en
Feedback
Kasuen Tech

Kasuen Tech

Open in Telegram

Tech insight

Show more
924
Subscribers
No data24 hours
-67 days
-2730 days
Posts Archive
Cross መስራት የምትፈጉ or paid promotion @library_Comment_bot

+1
#Biology unit1 GRADE11 SHORT NOTE የ11ኛ Biology ላስጨነቃችሁ ፍቱን መድሀኒት። #Share

@library_Comment_bot Paid and cross promotion

_TOPPER_TUTOR_17897671.apk23.19 MB

የሰዎችን ውለታ አትርሳ! ሰዎች ጊዜያቸውን, ጉልበታቸውን, ገንዘባቸውን ከፍ ሲልም ህይወታቸውን ላንተ የሚገብሩት ተርፏቸው አይምሰልህ።አንድም ሰብዓዊነት ይዟቸው በሌላ በኩል ደግሞ ወንድምነትህ ,እህትነትሽ ወይም ጓደኝነትህን/ሽን ትርጉም እንዲኖረው ከማድረግ አንፃር ነው። አንተም በመልሱ ታስፈልጋቸዋለህና  ጊዜህን ጠብቀህ በምትችለው ልክ ከጎናቸው በመሆን አለኝታነትህን አሳያቸው።      ❤❤   @fkrlovelove 🙏🙏

ለቁም ነገር ቢቻ የምትፈለግ ሁን! አለማችን እንደሚታወቀው ብዙ አይነት ሰዎችን ይዛለች።ይህን የምፅፍልህ ግን አለማችን ላይ ስላሉት የሰዎች ብዛት ልነግርህ ሳይሆን አንተስ ከየትኞቹ ነህ? የሚለውን ጥያቄ ላስታውስህ ነው።አንድ ቀለል ያለ እና መሆን የምትችለውን ነገር ልንገርህ።ቁም ነገረኛ ሁን። አንተ የተለየ አስተሳሰብና በጓደኞችህ ማንነት ጥገኛ ያለሆንክ, ጓደኞችህ ስለ ቁምነገር ሲያወሩ ስላንተ የሚያወሩልህ ሆነህ መገኘት መቻል አለብህ።ለማይረቡና ከዕድሜህ ጋር ለማይሄዱ ቀልዶች ቦታ አይኑርህ።መፍትሄ ለታጣላቸው ጉዳዮች መፍትሄ መፍጠር የምትችል ሰው ሁን። @fkrlovelove @fkrlovelove

#መንገድ_አለ! ለእያንዳንዱ ውድቀት ምትክ የሚሆን ድርጊት አለ፤ ያለብህ መፈለግ ብቻ ነው። መሰናክል ሲያጋጥምህ ሌላ መንገድ ተጠቀም። እንቅፋት ወይም መሰናክል ባጋጠመህ ጊዜ ቆም ብለህ እንዴት በዙሪያው ወይም በላዩ ላይ ወይም በውስጡ ማለፍ እንደምትችል አሰላስል። ለእያንዳንዱ መዘጋት ያንን እንቅፋት የምታልፍበትን ሶስት የተለያዩ ስልቶችን አምጣ። ሊሰሩ የሚችሉ ብዙ ዘዴዎች አሉ፤ የምታገኛቸው ግን እነርሱን ለመፈለግ ጊዜ ከወሰድክ ብቻ ነው። በአስተሳሰብህ ሁልጊዜ መፍትሔ ተኮር ሁን፤ የሚሰራ መንገድ እስክታገኝ ድረስ ፅና። አስቸጋሪ ሁኔታዎች የተሻሉ ነገሮችን ለማግኘት መልካም አጋጣሚዎች ናቸው፤ ወደ ታላቅ ልምምድ የሚወስዱን መረማመጃዎች ናቸው ... #እነሆ_የወዳጅ_ምክር- ብራይን አዳምስ እንዳለው አንድ በር ሲዘጋ ሁልጊዜም ሌላኛው ክፍት ነው። የተፈጥሮ ህግ ሚዛንን ለመጠበቅ ይህ ሊሆን ግድ ነው። የተዘጋውን በር ብቻ አትመልከት፤ ዞር ብትል የተከፈተም በር አለ፡፡ በተከፈተው በር ያውልህ፡፡ @fkrlovelove

ማንኛው group ያላቹ ከ2018 2019 2020 2022 የተከፈተ ካላቹ እንገዛቹሀለን 10members ጀምሮ ያለው @Altel_1

