cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

የግዮን ደጅ አፀድ

በአማራ ጥፋት የጀመረውን የሀገር ፍርሰት እናስቁም

Show more
Advertising posts
323
Subscribers
No data24 hours
-17 days
-1230 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

“በኢትዮጵያ ሁሉንም ተማሪዎች ካሳለፉ አምስት ትምህርት ቤቶች መካከል ሦስቱ በአማራ ክልል የሚገኙ ናቸው” ትምርት ቢሮ ተማሪዎች የጥይት ድምጽ እየሰሙ ተምረዋል፤ የጥይት ድምጽ እየሰሙ ተፈትነዋል፡፡ አብዘኛዎቹ የክልሉ ተማሪዎች በጦርነት ምክንያት በወደሙ እና በተዘረፉ ትምህርት ቤቶች ለመማር ተገድደዋል፡፡ በፈተና ወቅት በተፈጠረ አለመረጋጋት ፈተናውን አቋርጠው የወጡ ተማሪዎች መኖራቸውም አይዘነጋም፡፡ ፈተናዎች ቢበዙም፣ የተገኘው ውጤት አጥጋቢ ባይሆንም፣ ሰላም ከተረጋገጠ፣ የተረጋጋ እና የተስተካከለ ትምህርት መሥጠት ከተቻለ ግን ተስፋ ሰጪ ውጤቶች ታይተዋል፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር ከሰሞኑ ባወጣው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት 3 ነጥብ 2 በመቶ የሚሆኑት ብቻ ማለፋቸውን መግለጹ ይታወሳል፡፡ በኢትዮጵያ አምስት ትምህርት ቤቶች ደግሞ ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች ሙሉ ለሙሉ አሳልፈዋል፡፡ በአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የሥርዓተ ትምህርት ዝግጅት እና ትግበራ ዳይሬክተር ካሴ አባተ እንደ ሀገር አምስት ትምህርት ቤቶች ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች አሳልፈዋል፤ ሦስቱ ደግሞ በአማራ ክልል የሚገኙ ናቸው ብለዋል፡፡ ደሴ ልዩ የአዳሪ ትምህርት ቤት፣ ሐዲስ ዓለማየሁ ልዩ የአደሪ ትምህርት ቤት እና ባሕር ዳር ስቲም ትምህርት ቤት ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን ያሳለፉ ትምህርት ቤቶች ናቸው ተብሏል፡፡ አሚኮ !
Show all...
ሰበር‼️ሰበር‼️ሰበር‼️ አማራ  ሲቪሊያን በሮኬት ተደበደቡ‼️ ተደጋጋሚ ሽንፈት የገጠመው ፋሽስታዊና ሽብርተኛው የአብይ ስርዐት ኢንተርኔትና ኔትወርክ ዘግቶ ወደ ህዝብ ሮኬት እየተኮሰ መሆኑ ታውቋል። ዛሬ ጠዋት ደጋ ዳሞትና ቢቡኝ ወረዳ መካከል የወይን ውኃ የምትባል የገጠር መንደርን በሮኬት ደብድቧል። ወደ ፍኖተ ሰላምም ሮኬት እንዳስወነጨፈ ታውቋል። ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ ወገኖች እንደተጎዱም ተነግሯል።
Show all...
👍 1
Show all...
Amhara power

ፋሽስታዊው አገዛዝ በፍኖተሰላም ንፁሐንን በድሮን የጨፈጨፈው እንዲህ ነበር። መታገል መብታችን ሳይሆን የአማራነት ግዴታችን ነው ‼ ይሔ ገዳይ ስርዓት ወደመቃብር እንዲወርድ መታገል ግዴታችን ነው ‼

