ልብ ወለድ ነው። መጽሀፉ የሃርቫርድ የምልክት ጥናት ፕሮፌሰር የሆኑት ሮበርት ላንግዶን አንድ እብድ የሰራውን ግማሹን የአለም ህዝብ ሊያጠፋ የሚችለውን ቫይረስ ለማስቆም ሲሞክሩ የሚያደርጉትን ጀብዱ ይተርካል።✍️

✨✨በአይጥ ቤት ብቅል.....✨✨ ✍Shewit dorka

አንድ ሌባ ሞባይል ሲሰርቅ ተይዞ ዳኛ ፊት ይቀርባል። ዳኛው መዝገቡን📖 እያዩ ሌባውን፦        👨‍✈️ የክስ ቻርጅ ደርሶሃል? ሲሉት #ሌባው:- ክቡር ዳኛ ሞባይል ብቻ ነው የወሰድኩት ቻርጀሩ አልደረሰኝም። 🤷‍♂ @Kelid_zone

Repost from ግጥም
#የእኔና_አንቺ_ታሪክ ከሽህ ጦር አለቃ ከሽህ መውዜር ጓንዴ የእኔና አንቺ ፍቅር ይማርካል ውዴ ❤ ዘርሽን ሳልጠይቅ ዘሬን ሳታጣሪ በልቤ ውሰጥ ገብተሽ ፍቅርን ስታበሪ በሰውነት ሚዛን አክብረሽ ስትከብሪ ስወድሽ ስቶጅኝ ሳኮራሽ ስትኮሪ! ከሽህ ታንክ ጋጋታ ከሽህ መድፍ ማጓራት እኔና አንቺ ውዴ ማርኮናል ሰውነት ❤❤ ከዘር ዛር እርቀን በልባችን ጀልባ ቀጥፌ ስሰጥሽ የፍቅርን አበባ ሰውነቴ ገዝቶሽ ሰው መሆንሽ ገብቶኝ እኔነቴ ማርኮሽ አንችነትሽ ገዝቶኝ!!! በእቅድ ከሚመራ ከብዙ ጦር ልቆ የእኔና አንቺ ታሪክ ይነበባል ደምቆ https://t.me/+HsixAeVq6tJlNTI0

ከባድ ጊዜያት የጥንካሬ ቁልፎች ናቸው ፤ ስራህ ሲበላሽብህ የፍቅር ግንኙነትህ ላይ ችግር ሲያጋጥምህ የተለያዩ ነገሮች ወደአንተ ሲመጡ ያንን ጊዜ በሚገባ ተጠቀምበት ነገህን የተሻለ ለማድረግ የሚረዳህ ትልቁ ቁልፍህ ነው እና ራሰህን እይበት !

Repost from ግጥም
#አብረህ_አትርመጥመጥ ከትርምስ ዓለም ጋጋታ ከሞላው እየተጋፋፋ ከሚዘላለፈው ጥቂት ፈቀቅ በል እራስህን አድምጥ የአንተነህ ዋጋ በሌሎች አይዋጥ ጡዘቱ ከናረው ጠብቆ ከከረረው መናገር ብቻ እንጂ ማድመጥ ከሰለቸው ጥቂት ፈቀቅ በል ጥቂት እፎይ ምረጥ ከሚተራመሰው አብረህ አትርመጥመጥ ከልብህ ዋጋ ጋር እራስህን አድምጥ ከተፈጥሮ ጋራ ሀሳብ ተለዋወጥ!!! https://t.me/+HsixAeVq6tJlNTI0

ምን ይለቀቅ?