ብዙ ስትወድቅ ብዙ ትጠነክራለህ! መውደቅ ከህይወት ህጎች ውስጥ አንዱ ነው ዋናው ነገር ወድቀህ አለመቅረትህ ነው። የትኛውም ስኬታማ የምንላቸው ሰዎች በብዙ ውድቀቶች ያለፉና ነገር ግን እንደወደቁ ከመቅረት ይልቅ በውድቀታቸው እየተማሩ ከሚፈልጉት ለመድረስ ደጋግመው የሞከሩ ናቸው። አንተም ደጋግመህ መውደቅህ ውደደው ምክንያቱም አንዴ ከተነሳህ የሚመክትህ የማይኖር ድንቅና ጠንካራ ትሆናለህ።      @fkrlovelove

ማራኪ ግጥሞችን ማግኘት ይፈልጋሉ?
ማራኪ ግጥሞችን ማግኘት ይፈልጋሉ?

"ግን ለምን...."....አይን አይናቸውን እያየች ጠየቀች። "እሱን የሚያውቀው ፈጣሪ ብቻ ነው...ሁሉም ነገር በምክንያት ነው"...አሏት በድዳቸው ፈገግ እንደማለት እያሉ.... "መጥፎ ሰው አይደለሁም ያውቃሉ...እኔ እንደዚህ መሆን አልፈልግም...ነገስ ምን ይፈጠር ይሆን እያልኩ መኖር አልፈልግም... እኔ ኮ ሳቄን አላምነውም...ብዙ ስስቅ እምባዬ ሩቅ እንዳልሆነ ይሰማኛል...የሆነ አይነት ስሜት ነው...ውርር የሚያደርግ...አንዴ ከጥልቅ ወስዶ የሚወረውር...አንዴ ደግሞ ከነ አካቴው እልም ብሎ የሚጠፋ....በአንድ ሰአት ውስጥ መቶ ሺ ዝቅታ...መቶ ሺህ ብሶት...መቶ ሺህ ስብራት አስተናግዳለሁ....ድንገት መጥቶ እላዬ ላይ ሲደኮን ይታወቀኛል...ለሆነ ምናምነኛ ጊዜ ሞት ሞት ይለኛል..." "ለበጎ ነው...."....ብለው ነጠላቸውን ወደመቋጨት ገቡ...ካሁን አሁን ይቀጥላሉ ብላ ብትጠብቃቸውም እሳቸው ከነጠላቸው ጥለት አልነቀል አሉ.... "ሁላችሁም እንደዚህ ነው የምትሉት...'በምክንያት ነው...'....ትንሽ ለወጥ ካደረጋችሁት 'ለበጎ ነው'....በቃ ሌላ ምንም አታውቁም...እስቲ ንገሩኝ ምኑ ነው በጎ...?"....ስሜቷ ድምጿን አጎላው...የእሳቸውን እርጋታ ግን አልረበሸውም.... "ምን እንደምመኝ ያውቃሉ...."....አፈጠጠችባቸው.... መልሳቸውን ሳትጠብቅ ቀጠለች.... "አእምሮዬ ውስጥ ያለውን ድምፅ ላይመለስ መደምሰስ...በአንድ አይነት ጥሩ ስሜት ቀኔን መዋል...ይሰሙኛል ጠዋት ሌላ ሰው ማታ ሌላ ሰው መሆን ስልችት ብሎኛል...."....ከንግግሯ በኃላ አይኖቿ እምባ አረገዙ። "ልጄ...."....አሏት ንፋስ የገፈፋቸውን አዳፋ ነጠላ ትከሻቸው ላይ እየመለሱ...በተራዋ መልስ ነፈገቻቸው...አየት ካረጓት በኃላ ማውራታቸውን ቀጠሉ..... "አንዳንዴ ፈጣሪ ለተበጣጠሰው ጫማሽ ምትክ አዲስ ጫማ ሰጥቶ አይክስሽም....