en
Feedback
Min Keman ምን? ከማን?

Min Keman ምን? ከማን?

Open in Telegram

ይህ ትኩረቱን በጥራት እና ግብይት ላይ አድርጎ፣ ጥራትን በማህበረሰቡ ዉስጥ ባህል እንዲሆን በማድረግ የተቃና የግብይት ስርዓት ለመፍጠር የሚሰራ ማህበራዊ የሬዲዮ ፕሮግራም እና መጽሔት ዝግጅት ክፍል ነዉ። (በትርታ FM 97.6) ለተጨማሪ መረጃ፦ +251978111281

Show more
1 473
Subscribers
-124 hours
-147 days
-6630 days

Data loading in progress...

Attracting Subscribers
June '26
June '26
+25
in 0 channels
May '26
+208
in 0 channels
Get PRO
April '26
+781
in 0 channels
Get PRO
March '26
+17
in 0 channels
Get PRO
February '26
+19
in 0 channels
Get PRO
January '26
+21
in 0 channels
Get PRO
December '25
+26
in 0 channels
Get PRO
November '25
+29
in 0 channels
Get PRO
October '25
+30
in 0 channels
Get PRO
September '25
+19
in 0 channels
Get PRO
August '25
+29
in 0 channels
Get PRO
July '25
+20
in 0 channels
Get PRO
June '25
+41
in 0 channels
Get PRO
May '25
+39
in 0 channels
Get PRO
April '25
+30
in 0 channels
Get PRO
March '25
+35
in 0 channels
Get PRO
February '25
+51
in 0 channels
Get PRO
January '25
+22
in 0 channels
Get PRO
December '24
+21
in 0 channels
Get PRO
November '24
+54
in 2 channels
Get PRO
October '24
+71
in 1 channels
Get PRO
September '24
+31
in 0 channels
Get PRO
August '24
+28
in 0 channels
Get PRO
July '24
+23
in 0 channels
Get PRO
June '24
+16
in 0 channels
Get PRO
May '24
+21
in 1 channels
Get PRO
April '24
+18
in 0 channels
Get PRO
March '24
+33
in 1 channels
Get PRO
February '24
+29
in 0 channels
Get PRO
January '24
+40
in 0 channels
Get PRO
December '23
+35
in 0 channels
Get PRO
November '23
+28
in 0 channels
Get PRO
October '23
+245
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
17 June+3
16 June+1
15 June0
14 June+1
13 June+2
12 June+3
11 June+1
10 June+3
09 June0
08 June+1
07 June0
06 June+1
05 June+5
04 June+1
03 June+2
02 June0
01 June+1
Channel Posts
🎙📻☎️ ዛሬ ሰኔ 10 ☎️📻🎙 #ምን? #ከማን? 💫ይከታተላሉ! 💫ይሳተፉ! 💫ይሸለሙ! ከ 9:00 ሰዓት እስከ 11:00 ሰዓት በ #ትርታ 97.6FM፣ በ #ዚኖ_ራዲዮ ኦንላይን፣ እንዲሁም በምን? ከማን? የ #ፌስቡክና #ቴሌግራም እና #ቲክቶክ ላይቭ ገጾች ፕሮግራማችንን መከታተል ትችላላችሁ። በዛሬዉ ዝግጅታችን፦ 👂በ #ምን_እንዴት_እንግዛ ዝግጅት #የታሸገ_የድንች_ጥብስ ታሪካዊ አመጣጥ፣ አዘገጃጀት እና በግዢ ወቅት ሊደረጉ የሚገባቸዉን ጥንቃቄዎች እንመለከታለን፤ 👂በሳምንቱ #እንግዳ ዝግጅት፦ ከየኢትዮጵያ #ህብረተሰብ_ጤና ኢኒስቲትዩት የስራ ኃላፊዎች ጋር ቆይታ እናደርጋለን፤ 👂በተጨማሪም #መጣጥፍ፣ #ዘገባዎች እና ጠቃሚና አስተማሪ የሆኑ ቅንብሮችን ይዘንላችሁ እንቀርባለን! ፨፨፨ #ምን? _ #ከማን? ፨፨፨ 👍 የሶሻል ሚዲያ አማራጮቻችን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ Telegram : t.me/minkeman Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61550090741996&mibextid=ZbWKwL Tiktok: tiktok.com/@minkemand

2
ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት የግሉ ዘርፍ ጉልህ ሚና ሊወጣ እንደሚገባ ተገለጸ። ========================== የግሉ ዘርፍ ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት የሚጠበቅበትን ጉልህ ሚና ሊወጣ ይገ+2
ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት የግሉ ዘርፍ ጉልህ ሚና ሊወጣ እንደሚገባ ተገለጸ። ========================== የግሉ ዘርፍ ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት የሚጠበቅበትን ጉልህ ሚና ሊወጣ ይገባል አለ የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት፡፡ ምክር ቤቱ ከኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጋር በመተባበር "በሀገራዊ የምክክር ሂደት የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ" በሚል መሪ ሀሳብ ያዘጋጀው የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ ተካሄደ። ምክር ቤቱ በምክክር ሂደቱ ላይ መሳተፉ ለኢኮኖሚ ማገገምና ለረጅም ጊዜ ሀገራዊ ልማት ከፍተኛ እገዛ የሚያደርግ በመሆኑ የግሉን ዘርፍ የኢኮኖሚ ጥቅሞችን በመወከል መረጋጋትን በማስፈንና ለሀገራዊ ተግዳሮቶች ተግባራዊ መፍትሄዎችን በማበርከት በምክክሩ ሂደት ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ተነግሯል፡፡ #ምንከማን #minkeman #Addisabab #Ethiopia #Quality #Marketing Telegram: t.me/minkeman Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61550090741996&mibextid=ZbWKwL Tiktok: tiktok.com/@minkemand
195
3
የፕላስቲክ ከረጢት የሚያሰራጩ 41 የጅምላ አከፋይ መደብሮች ታሸጉ ========================== የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ከአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የአዲስ
የፕላስቲክ ከረጢት የሚያሰራጩ 41 የጅምላ አከፋይ መደብሮች ታሸጉ ========================== የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ከአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የአዲስ አበባ ፓሊስ ጋር በጋራ ባደረጉት የተቀናጀ የክትትልና ቁጥጥር ዘመቻ በከተማዋ ትልቁ የንግድ ማእከል መርካቶ ሲኒማ ራስ አካባቢ ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የላስቲክ ከረጢት የሚያሰራጩ 41 የጅምላ አከፋፋይ የንግድ ድርጅቶች እርምጃ ወስደዋል። እርምጃው የተወሰደው የፕላስቲክ ከረጢት አጠቃቀምን ለመገደብ የወጣውን የአዋጅ ቁጥር 1383/2017 ድንጋጌ መነሻ በማድረግ እንደሆነ ተገልጿል። የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የከተማዋን ስነ-ምህዳር ለመጠበቅ እና የብክለት ምንጮችን ለመቀነስ የጀመረውን የማስከበር ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል። #ምንከማን #minkeman #Addisabab #Ethiopia #Quality #Marketing Telegram: t.me/minkeman Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61550090741996&mibextid=ZbWKwL Tiktok: tiktok.com/@minkemand
193
4
#እንዲያውቁት #ነዳጅ የሚገኝባቸው ማደያዎች ================== የሰኔ 10 ዕሮብ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ #ነዳጅ_ማደያ አገልግሎት የሚሰጡ እና በማደያዎቹ በመሰራጨት ላይ ያለው የተሽከ+2
#እንዲያውቁት #ነዳጅ የሚገኝባቸው ማደያዎች ================== የሰኔ 10 ዕሮብ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ #ነዳጅ_ማደያ አገልግሎት የሚሰጡ እና በማደያዎቹ በመሰራጨት ላይ ያለው የተሽከርካሪዎች #ናፍጣ እና #ቤንዚን አቅርቦት መጠን መረጃ፤ #ምንከማን #minkeman #addisababa #Ethiopia #Oil #gasstation #HormuzStrait #usa #iran Telegram: t.me/minkeman Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61550090741996&mibextid=ZbWKwL Tiktok: tiktok.com/@minkemand
230
5
መንግሥት የሕዝቡን እሮሮ ሰምቶ የዜጎችን የመኖርና መሠረታዊ አገልግሎቶችን የማግኘት መብት ቅድሚ ይስጥ። ===== የኢትዮጵያ የሸማቾች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት በአገሪቱ የሚስተዋለዉን ወቅታዊ የኢኮኖሚ+6
