en
Feedback
የኡስታዝ አቡ ዐብዱልመናን ኻሊድ ቢን ጠይብ ቻናል

የኡስታዝ አቡ ዐብዱልመናን ኻሊድ ቢን ጠይብ ቻናል

Open in Telegram

📌 ይህ ቻናል በአላህ ፍቃድ የተወዳጁ ኡስታዝ አቡ አብዱልመናን ኻሊድ ጠይብ:- 🔛 ተቀርተው ያለቁ እና እየተቀሩ ያሉ ደርሶች 🔛 በፊት የተደረጉ እና አዳዲስ ሙሀደራዎች 🔛 ኹጥባዎች ጭምር የሚለቀቅበት ቻናል ነው።

Show more
3 168
Subscribers
No data24 hours
+197 days
+5030 days
Posts Archive
📂 ሸይኽ አሕመድ አን-ነጅሚ رحمه الله እንዲህ አሉ፦ «ወንድሞቼ ሆይ! እኛ የምንደሰትባቸውንና የምንጠቀምባቸውን የአላህ ጸጋዎች እናስብ። እነዚህ ታላላቅ ጸጋዎች ናቸው፤ ደህንነት፣ የተመቸ ኑሮ፣ የተስፋፋ ሲሳይ፣ ሀብትና ንብረት፣ አምልኮን በነፃነት የመፈጸም ነፃነት፣ እንዲሁም ከምናስበው በላይ የሆኑ ብዙ ጸጋዎች ናቸው። እነዚህ እኛ ያሉንን ጸጋዎች ሁሉም ሰዎች የሚመኙብን ናቸው።» 📓 ፈትሕ ረብብል-ዐቢድ፣ ገጽ 120 👌 አዎን የሌለንን ከመቁጠር ያለንን እንደሰትበት አላህንም እናመስግን። ይህን ካደረግን ባለን ላይ ይጨመርልናል ያለንም ይበረክትልናል❗️ ✍ አቡ አብድልመናን

👌 በጣም ይገርማል ፉደይል ኢብኑ ዒያድ አላህ ይዘንለት ስለዘመናችን ሰዎች የሚናገር ይመስላል እንዲህ ይላል:- «إنما نزل القرآن ليُعمل به، فاتخذ الناس قراءته عملاً» “ቁርአን የተወረደው በእርሱ ለመስራትና ትእዛዞቹን በተግባር ለማዋል ነው፤ ሰዎች ግን እሱን ማንበብን ብቻ እንደ ሥራ ወሰዱት።” ✍ አቡ አብድልመናን

📍 ሸይኽ ኢብን ዑሠይሚን رحمه الله تعالى በሸርሑል-ዐቂደቲል-ዋሲጢያ፣ ገጽ 378 እንዲህ ይላሉ፦ «አላህ በሂዳያ (በቀጥተኛ መንገድ መመራት)፣ መልካም ሥራ የመስራትን ስኬት፣ እንዲሁም መልካምን ነገር ሁሉ መውደድና መልካም ሰዎችን የመቅረብ በረከቱን እንደሰጠህ በራስህ ውስጥ ካየህ፣ ደስ ይበልህ! ይህ እንደሚያሳየው አንተ ከ‘አህሉል-ዩስራ’ (የቀላልነትና የመልካም ዕድል ሰዎች) መካከል ለመሆንህ ምልክት ነው፤ እነርሱም ደስታና ስኬት እንዲያገኙ የተወሰነላቸው ሰዎች ናቸው።» ✍ አቡ አብድልመናን

🌎ቀጥታ ስርጭት Live straem💥 📖የዛሬው እለት ከመግሪብ እስከ ዒሻ የተፍሲር ፕሮግራም 📖 ሱረቱ ኢብራሂም 📖 📚 ከ10ኛው አንቀፅ ይጀምራል 🎙የኡስታዝ አቡ ዐብዱልመናን ኻሊድ ቢን ጠይ
🌎ቀጥታ ስርጭት  Live straem💥 📖የዛሬው እለት ከመግሪብ እስከ ዒሻ የተፍሲር ፕሮግራም 📖 ሱረቱ ኢብራሂም 📖 📚  ከ10ኛው አንቀፅ ይጀምራል 🎙የኡስታዝ አቡ ዐብዱልመናን ኻሊድ ቢን ጠይብ አላህ ይጠብቀው። 🕌በታላቅዋ ፉርቃን መስጂድ አላህ ይጠብቃት። 📚የኪታቡ pdfለማግኘት👇👇 https://t.me/Al_Furqan_pdf/694 🛜ለቀጥታ ስርጭት👇👇 https://t.me/Abuabdlmenan?livestream https://t.me/Abuabdlmenan/2163

