en
Feedback
قناة ابن عبد الله الأرغوبي

قناة ابن عبد الله الأرغوبي

Open in Telegram

ይህ የሙሀመድ ኢብን ዐብዲላህ አል አርጎባ ቻናል ነው የዑለማዎች ፈታዋ:ሙሀደራ ዱሩሶች የሚለቀቅበት ነው

Show more
426
Subscribers
No data24 hours
-17 days
-330 days
Posts Archive
Part 44 ( 6 ) ማግባትን ለማሳወቅ ሲባል ሴቶች ድቢ መምታት ማግባቱ እንዲታወቅ እና ግልፅ እንዲወጣ ሴቶች ድቢ መምታት ይወደድላቸዋል። ነገር ግን በዘመናዊ እና በባህላዊ የሙዚቃ መሳሪያ እንዲሁም ተስረቅራቂ በሆነ ድምፅ መታጀብ የለበትም። ሴቶች ኒካሁን የተመለከተ ግጥሞችን ወንዶች ሳይሰሟቸው ቢገጥሙ ችግር የለውም። ለዚህም ማስረጃው የአላህ መልክተኛ ﷺ እንዲህ ይላሉ፦ { فصل ما بين الحلال والحرام الدف والصوت في النكاح } الترمذي النكاح (1088) ، النسائي النكاح (3369) ، ابن ماجه النكاح (1896) . رواه الخمسة إلا أبا داود ، وحسنه الترمذي . “በሐላል እና በሐራም መካከል የሚለየው ድቢ መምታትና የሰርግ ግጥሞችን መግጠም ነው” ይላሉ። (አቡ ዳውድ ሲቀር አምስቶች ዘግበውታል፤ቲርሚዚይ ሶሂህ ብለውታል) ኢማሙ አሸውካኒ “ነይሉል አውጧር” በሚባለው ኪታባቸው ጥራዝ 6 ገፅ 200 ላይ እንዲህ ይላሉ፦ “በሰርግ ጊዜ ድቢ መምታትና የተወሰኑ ቃላቶችን እንደ “አተይናኩም፣ አተይናኩም” (መጣናችሁ፣ መጣናችሁ) እና የመሳሰሉትን ማለት የሚቻል መሆኑን ሐዲሱ ያመለክታል። ነገር ግን ወደ መጥፎ የሚያመሩ ግጥሞችን እንደ ውበትን የሚገልፁ አይነት ግጥሞችን ማለት እና አላህን በማመፅ አስካሪ መጠጦችን መጥመቅ በማንኛውም ጊዜ እንደሚከለከለው በሰርግም ጊዜ ክልክል ናቸው። እንደዚሁም ሌሎችን የሙዚቃ መሳሪያ (ከድቢ ውጭ)መጠቀም ክልክል ነው።” ሙስሊም እህቴ ሆይ! ማግባትን ምክንያት በማድረግ ጌጣጌጦችን እና የቡቲክ ልብሶችን በመግዛት አባካኝ አትሁኝ። ይህ አላህ እንደማይወደው እና እንደሚጠላው የገለፀው ማባከንነው። አላህ እንዲህ ይላል፦ ﴿ وَلَا تُسْرِفُوا ۚ إِنَّهُ لَا يُحِبُّ الْمُسْرِفِينَ ﴾ [ سورة الأنعام: 141] “አታባክኑም። እርሱ (አላህ) አባካኞችን አይወድምና።” (አል አንዓም፡ 141) መፎካከርን በመተው በአግባቡ እንድትሆኚ አደራ እልሻለሁ። 📚✍ከተንቢሀት ዓላ አህካሚ ተኸተሱ ቢልሙእሚናት ከተሰኘው ከሸይኽ ሳሊህ አልፈውዛን ሀፊዘሁላህ ሪሳላህ የተወሰደ። https://t.me/ebinabdillahargobi https://t.me/abuhubeyib_mainchannel @ebniabdillah

فليس بمسلم من صرف شيئا من خصائص الربوبية أو الإلهية لغير الله تعالى...
فليس بمسلم من صرف شيئا من خصائص الربوبية أو الإلهية لغير الله تعالى...

ወዓለይኩሙስ ሰላም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ። አዎ፣ ነገር ግን በተወሰኑ ሁኔታዎች ብቻ። አንዲት ሴት ወልይ (አባት፣ አያት፣ ወንድም ወዘተ) ካላት፣ መጀመሪያ የኒካህ ሀላፊነት የወልዩ ነው። ነገር ግን
ወዓለይኩሙስ ሰላም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ። አዎ፣ ነገር ግን በተወሰኑ ሁኔታዎች ብቻ። አንዲት ሴት ወልይ (አባት፣ አያት፣ ወንድም ወዘተ) ካላት፣ መጀመሪያ የኒካህ ሀላፊነት የወልዩ ነው። ነገር ግን ወልዩ፦ ብቁና ዲን ያለውን ጠያቂ ያለ ሸሪዓዊ ምክንያት ከለከላት (ዐድል/العضل)፣ ወይም ጠፍቶ ካልተገኘ፣ ወይም የሀላፊነቱን ስራ ማከናወን ካልቻለ፣ በዚህ ጊዜ ጉዳዩ ወደ ሸሪዓ ፍርድ ቤት (ቃዲ) ይወሰዳል። ቃዲው ጉዳዩን ካረጋገጠ፣ ወልይነቱን ራሱ ይወስዳል ወይም ወደ ቀጣዩ ወልይ ያስተላልፋል። ይህ በነቢዩ ﷺ ሐዲስ ላይ የተመሠረተ ነው፦
«فَالسُّلْطَانُ وَلِيُّ مَنْ لَا وَلِيَّ لَهُ» "ወልይ ለሌለው ሰው ገዢው (ቃዲው) ወልይ ነው።"
ስለዚህ፣ ወልይ እያለ በቀጥታ ወደ ሸሪዓ ፍርድ ቤት ሄዳ ኒካህ ማድረግ አትችልም። መጀመሪያ ወልዩ ያለ ሸሪዓዊ ምክንያት እንደከለከላት ወይም ወልይነቱን ማከናወን እንዳልቻለ መረጋገጥ አለበት። ከዚያ በኋላ ቃዲው በሸሪዓ መሠረት ውሳኔ ይሰጣል። https://t.me/ebinabdillahargobi