መንግሥት የሕዝቡን እሮሮ ሰምቶ የዜጎችን የመኖርና መሠረታዊ አገልግሎቶችን የማግኘት መብት ቅድሚ ይስጥ። ===== የኢትዮጵያ የሸማቾች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት በአገሪቱ የሚስተዋለዉን ወቅታዊ የኢኮኖሚ ጫና፣ የታሪፍ ጭማሪ እና በአገልግሎት ክፍያዎች ላይ የሚታዩ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪዎችን በተመለከተ ጋዜጣዊ መግለጫ አውጥቷል። በመግለጫዉ በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ እየታየ ካለው ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት፣ የቤት ኪራይ ንረት፣ የብር የመግዛት አቅም መዳከም እና የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ጋር ተዳምሮ የመንግሥት መሠረታዊ አገልግሎቶች የታሪፍ ማሻሻያ በሚል በአንድ ጊዜ መናራቸው እንዳሳሰበው ገልጿል። የፓስፖርት ክፍያ ከ150 - 300% ማደጉ፣ የተሽከርካሪ ሰሌዳ ዋጋ እስከ 59,400 ብር መድረሱ፣ የቦሎ፣ የስም ዝውውር እና የጠፋ መንጃ ፈቃድ ማውጫ ክፍያዎች (ከ560% በላይ) ማደጋቸው በትራንስፖርት ዘርፉ ላይ ከፍተኛ ጫና በመፍጠር ዝቅተኛውን ሸማች በሰንሰለት የሚቀጣ ሲሆን፣ የኤሌክትሪክ እና የቴሌኮም አገልግሎቶች ላይ የተደረጉት የታሪፍ ማሻሻያዎችም በአጠቃላይ ምርትና ንግድ ላይ ተጨማሪ የዋጋ ንረት አስከትለዋል። እንደ ኬንያ ያሉ አገራት ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎች ከጭማሪ ነፃ የሚያደርግ የድጎማ ወለል የዘረጉ ሲሆን፣ ሩዋንዳ በዲጂታይዜሽን ወጪን በመቀነስ የአገልግሎት ዋጋ ስታቃልል ቬትናም ደግሞ ከከፍተኛ ተጠቃሚዎች በመሰብሰብ አነስተኛ ገቢ ያላቸውን የመደጎም መርህን ትከተላለች። ይህንን ማኅበራዊ ቀውስና ምሬት ለመቅረፍ ድርጅቱ በቅርቡ የወጡት ታሪፎች በአስቸኳይ ታግደው በገለልተኛ ባለሙያዎችና በሸማቾች ማኅበራት ተሳትፎ እንደገና እንዲሰሉ በመጠየቅ መንግሥት ራሱ ያወጣቸውን አዋጆችና ዓለም አቀፍ ስምምነቶች በማክበር የሕግ የበላይነትን እንዲያስከብር ጥሪ አቅርቧል። Tiktok: tiktok.com/@minkemand
244
6
#ነፃ_ሃሳብ አዲሱን የመኪና ታርጋ ዋጋን በተመለከተ ========================== 📣አዲሱን የመኪና ሰሌዳ ዋጋ በመቃወም ያቀረቡት አማራጭ ኀሳብ የመኪና ሠሌዳ ዋጋ አስመልክቶ አሁንም ጉ
#ነፃ_ሃሳብ አዲሱን የመኪና ታርጋ ዋጋን በተመለከተ ========================== 📣አዲሱን የመኪና ሰሌዳ ዋጋ በመቃወም ያቀረቡት አማራጭ ኀሳብ የመኪና ሠሌዳ ዋጋ አስመልክቶ አሁንም ጉዳዩ ትኩረት ይሻል፡፡ የ40 ሚሊዮን ብር ቅንጡ መኪና 200ሺ አሮጌ መኪና እኩል ወይም ደግሞ ከዚያ በታች ዋጋ ላላቸው መኪኖች ታርጋ መለጠፊያ መጠየቅ በምንም ዓይነት ተገቢ አይደለም፡፡ ልክ አይደለም ብሎ ማለፍ ብቻ ተገቢ ስላልሆነ፤ አማራጭ ማቅረብ ያስፈልጋል፡፡ ታርጋ ማምረቻ ዋጋ ወይም ሌላ በቂ ማስከፈያ ጉዳይ ካለ፣ ገንዘቡን በዚህ መንገድ መስብስብ ይቻላል፡፡ የሥም ዝውውር ማስከፈያ ዋጋ በመቶኛ ክፍያ በመቶኛ በብር 40,000,000.00 0.002 80,000.00 10,000,000.00 0.002 20,000.00 5,000,000.00 0.002 10,000.00 2,000,000.00 0.002 4,000.00 1,000,000.00 0.002 2,000.00 500,000.00 0.002 1,000.00 (ግርማ ሰይፉ) #ምንከማን #minkeman #Addisabab #Ethiopia #Quality #Marketing #PMOfficeEthiopia #Ethiopia #addisababa #minstryoftransportethiopia Telegram: t.me/minkeman Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61550090741996&mibextid=ZbWKwL Tiktok: tiktok.com/@minkemand
265
7
#ምንዛሪ አንድ የአሜሪካ ዶላር አማካይ ዋጋ 158 ብር ሆኖ ተመዘገበ። ========================== የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው ልዩ የውጭ ምንዛሬ
#ምንዛሪ አንድ የአሜሪካ ዶላር አማካይ ዋጋ 158 ብር ሆኖ ተመዘገበ። ========================== የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው ልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ 100 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የመደበ ቢሆንም በጨረታው ላይ የተሳተፉት የፋይናንስ ተቋማት ለመግዛት የጠየቁት አጠቃላይ የገንዘብ መጠን ማዕከላዊ ባንኩ ካቀረበው በሁለት እጥፍ በላይ በመብለጥ 236.30 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ደርሷል። በተካሄደው በዚህ ጨረታ፣ አንድ የአሜሪካ ዶላር አማካይ ዋጋው 158 ብር ሆኖ ተመዝግቧል። በዚህ ልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ላይ 16 የሀገር ውስጥ የንግድ ባንኮች የተሳተፉ ቢሆንም፣ ካለው የተገደበ አቅርቦት እና ከፍተኛ ፍላጎት የተነሳ የምንዛሬ ድልድሉን ማግኘት የቻሉት 8 ባንኮች ብቻ መሆናቸውን ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል። #ምንከማን #minkemman #Bank #Exchange #forexexchange #USD #pound #NationalBankOfEthiopia #commercialbankofethiopia #Berhanbank Telegram : t.me/minkeman Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61550090741996&mibextid=ZbWKwL Tiktok: tiktok.com/@minkemand