🌎ቀጥታ ስርጭት Live straem💥 📖የዛሬው እለት ከመግሪብ እስከ ዒሻ የተፍሲር ፕሮግራም 📖 ሱረቱ ኢብራሂም 📖 📚 ከመጀመሪያው አንቀፅ ይጀምራል 🎙የኡስታዝ አቡ ዐብዱልመናን ኻሊድ ቢን
🌎ቀጥታ ስርጭት  Live straem💥 📖የዛሬው እለት ከመግሪብ እስከ ዒሻ የተፍሲር ፕሮግራም 📖 ሱረቱ ኢብራሂም 📖 📚  ከመጀመሪያው አንቀፅ ይጀምራል 🎙የኡስታዝ አቡ ዐብዱልመናን ኻሊድ ቢን ጠይብ አላህ ይጠብቀው። 🕌በታላቅዋ ፉርቃን መስጂድ አላህ ይጠብቃት። 📚የኪታቡ pdfለማግኘት👇👇 https://t.me/Al_Furqan_pdf/694 🛜ለቀጥታ ስርጭት👇👇 https://t.me/Abuabdlmenan?livestream https://t.me/Abuabdlmenan/2152

🕋 የመካ ፍቅር — በልብ ውስጥ የሚኖር ፍቅር መካን መውደድ ተራ የአንድ ከተማ ፍቅር አይደለም፤ ይህ የኢማን ትዝታ፣ የአምልኮ ስሜትና የቅዱሱ ቤት ፍቅር ነው። በመካ የሚገኘው ካዕባ የሙስሊሞች ቂብላ ነው፤ በጸሎት ጊዜ ወደርሱ በልባቸውም በአካላቸውም ይመለሳሉ ይቅጣጫሉ መካን የሚወድ ሰው ወደ እርሷ ሲሄድ ልቡ ይረጋጋል፤ በመካ ሲቆይ ደስታ ይሰማዋል፤ ከእርሷ ሲለይ ደግሞ ናፍቆት ይይዘዋል። ወደ እርሷ በተመላለሰ ቁጥር አይሰለችም፤ ከእርሷ በራቀ ቁጥርም የመመለስ ፍላጎቱና የርሷ ናፍቆት ይጨምራል። መካ እንደ ማግኔት የሙስሊሞችን ልቦች ወደ እርሷ ትስባለች። አንዱ ከሩቅ ሀገር በአውሮፕላን ወደርሷ ይበራል፣ ሌላው ከሩቅ አህጉር በባህርም ወደርሷ ይጓዛል፤ ሏላውም በምድር ተሽከርካሪም በረሀን እያቋረጠ ወደርሷ ይከንፋል ሁሉም ግን አንድ ነገር ይፈልጋሉ፦ የአላህን ቤት ማየትና በዚያ አምልኮ ማድረግ። መካን የሚወዷት የእርሷ ሰዎች ብቻ አይደሉም፤ ወደ እርሷ የሚመጣ፣ በእርሷ የሚቆይ፣ የሚጎበኛት፣ ዑምራ ወይም ሐጅ የሚያደርግ ሰው ሁሉ የዚህን አያ ትርጉም በልቡ ያገኘዋል፦ ﴿وَإِذْ جَعَلْنَا الْبَيْتَ مَثَابَةً لِلنَّاسِ وَأَمْنًا﴾ «ቤቱንም ለሰዎች የሚመለሱበት መድረሻና የደኅንነት ቦታ አደረግነው።» ይህም ማለት፦ ሰዎች መካ በመጡ ቁጥር እርሷን አይሰለቹም፤ እንደውም ፍላጎታቸውም አይሞላም። በመጡ ቁጥር የበለጠ ይናፍቋታል፤ ከእርሷ በሄዱ ቁጥርም ወደ እርሷ የመመለስ ናፍቆታቸውና ጉጉታቸው ይመለስባቸዋል። ስለዚህ አላህ የመካን ፍቅር በሰዎች ልብ ውስጥ እንደ ማግኔት አደረገው ሁሌም ካሉበት ቦታ ወደራሷ ትስባቸዋለች። ነገር ግን የመካ ፍቅር በቃል ብቻ አይደለም፤ የአላህን ትእዛዝ በመከተል፣ ሶላትን በመጠበቅ፣ ከኃጢአት በመራቅና ወደ አላህ በመቅረብ ይገለፃል። እርሷ ውስጥ ክፋትን የሚሻ ይቀጠፋል ይዋረዳልም አላህ እንዲህ ብሏል:- ﴿وَمَن يُرِدْ فِيهِ بِإِلْحَادٍ بِظُلْمٍ نُذِقْهُ مِنْ عَذَابٍ أَلِيمٍ﴾ [الحج: 25] «በእርሱም (በመካ) ውስጥ በዓመፅ ወደ ክህደትና ወደ ጥፋት የሚያዘነብል ሰው ከአሳማሚ ቅጣት እናቀምሰዋለን።» ይህ አንቀፅ የመካን ቅድስናና ታላቅ ክብር ያሳያል፤ በዚያ ቦታ ሄዶ ክፉ ነገር ማድረግ ብቻ ሳይሆን፣ በግፍ ወደ ክፉ ነገር ማዘንበልና ማሰብም ከባድ ማስጠንቀቂያ ያለው ነው። 🤲አላህ ሆይ! የመካን ፍቅር በልባችን ጨምርልን፤ ወደ ቅዱሱ ቤትህም ደጋግመን እንድንመጣ እድል ስጠን። ዑምራችንንና ሐጃችንን ተቀበልልን፣ ኃጢአታችንንም ማርልን❗️ ✍ አቡ አብድልመናን