ሰማሺኝ ልጄ ለአንድ አሮጌ ጫማ ሌላ አዲስ ጫማ ላይሆን ይችላል ምላሹ...ምን አልባት ውድ ጫማሽ ላይ የሚያፈጠውን አንገትሽን ነቅሎ ወደ እርሱ እንዲያይ ያደረገው ነገር ይሆናል...ቀና ስትዪ እሱን ካየሽ ታተርፊያለሽ...አለምን ካየሽ ደግሞ ክስረት ነው....አየሽ ልጄ አይንሽ ጫማሽን ጠግቦ እርሱን ማየት እስኪጀምር ድረስ...የጫማሽ ኑረት እስኪጠፋሽ ድረስ አዲስ ጫማ ሰጥቶ ትንሿን ደስታ አያስደስትሽም......."....አሉና ወደ አዳፋ ነጠላቸው ጥለት ተመለሱ... "እማማ..." "እመት..." "እዚ መኖር ከጀመሩ ስንት ጊዜ ሆኖት..." "11 አመት...."....አሏት ጎዳና ሳይሆን የተመቻቸ ኑሮ እንደሚኖር ሰው ኮራ ብለው... "ቤተሰብ አሎት...?" "ነበረኝ...በአንድ ለሊት ነው ባለቤቴንም ልጆቼንም ያጣሁት..." "እና እንዴት ቻሉት....?".....የራሷን ችግር ለአፍታ ዘነጋች.... "እግዚአብሄር በዚች ትንሽ ነገር አይመረመርም....በቤተሰብ...በጤና...በገንዘብ እጦት ተመርኩዤ ለእኔ ያለውን ፍቅር የምዘነጋ አይደለሁም....ሁሉም የእርሱ ነው..." "እንዴት ውስጥዎ ዝም አሎት....እንዴት ጭንቅላቶት ደህና ሆነሎት....?"... "አዬዬዬ ልጄ ሳያመኝ ቀርቶ መሰለሽ....ሰላም ባለሽና በሌለሽ ነገር የሚወሰን ነገር ስላልሆነ እንጂ...ይልቁንም እግዚአብሄር የውስጥሽን ማዕበል ሲገስፅ የምታገኚው ነገር ስለሆነ እንጂ...እርሱ ማዕበሉን ገስፆልኝ እንጂ..." "እኔ እኮ ምን ብዬ መፀለይ እንዳለብኝ እንኳን አላውቅም...."...አለቻቸው የእርሷም ማዕበል እንዲረጋጋ በመሻት...ከነ እርጋታቸው መለሱላት.... "ምንም የምትፀልዪውን ባታውቂ እንኳን ዝም ብለሽ 'አውጣኝ' በይው...ፍቃዱ ካልሆነና ባያወጣሽ እንኳን ችግሩ ውስጥ መኖርሽን ያስረሳሻል...ደግሞስ እርሱ አይደል ምን እንደሚያረግ መች ይጠፋዋል... ደግሞ መጥፎ ነገር ሁልጊዜ መጥፎ ውጤት ብቻ አይኖረውም...ቅድም እንዳልኩሽ ነው....የሚያዳልጥ ጫማ ካለሽ ሳትወጂ በግድሽ ረጋ ብለሽ መጓዝ ትለምጃለሽ..."... "እማማ እኔ  ሀይማኖት ላይ ያን ያሀል አይደለሁም...እንደዚህ አይነት መልስ ለእኔ አይሆንም...." "አሁን ያለሽበትን ስቃይ መርጠሽው ነው የተሰጠሽ....?"....ጠየቋት... "አይ..." "ጥያቄው ከየት እንደመጣ ሳቲውቂ እንዴት መልስ ትመርጫለሽ......ምንጩን አድርቀሽ በውሀ ጥም ተቃጠልኩ ብለሽ መጮህሽ ምን ይፈይዳል...." ዝምታ.... ✍Shewit dorka https://t.me/shewitdorka