284
8
ኢ.ቴ.ባ የጥራት ስራ አመራር ምስክር ወረቀት አገኘ ========================== የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለስልጣን የሚያከናውናቸውን የቴክኖሎጂ ቁጥጥር ስራዎች አለምዓቀፍ ስታንዳርዶችን የ
ኢ.ቴ.ባ የጥራት ስራ አመራር ምስክር ወረቀት አገኘ ========================== የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለስልጣን የሚያከናውናቸውን የቴክኖሎጂ ቁጥጥር ስራዎች አለምዓቀፍ ስታንዳርዶችን የተከተሉ እንዲሆኑ የጥራት ስራ አመራር መርሆዎችን ለመተግበር ተከታታይ ጥረቶችን ሲያደርግ ቆይቶ ሰኔ 9/2018 በ #ISO 9001:2015 የምስክር ወረቀት አገኘ፡፡ በዚህ እንቅስቃሴ ውስጥ ባለስልጣኑ የጥራት ስራ አመራር ማስተግበሪያ ዋና ዋና ሰነዶች ከሆኑት ውስጥ የጥራት ማኑዋል፣ ዓላማ፣ ፖሊሲዎች፣ ፕሮሲጀሮች አና ልዩ ልዩ ቅጾች ማዘጋጀቱ ተገልጿል፡፡ በምስክር ወረቀት አሰጣጥ ስነ-ስርዓቱ ወቅት የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሰለሞን ጌታቸው(ዶ/ር)፣ ይህን የምስክር ወረቀት ለማግኘት ብዙ ውጣ ውረድ የነበረባቸው ስራዎች መከናወናቸውን ጠቆሙው በዚህ ሂደት ውስጥ ተዋንውያን የነበሩ አመራሮች፣ የጥራት ስራ አመራር የውስጥ ኦዲት ኮሚቴ አባላትና መላው ሰራተኛ ለነበራቸው አስተዋጽኦ በማመስገን የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ በዕለቱ የምስክር ወረቀት አሰጣጥ ስነስርዓት ላይ በክብር እንግድነት የተገኙናት የኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር መዓዛ አበራ፣ ለተመዘገበው ስኬት እንኳን ደስ አላችሁ በማለት ቀጣይ የጥራት ስራ አመራር ስራዎችን በውጤት ለማጀብ ጠንክሮ መስራት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። #ምንከማን #minkeman #Addisabab #Ethiopia #Quality #Marketing #ETA #ECAS Telegram: t.me/minkeman Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61550090741996&mibextid=ZbWKwL Tiktok: tiktok.com/@minkemand
291
9
የምግብ ስርዓት እና ስርዓተ-ምግብ ረቂቅ አዋጅ ላይ ይፋዊ የሕዝብ ውይይት ተካሄደ። ========================== የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የምግብ ስር
የምግብ ስርዓት እና ስርዓተ-ምግብ ረቂቅ አዋጅ ላይ ይፋዊ የሕዝብ ውይይት ተካሄደ። ========================== የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የምግብ ስርዓት እና ስርዓተ-ምግብ ረቂቅ አዋጅ ላይ በትላንት ዕለት ይፋዊ የሕዝብ ውይይት መድረክ አካሒዷል፡፡ ረቂቅ አዋጁ ሀገራዊ የምግብ ስርዓት እና ስርዓተ-ምግብን ለማሻሻል ወሳኝ መሰረት የሚጥል መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወርቅ ሰሙ ማሞ ገለጸዋል፡፡ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ የአዋጁን አስፈላጊነት በተመለከተ ባቀረቡት ገለጻ፤ የምግብ ስርዓት እና ስርዓተ-ምግብ የምግብን ከእርሻ እስከ ጉርሻ ድረስ ያለውን አጠቃላይ ሰንሰለት የሚያመላክት ነው ብለዋል። ረቂቅ አዋጁ ዜጎች በልዩ ልዩ ንጥረ ነገሮች የበለጸገ ምግብ እንዲያገኙ በማስቻል ጤናማ እና አምራች ትውልድ ለመገንባት ወሳኝ ሚና እንደሚያበረክት አመላክተዋል፡፡ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን እንደ መነሻ በመውሰድ የተዘጋጀው ይህ አዋጅ፥ ዘርፉ በሀገር አቀፍ ደረጃ በሕግ እንዲመራ ከማስቻሉም በላይ የተቋማትን ቅንጅታዊ ሥራ ይበልጥ እንደሚያጠናክር ገልጸዋል፡፡ በመድረኩ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ተወካይ ገነት ስዩም፤ የነገ ሀገር ተረካቢ ጤናማ ትውልድ ለማፍራት ረቂቅ አዋጁ ወሳኝ እና አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የምግብ ስርዓት እና ስርዓተ ምግብ ሳይንስ ተባባሪ ፕሮፌሰር አሻግረው ዘውዱ (ዶር) በበኩላቸው፤ የሀገርን ብልጽግና ለማረጋገጥ የምግብ ስርዓት እና ስርዓተ-ምግብ በህግ እንዲመራ ማድረግ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። #minkeman #Quality #Marketing Tiktok: tiktok.com/@minkemand
304
10
#እንዲያውቁት #ነዳጅ የሚገኝባቸው ማደያዎች ================== የሰኔ 9 ማክሰኞ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ #ነዳጅ_ማደያ አገልግሎት የሚሰጡ እና በማደያዎቹ በመሰራጨት ላይ ያለው የተሽከ+2