Part 43  ( 5  ) 🌺🌺3️⃣ አግብታ የምታውቀዋ ሴት ልጅ፦ እርሷን ያለ ፍቃዷ መዳር አይቻልም፤ፍቃዷም ከልጅ አገረዷ በተቃራኒው በንግግር ነው። ኢብኑ ቁዳማህ “አልሙግኒ” በሚባለው ኪታባቸው ጥራዝ 6 ገፅ 493 ላይ አግብታ የምታውቀው ሴት ፍቃዷ በመናገር ስለመሆኑ በኢስላም ሊቃውንቶች መካከል ልዩነት አናውቅም። ምክንያቱም በልብ ውስጥ ያለውን የሚገልፀው ምላስ ነውና። በሁሉም ጉዳይ ላይ የሚገለፀው በምላስ ነው። ፍቃድም በእሱ(በምላስ) ይገለፃል። ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያህ መጅሙል ፈታዋ በሚባለው ኪታባቸው ጥራዝ 32 ገፅ 39_40 እንዲህ ይላሉ፦ “አንዲት ሴት ካልፈቀደች በስተቀር ማንም ሰው ያለ ፈቃዷ መዳር አይችልም። ማግባትን የምትጠላ ከሆነ አግቢ ተብላ አትገደድም። በእድሜ ትንሽ የሆነችው ሴት ልጅ ግን እርሷ መፍቀድ ስለማትችል አባቷ ፈቃድ ሳይጠይቃት ይድራታል። አግብታ የምታውቀውን ሴት አባቷም ይሁን ሌላ ሰው ያለፈቃዷ ሊድራት እንደማይችል ዑለሞች ይስማማሉ። እንዲሁም በእድሜዋ የበሰለችውን አግብታ የማታውቀውን ሴት ከአባቷ እና ከአያቷ ውጭ ማንም ያለፈቃዷ ሊድራት እንደማይችል እንደዚሁ ዑለሞች ይስማማሉ። አባቷ እና አያቷም ቢሆኑ ማስፈቀድ አለባቸው። ማስፈቀዱ ግዴታ ወይስ የሚወደድ በሚለው ላይ የዑለሞች ልዩነት ያለበት ሲሆን ትክክለኛው ግዴታ ነው የሚለው ነው። የሴት ልጅ ሀላፊዎች(ወልዮች) ለማን እንደሚድሯት እና ቢጤዋ ነው አይደለም ብለው ማየት፣ አላህን መፍራት ይጠበቅባቸዋል። የሚድሯት ለእርሷ ምቾት እንጅ ለእርሱ ምቾት አይደለም። ሴት ልጅን ለመዳር ወልይ (ሀላፊነት) መስፈርት ስለመሆኑ ሴት ልጅ ለእርሷ የሚስማማትን ባል የመምረጥ መብቱን መስጠት ማለት በቤተሰቧ እና በቅርብ ዘመዶቿ ላይ ችግርም ቢፈጠር የፈለገችውን እንድታገባ የሚገታትን ልጓም አውጥቶ እንደፈለገች ትሆናለች ማለት አይደለም። የእርሷ ምርጫ በበላይነት ከሚቆጣጠረው እና ወደ ጥሩ ነገር ከሚመራት ሃላፊዋ(ወልይዋ)ጋር የተቆራኘ ነው። እርሷ እራሷን መዳር አትችልም። ራሷን የምትድር ከሆነ እስሩ ፉርሽ (ብልሹ) ነው። “ሱነኖቹ” መፅሀፎች ውስጥ ዓኢሻ رضي الله عنها ባስተላለፉት ሐዲስ እንዲህ ይላሉ፦ { أيما امرأة نكحت نفسها بغير إذن وليها فنكاحها باطل، فنكاحها باطل، فنكاحها باطل. } الترمذي النكاح (1102) ، أبو داود النكاح (2083) ، ابن ماجه النكاح (1879) ، أحمد (6/66) ، الدارمي النكاح (2184) . “ማንኛዋም ሴት ያለ ሃላፊዋ(ወልይዋ) ፈቃድ እራሷን የምትድር ከሆነ መዳሯ(ኒካኋ) ውድቅ ነው፤መዳሯ ውድቅ ነው፤ መዳሯ ውድቅ ነው ብለዋል።” በአራቱ የ“ሱነን” መፅሐፎች ላይ እንደተዘገበው ደግሞ፦ { لا نكاح إلا بولي } الترمذي النكاح (1101) ، أبو داود النكاح (2085) ، ابن ماجه النكاح (1881) ، أحمد (4/418) ، الدارمي النكاح (2182) . “ያለ ሀላፊ ኒካህ የለም” ይላል። ከሁለቱ ሐዲሶች እና የእነርሱን አይነት ተመሳሳይ ትርጉም ካላቸው ሐዲሶች እንደምንረዳው ያለ ሀላፊ ማግባት እንደማይቻል ነው። አንድ ነገር ክልክል ነው ሲባል ያ ነገር ተቀባይነት አለመኖሩን ያመለክታል። ቲርሚዝይ እንዳሉት ይህ የእውቀት ባለቤቶች ዘንድ የሚሰራበት ነው። ከእነዚህ ውስጥ ኡመር፣ ዐልይ፣ ኢብኑ ዐባስ፣ አቡ ሀረይራ እና ሌሎችም ይገኙበታል። ከሶሃቦች ቀጥለው የመጡት ተከታዮች እንደ ሻፊዒይ፣ አሕመድ እና ኢስሃቅ ያለ ወልይ ኒካህ የለም ማለታቸው ተዘግቧል። ለበለጠ መረጃ “ሙግኒን” ጥራዝ 6 ገፅ 449 ላይ ይመልከቱ። 📚✍ከተንቢሀት ዓላ አህካሚ ተኸተሱ ቢልሙእሚናት ከተሰኘው ከሸይኽ ሳሊህ አልፈውዛን ሀፊዘሁላህ ሪሳላህ የተወሰደ። https://t.me/ebinabdillahargobi https://t.me/abuhubeyib_mainchannel @ebniabdillah