photo content

"ግን ለምን...."....አይን አይናቸውን እያየች ጠየቀች። "እሱን የሚያውቀው ፈጣሪ ብቻ ነው...ሁሉም ነገር በምክንያት ነው"...አሏት በድዳቸው ፈገግ እንደማለት እያሉ.... "መጥፎ ሰው አይደለሁም ያውቃሉ...እኔ እንደዚህ መሆን አልፈልግም...ነገስ ምን ይፈጠር ይሆን እያልኩ መኖር አልፈልግም... እኔ ኮ ሳቄን አላምነውም...ብዙ ስስቅ እምባዬ ሩቅ እንዳልሆነ ይሰማኛል...የሆነ አይነት ስሜት ነው...ውርር የሚያደርግ...አንዴ ከጥልቅ ወስዶ የሚወረውር...አንዴ ደግሞ ከነ አካቴው እልም ብሎ የሚጠፋ....በአንድ ሰአት ውስጥ መቶ ሺ ዝቅታ...መቶ ሺህ ብሶት...መቶ ሺህ ስብራት አስተናግዳለሁ....ድንገት መጥቶ እላዬ ላይ ሲደኮን ይታወቀኛል...ለሆነ ምናምነኛ ጊዜ ሞት ሞት ይለኛል..." "ለበጎ ነው...."....ብለው ነጠላቸውን ወደመቋጨት ገቡ...ካሁን አሁን ይቀጥላሉ ብላ ብትጠብቃቸውም እሳቸው ከነጠላቸው ጥለት አልነቀል አሉ.... "ሁላችሁም እንደዚህ ነው የምትሉት...'በምክንያት ነው...'....ትንሽ ለወጥ ካደረጋችሁት 'ለበጎ ነው'....በቃ ሌላ ምንም አታውቁም...እስቲ ንገሩኝ ምኑ ነው በጎ...?"....ስሜቷ ድምጿን አጎላው...የእሳቸውን እርጋታ ግን አልረበሸውም.... "ምን እንደምመኝ ያውቃሉ...."....አፈጠጠችባቸው.... መልሳቸውን ሳትጠብቅ ቀጠለች.... "አእምሮዬ ውስጥ ያለውን ድምፅ ላይመለስ መደምሰስ...በአንድ አይነት ጥሩ ስሜት ቀኔን መዋል...ይሰሙኛል ጠዋት ሌላ ሰው ማታ ሌላ ሰው መሆን ስልችት ብሎኛል...."....ከንግግሯ በኃላ አይኖቿ እምባ አረገዙ። "ልጄ...."....አሏት ንፋስ የገፈፋቸውን አዳፋ ነጠላ ትከሻቸው ላይ እየመለሱ...በተራዋ መልስ ነፈገቻቸው...አየት ካረጓት በኃላ ማውራታቸውን ቀጠሉ..... "አንዳንዴ ፈጣሪ ለተበጣጠሰው ጫማሽ ምትክ አዲስ ጫማ ሰጥቶ አይክስሽም....ሰማሺኝ ልጄ ለአንድ አሮጌ ጫማ ሌላ አዲስ ጫማ ላይሆን ይችላል ምላሹ...ምን አልባት ውድ ጫማሽ ላይ የሚያፈጠውን አንገትሽን ነቅሎ ወደ እርሱ እንዲያይ ያደረገው ነገር ይሆናል...ቀና ስትዪ እሱን ካየሽ ታተርፊያለሽ...አለምን ካየሽ ደግሞ ክስረት ነው....አየሽ ልጄ አይንሽ ጫማሽን ጠግቦ እርሱን ማየት እስኪጀምር ድረስ...የጫማሽ ኑረት እስኪጠፋሽ ድረስ አዲስ ጫማ ሰጥቶ ትንሿን ደስታ አያስደስትሽም......."....አሉና ወደ አዳፋ ነጠላቸው ጥለት ተመለሱ... "እማማ..." "እመት..." "እዚ መኖር ከጀመሩ ስንት ጊዜ ሆኖት..." "11 አመት...."....አሏት ጎዳና ሳይሆን የተመቻቸ ኑሮ እንደሚኖር ሰው ኮራ ብለው... "ቤተሰብ አሎት...?" "ነበረኝ...በአንድ ለሊት ነው ባለቤቴንም ልጆቼንም ያጣሁት..." "እና እንዴት ቻሉት....?".....የራሷን ችግር ለአፍታ ዘነጋች.... "እግዚአብሄር በዚች ትንሽ ነገር አይመረመርም....በቤተሰብ...በጤና...በገንዘብ እጦት ተመርኩዤ ለእኔ ያለውን ፍቅር የምዘነጋ አይደለሁም....ሁሉም የእርሱ ነው..." "እንዴት ውስጥዎ ዝም አሎት....እንዴት ጭንቅላቶት ደህና ሆነሎት....?"... "አዬዬዬ ልጄ ሳያመኝ ቀርቶ መሰለሽ....ሰላም ባለሽና በሌለሽ ነገር የሚወሰን ነገር ስላልሆነ እንጂ...ይልቁንም እግዚአብሄር የውስጥሽን ማዕበል ሲገስፅ የምታገኚው ነገር ስለሆነ እንጂ...እርሱ ማዕበሉን ገስፆልኝ እንጂ..." "እኔ እኮ ምን ብዬ መፀለይ እንዳለብኝ እንኳን አላውቅም...."...አለቻቸው የእርሷም ማዕበል እንዲረጋጋ በመሻት...ከነ እርጋታቸው መለሱላት.... "ምንም የምትፀልዪውን ባታውቂ እንኳን ዝም ብለሽ 'አውጣኝ' በይው...ፍቃዱ ካልሆነና ባያወጣሽ እንኳን ችግሩ ውስጥ መኖርሽን ያስረሳሻል...ደግሞስ እርሱ አይደል ምን እንደሚያረግ መች ይጠፋዋል... ደግሞ መጥፎ ነገር ሁልጊዜ መጥፎ ውጤት ብቻ አይኖረውም...ቅድም እንዳልኩሽ ነው....የሚያዳልጥ ጫማ ካለሽ ሳትወጂ በግድሽ ረጋ ብለሽ መጓዝ ትለምጃለሽ..."... "እማማ እኔ  ሀይማኖት ላይ ያን ያሀል አይደለሁም...እንደዚህ አይነት መልስ ለእኔ አይሆንም...." "አሁን ያለሽበትን ስቃይ መርጠሽው ነው የተሰጠሽ....?"....ጠየቋት... "አይ..." "ጥያቄው ከየት እንደመጣ ሳቲውቂ እንዴት መልስ ትመርጫለሽ......ምንጩን አድርቀሽ በውሀ ጥም ተቃጠልኩ ብለሽ መጮህሽ ምን ይፈይዳል...." ዝምታ....