#እንዲያውቁት #ነዳጅ የሚገኝባቸው ማደያዎች ================== የሰኔ 9 ማክሰኞ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ #ነዳጅ_ማደያ አገልግሎት የሚሰጡ እና በማደያዎቹ በመሰራጨት ላይ ያለው የተሽከርካሪዎች #ናፍጣ እና #ቤንዚን አቅርቦት መጠን መረጃ፤ #ምንከማን #minkeman #addisababa #Ethiopia #Oil #gasstation #HormuzStrait #usa #iran Telegram: t.me/minkeman Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61550090741996&mibextid=ZbWKwL Tiktok: tiktok.com/@minkemand
318
11
በያዝነው የክረምት ወቅት 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ታቅዷል። ========================== ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በይፋ
በያዝነው የክረምት ወቅት 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ታቅዷል። ========================== ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በይፋ ሲያስጀምሩ ባስተላለፉት መልዕክት፣ በያዝነው የክረምት ወቅት 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ትልቅ ግብ መቀመጡን አስታወቁ። መላው የኅብረተሰብ ክፍል የተጀመረውን አገራዊ ንቅናቄ በመቀላቀል ለመጪው ትውልድ የሚተርፍ የአረንጓዴ ዐሻራቸውን እንዲያሳርፉ ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥሪ አቅርበዋል። #ምንከማን #minkeman #Addisabab #Ethiopia #Quality #Marketing #GreenLegacy Telegram: t.me/minkeman Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61550090741996&mibextid=ZbWKwL Tiktok: tiktok.com/@minkemand
307
12
#ምንዛሪ በቴክኒክ ችግር ተሰርዞ የነበረው የ100 ሚሊዮን ዶላር ልዩ ጨረታ ነገ ይካሄዳል። ========================== የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባልታሰቡ የቴክኒክ ችግሮች ምክንያት መ
#ምንዛሪ በቴክኒክ ችግር ተሰርዞ የነበረው የ100 ሚሊዮን ዶላር ልዩ ጨረታ ነገ ይካሄዳል። ========================== የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባልታሰቡ የቴክኒክ ችግሮች ምክንያት መሰረዙን ያስታወቀውን ልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ፣ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም በድጋሚ እንደሚያካሂድ አስታውቋል። ለዚህ ጨረታ የቀረበው የገንዘብ መጠን 100 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ሲሆን፣ ፍላጎት ያላቸው የሀገሪቱ የንግድ ባንኮች በተቀመጠው ዝርዝር መመሪያ መሠረት ዝግጅት በማድረግ በጨረታው ላይ መሳተፍ እንደሚችሉ ተገልጿል። #ምንከማን #minkemman #Bank #Exchange #forexexchange #USD #pound #NationalBankOfEthiopia #commercialbankofethiopia #Berhanbank Telegram : t.me/minkeman Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61550090741996&mibextid=ZbWKwL Tiktok: tiktok.com/@minkemand
312
13
#ነፃ_ሃሳብ የፓርላማ ውሎ የምግብና ሥርዓተ-ምግብ አዋጅ የሕዝብ መድረክ ========================= ዛሬ በምግብና ሥርዓተ-ምግብ አዋጅ ላይ በተዘጋጀ የሕዝብ ማዳመጫ መድረክ ለመሳተፍ እ
#ነፃ_ሃሳብ የፓርላማ ውሎ የምግብና ሥርዓተ-ምግብ አዋጅ የሕዝብ መድረክ ========================= ዛሬ በምግብና ሥርዓተ-ምግብ አዋጅ ላይ በተዘጋጀ የሕዝብ ማዳመጫ መድረክ ለመሳተፍ እድል አግኝቼ ነበር። ይህም በእንደዚህ ዓይነት የሕግ ማዘጋጃ ሂደት ውስጥ የተሳተፍኩበት የመጀመሪያ ልምዴ ነበር። ከዚህ ተሞክሮ የተማርኩት አንዱ ነገር የሕግ ማዘጋጃ ሂደታችን በመርህ ደረጃ የተደራጀ፣ ግልጽ እና አሳታፊ መሆኑን ነው። የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ሐሳባቸውንና ሙያዊ አስተያየታቸውን እንዲያቀርቡ በቂ ዕድል ይሰጣል። ችግሩ ብዙ ጊዜ በሥርዓቱ ወይም በመመሪያዎቹ ላይ ሳይሆን በአፈጻጸም ውስንነት፣ በክትትል እጥረት፣ በአቅም ማነስ ወይም በጥቅም ግጭት ምክንያት ሊፈጠር በሚችል መዛባት ላይ እንደሚሆን ተገንዝቤያለሁ። በመድረኩ ላይ ሙያዊ ምክረ ሐሳቦቼን በግልጽነት