💥 ዝምተኛና ተዋጊ ቀስቶች ሸይኽ ፈይሰል አልሓሺዲ አላህ ይጠብቀው እንዲህ ይላል:- • 🏹 ቁጣ • 🏹 ሀዘን • 🏹 ጭንቀት • 🏹 ውጥረት እነዚህ ዝምተኛና ተዋጊ ቀስቶች ናቸው፤ ከሚቃረኑህና ከሚቃወሙህ ሰዎች ሊመጡ ይችላሉ፣ ወይም ከሌሎች ምክንያቶች ሊነሱ ይችላሉ። ሆኖም አንተ ሳታስተውል በጤንነትህና በእረፍትህ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳሉ። 👌 ነገር ግን ለእነዚህ ነገሮች እጅ በመስጠት ካልተንበረከክና፣ በልብህም ውስጥ ቦታ ካልሰጠሃቸው፣ በእግርህ ስር ይሰባበራሉ፤ ማንም ሊነጥቅህ የማይችለውንም የልብ ሰላምና እረፍት ታገኛለህ❗️ ⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️ 🫵 ስለዚህ ለጠላትህም ይሁን ለገጠመህ ችግር ሰንፈህና በሐዘን ቆዝመህ አታስደስተው ቀና በል ከሀይልህና ብልሀትህ እራስህን አጥራና በልእለ ሀያሉ ጌታህ ተመካ በዒባዳህ ተጠናከር በአላህ ፍቃድ ውጤቱን ያማረ ሆኖ ታገኘዋለህ👇 አላህ እንዲህ ብሏልና ﴿وَلَا تَهِنُوا وَلَا تَحْزَنُوا وَأَنْتُمُ الْأَعْلَوْنَ إِنْ كُنْتُمْ مُؤْمِنِينَ﴾ [آل عمران: 139] «አትድከሙ፣ አትዘኑም፤ አማኞች ከሆናችሁ እናንተ የበላይ ናችሁ ።» ✍🏻 አቡ አብድልመናን

📱በሚድያ አጠቃቀም ላይ የልቅነት መዘዙ⁉️ 🛑አሁን ባለንበት ሁኔታ ለተራ ሚድያ ላገነነውና ለተራ ነገራቶች ከህፃን እስከ ሽማግሌ፤ ከሊቅ እስከ ደቂቅ፤ ከሴት እስከ ወንዱ፤ከተራ ጃሂል እስከ ኡስታዝ ተብዬ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ሲንጋጋ፤ ገንዘብና ወቅቱ እየገበረ ለሊት ደግሞ እንቅልፉ አጥቶ ሲያነጋ ስታይ!!! ስለደጃል ያሁሉ ተነግሮን ሲያበቃ ከዛ ሁሉ ማታለያውጋ ቢመጣ ስንት ሰው እንደ ሚከተለው ለማሰብ ቀላል ነው። 🎙ኡስታዝ አቡ ዐብዱልመናን ኻሊድ ቢን ጠይብ 📎https://t.me/Al_Furqan_Islamic_Studio/20955

🍯 ማርን ከውሃ ጋር በባዶ ሆድ መጠጣት 🍯 ጥበበኛው ጌታችን ስለ ንብና ስለአስደናቂው ምርቷ እንዲህ ሲል ነግሮናል:-
﴿.... يَخْرُجُ مِنْ بُطُونِهَا شَرَابٌ مُّخْتَلِفٌ أَلْوَانُهُ فِيهِ شِفَاءٌ لِّلنَّاسِ ۗ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً لِّقَوْمٍ يَتَفَكَّرُونَ﴾ [النحل: 68-69
«... ከሆዷም የተለያዩ ቀለማት ያሉት መጠጥ ይወጣል፤ በውስጡም ለሰዎች ፈውስ አለ። በዚህ ውስጥ ለሚያስተነትኑ ሰዎች ታላቅ ተአምር አለበት።»
🖋 ኢማም ኢብኑል-ቀይም رحمه الله ባማረው ኪታባቸው ዛዱል-መዓድ፣ 4/35 ውስጥ እንዲህ ይላሉ፦ «ነቢዩ ﷺ ማርን ከውሃ ጋር በባዶ ሆድ ይጠጡ ነበር። በዚህም ጤናን ለመጠበቅ የሚያስደንቅ ምስጢር አለ፤ ይህንንም ምስጢር ብልህና ጥበበኛ የሆነ ሰው ብቻ ሊገነዘበው ይችላል።» 👌ማርን በመጠቀም ጤንነታችንን እንጠብቅ❗️ ✍ አቡ አብድልመናን