በአማራነታቸው ተለይተው አዋሽ 40 የታፈኑ የህሊና እስረኞች የረሃብ አድማ ሊያደርጉ ነው። ኤቢሲ ቲቪII መስከረም 20 2016 ዓ/ም የህሊና እስረኞቹ ለ ኤቢሲ ቲቪ በላኩት ደብዳቤ “በአዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ ታግተን የምንገኝ የማንነት፣ የህሊና እና የፖለቲካ እስረኞች ከዛሬ ሰኞ መስከረም 21/ 2016 ጀምሮ በሚከተሉት ነጥቦች ምክንያት የርሃብ አድማ አድርገናል፡፡” ሲሉ ገልፀዋል። የረሃብ አድማ የሚያደርጉ ምክንያትም 1. በአማራ ሕዝብ ላይ የተከፈተውን የዘር ፍጅት፣ ጅምላ ጭፍጨፋ እና ማንነት ተኮር ጥቃት በመቃወም 2. በአማራዊ ማንነታችን ምክንያት በአዋሽ 40 ወታደራዊ ካምፕ ታግተን የሚደርስብን የሰብዓዊ መብት ጥሰት፣ የሕክምና እጥረት፣ የምግብ እጥረት በመቃወም 3. በወታደራዊ ካምፕ ውስጥ ከፍርድ ቤት እውቅና ውጭ ታግተን ለፍርድ አለመቅረባችን ፤ ለከፍተኛ የበሽታ ወረርሽኝ መጋለጣችን እንዲሁም ለከፋ የአየር ንብረት ሙቀት መጋለጣችንን በመቃወም 4. በታገትንበት ካምፕ ውስጥ የሥርዓቱ ገዳይ ቡድን የሚያደርስብን የግድያ ዛቻ፣ አማራ ተኮር ስድብ፣ ዛቻ፣ ማስፈራራትና ማንቋሸሽ በመቃወም፡፡ በመሆኑም በእነዚህ ምክንያት የርሃብ አድማ እና መሰል እርምጃዎችን ተፈጥሯዊ መብታችንን ተጠቅመን የምንጀምር መሆኑን እየገለጽን  የፍትሕ ተቋማት፣ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች፣ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ሃገራዊ፣ አሁጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ተቋማት በመንግሥት ላይ ተጽዕኖ  በማድረግ ታሪካዊ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ እንጠይቃለን ይላል ለ ኤቢሲ የላኩት ደብዳቤ።
Show all...
አገዛዙ ፋብሪካን ወደእሥር ቤት ቀየረ የአገዛዙ ጦር ሠራዊት የጥረት ኮርፖሬት ንብረት የሆነውንና በወልድያ የሚገኘውን የጁ ማር ማቀነባበሪያ ፋብሪካ የአማራ ተወላጅ ወታደሮች እስር ቤት አደረገው። ከሠራዊቱ ተለይተው የሚታሠሩ የአማራ ተወላጆች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ቀጥሏል። በ8ኛ ዕዝ አባላት የነበሩ በመቶዎች የሚቆጠሩ የአማራ ተወላጅ የሠራዊት አባላት ወልድያ ውስጥ ታስረዋል። የሠራዊቱ አባላት ትጥቅ ፈተው እንዲቆዩ ከተደረጉ በኋላ ፡ የሲቨል ልብሳቸውንና ስልካቸውን በመቀማት እንቅስቃሴያቸው ተገድቦ ቆይቷል። የሠራዊቱ አባላት አሁን ወልድያ በሚገኘው የጥረት ኮርፖሬት ንብረት በሆነው የጁ ማር ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ግቢ ውስጥ ታስረዋል። ቁጥራቸው በውል ያልተለዩ ወታደሮች ያለፉትን ሶስት ሳምንታት በፋብሪካው የተለያዩ አዳራሾች ታስረው የሚገኙ ሲሆን በመቶዎች እንደሚቆጠሩ ወታደራዊ ምንጮች ገልፀዋል።  ወታደሮቹ አላማጣ በተቋቋመ ወታደራዊ ፍርድ ይቀርባሉ ቢባሉም ባለፉት ወራቶች በሠመራና ቡሬ የሚገኙት ወታደሮች ከእንግልት ሊወጡ አልቻሉም። ከዚህ ቀደም ከሠራዊቱ ተለይተው የታሠሩ በአስር ሺህዎች የሚቆጠሩ የአማራ ተወላጆች በአፋር ሠመራ ፣ በአፋር ቡሬ፣ በሐረር፣ እና ሌሎችም የአገሪቱ ክፍሎች ከሠራዊት ክፍላቸው እየተለዩ ታጉረው በእንግልት ላይ ይገኛሉ። በቅርቡ ይፋ የሆነው የአገዛዙ የጦርነት ግምገማ ሰነድ በከፍተኛ ደረጃ ለሾማቸው ወታደራዊ ጀነራሎች ከፍተኛ ያደለውን የገንዘብ እና መሬት እደላ መሠል ማባበያ ለመስመራዊ መኮንኖችና የበታች ሹሞችም በማደል ስርዓቱን እንዲጠብቁና የመፈንቅለ መንግስት ስጋቱን ለማቅለል ማቀዱ ይታወሳል። በተመሳሳይ በጦር ግንባር ያሉ ጦርነቱን የሚቃወሙና የማይቀበሉ የሠራዊቱ እግረኛ ወታደሮች ላይ ግን አስተማሪ የሆነ የቅጣት እርምጃ ይወሰድ የሚል ትዕዛዝ አስቀምጧል።