እና ያለምንም እንቅፋት ማቅረብ ችያለሁ። ይህም በሀገራችን የፖሊሲና የሕግ ማዘጋጃ ሂደቶች ውስጥ ሙያተኞች፣ ተመራማሪዎች፣ የአካዳሚ ተቋማት፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች እና የግሉ ዘርፍ ተዋናዮች ከመነሻው ጀምሮ እስከ መጨረሻው ድረስ በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸው እምነቴን አጠናክሮልኛል። ⚖️ሕጎችና ፖሊሲዎች በሳይንሳዊ ማስረጃ፣ በተግባራዊ ልምድ እና በሰፊ ተሳትፎ ሲደገፉ ይበልጥ ጠንካራና ውጤታማ ይሆናሉ። በእነዚህ ሂደቶች መሳተፍ መብት ብቻ ሳይሆን ለተሻለ፣ ለጤናማ እና ለምግብ ዋስትና የተረጋገጠች ኢትዮጵያ የምናበረክተው ኃላፊነትም ነው። ስለዚህ ሁሉንም ሙያተኞችና ተቋማት እንዲህ ያሉ የሕዝብ ውይይትና ምክክር መድረኮችን በንቃት እንዲከታተሉና ድምፃቸውን እንዲያሰሙ አበረታታለሁ። (ዶ/ር አሻግሬ ዘውዱ) #minkeman #Addisabab #Ethiopia #Quality #Marketing Tiktok: tiktok.com/@minkemand
325
14
የምግብና አልኮል ያልሆኑ መጠጦች ዋጋ ግሽበት 14.6% ጨመረ። ========================== የ2018 ዓ.ም የግንቦት ወር አጠቃላይ #የዋጋ_ግሽበት መጠን 13.4 በመቶ ሆኖ መመዝገቡን
የምግብና አልኮል ያልሆኑ መጠጦች ዋጋ ግሽበት 14.6% ጨመረ። ========================== የ2018 ዓ.ም የግንቦት ወር አጠቃላይ #የዋጋ_ግሽበት መጠን 13.4 በመቶ ሆኖ መመዝገቡን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አስታውቋል። ይህም በሚያዝያ ወር 2018 ዓ.ም ከነበረው 11.7 በመቶ ጋር ሲነፃፀር የ1.7 በመቶ ከፍተኛ ጭማሪ ያሳየ ሲሆን፣ ባለፉት ጥቂት ወራት በሀገሪቱ እየታየ ያለዉ የዋጋ ንረት በግንቦት ወር ላይም በስፋት የተስተዋለ ሲሆን በዋናነት ደግሞ በምግብ ሸቀጦች ላይ የታየዉ ጭማሪ መሆኑን የተቋሙ ሪፖርት ያሳያል። በወሩ የምግብና አልኮል ያልሆኑ መጠጦች ዋጋ ግሽበት 14.6 በመቶ የጨመረ ሲሆን፣ ለዚህም ዋነኛ መንስኤ የሆነው በዕለት ተዕለት የህዝብ ፍጆታ ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ ያላቸው እንደ አትክልት፣ ስጋ፣ የወተት ተዋፅኦዎች፣ እንቁላል፣ ፍራፍሬ፣ የምግብ ዘይትና ስኳር የመሳሰሉት መሰረታዊ የምግብ ሸቀጦች ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመራቸው እንደሆነ መረጃው ያስረዳል። በሌላ በኩል ምግብ ነክ ያልሆኑ የዋጋ ግሽበት መጠን በግንቦት ወር 11.1 በመቶ የደረሰ ሲሆን፣ በዚህ ዘርፍ ስር የሚገኙ ልዩ ልዩ የአገልግሎትና የዕቃዎች ክፍሎችም ከፍተኛ ጭማሪ አሳይተዋል። በዚህም መሠረት ሌሎች እቃዎችና አገልግሎቶች 17.9 በመቶ፣ አልኮል መጠጦችና ትምባሆ 14.6 በመቶ፣ ትራንሰፖርት 12.1 በመቶ፣ ምግብ ቤቶችና ሆቴሎች 10.5 በመቶ እንዲሁም ኮሙዩኒኬሽን 9.1 በመቶ ሆነው መመዝገባቸው ተመልክቷል። #ምንከማን #minkeman #Addisabab #Ethiopia #Quality #Marketing #inflation Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61550090741996&mibextid=ZbWKwL Tiktok: tiktok.com/@minkemand
320
15
#እንዲያውቁት #ነዳጅ የሚገኝባቸው ማደያዎች ================== የሰኔ 8 ሰኞ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ #ነዳጅ_ማደያ አገልግሎት የሚሰጡ እና በማደያዎቹ በመሰራጨት ላይ ያለው የተሽከርካ+2
#እንዲያውቁት #ነዳጅ የሚገኝባቸው ማደያዎች ================== የሰኔ 8 ሰኞ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ #ነዳጅ_ማደያ አገልግሎት የሚሰጡ እና በማደያዎቹ በመሰራጨት ላይ ያለው የተሽከርካሪዎች #ናፍጣ እና #ቤንዚን አቅርቦት መጠን መረጃ፤ #ምንከማን #minkeman #addisababa #Ethiopia #Oil #gasstation #HormuzStrait #usa #iran Telegram: t.me/minkeman Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61550090741996&mibextid=ZbWKwL Tiktok: tiktok.com/@minkemand
327
16