Part 42 ( 4 ) 🌺🌺ሴት ልጅን ለመዳር ሲፈለግ አስተያየቷን መቀበል:— ለመዳር የምትታሰበዋ ሴት ከሶስት ባንዱ ሁኔታ ትሆናለች። 1️⃣ ወይ በእድሜ ትንሽ ልጅ አገረድ 2️⃣ ወይም በእድሜዋ የደረሰች ልጅ አገረድ 3️⃣ ወይም አግብታ የፈታች(ጋለሞታ) ትሆናለች። ለየሁሉም የራሳቸው የሆነ እነርሱን የሚመለከቱ ህጎች አሏቸው። 1️⃣ በእድሜዋ ትንሽ የሆነችዋ ልጅ አገረድ፦ እርሷ መፍቀድ ስለማትችል አባቷ ፍቃድ ሳይጠይቃት የሚድራት መሆኑን በኢስላም ሊቃውንት መካከል ምንም አይነት ልዩነት የለም። ለዚህም ማስረጃው አቡበከር አሲዲቅ رضي الله عنه ልጃቸውን ዓኢሻን رضي الله عنها የስድስት አመት ልጅ ሆና ለአላህ መልክተኛ ﷺ ተዳረች። ዘጠኝ አመት ሲሞላት ወደ ቤታቸው ገባች። (1) (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል) ኢማሙ አሸውካኒ “ነይሉል አውጧር” በሚባለው ኪታባቸው (6ኛው ጥራዝ ከገፅ 128-129) ሲናገሩ፦ “አባት ሴት ልጁን ለአቅመ ሂዋን ከመድረሷ በፊት መዳር እንደሚፈቀድለት በሐዲሱ ውስጥ መረጃ አለ” ይላሉ። እንደዚሁም ሸይኹ በተጨማሪ “በእድሜዋ ትንሽ የሆነችን ሴት በእድሜ የሚበልጣትን (በጣም ትልቅ የሆነን) ወንድ መዳር (ማግባት) የሚቻል መሆኑን ሐዲሱ ያመለክታል። በእርግጥ ቡኻሪም ለዚህ ርእስ ሰጥቶ የእናታችን ዓኢሻንل ሐዲስ አንስቷል። ፈትሁልባሪ (የቡኻሪ ሸረህ) ላይም በዚህ ላይ የኢስላም ሊቃውንቶች ስምምነት ተጠቅሷል” ይላሉ። ኢብኑ ቁዳማ አልሙግኒ በሚባለው ኪታባቸው 6ኛው ጥራዝ ገፅ 487 ላይ “ኢብኑል ሙንዚር እንዳሉት፦ አባት ትንሽ የሆነቺውን ሴት ልጁን በቢጤዋ የሚሰጣት ከሆነ መዳር እንደሚችል ለንግግራቸው ቦታ የሚሰጣቸው የሆኑ የእውቀት ባለቤቶች በዚህ ጉዳይ ላይ የጋራ አቋም አላቸው።” አቡበክር رضي الله عنه ልጃቸውን ዓኢሻን رضي الله عنها በስድስት አመቷ ለነብዩ ﷺ መዳራቸው ሴት ልጅ በልጅነቷ ለትልቅ ሰው መዳሯን የሚቃዎሙ እና በመጥፎ ገፅታ እንድትታይ ለሚያደርጉ ሰዎች እንዲሁም እሱም መጥፎ ነው ብለው ለሚያስቡ ሰዎች በቂ መልስ ነው። ይህንን ያሉበት ምክንያት ባለማወቅ ወይም ስውር አላማ ያላቸው ሰዎች ናቸው እላለሁ። 2️⃣ አግብታ የማታውቅ ለአቅመ ሂዋን የደረሰችን ሴት አባቷ ያለፈቃዷ መዳር የማይቻል ስለመሆኑ አግብታ የማታውቅ ለአቅመ ሄዋን የደረሰችን ሴት አባቷ ያለፈቃዷ መዳር አይችልም። ፍቃዷም ዝምታዋ ነው። ለዚህም ነብዩ ﷺ እንዲህ ይላሉ፦ { ولا تنكح البكر حتى تستأذن، قالوا: يا رسول الله فكيف إذنها ؟ قال: أن تسكت } البخاري النكاح (4843) ، الترمذي النكاح (1107) ، النسائي النكاح (3265) ، أبو داود النكاح (2092) ، ابن ماجه النكاح (1871) ، أحمد (2/434) ، الدارمي النكاح (2186) . متفق عليه . “ልጅ አገረድ ፍቃድ ሳትጠየቅ አትዳርም አንቱ የአላህ መልክተኛ ሆይ ፍቃዷ እንዴት ነው?” ተብሎ ሲጠየቁ “ዝምታዋ ነው” ብለው ተናግረዋል። (የቡኻሪና ሙስሊም የጋራ ዘገባ ነው) ከዑለማዎች አቋም በትክክለኛው መሰረት የሚድራት አባቷ እንኳን ቢሆን ማስፈቀዱ የማይቀር ነው። ኢብኑል ቀይም “አልሀድይ ” በሚባለው ኪታባቸው ጥራዝ 5 ገፅ 96 ላይ ይህ(ለመዳር ፍቃድ መጠየቅ) የአብዛኛዎቹ ቀደምቶች ንግግር ነው። የአቡ ሀኒፋ እና በአንደኛው ሀሳባቸው የአህመድ አካሄድ ነው። ይህም ለአላህ የምንገዛበት ህግ እና ሌላን ህግ የማናስብበት ነው። ይህም ለአላህ መልክተኛ ﷺ ትዕዛዝ እና ክልከላ የሚስማማ ነው።” 📚✍ከተንቢሀት ዓላ አህካሚ ተኸተሱ ቢልሙእሚናት ከተሰኘው ከሸይኽ ሳሊህ አልፈውዛን ሀፊዘሁላህ ሪሳላህ የተወሰደ። https://t.me/ebinabdillahargobi https://t.me/abuhubeyib_mainchannel @ebniabdillah

أفضل الصلوات عند الله صلاة الصبح يوم ...
أفضل الصلوات عند الله صلاة الصبح يوم ...

منصة القرآن على التليقرام ( أشمل مكتبة قرانية صوتية ) Quran Bot on Telegram ( The Most Comprehensive Quranic Libs ) 👇👇👇👇 @IslamicQuranBot