👇አንዳንድ ታሪኮቻችንን ስናዳምጥ አሊያም ስናነብ ሰውነታችንን ቢነዝረንም ተስፋ ግን አንቆርጥም❗️ 🍒 በአንደሉስ የክብርና የብልጽግና ዘመን፣ የአውሮፓ ወጣቶች የነሳራዎችን ሥነ-ጽሑፍን ይንቁ ነበር
👇አንዳንድ ታሪኮቻችንን ስናዳምጥ አሊያም ስናነብ ሰውነታችንን ቢነዝረንም ተስፋ ግን አንቆርጥም❗️ 🍒 በአንደሉስ የክብርና የብልጽግና ዘመን፣ የአውሮፓ ወጣቶች የነሳራዎችን ሥነ-ጽሑፍን ይንቁ ነበር፤ ይልቁንም የዐረብኛ ሥነ-ጽሑፍንና ግጥምን ይማሩና ያጠኑ ነበር። እስከዚህም ደረጃ ድረስ፣ በላቲን ቋንቋ ለጓደኛው ደብዳቤ መጻፍ ከሚችል አንድ ሰው ጋር ሲነጻጸር፣ በሚያምር ዐረብኛ የልባቸውን ሐሳብ መግለጽ የሚችሉ አንድ ሺህ ሰዎች ነበሩ፤ እንዲሁም ከዐረቦች እንኳን በተሻለ የዐረብኛ ቋንቋ ግጥሞችን ይጽፉ ነበር። ማቲው ካር 👍 ግን እድል አለን እኛ ሙስሊሞች ነንና ተስፋ አንቆርጥም❗️ አዎ እኛ ሙስሊሞች:- ሊታመም የሚችል፣ ነገር ግን የማይሞት ሕዝብ ነን። እኛ ሊደናቀፍ የሚችል፣ ነገር ግን የማይወድቅ ሕዝብ ነን። እኛ ሊደክም የሚችል፣ ነገር ግን የማይሰበር ሕዝብ ነን። እኛ ሙስሊሞች በበርካታ መከራና ፈተናዎች ውስጥ ልናልፍ የምንችል ሕዝብ ነን፤ ነገር ግን በአላህ መጽሐፍና በመልእክተኛው ﷺ ሱና ውስጥ እስካለን ድረስ ዳግመኛ እንነሳለን❗️ ሀያሉ ጌታችን እንዲህ ብሏልና:- ﴿وَإِنَّ جُندَنَا لَهُمُ الْغَالِبُونَ﴾ «እነሆ፣ የእኛ ወታደሮች በእርግጥ አሸናፊዎቹ ናቸው።» [ሱረቱ አስ-ሷፋት፦ 173] 👌 ይህ ማለት፦ የአላህ ሠራዊት የሆኑት አማኞች በመጨረሻ ድልና የበላይነት የሚያገኙት እነርሱ ናቸው። ✍ አቡ አብድልመናን

