Abdulkerim Hussein Channel
Open in Telegram
قال تعالى«مَنۡ عَمِلَ صَٰلِحٗا مِّن ذَكَرٍ أَوۡ أُنثَىٰ وَهُوَ مُؤۡمِنٞ فَلَنُحۡيِيَنَّهُۥ حَيَوٰةٗ طَيِّبَةٗۖ»(النحل :٩٧.) የላቀው አላህ አለ፦ «ከወንድም ሆነ ከሴት እርሱ አማኝ ሆኖ በጎን የሰራ በእርግጥም ጥሩ የሆነ ኑሮን እናኖረዋለን (አን_ነሕል ፡97) ይቀላቀሉ፦ t.me/Abu_suleyman_dera
Show more2 065
Subscribers
-124 hours
-127 days
-5530 days
Posts Archive
ደግ አንደበተ ርቱዑ ሼይኽ አዚዝ ቢን ፈርሃን አል-ዐነዚ አላህ ይጠብቃቸውና «ቢዩቱን ሙጥመኢንናህ» (የተረጋጉ ቤቶች) በተሰኘው ማራኪ ፕሮግራማቸው አማካኝነት የልባችንን እይታ የኑሯችንን ሁኔታ በጣፋጭ አንደበት በጥልቅ አይታ መቃኘታቸውን ቀጥለዋል።
«እረፍትን (ስኪናን) አታዘግዩ» በሚል ርዕስ ባቀረቡት ሦስተኛው ትምህርታቸው ውስጥ ከተናገሩት ምክር መካከል ይህ ላካፍላችሁ «ልጄ እህቴ ሆይ! ቤቶች የሚገነቡት በይስሙላና በውጫዊ ገፅታ ሳይሆን በተረጋጋ መንፈስና በሰኪናህ እንደሆነ አውቂ! ቤቶች በሀብት ብዛት ሳይሆን በኢማን በረካ ይፀናሉ።
ስለዚህ አንቺ ልትፈልጊው የሚገባው ትልቁ ነገር የበዛ ሀብት ያለውን ሰው ሳይሆን፣ አላህን አብልጦ የሚፈራውን ሰው ነው! አንድ ወጣት ሊፈልገው የሚገባው ትልቁ ነገር ውብ ፊትን ሳይሆን፣ ውብ ልብን ነው! እንዲሁም ቤተሰብ በአጠቃላይ ለልጃቸው ሊመርጡ የሚገባው ከአጪዎች መካከል እጅግ ሀብታሙን ሳይሆን፣ አደራ ጠባቂውንና አላህን ፈሪውን ነው...»
አላህ ይጠብቃቸው፤ መልካም ምንዳን ይክፈላቸው፤ በእውቀታቸውና በሥራቸውም በረካ ያድርግላቸው...
ሰ*ለ*ፍ*ያ!
~
*ሰ*ለ*ፍ*ያ* የዚህን ድንቅና ግዙፍ ስም እውነተኛ ትርጉም፣ ገዝፎ የተሸከመውን ታሪካዊ ክብደትና የተከበረ ቦታ በትክክል ለመረዳት፣ ስሙን ብቻ ማንበብ በቂ አይደለም። ይህን ስም ለመረዳት ከጀርባው የተዘረጋውን የዘመናት ታሪክ፣ በዚያ ጎዳና ላይ የተከፈለውን የእውቀትና የደም ዋጋ፣ ከተዛቡ እምነቶችና ከቢድዓ ጋር የተደረገውን የረጅም ዘመን ተጋድሎ ማስተዋል ያስፈልጋል።