Repost from ግጥም
#ካልመጣሽ_ላይነቃ በመቅረትሽ ዜማ በናፍቆት ቆዝሜ ደህና ነኝ እያልኩኝ በፍቅርሽ ታምሜ እጠብቅሻለሁ ከትዝታሽ ማዶ ልቤ ከልብሽ ጋር አንድ ላይ ተዛምዶ። ልብ አልባ እኔነቴ በደመነፍስ ቀርቶ በድንዛዜ ስልት ብቻውን ሸፍቶ ከሰው በመነጠል የእራሱ ዓለም ሰርቶ ካልመጣሽ ላይነቃ ለእራሱ ቃል ገብቶ ዛሬም ይጠብቃል ተስፋን ባለመቁረጥ ከአስቀመጥሽው ቦታ ታምኖ በመቀመጥ። @gitm_post ♡ ㅤ     ❍ㅤ         ⌲               ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢʰᵃʳᵉ

የራስህን ዋጋ እወቅ! አንተ ለራስህ የምትሰጠው ዋጋ,አንተ ለራስህ ያለህ አስተሳሰብና አንተ ለራስህ ያለህ ክብር ህይወትህ ላይ ትልቅ ተፅዕኖ ይኖረዋል። አንተ ውስጥ ያንተን እንክብካቤ,ያንተን ፍቅር,ያንተን ሰላም,ያንተን ደስታ የሚያስፈልገው ሌላ የራስህ ማንነት አለ።በፍፁም እራስህን ሰዎች እጅ ላይ በሚገኙ ቁሳቁስ አትለካ። ምንም ያክል ነገሮች ካንተ የራቁና የማታገኛቸው መስለው ቢታዩህ  ሁሉንም ነገሮች ካንተ በታች ናቸው።     @fkrlovelove

01 ስለ ተሮጠ አይደረስም_ስለተቸኮለ አይጨበጥም። ምናልባት ውስጡ የጠበቅነውን እና የጓጓንለትን ያህል እነደውጪው ላያምር ይችላል። ለምን በኔስ ይቅር እስቲ ልሞክረው ብለን ሄደን ሠምጠን እንዳንቀር ሰጋለሁ።የበዛች ድፍረታችን ናት...የውድቀታችንን በር የምትከፍት። ከማንችለው መግጠማችን ...የሽንፈታችን ጅማሮ ሊሆን እንደሚችል ባንዘነጋስ? እንደ እንትና ብለን ስንንጠራራ ነው...እኛነታችንን የጣልነው። የሌሎችን መንገድ በማሳደድ ተጠምደን ነው...ከጎዳናችን የሳትነው። ✍🏽yori_17-12-15 🔮🔮 @yori_724 🔮🔮