#የአዘጋጅ_መልዕክት ወተት ለጤና፣ ለምግብ ደህንነት እና ለዘላቂ ልማት ========================== አለም አቀፍ የወተት ቀን ወተት እና የወተት ተዋጽኦዎች በሰው ጤና፣ በምግብ ደህንነት፣ በኢኮኖሚ ዕድገት እና በዘላቂ ልማት ላይ ያላቸውን አስፈላጊ ሚና ለማስገንዘብ የሚከበር ዓለም አቀፍ ቀን ነው። ይህ ቀን በ2001 ዓ.ም. በየተባበሩት መንግስታት የምግብና ግብርና ድርጅት (FAO) ተጀምሮ በዓለም ዙሪያ በመንግስታት፣ በግል ዘርፍ ተቋማት፣ በአምራቾች ማህበራት፣ በምርምር ተቋማት እና በሸማቾች ተሳትፎ በሰፊው ይከበራል። #ወተት ለብዙ ሺህ ዓመታት የሰው ልጅ የምግብ ስርዓት ዋና አካል ሆኖ ቆይቷል። ዛሬም ቢሆን በብዙ አገሮች የቤተሰብ ዕለታዊ ምግብ አስፈላጊ ክፍል ሲሆን፣ ለሰውነት እድገትና ጤንነት የሚያስፈልጉ ንጥረ-ምግቦችን በቀላሉ ለማግኘት ያስችላል። በፕሮቲን፣ በካልሲየም፣ በፎስፈረስ፣ በፖታስየም፣ በቫይታሚን B12 እና በሌሎች ጠቃሚ ንጥረ-ምግቦች የበለጸገ በመሆኑ ለአጥንት ጥንካሬ፣ ለጡንቻ እድገት፣ ለአካል እንቅስቃሴ እና ለአጠቃላይ ጤና ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረክታል። 🥛ወተት እና የሰው ጤና 👂የተመጣጠነ ምግብ ጤናማ ሕይወት መሠረት ነው። በተለይም ለሕፃናትና ወጣቶች የአጥንትና የጥርስ እድገት ካልሲየምን በበቂ መጠን ማግኘት አስፈላጊ ሲሆን፣ ወተት ይህንን ፍላጎት ለማሟላት ከሚረዱ ዋና ምግቦች አንዱ ነው። 👂በወተት ውስጥ የሚገኘው ፕሮቲን ለጡንቻ እድገትና ጥገና አስፈላጊ ሲሆን፣ ቫይታሚኖችና ማዕድናት ደግሞ የሰውነትን ተፈጥሯዊ የመከላከል አቅም ለማጠናከር ይረዳሉ። 👂ለእርጉዝ እናቶች፣ ለአጥቢ እናቶች፣ ለአዛውንቶች እና ከፍተኛ የአካል እንቅስቃሴ ለሚያደርጉ ሰዎችም ወተት እና የወተት ተዋጽኦዎች ጠቃሚ የንጥረ-ምግብ ምንጮች ናቸው። ስለዚህ ወተት በጤናማ አመጋገብ ውስጥ ጠቃሚ ቦታ ያለው ምግብ ነው። 🥛ወተት እና ምግብ ደህንነት 🌏ዓለም በምግብ እጥረት፣ በየአየር ንብረት ለውጥ፣ በሕዝብ ቁጥር መጨመር እና በኢኮኖሚ ችግሮች ምክንያት ከፍተኛ ፈተናዎችን እየተጋፈጠች ባለችበት ወቅት፣ ወተት እና የወተት ምርቶች ለምግብ ደህንነት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረክታሉ። 🌍የወተት ምርት በተለይ በገጠር አካባቢዎች ለቤተሰቦች ተከታታይ የምግብ እና የገቢ ምንጭ በመሆን ሕይወታቸውን ለማሻሻል ያግዛል። በብዙ አገሮች በአነስተኛ እርሻ ላይ የተመሰረቱ የወተት አምራቾች ለአካባቢያቸው የምግብ አቅርቦት ሥርዓት ዋና ድጋፍ ናቸው። ይህም የወተት ዘርፍ በምግብ ዋስትና ረገድ ያለውን ጠቀሜታ ያሳያል። 🍶የወተት ዘርፍ እና ኢኮኖሚያዊ እድገት ⚙️የወተት ኢንዱስትሪ ከእርሻ ምርት እስከ ማቀነባበር፣ ማጓጓዝ፣ ግብይት እና ስርጭት ድረስ ሰፊ የእሴት ሰንሰለት ያለው ዘርፍ ነው። ይህ ሰንሰለት ለሚሊዮኖች ሰዎች የሥራ ዕድልና የገቢ ምንጭ ይፈጥራል። ⚙️በኢትዮጵያም የወተት ዘርፍ በግብርናው ውስጥ ጠቃሚ ሚና ያለው ሲሆን፣ ለከተማና ለገጠር ኢኮኖሚ እድገት የሚያበረክተው አስተዋፅኦ ከፍተኛ ነው። ⚙️የወተት ምርትን ማሳደግ፣ የምርት ጥራትን ማሻሻል እና የገበያ ተደራሽነትን ማጠናከር በሀገሪቱ የምግብ ደህንነትና የኢኮኖሚ ልማት ውስጥ የላቀ ድርሻ ሊኖረው ይችላል። 🔬የጥራት እና የደህንነት ጉዳይ የወተት ምርቶች ከጤና ጋር በቀጥታ የተያያዙ በመሆናቸው ጥራታቸውንና ደህንነታቸውን ማረጋገጥ እጅግ አስፈላጊ ነው። ከምርት ጀምሮ እስከ ተጠቃሚው ድረስ ያሉ ሂደቶች የተቀመጡ የጥራት እና የደህንነት መስፈርቶችን ማሟላት ይገባቸዋል። ይህም ሸማቾች ደህንነታቸው የተጠበቀ እና ጥራቱ የተረጋገጠ ምርት እንዲያገኙ ያስችላል። የጥራት መሠረተ ልማት ተቋማት፣ የቁጥጥር አካላት፣ አምራቾች እና ሸማቾች በጋራ በመስራት የወተት ምርቶች የጥራት ደረጃ እንዲጠበቅ እና የምግብ ደህንነት እንዲረጋገጥ የራሳቸውን ኃላፊነት መወጣት ይኖርባቸዋል። 📝ማጠቃለያ አለም አቀፍ የወተት ቀን ወተት በጤና፣ በምግብ ደህንነት፣ በኢኮኖሚ ዕድገት እና በዘላቂ ልማት ላይ ያለውን ከፍተኛ አስተዋፅኦ የምናስታውስበት እና የምናከብርበት ወሳኝ አጋጣሚ ነው። 🥛የወተት ዘርፍን ማጠናከር፣ የምርት ጥራትን ማሻሻል፣ የምግብ ደህንነትን ማረጋገጥ እና የአምራቾችን አቅም ማሳደግ ጤናማ ማህበረሰብ እና ዘላቂ ኢኮኖሚ ለመገንባት አስፈላጊ ናቸው። 💫"ወተት የጤና ምንጭ፣ የምግብ ዋስትና መሠረት እና የዘላቂ ልማት አንዱ ምሶሶ ነዉ!"💫 #ምንከማን #minkeman #Addisabab #Ethiopia #Quality #Marketing #Milk Telegram: t.me/minkeman Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61550090741996&mibextid=ZbWKwL Tiktok: tiktok.com/@minkemand
325
17
#መረጃ አለም አቀፍ የአክሪዲቴሽን ቀን ሲታሰብ... ============================ #ምንከማን #minkeman #Addisabab #Ethiopia #Quality #Marketing #WHO Telegram: t.me/minkeman Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61550090741996&mibextid=ZbWKwL Tiktok: tiktok.com/@minkemand
342
18
#ዘገባ የሳምንቱ አንኳር ዘገባዎች ================ #News #NewsUpdate #Ethiopia #addisababa #quality #marketingtips #minkeman #ምንከማን #ዜና #
#ዘገባ የሳምንቱ አንኳር ዘገባዎች ================ #News #NewsUpdate #Ethiopia #addisababa #quality #marketingtips #minkeman #ምንከማን #ዜና #ወቅታዊ Telegram : t.me/minkeman Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61550090741996&mibextid=ZbWKwL Tiktok: tiktok.com/@minkemand