👉 ዛሬ ቅዳሜ 23/12/18 በፉርቃን መስጂድ የምንጀምረው የሱረቱ ኢብራሂም መልእክት ጥቅል ይዘት ሱረቱ ኢብራሂም መካ ውስጥ የተወረደች ሱራ ስትሆን፣ 52 አንቀጾች አሏት። ዋናው መልእክቷም አላህን ብቻ ማምለክ፣ የእርሱን ጸጋዎች ማመስገን፣ ከክህደትና ከአላህ ጋር ጣዖታቶችን ከማጋራት መጠንቀቅ እና የከሓዲዎችን መጨረሻ እጅግ የከፋ መሆኑን መግለፅ ነው። 1. ቁርኣን ሰዎችን ከጨለማ ወደ ብርሃን ያወጣል። አላህ ቁርኣንን ሰዎችን ከክህደትና ከድንቁርና ጨለማ ወደ እምነት፣ ወደ እውነትና ወደ አላህ ብርሃን ለማውጣት እንዳወረደው ትገልጻለች። 2. የመልእክተኞች ጥሪ ወደ ተውሒድ ነበር። መልእክተኞች ሁሉ ሕዝቦቻቸውን አላህን ብቻ እንዲያመልኩ ጠርተዋል። የመልእክታቸው መሠረትም የአላህ አንድነት እና እርሱን ብቻ ማምለክ ነው። 3. የአላህን ጸጋዎች ማመስገን። ከሱራዋ ታላላቅ መልእክቶች አንዱ ጸጋን ማመስገን እንደሚገባ ነው። አላህም፦ «ብታመሰግኑኝ በእርግጥ እጨምርላችኋለሁ፤ ብትክዱም ቅጣቴ ከባድ ነው» ብሏል። 4. የሙሳ ዐለይሂሰላምና የፈርዖን ታሪክ። ሙሳ ዐለይሂሰላም ሕዝቡን ከጨለማ ወደ ብርሃን እንዲወጡ ተጣራ፤ ፊርዐውንና ተከታዮቹ ግን ክህደትን በመምረጣቸው ተዋረዱ። ይህም አንድ ትልቅ መርህን ይጠቁማል እርሱም በየትኛውም ዘመንም ይሁን ቦታ የእውነትን መንገድ የሚቃወም ሰው የመጨረሻ ውጤቱ ኪሳራ ነው። 5. የክህደትና የሽርክ መጨረሻ። በቂያማ ቀን ከሓዲዎች በኃይለኛ ጸጸት ውስጥ ይሆናሉ፤ ሰይጣንም ተከታዮቹን ይክዳል። 6. የመልካም ቃል ምሳሌ። አላህ የመልካም ቃልን—በተለይም የተውሒድን ቃል—ከመልካም ዛፍ ጋር ያመሳስለዋል፤ ሥሩ ጽኑ ነው፣ ቅርንጫፎቹም ወደ ሰማይ ይወጣሉ። 7. የኢብራሂም ዐለይሂሰላም ታላላቅ ዱዓዎች። ሱራዋ በኢብራሂም ዐለይሂሰላም ዱዓ ትደመደማለች። ከዱዓዎቹም ውስጥ ለመካና ለዘሮቹ ደህንነት፣ ሶላትን በጽናት እንዲያቆሙ፣ ለራሳቸው፣ ለወላጆቹና ለምእመናን ምሕረት እንዲሰጥ የጠየቀው ይገኛል። 👌በአጭሩ፦ ሱረቱ ኢብራሂም የሚያስተምረን፣ አላህን ብቻ ማምለክ፣ በቁርኣንና በመልእክተኞቹ ማመን፣ የአላህን ጸጋዎች ማመስገን፣ በእውነት ላይ መጽናት እና ከክህደት፣ ከሽርክና ከበደል መራቅ የመዳን መንገድ መሆኑን ነው። 🤲አላህ ቁርኣንን ተረድተው ከሚሰሩበት ባሮቹ ይጨምረን❗️ ✍ አቡ አብድልመናን

🌎ቀጥታ ስርጭት Live straem💥 📖የዛሬው እለት ከመግሪብ እስከ ዒሻ የተፍሲር ፕሮግራም 📖 ሱረቱ ኢብራሂም 📖 📚 ከመጀመሪያው አንቀፅ ይጀምራል 🎙የኡስታዝ አቡ ዐብዱልመናን ኻሊድ ቢን
🌎ቀጥታ ስርጭት  Live straem💥 📖የዛሬው እለት ከመግሪብ እስከ ዒሻ የተፍሲር ፕሮግራም 📖 ሱረቱ ኢብራሂም 📖 📚  ከመጀመሪያው አንቀፅ ይጀምራል 🎙የኡስታዝ አቡ ዐብዱልመናን ኻሊድ ቢን ጠይብ አላህ ይጠብቀው። 🕌በታላቅዋ ፉርቃን መስጂድ አላህ ይጠብቃት። 📚የኪታቡ pdfለማግኘት👇👇 https://t.me/Al_Furqan_pdf/694 🛜ለቀጥታ ስርጭት👇👇 https://t.me/Abuabdlmenan?livestream

🍒 የሰውን ልብ ከሚያሳምሙ ንግግሮችና ድርጊቶች ተጠንቀቁ❗️ ታላቁ ሼይኽ ፈይሰል አል-ሐሻዲ አላህ ይጠብቀው እንዲህ ይላል:- አሳማሚ ቃላት፣ ወንድምህን በንግግር ማስከፋት እና ከበባድ ቀልዶች ልብን ከሚጎዱ ነገሮች መካከል ናቸው። እነዚህ ስሜትን ይጎዳሉ፣ በሰው ልብ ውስጥም ረጅም ጊዜ ሊቆይ የሚችል ቁስል ይተዋሉ፤ ምንም እንኳ ቀልድ በሚል ሽፋን ቢቀርብም። ስለዚህ በሰው ላይ ከማሾፍ፣ በሰው መልክ፣ ክብደትና አካላዊ ቁመና ላይ አስተያየት ከመስጠት ተጠንቀቅ። እንዲሁም ከሚያስከፉ እንቅስቃሴዎች፣ ፌዝ ወይም ንቀት ከተሞላባቸው እይታዎች ተጠንቀቅ፤ እነዚህም ተግባሮች በልብ ውስጥ ቃላቶች እንደሚተዉት ያህል ከባድ ሕመምን ሊተዉ ይችላሉ❗️ ✍ አቡ አብድልመናን