ይህ ስም በሆነ ቀን የተሰበሰቡ ሰዎች የተሰጠ የቡድን መጠሪያ ስም አይደለም! እንዲሁም ለአንድ ሰው፣ ለአንድ ሸይኽ ወይም ለአንድ ድርጅት የሚያገለግል የግል መለያ አይደለም። ከዚያ የበለጠ ሰፊና ጥልቅ ትርጉም ይዟል። የቀደምት ሰለፎች የእምነትና የመረጃ መንገድ እንዳይደለዝ፣ እንዳይበረዝና ከትውልድ ወደ ትውልድ በንጽሕና እንዲደርስ የተደረገውን ትልቅ ትግል የሚወክል ስም ነው።
የእስልምናን መሠረታዊ እምነት ከግል አስተሳሰብ፣ ከፍልስፍናዊ ማምታቻና ከተዛቡ ትርጓሜዎች ለመጠበቅ፤ ቁርአንና ሐዲስን እንደመሠረታዊ መረጃ ለመያዝ፤ የቀደምት ሰለፎችን መንገድ ለመጠበቅ የተደረገው የዘመናት ገድል በዚህ ስም ውስጥ ይንጸባረቃል።
ከጥንቱ የኸዋሪጆች ፊትና ጀምሮ፣ በየዘመኑ በተለያዩ መልክ የተነሱ የጥመትና የቢድዓ አስተሳሰቦች ሲያቆጠቁጡ፣ በሐቅ መረጃ ቀንድ ቀንዳቸውን እያለ ልክ ሲያስገባቸው፣ የተዛቡ እምነቶች በማስረጃ ሲመለሱ፣ እና የእስልምና አቂዳ ከመደበላለቅ ሲጠበቅ የመጣውን ረጅም ተጋድሎ ስትመለከት፣ የዚህ ስም ክብደት ይበልጥ ይገለጥልሃል።
ስለዚህ ይህንን ስም አደራህን....!አደራህንን....! አደራህን...! ከአንድ ሰው ጋር ብቻ አታስተሳስረው፤ ከአንድ ሸይኽ ጋር ብቻ አትገድበው፤ ለአንድ ቡድንም የግል ንብረት አታድርገው። የስሙን ታሪክና ክብደት ሳታውቅ ለግለሰብ ማንነት መለያ ማድረግ፣ ስሙን ከትልቁ ትርጉሙ ማሳነስ ነው።
ይህ ስም ከግለሰቦች የሚበልጥ፣ ከቡድኖች የሚሰፋ፣ ከዘመናት የሚሻገር ትርጉም የያዘ ስም ነው።
🖊 Abdulkerim Husen
"ራፊዷ በሙስሊሙ ላይ ያደረሰውን ግፍ እየተበቀልን ነው። ለሶሃቦች ከምንም በላይ ለሙእሚኖች እናት ለሆነችው አኢሻ ንፅህና ለነብዩ ክብር ሲባል እየተጋደልን ነው።"*[ አንድ ሰለፍይ ወታደር ከየመን]
ጀሰዳችን ሀበሻ ቀልባችን ቀይ ባህሩን ተሻግሮ የመን ወንዝ ተራሮቾ መሃል ከትሞ ነው ያለው!
አላህ ሆይ! የመንን ኢማኗን እና ሂክማዋን መልስላት! ያረብ..! ዲንኑን ያዋረደ የነብዩን ክብር ያጎደፈን ሶሃቦቹን የጠላን ውርደት ሽንፈትን አከናንበው ያረብ!
ከሺአ ጋር የሚደረግ ትግል ለእስልምና የሚደረግ ትግል ነው። ለተጣሰው #የአላህ እና #የመልእክተኛው ሀቅ ሲባል የሚደረግ ትግል! ለበረዙት #ቁርአን ለተሳለቁበት #ሃዲስ ጥብቅና! #ለሙእሚን እናቶች #ለነቢ ባለቤቶች ክብር እና ንፅህና የሚደረግ ውግያ ነው! ክብር ደረጃቸው ለተጣሰው ተንቀው ለተዋረዱ #ሶሃቦች ክብር እና ልቅና ሲባል የሚደረግ ትግል ነው። ለዚህ ሲባል እንኳን በባዶ እግር በእፉቅቅ ይኬዳል! አላህ ለሰለፍዮች ድልን ያጎናፅፍ!
#የመንን_በሰለፍዮች_ክንድ_አላህ_እንደሚያፀዳት_አልጠራጠረም!