357
19
አከራይ #ዋጋ_ጨምር ማለት አይችልም፤ ዋጋ መጨመር የሚችለው መንግሥት ነው። ============ ሰኔ 30 የሚያበቃውን የቤት ክራይ ውል ተንተርሶ አከራዮች በተከራዮች ላይ፦ 💸ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ እ
አከራይ #ዋጋ_ጨምር ማለት አይችልም፤ ዋጋ መጨመር የሚችለው መንግሥት ነው። ============ ሰኔ 30 የሚያበቃውን የቤት ክራይ ውል ተንተርሶ አከራዮች በተከራዮች ላይ፦ 💸ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ እንደሚያደርጉ፣ 🏢ቤቱን እፈልገዋለሁ ውጡ፣ 🏢ቤቱ ተሽጧል ውጡ በማለት ጫና እያሳደሩ መሆኑ ተገልጿል። ከቤት ኪራይ ጭማሪ ጋር በተያያዘ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ መቅደስ፣ ተከራዮች በህግ የተሰጣቸው መብታቸውን በደምብ መጠቀም እንደሚጠበቅባቸው በማስገንዘብ አከራዮችም መብትና ግዴታቸውን በአግባቡ መጠቀም ይኖርባቸዋል ብለዋል። 📝ወደ 500 ሺህ የሚጠጉ የኪራይ ቤቶችን በመመዝገብ የት ክ/ከተማ፣ የት ወረዳ፣ የትኛው የቤት ቁጥር፣ ባለስንት መኝታ ቤት፣ በስንት ብር ተከራየ፣ ማነውስ የተከራየው የሚለው ዳታ አለ። የቢሮ ኃላፊዋ፣ በአመት አንድ ጊዜ ሰኔ 30 ላይ በሚመጣው የዋጋ ጥናት መሰረት ዋጋ መጨመር የሚችለው መንግሥት ነው፤ አከራዩ 'ዋጋ ጨምር' ማለት አይችልም በማለት በምሳሌ ሲያስረዱ፦ አንድ ቤት 1 ሺህ ብር ተከራይቶ ቢሆን 1,100 ብር ማድረግ የሚችለው መንግሥት ነው። የማርኬት አሰስመንት ሰርቶ በምን ያህል መጠን ዋጋ ከፍ እንዳለ አስልቶ የሚጨምረው መንግሥት ነው በማለት ገልጸዋል። አክለውም ተከራዮችም መብታቸውን መጠቀም አለባቸው። አከራይ 'ዋጋ ጨምር' ስላለው ብቻ ዋጋ መጨመር የለበትም። ውላቸው እኛ ጋር አለ። ውላቸው የሚያበቃው ከሰኔ 30 በኋላ ነው። ውላቸው ውስጥ ሆነው ዋጋ መጨመር ስለማይጠበቅባቸው እንዲህ አይነት ችግር ሲያጋጥም በቅርባቸው ወረዳ አለ ስራ አስፈጻሚ የሚመራው፣ ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ አለ፣ ወረዳው ካልፈታ ክ/ከተማ ይፈታል፣ ቢሮ እኛም ጋር አለ። እነዚህ ቦታዎች ላይ እየመጣ ቅሬታውን ማቅረብ ይችላል። #minkeman #Quality #Marketing #AMN
459
20
ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች ተያዙ። ========================== የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረገው ክት+2
ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች ተያዙ። ========================== የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረገው ክትትል 969.4 ሚሊዮን ብር የገቢ የኮንትሮባንድ እቃዎች እና 20.5 ሚሊዮን ብር የወጭ፤ በድምሩ 989.99 ሚሊዮን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች በተለያዩ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ተይዘዋል፡፡ በቁጥጥር ስር ከዋሉት የኮንትሮባንድ እቃዎች መካከል፦ 🔐አዳዲስና ልባሽ ጨርቆች፣ 🔐ኤሌክትሮኒክስ፣ 🔐የግንባታ እቃዎች፣ 🔐ቡና፣ 🔐ጥራጥሬ፣ 🔐የተሽከርካሪ መለዋወጫ፣ 🔐የመዋቢያ እቃዎች፣ 🔐ጫት፣ 🔐አደንዛዥ እጾች፣ 🔐መድኃኒት፣ 🔐ማዕድናት፣ 🔐የቁም እንስሳት እና 🔐የውጭ ሀገር ገንዘቦች ይገኙበታል፡፡ በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ የገቢ እና የወጭ ኮንትሮባንድን በመቆጣጠር አዋሽ፣ ጅግጅጋ እና ሞያሌ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ቀዳሚውን ስፍራ ሲይዙ በቅደም ተከተላቸውም 675 ሚሊዮን፣ 102 ሚሊዮን እና 78 ሚሊዮን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎችን መያዝ ችለዋል፡፡ የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹ በጉምሩክ ኮሚሽን ሰራተኞች፣ በፌደራል ፖሊስ፣ በክልል ፖሊስ አባላት እና ህብረተሰቡ ባደረጉት የጋራ ጥረት በፍተሻ፣ በጥቆማ እና በበረራ የተያዙ ሲሆን የኮንትሮባንድ እቃዎቹን ሲያዘዋውሩ የተገኙ 16 ተጠርጣሪዎች እና 21 ተሽከርካሪዎችም በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ (የገቢዎች ሚኒስቴር) #ምንከማን #minkeman #Addisabab #Ethiopia #Quality #Marketing Telegram: t.me/minkeman Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61550090741996&mibextid=ZbWKwL Tiktok: tiktok.com/@minkemand
480