🤲 ሁሌም ዱዓ ከማድረግ አትቦዝን❗️ ሀያሉ ጌታህ እንዲህ ብሏልና:- وَقَالَ رَبُّكُمُ ادْعُونِي أَسْتَجِبْ لَكُمْ «ጌታችሁም፦ ‘ጠይቁኝ፤ እቀበላችኋለሁ’ አለ።» 🫵 በየትኛው መንገድ ላይ መልካም ነገር እንደተደበቀልህ አታውቅም፤ ነገር ግን አላህ ወደዚህ መልካም ነገር እንደሚመራህ በእርግጠኝነት እመን❗️ 🍒 አራት የዱዓ ቃላቶች መልካምን ነገር ሁሉ የሚያካትቱ ናቸውና እንካችሁ። 🍃 🔶 ከዐብዱላህ ኢብኑ መስዑድ ረዲየላሁ ዐንሁ ተዘግቦ እንደመጣው፣ ነቢዩ ﷺ እንዲህ ይሉ ነበር፦ "اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ الْهُدَى، وَالتُّقَى، وَالْعَفَافَ، وَالْغِنَى." «አላህ ሆይ! መመሪያን፣ ተቅዋን (አላህን መፍራትን)፣ ንጽሕናን እና መብቃቃትን እጠይቅሃለሁ።» 📚 ኢማሙ ሙስሊም ዘግበውታል። 🍃 ማብራሪያው፦ አላህን እንዲመራን፣ በትእዛዙ ላይ እንድንጸና፣ ከክልክል ነገር እንድንጠበቅና ከፍጡራን እንዳንሻ በአላህ ተብቃቂ እንድንሆን እንጠይቀዋለን። ሁሌም በዚህ ዱዓ አላህን እንማፀነው❗️ ✍ አቡ አብድልመናን

👌 አሁንም ከበረከትህ ነፃ መሆን አልችልም❗️ “አላህ ሆይ! አንተ እንጂ ማንም አላሳደገኝም፤ አንተ ልግስናንና በጎነትን በቀር ምንም አላስለመድከኝም። ፍርሃቴን አረጋጋህልኝ፣ ነውሮቼን ሸፈንክልኝ፣ ሕይወቴንም አበጀኸልኝ። ብዙና የተትረፈረፈ መልካምን ላክልኝ፤ እኔ ወንጀለኛው ባሪያህ ለዚያ ሁሉ ስጦታህ ብቁና ተገቢ ባልሆንም አንተ ግን ለመስጠት ብቁና ቻይ በባህሪህም አዛኝና ቸር ጌታ ነህ❗️ ብቸኝነቴን አስወገድክኝ፣ ከጭንቀቴ ሁሉ ገላከልከኝ፣ በየትኛውም ጉዳዬ መጠጊያ ሆንከኝ፣ አጠጣኸኝ፣ አበላኸኝ፣ በተሟላ የጤንነት ልብስ አጌጥከኝ ለኔ ምንም ኃይልና ችሎታ ሳይኖረኝ ሙሉ ከሆነው ከማይነጥፈው ካዝናህ ያማረ ሲሳይንም ሰጠኸኝ❗️ 💯 አምላኬ ሆይ አንተ የምስጋና ባለቤትና ምስጋና የተገባህ ብቸኛ ጌታ ነህና ምስጋናዬ ላንተ ይሁን❗️ አሁንም አስከመጨረሻው እኔ....👇 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 ﴿رَبِّ إِنِّي لِمَا أَنْزَلْتَ إِلَيَّ مِنْ خَيْرٍ فَقِيرٌ﴾ [القصص: 24] “ጌታዬ ሆይ! ከአንተ የሚመጣን ማንኛውንም በጎ ነገር በእጅጉ እፈልጋለሁ።” ✍ አቡ አብድልመናን https://t.me/Abuabdlmenan/2146