የሰይድ ቁጥብ ኪታቦችን ለማንበብ እንመክር ዘንዳ ኣሊም ሁኖ ከመፅሃፍቱ ቁም ነገር ይገኛል ብለን አናስብም። ኢማም ሁኖ ከጥልቅ ምርምሮቹ እንጠቀማለን አንልም! ሰይድ ቁጥብ አንድ ተራ የስነ-ፅሁፍ ሰው ደራሲ ነው። [የሆኑ ሸይኽ]
﴿وَالْمُؤْمِنُونَ وَالْمُؤْمِنَاتُ بَعْضُهُمْ أَوْلِيَاءُ بَعْضٍ يَأْمُرُونَ بِالْمَعْرُوفِ وَيَنْهَوْنَ عَنِ الْمُنْكَرِ وَيُقِيمُونَ الصَّلَاةَ وَيُؤْتُونَ الزَّكَاةَ وَيُطِيعُونَ اللَّهَ وَرَسُولَهُ أُولَئِكَ سَيَرْحَمُهُمُ اللَّهُ إِنَّ اللَّهَ عَزِيزٌ حَكِيمٌ﴾
አዲስ ሙሓደራ ርዕስ፦ አላህን ከማመፅ መጠንቀቅ!
🏙️በከለላ ከተማ መስጂደ ረውዷ
🎙በወንድም ጀማል ሰዒድ ሐፊዞሁሏህ
የቴሌግራም ቻናል፦
¤t.me/kelelaqiratcenter
¤t.me/kelelaqiratcenter
የቴሌግራም ጉርፕ፦
¤t.me/yeselefyadaewakelela
¤t.me/yeselefyadaewakelela
﴿رَبَّنَا لاَ تُؤَاخِذْنَا إِن نَّسِينَا أَوْ أَخْطَأْنَا رَبَّنَا وَلاَ تَحْمِلْ عَلَيْنَا إِصْرًا كَمَا حَمَلْتَهُ عَلَى الَّذِينَ مِن قَبْلِنَا رَبَّنَا وَلاَ تُحَمِّلْنَا مَا لاَ طَاقَةَ لَنَا بِهِ وَاعْفُ عَنَّا وَاغْفِرْ لَنَا وَارْحَمْنَا أَنتَ مَوْلانَا﴾
¤t.me/Abu_suleyman_dera
ዛሬ ካነበብኩት!
~~~
የግብፁ ታዋቂ ታሪክ ጸሐፊ እና ተመራማሪ አል-ጀበርቲ رحمه الله እንደገለፁት ናፖሊዮን ቦናፓርት ግብፅን በ1798 ዓ.ም. በወረረበት ጊዜ፣ ሱፍያዎችና የመውሊድ በዓላትን የሚያዘጋጁ ሰዎች የመውሊድ እንቅስቃሴያቸውን ቀንሰው ነበር። በዚህም ጊዜ ናፖሊዮን የጦር አዛዡን በማስጠራት፦ “ድሮ እንደምታደርጉት እንደ ልማዳችሁ ለምን አሁንስ አታከብሩትም?” ብለህ ጠይቅልኝ ይለዋል። የጦር ሰራዊት አዛዡም ሸይኽ አል-በክሪን አግኝቶ ስለሁኔታው እንዲያስረዱት ይጠይቃቸዋል።
ሸይኽ አል-በክሪ "የነበረው የእንቅስቃሴ ሁኔታ በመቆሙ፣ ሥራዎች በመስተጓጎላቸውና ወጪ ለማውጣት ገንዘብ ባለመኖሩ ምክንያት የመውሊድ በአል ላይ የሚደረገው ተሳትፎ መቀነሱን በማዘን ገለፁለት።
አዛዡም፦ “የመውሊድ በአል የግድ መከናወን እንዳለበት እና ወራሪው ቡድንም እርዳታ እንደሚያደርግላቸው በማስረዳት መውሊዱን ለማክበር እንዲጠቀሙበት 300 የፈረንሳይ ገንዘብ እንዲሰጣቸው አዘዘ።
ከዚያም የተለያዩ ገመዶችንና መብራቶችን በየ መንገዱ እና በየ አደባባዩ ላይ ሰቀሉ፤ ፈረንሳዮችም ባእሉን በደማቅ ሁኔታ ለማክበር ከእነርሱ ጋር ተሰበሰቡ። ከበሮዎቻቸውን በመደለቅ፣ መድፍም በመተኮስ ፤ እንደ ሮኬት ያሉ ሰማይ ደርሰው በውብ ቀለማት የሚፈነዱ ነገሮችም በማስወንጨፍ ባእሉን ድል ባለ መልኩ አከበሩ።
ግን ናፖሊዮንና ወታደሮቹ ከዚህ ሁሉ ፌሽታ በስተጀርባ ያላቸው ዓላማ ምን ነበር?