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
የቀድሞው የአማራ ክልል ርዕሠ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ዛሬ በአዲስ አበባ ከነጠባቂዎቻቸው ተይዘው ተለቀቁ። አቶ ገዱ ቡልጋሪያ ማዞሪያ የሚባለው አካባቢ ከአምስት በላይ በሚሆኑ የብሔራዊ መረጃ እና የፌዴራል ፖሊስ መኪኖች በተጫኑ የፀጥታ ኃይሎች መንገድ ላይ አስቁመዋቸው ከፈተሿቸውና እንደመገፈታተር ሁሉ ካደረጓቸው በኋላ ስልካቸውን እና ላፕቶፓቸውን እንደወሰዱባቸው የዓይን እማኞች ነን ያሉ ወገኖች ተናግረዋል። ከገዱ በተጨማሪ የጠባቂዎቻቸውና የሹፌሮቻቸው ስልክ ተወስዷል መባሉን ሰምተናል።
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
"ፋኖ ሁለተኛውን ዙር ጠላትን የማሽመድመድ ዘመቻውን በሁሉም አቅጣጫ እየከወነ ይገኛል:: ይህ የሚጠበቅ ነው:: በሸዋ ግንባር ደራ በፋኖዎች ቁጥጥር ስር ሆናለች!  የሸዋ አርበኞች ቁንጮ የሆኑት የራስ አበበ አረጋይ ልጆች በመጀመሪያው ዙር ነፃ ያደረጉትን ወረዳዎች የመንዝ የይፋትና የመሀል ሜዳ ወዘተ ወረዳዎች ዛሬም እንደተቆጣጠሩት ይገኛል:: በሰሜን ሸዋ በኩል ፋኖ እየገፋ ነው ያለው የኦሮሙማ ፋሺስት ቡድን  ሸኖ ላይ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰራዊት እያከማቸ ነው:: ይህ ሰራዊት ከሚሉት ይልቅ  በ አለም አቀፍ ሩጫ ላይ ቢያሳትፉት ይመረጥ ነበር:: በጎጃም ግንባር እየተደረገ ያለው ተጋድሎ እጅግ በጣም የሚያስቀና እኔስ መች ይሆን ከነዚህ ጀግናዎች ጋር የምሰለፍ ብሎ የሚመኝበት ወቅት ደርሰናል:: ጎጃም ከባህር ዳር በስተቀር ዛሬ 90% በፋኖዎች ቁጥጥር ስር ነው:: ፋኖ ደብረማርቆስና የጁቤ ላይ ከፍተኛ ገድል ፈፅመው የፋሺስቱን ጦር ብትንትኑን አውጥተውታል:: የገናናው አርበኛ የበላይ ዘለቀ እስትንፋሶች በርግጥም  የበላይን ስጋና ደም ልብና ወኔን ተላብሰው ተፈጥረዋል:: በአስር ሽዎች የሚቆጠሩ የበላይ ልጆች ጎጃም ላይ የሚፈፅሙት ጀብድ ወደፊት በፊልም ተቀርጾ ለታሪክ የሚቀመጥ ይሆናል:: ብቸና ደጋ ዳሞት ቡሬ ዳንግላ ማርቆስ ሉማሜ አማኑዔል መራዊ አቸፈር  ደንበጫና ሌሎች እዚህ ያልተጠቀሱ አካባቢዎች ያሉ ፋኖዎች የሰሩት ጀብዱ እጃችንን አፍ ላይ አሁን ድረስ አስጭኖናል:: በጎንደር ግንባር የኢትዮጵያ ባል የኢየሩሳሌም እጮኛ ተብለው የሚጠሩት የገናናው ንጉስ የመይሳው ካሳ ልጆች በደቡብ ጎንደር በደብረታቦር በማክሰኚት በእብናት በሁሉም ፋርጣ ወረዳዎች ጠላትን እንደ ተርብ እየተገተጉት ውልቅልቁን አውጥተውታል:: የጎንደር ፋኖዎች አርሶ አደሩን ሙሉ በሙሉ ከጎናቸው  እንዲሰለፍ አድርገዋል:: በአሁኑ ወቅት የፋሺስቱ ጦር በደብረታቦር በጥቂት ሆቴል ላይ መሽጎ መውጫው ጠፍቶት ተከቦ ይገኛል:: ሁለተኛ እንዳይሞክር አድርጎ ብትንትኑን የወጣውየፋሺስቱ ጦር በዚህ ጦርነት በጀግኖቹ የጎንደር ፋኖዎች ከፍተኛ ምትና ሽንፈት ደርሶበታል:: በወሎ ግንባር የንጉስ ሚካኤል እስትንፋሶች ጠላትን በሁሉም ግንባሮች በሚያስገርም ሁኔታ እያንቀጠቀጡት ሲሆን በላሊበላና በቆቦ የጠላት ሀይል ላይ ባሳረፉት ምት የጠላት ሰራዊት እንዳይሆን ሆኖ ብትንትኑ እንዲወጣ ተደርጓል:: ላሊበላ ላይ ከሶስት ቀን በፊት የአንድ አማራ ወጣት ብልት የቆረጠው primitive የኦሮሙማ እኩይ ሰራዊት ከወሎ ቤተ አማራ ምድር በህይወት እንዳይወጣ እንደሚሰሩ ጀግኖቹ የአሳምነው ልጆች የምስራቅ አማራ ፋኖዎች ቃል ገብተዋል:: ጃውሳ እንዲህ ከሆነ አዎ ሺህ ግዜ ጃውሳ ነኝ ያውም የሰማይ በራሪ ንስር!!! ድል ለሰፊው የአማራ ህዝብ!!!"
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
"የፋሺስቱ ሚድያ ሰሞኑን ገድዬዋለሁ ያለው ጀግናው ወንድማችን የላስታ አሳምነው ፅጌ ብርጌድ ዋና አዛዥ ኮማንደር ፍቅሩ አንማው ዛሬ ከሞት ተነስቶ በኢትዮ 360 ላይ አሁን እየተናገረ ይገኛል::"
Show all...