▶አጫጭር ታሪኮች ▶ ጥቅሶች ▶ አነቃቂ ንግግሮች 👇👇👇👇👇👇👇👇👇ይቀላቀሉ https://t.me/+kD69ypHMp2ZmNTc8

ዘመም ይላል እንጂ (በእውቀቱ ስዩም) እንደ ጊዜው መክፋት እንደ ግፉ መስፋት እንዳገሩ ክስመት እንዳገሬው ጥመት እንደሰው ጭካኔ፤ እንደ ልቡ ፍሬ ታምር ነው መትረፍሽ ፤ ታምር ነው መኖሬ:: የበጎ ሰው ሀሳብ ፤ ሲካድ እለት በለት ጉድጏድ ተምሶለት ሰብእና ሲቀበር፤ በዚህ ምድር መኖር ፤ አያስመኝም ነበር:: ምድሩ ሳር ቅጠሉ፤ በስጋት ተሞልቶ የማለዳው ሰማይ፤ እንዳንቀልባ ቀልቶ ታረደ ነደደ ከዘብጥያ ወጥቶ ዘብጥያ ወረደ የሚል ዜና ብቻ አየሩን ሲሞላው ሰው በገዛ ጥላው በርግጎ ሲሸበር በዚህ ምድር መኖር ፤አያስመኝም ነበር:: አዎ ለጊዜውም ቢሆን፤ ግፍ ያደነዝዛል በደል ያስተክዛል ጊዜም ጠብን ሽሮ፤ ወደ ፊት ይጏዛል በልብ ሰሌዳ ላይ ፤ቂም ይደበዝዛል በነገ ያመነ ልጁን ቀብሮ መጥቶ፤ ሚስቱን ያስረግዛል:: ይቅርታና ምህረት ፍቅርና ህብረት ከግፍ ጋር ፍልሚያቸው ፤ ቢሆን የሞት ሽረት ዳገት ይወጣሉ ፤ በንጥፍጣፊ አቅም የመኖር ፍላጎት ዘመም ይላል እንጂ ፤ ተገርስሶ አይወድቅም::

Repost from ግጥም
#የእኔና_አንቺ_ታሪክ ከሽህ ጦር አለቃ ከሽህ መውዜር ጓንዴ የእኔና አንቺ ፍቅር ይማርካል ውዴ ❤ ዘርሽን ሳልጠይቅ ዘሬን ሳታጣሪ በልቤ ውሰጥ ገብተሽ ፍቅርን ስታበሪ በሰውነት ሚዛን አክብረሽ ስትከብሪ ስወድሽ ስቶጅኝ ሳኮራሽ ስትኮሪ! ከሽህ ታንክ ጋጋታ ከሽህ መድፍ ማጓራት እኔና አንቺ ውዴ ማርኮናል ሰውነት ❤❤ ከዘር ዛር እርቀን በልባችን ጀልባ ቀጥፌ ስሰጥሽ የፍቅርን አበባ ሰውነቴ ገዝቶሽ ሰው መሆንሽ ገብቶኝ እኔነቴ ማርኮሽ አንችነትሽ ገዝቶኝ!!! በእቅድ ከሚመራ ከብዙ ጦር ልቆ የእኔና አንቺ ታሪክ ይነበባል ደምቆ https://t.me/+HsixAeVq6tJlNTI0

💖አስተማሪ ታሪኮች💚 💖አነቃቂ ንግግሮች 💛 💖ጥቅሶች 🤍 ሰው መሆን(ከውስጥ ወደ ውጪ መኖር ): https://t.me/+kD69ypHMp2ZmNTc8 Sher it to group,friend ..

አሁን ከምታገኘው ነገር በላይ ጊዜ ወስደህ ማሰብ ያለብህ ስለምትሆነው ነው፤ ምክንያቱም የምትሆነው ማንነት ነው ነገ የምታገኘውን ደስታ፣ ሀብት፣ ዝና እና ክብር የሚወስነው። በቢዝነስ ትልቅ ሀብት መገንባት የሚፈልግ ሰው ገንዘብ ከመሰብሰቡ በፊት የቢዝነስ ሰዎች ያላቸውን ማንነት ቀድሞ መላበስ አለበት፤ ታላቅ የጥበብ ሰው ሆኖ ለመከበር የሚፈልግ ሰው ከዝናው በፊት የጥበብ ሰው ማንነት እንዲኖረው ቀድሞ ራሱ ላይ መስራት አለበት። ጊዜ ወስደህ ራስህ ላይ ከሰራህ አትጠራጠር መሆን ከምትፈልጋቸው ሰዎች በላይ አንተ ታላቅ ትሆናለህ! 🙏እጅግ የተዋበ ምሽት🙏

#በዜሮ__ይባዛል ተግቼ #ብፀልይ እጆቼን ዘርግቼ ቤቴ ባዶ ቢቀር ያለኝን መፅውቼ ቀኑን ሙሉ #ብፆም እስኪቆርጥ አንጀቴ ዘወትር ብሰግድ እስኪዝል ጉልበቴ ብቀድስ #ባስቀድስ በመቅደሱ ግርማ ብዘምር ባወድስ በሚጣፍጥ ዜማ #ወንጌልን ብሰብክ ምስጢር አመስጥሬ ብናገር ባስተምር ትርጉምን ዘርዝሬ ጥልና ክርክር ካሉ በህይወቴ ሐሜት አድመኝነት ካልጠፉ ከቤቴ #በዜሮ_ይባዛል_ፍቅር_በማጣቴ!! #___ሰናይ____ምሽት 🙏🙏 ምንጭ ; ከአጫጭር ግጥሞች🙋