عذاب الذي ينام عن الصلاة المكتوبة
عذاب الذي ينام عن الصلاة المكتوبة

part 41 ( 3 ) 🌺🌺በትዳር እና መጠናቀቁ(ፍች) ሴት ልጅ የምትለይባቸው ህጎች ሸይኻችን ሸይኽ ሙሐመድ አሚን አሽንቂጢይ “አዷኡል-በያን” በሚባለው ኪታባቸው ጥራዝ 3 ገፅ 422 ላይ እንዲህ ይላሉ፦ “እኔንም አንተንም ለሚወደው እና ለሚፈቅደው ይምራን እና እወቅ! ይህቺ የተሳሳተች፣ የከሰረች፣ ለገሀዱ ዓለም እና ለሎጅክ ተቃራኒ የሆነች፣ ከሠማይ ለወረደው ለፈጣሪ“ወህይ” እና አስገኝ ለሆነው አላህ ድንጋጌ ተፃራሪ የሆነች አመለካከት ሴት ልጅን ያለምንም ልዩነት በሁሉም ህግጋት እና መድረክ ከወንድ ጋር አንድ የምታደርግ ናት። ይህቺ አመለካከት የውስጥ አይኑ የታወረበት ሲቀር ከማንም የምትደበቅ አይደለችም። በውስጧ ውድመትን ያዘለች እና ማህበረሰብን ያናወጠች ናት። አሸናፊ እና ሃያል የሆነው አላህ ሴት ልጅን ልዩ በሆነው ባህሪዋ በማህበረሰብ ግንባታ ዘርፎች ላይ ለእርሷ በሚስማማው ተሳታፊ አድርጓታል። ይህም ተስማሚነቷ ለቦታው ሌላ አካል የማይስማማው ነው። እሱም እንደ ማርገዝ፣ መውለድ፣ ማጥባት፣ ልጆችን ማሳደግ፣ ቤትን መንከባከብ እና የቤት ስራን እንደ መቀቀል፣ ማቡካት፣ ማፅዳት እና ሌሎችም ተግባሮች ናቸው። በቤቷ ውስጥ ሆና በመሰተር፣ በጥብቅነት፣ በቁጥብነት የበላይነቷን እና ክብሯ በመጠበቅ ጨዋነትን ተላብሳ ለማህበረሰቡ አገልግሎት በመስጠት የምትቆምበት ወንዶች በመከሰብ ከሚሰጡት አገልግሎት የሚተናነስ አይደለም። ቂሎች እና መህይሞች የሆኑ ካፊሮች እና የእነርሱ ተከታዮች ሴት ልጅ በእርግዝና፣ በማጥባት እና በወሊድ ደም ወቅት እያለች እና በዚህ ወቅት ማንኛውም ሰው እንደሚታዘበው የትኛውንም ስራ ለመስራት የምትቸገርበት ሆና እያለች ልክ እንደ ወንዶች ተመሳሳይ አገልግሎት ከቤቷ ውጭ ወጥታ መስጠት አለባት ሲሉ ይለፍፋሉ። እርሷ እና ባሏ ከቤት የሚወጡ ከሆነ ትናንሽ ልጆችን የሚጠብቃቸው ይጠፋል፣ መጥባት እድሜ ላይ ያሉ ህፃናት ያለ አጥቢ ይቀራሉ፤ ባል ከስራ ሲመለስ የሚበላው እና የሚጠጣው የሚያዘጋጅ ይጠፋል። ሁሉም ነገር ይወድማል። የእርሷን ቦታ የሚተካ ሰው ባል ቢቀጥር ያ የተቀጠረው ሰው እርሷ ሸሽታ ጥላው የወጣችውን ስራ በመስራት እሱም ሌላ ስራ እንዳይሰራ ይሆናል። የዚህም ውጤቱ ወደ እርሷው ተመላሽ ይሆናል። የሴት ልጅ ውጭ መውጣት እና ጊዜዋን ከቤት ውጭ ማሳለፏ የሴት ልጅን ክብር እና ዲን የሚያጠፋ ነው...።” ሙስሊም እህቴ ሆይ! አላህን ፍሪ፤በአላማ አዘል ተጣሪዎች አትሸንገይ (አትሸወጂ)። በዚህ ጥሪ የተታለሉ ሴቶች ምን ያክል ህይወታቸው እንደተበላሸ እና እንደከሸፈባቸው እነርሱ ለአንቺ ጥሩ ምስክር ናቸው። ሙከራ(በሌላዋ ላይ ሲሆን ማየት) ጥሩ ማስረጃ ነው። ሙስሊም እህቴ ሆይ! በወጣትነትሽ እና ተፈላጊ በሆንሽበት ስዓት ለማግባት ፍጠኝ፤ ትምህርትን ለመቀጠል ወይም ለአንድ የስራ ሀላፊነት ብለሽ ትዳርሽን አታዘግይ። የተሳካ የሆነ ትዳር ደስታሽ እና አላማሽ እሱ ነው። የትኛውንም ትምህርት እና ስራ ትዳር ይተካዋል። ነገር ግን የትኛውም ደረጃ ቢደርስ ትምህርት ወይም ስራ ትዳርን አይተካም። በቤትሽ ስራ እና ልጆችሽን በመንከባከብ ቋሚ ሁኝ። ይህ በህይወትሽ ፍሬያማ የሆነው መሰረታዊ ስራሽ ነው። ይህን ስራሽን ምንም የሚመጣጠነው ነገር ስለሌለ በእሱ ቅያሬን አትፈልጊ። ጥሩ የሆነ ባል አያምልጥሽ። የአላህ መልክተኛ ﷺ እንዲህ ይላሉ፦ { إذا جاءكم من ترضون دينه وخلقه فأنكحوه، إلا تفعلوا تكن فتنة في الأرض وفساد } الترمذي النكاح (1085) . رواه الترمذي وحسنه وله شواهد . “ዲኑን እና ፀባዩን የምትወዱት ከመጣችሁ አጋቡት፤ይህን የማትፈፅሙ ከሆነ በምድር ላይ ፈተና እና ትልቅ ውድመት (ጥፋት) ይከሰታል።” (ቲርሚዝይ ዘግበውታል) 📚✍ከተንቢሀት ዓላ አህካሚ ተኸተሱ ቢልሙእሚናት ከተሰኘው ከሸይኽ ሳሊህ አልፈውዛን ሀፊዘሁላህ ሪሳላህ የተወሰደ። https://t.me/ebinabdillahargobi https://t.me/abuhubeyib_mainchannel @ebniabdillah

part 41 ( 3 ) 🌺🌺በትዳር እና መጠናቀቁ(ፍች) ሴት ልጅ የምትለይባቸው ህጎች ሸይኻችን ሸይኽ ሙሐመድ አሚን አሽንቂጢይ “አዷኡል-በያን” በሚባለው ኪታባቸው ጥራዝ 3 ገፅ 422 ላይ እንዲህ ይላሉ፦ “እኔንም አንተንም ለሚወደው እና ለሚፈቅደው ይምራን እና እወቅ! ይህቺ የተሳሳተች፣ የከሰረች፣ ለገሀዱ ዓለም እና ለሎጅክ ተቃራኒ የሆነች፣ ከሠማይ ለወረደው ለፈጣሪ“ወህይ” እና አስገኝ ለሆነው አላህ ድንጋጌ ተፃራሪ የሆነች አመለካከት ሴት ልጅን ያለምንም ልዩነት በሁሉም ህግጋት እና መድረክ ከወንድ ጋር አንድ የምታደርግ ናት። ይህቺ አመለካከት የውስጥ አይኑ የታወረበት ሲቀር ከማንም የምትደበቅ አይደለችም። በውስጧ ውድመትን ያዘለች እና ማህበረሰብን ያናወጠች ናት። አሸናፊ እና ሃያል የሆነው አላህ ሴት ልጅን ልዩ በሆነው ባህሪዋ በማህበረሰብ ግንባታ ዘርፎች ላይ ለእርሷ በሚስማማው ተሳታፊ አድርጓታል። ይህም ተስማሚነቷ ለቦታው ሌላ አካል የማይስማማው ነው። እሱም እንደ ማርገዝ፣ መውለድ፣ ማጥባት፣ ልጆችን ማሳደግ፣ ቤትን መንከባከብ እና የቤት ስራን እንደ መቀቀል፣ ማቡካት፣ ማፅዳት እና ሌሎችም ተግባሮች ናቸው። በቤቷ ውስጥ ሆና በመሰተር፣ በጥብቅነት፣ በቁጥብነት የበላይነቷን እና ክብሯ በመጠበቅ ጨዋነትን ተላብሳ ለማህበረሰቡ አገልግሎት በመስጠት የምትቆምበት ወንዶች በመከሰብ ከሚሰጡት አገልግሎት የሚተናነስ አይደለም። ቂሎች እና መህይሞች የሆኑ ካፊሮች እና የእነርሱ ተከታዮች ሴት ልጅ በእርግዝና፣ በማጥባት እና በወሊድ ደም ወቅት እያለች እና በዚህ ወቅት ማንኛውም ሰው እንደሚታዘበው የትኛውንም ስራ ለመስራት የምትቸገርበት ሆና እያለች ልክ እንደ ወንዶች ተመሳሳይ አገልግሎት ከቤቷ ውጭ ወጥታ መስጠት አለባት ሲሉ ይለፍፋሉ። እርሷ እና ባሏ ከቤት የሚወጡ ከሆነ ትናንሽ ልጆችን የሚጠብቃቸው ይጠፋል፣ መጥባት እድሜ ላይ ያሉ ህፃናት ያለ አጥቢ ይቀራሉ፤ ባል ከስራ ሲመለስ የሚበላው እና የሚጠጣው የሚያዘጋጅ ይጠፋል። ሁሉም ነገር ይወድማል። የእርሷን ቦታ የሚተካ ሰው ባል ቢቀጥር ያ የተቀጠረው ሰው እርሷ ሸሽታ ጥላው የወጣችውን ስራ በመስራት እሱም ሌላ ስራ እንዳይሰራ ይሆናል። የዚህም ውጤቱ ወደ እርሷው ተመላሽ ይሆናል። የሴት ልጅ ውጭ መውጣት እና ጊዜዋን ከቤት ውጭ ማሳለፏ የሴት ልጅን ክብር እና ዲን የሚያጠፋ ነው...።” ሙስሊም እህቴ ሆይ! አላህን ፍሪ፤በአላማ አዘል ተጣሪዎች አትሸንገይ (አትሸወጂ)። በዚህ ጥሪ የተታለሉ ሴቶች ምን ያክል ህይወታቸው እንደተበላሸ እና እንደከሸፈባቸው እነርሱ ለአንቺ ጥሩ ምስክር ናቸው። ሙከራ(በሌላዋ ላይ ሲሆን ማየት) ጥሩ ማስረጃ ነው። ሙስሊም እህቴ ሆይ! በወጣትነትሽ እና ተፈላጊ በሆንሽበት ስዓት ለማግባት ፍጠኝ፤ ትምህርትን ለመቀጠል ወይም ለአንድ የስራ ሀላፊነት ብለሽ ትዳርሽን አታዘግይ። የተሳካ የሆነ ትዳር ደስታሽ እና አላማሽ እሱ ነው። የትኛውንም ትምህርት እና ስራ ትዳር ይተካዋል። ነገር ግን የትኛውም ደረጃ ቢደርስ ትምህርት ወይም ስራ ትዳርን አይተካም። በቤትሽ ስራ እና ልጆችሽን በመንከባከብ ቋሚ ሁኝ። ይህ በህይወትሽ ፍሬያማ የሆነው መሰረታዊ ስራሽ ነው። ይህን ስራሽን ምንም የሚመጣጠነው ነገር ስለሌለ በእሱ ቅያሬን አትፈልጊ። ጥሩ የሆነ ባል አያምልጥሽ። የአላህ መልክተኛ  እንዲህ ይላሉ፦ { إذا جاءكم من ترضون دينه وخلقه فأنكحوه، إلا تفعلوا تكن فتنة في الأرض وفساد } الترمذي النكاح (1085) . رواه الترمذي وحسنه وله شواهد . “ዲኑን እና ፀባዩን የምትወዱት ከመጣችሁ አጋቡት፤ይህን የማትፈፅሙ ከሆነ በምድር ላይ ፈተና እና ትልቅ ውድመት (ጥፋት) ይከሰታል።” (ቲርሚዝይ ዘግበውታል) 📚✍ከተንቢሀት ዓላ አህካሚ ተኸተሱ ቢልሙእሚናት ከተሰኘው ከሸይኽ ሳሊህ አልፈውዛን ሀፊዘሁላህ ሪሳላህ የተወሰደ። https://t.me/ebinabdillahargobi https://t.me/abuhubeyib_mainchannel @ebniabdillah