አል-ጀበርቲ ራሱ መልሱን ይሰጠናል። እንዲህ ይላል፦
“ፈረንሳዮቹም ይህንን ለሰዎች (በነፃነት እንዲያከብሩ) የፈቀዱበት፤ ዋና አላማ በዚህ ውስጥ ሰዎች ከሸሪዓ ሕግጋቶች አፈንግጠው ሲወጡ፣ ልቅ በሆነ መልኩ ሴቶችና ወንዶች በአንድ ላይ ሲሰሰሰቡ ፣ የነፍሲያ ፍላጎታቸውንም ሲከተሉ፣ ለአላህ ትዕዛዝ ተገዢ ከመሆን ይልቅ መረን በለቀቀ መዝናናት ላይ ተጠምደው እና የተከለከሉ ነገሮችን በመዳፈር ከዲናቸው የመዘናጋትን ሁኔታ ስላዩበት ነው።” ይሉናል!
የግብፁ ታሪክ ጸሐፊ እና ተመራማሪ አል-ጀበርቲ፣ ዓጃኢቡል-ኣሣር ፊት-ተራጂም ወል-አኽባር፣ 2/201 በሚለው እና መዝሀሩት-ተቅዲስ ቢዘዋሊ ደውለቲል-ፈረንሲስ፣ ገጽ 47 በሚለው ኪታብ ላይ እንደተገለፀው!
﴿إِنَّ رَبَّكُمُ اللَّهُ الَّذِي خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ فِي سِتَّةِ أَيَّامٍ ثُمَّ اسْتَوَىٰ عَلَى الْعَرْشِ يُغْشِي اللَّيْلَ النَّهَارَ يَطْلُبُهُ حَثِيثًا وَالشَّمْسَ وَالْقَمَرَ وَالنُّجُومَ مُسَخَّرَاتٍ بِأَمْرِهِ ۗ أَلَا لَهُ الْخَلْقُ وَالْأَمْرُ ۗ﴾
¤t.me/Abu_suleyman_dera
﴿إِلَّا الْمُصَلِّينَ * الَّذِينَ هُمْ عَلَىٰ صَلَاتِهِمْ دَائِمُونَ﴾🤍.
﴿وَإِنْ لَمْ تَغْفِرْ لَنَا وَتَرْحَمْنَا لَنَكُونَنَّ مِنَ الْخَاسِرِينَ﴾
ባትምረን፣ ባታዝንልንም በእርግጥም ከከሳሪዎች እንሆናለን። ያረብ እኛ ደካሞች ነን ከእዝነትህ አታርቀን
¤t.me/Abu_suleyman_dera
﴿وَمَا تَوْفِيقِي إِلاَّ بِاللَّهِ عَلَيْهِ تَوَكَّلْتُ وَإِلَيْهِ أُنِيبُ﴾.
መልካምን መገጠሜም በአላህ እንጂ ሌላ አይደለም በሱ ላይ ተመካሁ መመለሻየም ወደ አላህ ነው።
የቴሌግራም ቻናል፦
¤t.me/Abu_suleyman_dera
﴿فَتَوَكَّلۡ عَلَى ٱللَّهِۚ إِنَّ ٱللَّهَ یُحِبُّ ٱلۡمُتَوَكِّلِینَ﴾
በአላህ ላይ ተመካ! አላህ በሱ የሚመኩትን ይወዳል።
የቴሌግራም ቻናል፦
¤t.me/Abu_suleyman_dera