🍒ዱንያን በኪሳችን እንጂ በልባችን ውስጥ አናስገባት ❗️ قال: فجلست حين رأيته تبسم، فرفعت بصري في بيته، فوالله ما رأيت فيه شيئًا يرد البصر غير أُهُبٍ ثلاثة. فقلت: يا رسول الله، ادع الله فليوسع على أمتك، فإن فارس والروم قد وسع عليهم وأعطوا الدنيا وهم لا يعبدون الله. فاستوى جالسًا، فقال: «أفي شك أنت يا ابن الخطاب؟ أولئك قوم عُجِّلت لهم طيباتهم في الحياة الدنيا». فقلت: استغفر لي يا رسول الله». ከዚያም ወደ ነቢዩ ﷺ ገባሁ። እሳቸውም በአንድ ምንጣፍ ላይ ተኝተው ነበር። በእሳቸውና በምንጣፉ መካከል ሌላ አልጋ ወይም አልጋ መሸፈኛ አልነበረም። የምንጣፉ ምልክት በጎናቸው ላይ ታይቶ ነበር። በቆዳ የተሠራ ትራስ ላይም ተደግፈው ነበር፤ ውስጡም የዘንባባ ቅጠል ፋይበር ነበር። እሳቸው ፈገግ ሲሉ ባየሁ ጊዜ ተቀመጥኩ። ከዚያም በቤታቸው ውስጥ ዙሪያዬን ተመለከትኩ። በአላህ እምላለሁ፣ ዓይንን የሚስብ ምንም ነገር አላየሁም፤ ከሶስት የእንስሳት ቆዳዎች በስተቀር። እኔም፦ “የአላህ መልእክተኛ ሆይ! ለዑማህ አላህን ለምንላቸው ፋርሳውያንና ሮማውያንኮ አምልኮትን ለአላህ ሳያደርጉ የዓለም ሀብት ተሰጥቷቸዋል ” አልኳቸው። ነቢዩም ﷺ ተቀመጡና እንዲህ አሉ ፦ “አንተ ኢብኑል-ኸጧብ ሆይ! በጥርጣሬ ውስጥ ነህን? እነዚያ ሰዎች የዓለም መልካም ደስታዎች በዚህች የዱንያ ሕይወት ውስጥ በፍጥነት የተሰጣቸው ሰዎች ናቸው” እኔም፦ “የአላህ መልእክተኛ ሆይ! ምሕረት ጠይቁልኝ” አልኳቸው። ✍ አቡ አብድልመናን

🍒 ተስፋ አትቁረጥ❗️ አላህ በኢብራሂም (ዐለይሂ ሰላም) አንደበት እንዲህ ይላል፦ ﴿وَمَن يَقْنَطُ مِن رَّحْمَةِ رَبِّهِ إِلَّا الضَّالُّونَ﴾ «ከጌታው ምሕረት ተስፋ የሚቆርጥ ከጠመሙት ሰዎች በስተቀር ማን ነው?» [ሱረቱል ሒጅር፡ 56] 👆 ይህች አንቀጽ በዱንያ ሕይወት ለተጨነቀ፣ ኃጢአቱ በዝቶበት ልቡ ለተሰበረ ሰው ሁሉ ታላቅ ምክር ይዛለች። ከአላህ ምሕረት ተስፋ አትቁረጥ፤ ኃጢአትህም ከአላህ ምሕረት ይበልጣል ብለህ አታስብ። ነቢዩ ኢብራሂም ዐለይሂ ሰላም በአላህ ዘንድ ከፍተኛ ደረጃ ያለው ነቢይ ሆኖ እንኳን፣ አላህን የሚያውቅና በእርሱ ላይ ጥሩ ግምት ያለው ሙእሚን ከአላህ ምሕረት ተስፋ መቁረጥ እንደሌለበት አስተምሮናል። አላህ ምሕረቱ ሰፊ ነው፤ ተውበትን ይቀበላል፤ ወደ እርሱ ለሚመለስም ኃጢአቱን ይምራል። ስለዚህ ምንም ያህል ብትሳሳት «ጠፋሁ» አትበል፤ «አላህ አይምረኝም» አትበል። ይልቁንም ወደ አላህ ተመለስ፣ ምሕረትን ለምን፣ በአላህም ላይ መልካም ግምት ይኑርህ፣ እንደገናም ጀምር። አላህም እንዲህ ይላል፦ ﴿قُلْ يَا عِبَادِيَ الَّذِينَ أَسْرَفُوا عَلَى أَنفُسِهِمْ لَا تَقْنَطُوا مِن رَّحْمَةِ اللَّهِ ۚ إِنَّ اللَّهَ يَغْفِرُ الذُّنُوبَ جَمِيعًا﴾ «እነዚያ በራሳቸው ላይ ወሰን ያለፉ ባሮቼ ሆይ! ከአላህ ምሕረት ተስፋ አትቁረጡ፤ እነሆ አላህ ኃጢአቶችን ሁሉ ይምራል።» [ሱረቱዝ-ዙመር፡ 53] ዋናው መልእክት፦ ኃጢአትህን ዒባዳን ለመተው ምክንያት አታድርገው፤ የፈለግኸው መፍትሔ ስላልመጣም ተስፋ አትቁረጥ። ወደ አላህ ተመለስ፤ የእርሱ የምሕረት በር ክፍት ነው። ከአላህ ጋር እውነተኛ የሚሆን ሰውን አላህ አያጠፋውም። ✍ አቡ አብድልመናን