قَالَ شيخ الإسلام ابن تيمية رحمه الله «وَلَا يَحِلُّ لِلْمُسْلِمِينَ أَنْ يَتَشَبَّهُوا بِهِمْ فِي شَيْءٍ مِمَّا يَخْتَصُّ بِ
قَالَ شيخ الإسلام ابن تيمية رحمه الله  «وَلَا يَحِلُّ لِلْمُسْلِمِينَ أَنْ يَتَشَبَّهُوا بِهِمْ فِي شَيْءٍ مِمَّا يَخْتَصُّ بِأَعْيَادِهِمْ، لَا مِنْ طَعَامٍ، وَلَا لِبَاسٍ، وَلَا إِهْدَاءٍ، وَلَا بَيْعٍ، وَلَا غَيْرِ ذَلِكَ، بَلْ يَكُونُ يَوْمُ عِيدِهِمْ عِنْدَ الْمُسْلِمِينَ كَسَائِرِ الْأَيَّامِ.» اقْتِضَاءُ الصِّرَاطِ الْمُسْتَقِيمِ "ሙስሊሞች ከእነርሱ የበዓላቸው ልዩ ምልክቶች በሆኑ ነገሮች ሁሉ ሊመስሏቸው አይፈቀድላቸውም፤ በምግብ፣ በልብስ፣ በስጦታ፣ በግብይትም ሆነ በሌላ ማንኛውም ነገር። የእነርሱ የበዓል ቀን በሙስሊሞች ዘንድ እንደ ሌሎች ተራ ቀናት መሆን አለበት።"الإمام أحمد بن حنبل رحمه الله سُئِلَ الْإِمَامُ أَحْمَدُ عَنْ شُهُودِ أَعْيَادِ النَّصَارَى، فَقَالَ: «لَا يَشْهَدُ أَعْيَادَهُمْ.» ኢማም አህመድ ኢብን ሐንበል (ረሂመሁላህ) የነሷራዎችን በዓላት ስለመገኘት ሲጠየቁ፦ "በበዓላቸው አይገኝም።" قال الشيخ محمد بن صالح العثيمين  رحمه الله «لَا يَجُوزُ قَبُولُ هَدِيَّةِ الْكَافِرِ الَّتِي أَهْدَاهَا مِنْ أَجْلِ عِيدِهِ؛ لِأَنَّ قَبُولَهَا إِعَانَةٌ لَهُ عَلَى إِظْهَارِ شَعَائِرِ عِيدِهِ.» "ካፊሩ ለበዓሉ ምክንያት የሰጠውን ስጦታ መቀበል አይፈቀድም፤ ምክንያቱም ይህ የበዓሉን ሥርዓት እንዲያሳይ መርዳት ይሆናል።" https://t.me/ebinabdillahargobi