🌎ቀጥታ ስርጭት Live straem💥 📖የዛሬው እለት ከመግሪብ እስከ ዒሻ የተፍሲር ፕሮግራም 📖 ሱረቱ አል-ሒጅር 📖 📚 ከ16ኛው አንቀፅ ይጀምራል 🎙የኡስታዝ አቡ ዐብዱልመናን ኻሊድ ቢን ጠ
🌎ቀጥታ ስርጭት  Live straem💥 📖የዛሬው እለት ከመግሪብ እስከ ዒሻ የተፍሲር ፕሮግራም 📖 ሱረቱ አል-ሒጅር 📖 📚  ከ16ኛው አንቀፅ ይጀምራል 🎙የኡስታዝ አቡ ዐብዱልመናን ኻሊድ ቢን ጠይብ አላህ ይጠብቀው። 🕌በታላቅዋ ፉርቃን መስጂድ አላህ ይጠብቃት። 📚የኪታቡ pdfለማግኘት👇👇 https://t.me/Al_Furqan_pdf/694 🛜ለቀጥታ ስርጭት👇👇 https://t.me/Abuabdlmenan?livestream https://t.me/Abuabdlmenan/2116

🫴 ትልቅ የምስራች ለህመምተኞች ሁሉ❗️ አዎን አንድ ሰው ሲታመምና የአልጋ ቁራኛ ሲሆን ከሚሰራቸው መልካም ስራዎች ሊቋረጥና ሊያዝን ይችላል ዓለማዊው እንቅስቃሴም ስለሚገታ ልቡ ሊጨናነቅና እራሱን እንደሸክም ሊቆጥር ይችላል ግን አብሽር የሚከተሉትን ሐዲሶች እንደመፅናኛ ተጠቀምባቸውና እራስህን አረጋጋ። *⊰≼ የምስራች ⋟⊱* አቡ ሁረይራ ረዲየላሁ ዐንሁ እንደዘገበው የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ "إنَّ اللهَ تعالى يَبتلِي عبدَهُ المؤمن بالسَّقَمِ؛ حتى يُكفِّرَ عنهُ كلَّ ذنْبٍ". 📚 صحيح الجامع : (1870) «አላህ አንድን ሙእሚን በሕመም ይፈትነዋል ይህም ከኃጢአቱ ሁሉ እስኪያስወግድለት ድረስ ነው።» በሌላ አቡ ሁረይራ ረዲየላሁ ዐንሁ ባስተላለፈው ሐዲስ የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ مَا يُصِيبُ الْمُسْلِمَ مِنْ نَصَبٍ، وَلَا وَصَبٍ، وَلَا هَمٍّ، وَلَا حَزَنٍ، وَلَا أَذًى، وَلَا غَمٍّ، حَتَّى الشَّوْكَةِ يُشَاكُهَا، إِلَّا كَفَّرَ اللَّهُ بِهَا مِنْ خَطَايَاهُ. 📚 رواه البخاري ومسلم "አንድ ሙስሊም የሚደርስበት ድካም፣ ሕመም፣ ጭንቀት፣ ሀዘን፣ ጉዳት ወይም መከራ፤ እሾህ ቢወጋው እንኳ፣ አላህ በዚያ ምክንያት ከኃጢአቶቹ የተወሰኑትን ይሰርዝለታል።" ኢማም ኢብኑል ቀይም አላህ ይዘንለት እንዲህ ይላሉ፦ *«ولا يزال البلاء بالمؤمن حتى يمشي على وجه الأرض وليس عليه خطيئة»* 📚 إغاثة اللهفان (2/188) «አንድ አማኝ ከኃጢአት የፀዳ ሆኖ በምድር ላይ እስኪሄድ ድረስ መፈተኑ አይቋረጥም።» ┈┉┅┅●📘📕📗●┅┅┉┈ 👌 ስለዚህ በህመም ውስጥ ያላችሁ ወንድም እህቶቼ ሆይ አብሽሩ እንዳታማርሩ ያላችሁበትን ፈታኝና አስቸጋሪ ወቅት ለኸይር ነው ብላችሁ በትዕግስት እለፉት። 🤲 አላህ የዓፊያ ልብስን ያልብሳቹ❗️ ✍ አቡ አብድልመናን

አብሽሩ ከታገሳቹ አጅር አላቹ
አብሽሩ ከታገሳቹ አጅር አላቹ