حكم الإنحناء في التحية الرياضية؟
حكم الإنحناء في التحية الرياضية؟

Part 40 ( 2 ) 🌺🌺በትዳር እና መጠናቀቁ(ፍች) ሴት ልጅ የምትለይባቸው ህጎች ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያህ “መጅሙል-ፈታዋ” ኪታባቸው ጥራዝ 32 ገፅ 90 ላይ እንዲህ ይላሉ፦ “አላህ ለሙእሚኖች እንዲያገቡና እንዲፈቱ፣ የተፈታችም ሴት ሌላ ባል አግብታ ከተፈታች በኋላ መልሰው እንዲጋቡ ፈቅዶላቸዋል። ክርስቲያኖች፦በአንዳንድ ህዝቦቻቸው ላይ ማግባትን እርም (የተከለከለ) አድርገዋል፤በአንዳንዶቹ ላይ ደግሞ ማግባት ከፈቀዱላቸው ፍችን እርም ያደርጉባቸዋል። አይሁዶች፦ፍችን ይቀበላሉ። ነገር ግን አንዲት ሴት ከተፈታች በኋላ ሌላ ባል አግብታ ብትፈታ ወደ መጀመያው ባሏ መመለስን ይከለክሏታል። ጠቅለል ባለ መልኩ ክርስቲያኖች ዘንድ ፍች የተከለከለ ሲሆን አይሁዶች ዘንድ ደግሞ ሌላ ባል አግብታ ከተፈታች ወደ መጀመሪያው ባሏ መመለስን ይከለክላሉ። አላህ ለሙእሚኖች ያንንም ይኸንንም( መፍታትንም መመለስንም) ፈቀደላቸው። ኢብኑል ቀይም “አልሀዲ አን-ነበውይ” በሚባለው ኪታባቸው 3ኛው ጥራዝ ገፅ 149 ላይ የትዳር አንዱ አላማ የሆነውን የግንኙነትን ጥቅም ሲገልፁ፡ ግንኙነት ለሶስት መሰረታዊ ነገር የተቀመጠ ነው። ዋና መረታዊ አላማውም እሱ ነው። አንደኛው፦ ትውልድን ማስቀጠል ሲሆን አላህ የሰው ዘር አይነቶች ወደዚህ አለም የሚመጡበትን የወሰነው ጊዜ እስከሚጠናቀቅ ድረስ እንዲቀጥል ማድረግ ነው። ሁለተኛው፦ ፦ ሰውነት ውስጥ ታፍኖ መቆየቱ እና መከማቸቱ የሚያስቸግር የሆነውን ውሃ ማስወገድ ነው። ሶስተኛው፦ ፦ ስሜትን መወጣት፣ እርካታን ማግኘት እና በአላህ ፀጋ መጠቀም ነው። ንግግራቸው ተቋጨ። ትዳር በውስጡ በርካታ ታላላቅ ጥቅሞች ያሉት ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ ዋናው ከዝሙት መጠበቅና ሀራምን ከማየት መገታት ነው። ✔ ከትዳር ጥቅሞች መካከል፦ ልጅን ማግኘት እና ዘር መጠበቅ ነው። ✔ ከትዳር ጥቅሞች መካከል፦ በሁለት ባል እና ሚስቶች መካከል በመልካም መኗኗር እና የነፍስ መረጋጋት ማግኘት ነው። ✔ ከትዳር ጥቅሞች መካከል፦ ሁለት ባል እና ሚስት ጥሩ ቤተሰብ በመገንባት ላይ መረዳዳት ይህን ቤተሰብ መገንባት ማህበረሰብን ለመገንባት አንዷ ጡብ ስለሆነች ነው። ✔ ከትዳር ጥቅሞች መካከል፦ ባል ሚስትን በማስተዳደር እና በመጠበቅ ላይ መቆም እንዲሁም ሚስትም በቤቷ ስራ ላይ በመቆም በህይወቷ ውስጥ ትክክለኛ የሆነውን ሃላፊነት(የቤቷ ስራ) መወጣት ነው። የሴት ልጅ እና የማህበረሰብ ጠላት የሆኑት ሴት ልጅ ከቤት ውጭ በስራ የወንድ አጋር ናት እንደሚሉት አይደለም። ሴት ልጅ ከቤት ውጭ መስራት አለባት በማለት ከቤቷ አስወጧት፤ ከትክክለኛ የስራ ድርሻዋም አስወገዷት፤ የእርሷ ያልሆነን ስራ ለእርሷ በመስጠት የእርሷን ስራ ተገቢ ላልሆነ አካል አሳልፈው ሰጡባት፤ በዚህ ምክንያት የቤተሰብ መዋቅሩ እንከን ገጠመው፤ በባል እና በሚስት መካከል መጥፎ የሆነ ጥርጣሬ ተፈጠረ፤ ይህም ለአብዛኛዎቹ ባሎች እና ሚስቶች መለያየት ምክንያት ወይም በመቃቃር እና በንትርክ እንዲኖሩ ምክንያት ሆኗል።

ወዓለይኩሙስ ሰላም ወረህመቱላሂ ወበረካቱ። አላህ ይባሪክ ፊክ ጥያቄው ጠቃሚ ነው። አዎ፣ ሽርኩል አክባር (الشرك الأكبر) ሰውን ከእስልምና ያወጣል። አላህ እንዲህ ብሏል፦ ﴿لَئِنْ أَشْر
ወዓለይኩሙስ ሰላም ወረህመቱላሂ ወበረካቱ። አላህ ይባሪክ ፊክ ጥያቄው ጠቃሚ ነው። አዎ፣ ሽርኩል አክባር (الشرك الأكبر) ሰውን ከእስልምና ያወጣል። አላህ እንዲህ ብሏል፦
﴿لَئِنْ أَشْرَكْتَ لَيَحْبَطَنَّ عَمَلُكَ وَلَتَكُونَنَّ مِنَ الْخَاسِرِينَ﴾ "ብታጋራ (ሽርክ ብትሠራ) ሥራህ በእርግጥ ይበላሻል፣ ከከሳሪዎችም ትሆናለህ።" (አዝ-ዙመር፥ 65)
አንድ ሰው በሽርኩል አክባር ውስጥ ከነበረ በኋላ በእውነት ወደ አላህ ከተመለሰ፣ ተውባው የሚሟላው፦ ከሽርኩ ፈጽሞ መተው። በሠራው ማፀፀት። ወደዚያ እንዳይመለስ ቆርጦ መወሰን። ወደ እስልምና መመለሱን በሁለቱ ሸሀዳዎች (الشهادتان) ማሳወቅ። ስለዚህ ሽርኩል አክባር ከእስልምና ካወጣው፣ "አስተግፊሩላህ" ብቻ በቂ አይደለም፤ ወደ እስልምና መግባቱን በሸሀዳ ማደስ ያስፈልጋል። ይህንን ብዙ ዑለማዎች ጠቅሰዋል። የሚለውን ይላል፦
أشهد أن لا إله إلا الله، وأشهد أن محمدًا رسول الل
ه . ከዚያም እጅግ ብዙ እስቲግፋርና መልካም ሥራ ያበዛል። አላህ ተውባ ለሚያደርጉ እንዲህ ብ
ሏ ል ፦ ﴿قُلْ يَا عِبَادِيَ الَّذِينَ أَسْرَفُوا عَلَى أَنْفُسِهِمْ لَا تَقْنَطُوا مِنْ رَحْمَةِ اللَّهِ ۚ إِنَّ اللَّهَ يَغْفِرُ الذُّنُوبَ جَمِيعًا﴾ (الزمر:
5 3 ) "በላቸው፦ እናንተ በራሳችሁ ላይ ያሳለፋችሁ ባሮቼ ሆይ፣ ከአላህ ምሕረት ተስፋ አትቁረጡ፤ አላህ ኃጢአቶችን ሁሉ ይምራል።" አላህ በተውሒድ ላይ ያጽናን፣ ከሽርክም በግልጽና በተሰወረ መልኩ ይጠብቀን። አሚን። https://t.me/ebinabdillahargobi

❌❌   نقض شبهة استدل بها المخالفون من كلام الشيخ محمد بن عبد الوهاب رحمه الله ክፍል 5 وقال رحمه الله في نقله عن "ابن تيمية" رحمه الله: እርሱም (አላህ ይዘንለት) ከኢብን ተይሚያ (አላህ ይዘንለት) በጠቀሰው ውስጥ እንዲህ አለ፦ وقال أيضًا في أثناء كلامه على المتكلِّمين ومن شاكلهم، لما ذكر عن أئمتهم شيئًا من أنواع الردة والكفر، وقال رحمه الله: እንዲሁም ሙተከሊሞችንና እነርሱን የሚመስሉትን በሚናገርበት ጊዜ፣ ከመሪዎቻቸው ስለ አንዳንድ የርዳ (ከእስልምና መውጣት) እና የኩፍር አይነቶች ከጠቀሰ በኋላ እንዲህ አለ፦ وهذا إذا كان في المقالات الخفية، فقد يقال: إنه فيها مخطئ ضال، لم تقم عليه الحجة التي يكفر صاحبها، ይህ ግን በተሰወሩ አስተሳሰቦች ውስጥ ከሆነ፣ በዚያ ጉዳይ ተሳስቶና ጠፍቶ ነው፣ ባለቤቱ የሚከፈርበት ሁጃ አልተቋቋመበትም ሊባል ይችላል። لكن ذلك يقع في طوائف منهم في الأمور الظاهرة، التي يعلم المشركون واليهود والنصارى أن محمدًا صلى الله عليه وسلم بعث بها وكفَّر من خالفها، ነገር ግን ይህ ከእነርሱ አንዳንድ ቡድኖች ዘንድ በግልጽ ጉዳዮች ውስጥ ይከሰታል፤ ሙሽሪኮች፣ አይሁዶችና ነሳራዎችም ሙሐመድ ﷺ በእነዚህ እንደተላከና የሚቃወማቸውንም እንደከፈረ ያውቃሉ። مثل أمره بعبادة الله وحده لا شريك له، ونهيه عن عبادة أحد سواه من النبيين والملائكة وغيرهم، فإن هذا أظهر شرائع الإسلام، ለምሳሌ፦ አላህን ብቻውን፣ ተጋሪ ሳይኖረው እንዲመለክ ማዘዙ፣ ከነቢያት፣ ከመላእክትና ከሌሎችም ማንንም ከእርሱ ሌላ እንዳይመለክ መከልከሉ፤ ይህም ከእስልምና ሕግጋት ሁሉ የበለጠ ግልጽ ነው። ثم تجد كثيرًا من رؤوسهم وقعوا في هذه الأنواع، فكانوا مرتدين، وكثير منهم تارة يرتد عن الإسلام ردة صريحة، وتارة يعود إليه مع مرض في قلبه ونفاق، والحكاية عنهم في ذلك مشهورة. **ከዚያም ከመሪዎቻቸው ብዙዎች በእነዚህ ዓይነቶች ውስጥ እንደወደቁ ታገኛለህ፤ ስለዚህ ሙርተዶች ሆነዋል። ከእነርሱም ብዙዎች አንዳንዴ ግልጽ የሆነ ርዳ ይወድቃሉ፤ አንዳንዴም በልባቸው ውስጥ በሽታና ኒፋቅ እያለ ወደ እስልምና ይመለሳሉ፤ ስለዚህ የተነገረው ታሪካቸው ታዋቂ ነው። وقال رحمه الله تعالى في رسالة عامة للمسلمين: እርሱም (አላህ ይዘንለት) ለሙስሊሞች በጻፈው አጠቃላይ መልእክት እንዲህ አለ፦ فإذا عرفت ما قلت لك معرفة قلب، وعرفت الشرك بالله الذي قال الله فيه: ﴿إِنَّ اللَّهَ لَا يَغْفِرُ أَنْ يُشْرَكَ بِهِ وَيَغْفِرُ مَا دُونَ ذَلِكَ لِمَنْ يَشَاءُ﴾ الآية [النساء: 48]، እንግዲህ የነገርኩህን በልብህ የተረዳህ እውቀት ካወቅህ፣ እንዲሁም አላህ ስለ እርሱ፦ ﴿አላህ በእርሱ እንዲጋራበት አይምርም፤ ከዚያ ውጭ ያለውን ግን ለሚፈልገው ይምራል﴾ [አን-ኒሳእ፡ 48] ያለውን በአላህ ላይ ሽርክን ካወቅህ፣ وعرفت دين الله الذي بعث به الرسل من أولهم إلى آخرهم، الذي لا يقبل الله من أحد دينًا سواه، وعرفت ما أصبح غالب الناس فيه من الجهل بهذا، أفادك فائدتين: እንዲሁም ከመጀመሪያዎቹ ነቢያት እስከ መጨረሻቸው ድረስ የተላኩበትን፣ አላህም ከእርሱ ውጭ ከማንም የማይቀበለውን የአላህን ዲን ካወቅህ፣ እንዲሁም ዛሬ አብዛኛው ሰው በዚህ ላይ ባለው ድንቁርና ካወቅህ፣ ሁለት ጥቅሞችን ታገኛለህ። الأولى: الفرح بفضل الله وبرحمته؛ قال الله تعالى: ﴿قُلْ بِفَضْلِ اللَّهِ وَبِرَحْمَتِهِ فَبِذَلِكَ فَلْيَفْرَحُوا هُوَ خَيْرٌ مِمَّا يَجْمَعُونَ﴾ [يونس: 58]. የመጀመሪያው፦ በአላህ ችሮታና በምሕረቱ መደሰት ነው። አላህ ተዓላ እንዲህ ብሏል፦ ﴿በአላህ ችሮታና በምሕረቱ ይደሰቱ፤ ይህ ከሚሰበስቡት ሁሉ የተሻለ ነው﴾ [ዩኑስ፡ 58]። وأفادك أيضًا: الخوف العظيم؛ فإنك إذا عرفت أن الإنسان يكفر بكلمة يخرجها من لسانه، وقد يقولها وهو جاهل فلا يعذر بالجهل، وقد يقولها وهو يظن أنها تقربه إلى الله، ሁለተኛውም፦ ታላቅ ፍርሃትን ያገኛል። ምክንያቱም ሰው ከአንደበቱ በሚያወጣት አንዲት ቃል ሊከፍር እንደሚችል ካወቅህ፣ አንዳንዴም በድንቁርና ሊናገራት ይችላል፣ በድንቁርናውም አይታደግም፤ አንዳንዴም ወደ አላህ ያቀርበኛል ብሎ እያሰበ ሊናገራት ይችላል። خصوصًا إن ألهمك الله ما قص عن قوم موسى مع صلاحهم وعلمهم، أنهم أتوه قائلين: ﴿اجعل لنا إلهًا كما لهم آلهة﴾ [الأعراف: 138]، فحينئذ يعظم خوفك. በተለይም አላህ ስለ ሙሳ ሕዝብ፣ ጻድቃንና ዕውቀት ባለቤቶች ሆነው ሳሉ፦ ﴿እነርሱ አማልክት እንዳሏቸው እኛም አምላክ አድርግልን﴾ [አል-አዕራፍ፡ 138] ብለው የጠየቁትን ካሳወቀህ፣ በዚያን ጊዜ ፍርሃትህ ይበልጣል። ይ               ቀ              ጥ                    ላ                          ል..... https://t.me/ebinabdillahargobi

من موانع تدبر القرآن : الغناء فهو ....
من موانع تدبر القرآن : الغناء فهو ....

Part 39 ( 1 ) 🌺🌺በትዳር እና መጠናቀቁ(ፍች) ሴት ልጅ የምትለይባቸው ህጎች አላህ እንዲህ ይላል፦ ﴿ وَمِنْ آيَاتِهِ أَنْ خَلَقَ لَكُم مِّنْ أَنفُسِكُمْ أَزْوَاجًا لِّتَسْكُنُوا إِلَيْهَا وَجَعَلَ بَيْنَكُم مَّوَدَّةً وَرَحْمَةً ۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَاتٍ لِّقَوْمٍ يَتَفَكَّرُونَ ﴾ [ سورة الروم: 21] “ለእናንተም ከነፍሶቻችሁ (ከጎሶቻችሁ) ሚስቶችን ወደ እነርሱ ትረኩ ዘንድ መፍጠሩ፣ በመካከላችሁም ፍቅርንና እዝነትን ማድረጉ ከአስደናቂ ምልክቶቹ ነው። በዚህ ውስጥ ለሚያስተውሉ ሕዝቦች ተዓምራቶች አልሉ።” (አር-ሩም፡ 21) በሌላም አንቀፅ አላህ እንዲህ ይላል፦ ﴿ وَأَنكِحُوا الْأَيَامَىٰ مِنكُمْ وَالصَّالِحِينَ مِنْ عِبَادِكُمْ وَإِمَائِكُمْ ۚ إِن يَكُونُوا فُقَرَاءَ يُغْنِهِمُ اللَّهُ مِن فَضْلِهِ ۗ وَاللَّهُ وَاسِعٌ عَلِيمٌ ﴾ [ سورة النور: 32] “ከናንተም ትዳር የሌላቸውን አጋቡ። ከወንዶች ባሮቻችሁና ከሴቶች ባሮቻችሁም ለጋብቻ ብቁ የኾኑትን (አጋቡ)። ድኾች ቢኾኑ አላህ ከችሮታው ያከብራቸዋል። አላህም ስጦታው ሰፊ ዐዋቂ ነው።” (አን-ኑር፡ 32) ኢብኑ ከሲር رضي الله عنه እንዲህ ይላል፦ “ይህ በማጋባት ላይትዕዛዝ ነው::እንድያውም አንዳንድ ዑለሞች ይህን ተመርኩዘው ማግባት ትዳርን በሚችል ላይ ሁሉ ግደታ መሆኑን ይጠቅሳሉ:: ለዚህም የነብዩን  ሀዲስ በማስረጃነት ይጠቅሳሉ። ይኸውም፦ { يا معشر الشباب، من استطاع منكم الباءة فليتزوج، فإنه أغض للبصر وأحصن للفرج، ومن لم يستطع فعليه بالصوم، فإنه له وجاء } البخاري النكاح (4778) ، مسلم النكاح (1400) ، الترمذي النكاح (1081) ، النسائي الصيام (2240) ، أبو داود النكاح (2046) ، ابن ماجه النكاح (1845) ، أحمد (1/378) ، الدارمي النكاح (2165) . “እናንተ ወጣቶች ሆይ ከእናንተ ማግባት የቻለ ያግባ፤ ይህ ማግባቱ አይኑን ይሰብርለታል፤ብልቱንም ይጠብቅለታል። ያልቻለ ደግሞ ይፁም፤ መፆሙ ለእርሱ መኮለስ ነው።” ኢብኑ መስዑድን ዋቢ አድርገው ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል። ማግባት ለመክበር ምክንያት እንደሆነ ኢብን ከሲር ይናገራሉ። ለዚህም መረጃው የአላህ ንግግር ነው፦ ﴿ إِن يَكُونُوا فُقَرَاءَ يُغْنِهِمُ اللَّهُ مِن فَضْلِهِ ۗ وَاللَّهُ وَاسِعٌ عَلِيمٌ ﴾ [ سورة النور: 32] “ድኾች ቢኾኑ አላህ ከችሮታው ያከብራቸዋል። አላህም ስጦታው ሰፊ ዐዋቂ ነው።” (አን-ኑር፡ 32) ከአቡበክር አስሲዲቅ رضي الله عنه እንደተወራው እንዲህ ይላሉ፦ “የቀጠራችሁን ክብረት ይሞላላችሁ ዘንድ በማግባት የታዘዛችሁትን ትእዛዝ ፈፅሙ።” አላህ እንዲህ ይላል፦ ﴿ إِن يَكُونُوا فُقَرَاءَ يُغْنِهِمُ اللَّهُ مِن فَضْلِهِ ۗ وَاللَّهُ وَاسِعٌ عَلِيمٌ ﴾ [ سورة النور: 32] “ድኾች ቢኾኑ አላህ ከችሮታው ያከብራቸዋል። አላህም ስጦታው ሰፊ ዐዋቂ ነው።” (አን-ኑር፡ 32) ዐብደላህ ኢብኑ መስዑድ رضي الله عنه ሀብትን በትዳር ላይ ፈልጓት። አላህ እንዲህ ይላል፦ ﴿ إِن يَكُونُوا فُقَرَاءَ يُغْنِهِمُ اللَّهُ مِن فَضْلِهِ ۗ وَاللَّهُ وَاسِعٌ عَلِيمٌ ﴾ [ سورة النور: 32] “ድኾች ቢኾኑ አላህ ከችሮታው ያከብራቸዋል። አላህም ስጦታው ሰፊ ዐዋቂ ነው።” (አን-ኑር፡ 32) ኢቡኑ ጀሪርም ዘግበውታል። በገውይም ከዑመር እንደዚሁ አውርተዋል።” ከኢብኑ ከሲር የተወሰደ...( ተፍሲር ኢብኑ ከሲር 5/ 94-95) 📚✍ከተንቢሀት ዓላ አህካሚ ተኸተሱ ቢልሙእሚናት ከተሰኘው ከሸይኽ ሳሊህ አልፈውዛን ሀፊዘሁላህ ሪሳላህ የተወሰደ። https://t.me/ebinabdillahargobi https://t.me/abuhubeyib_mainchannel @ebniabdillah

تعلن الجامعة الإسلامية بالمدينة المنورة بالتعاون مع وقف خادم الحرمين الشريفين الملك عبد الله بن عبد العزيز لوالديه عن فتح باب
تعلن الجامعة الإسلامية بالمدينة المنورة بالتعاون مع وقف خادم الحرمين الشريفين الملك عبد الله بن عبد العزيز لوالديه عن فتح باب التقديم على برنامج بكالوريوس الشريعة 《عن بعد 》 مع تقديم منح دراسية مجانية للطلاب والطالبات الدوليين المستوفين لشروط القبول وذلك للعام الجامعي 1448 ھ رابط التقديم: https://bit.ly/44ORbA0 للاطلاع على دليل القبول: https://bit.ly/4pFD5KE

❌❌   نقض شبهة استدل بها المخالفون من كلام الشيخ محمد بن عبد الوهاب رحمه الله ክፍል 4 وكذلك إجماع السلف على تكفير غلاة القدَرية وغيرهم، مع عِلمهم وشدة عبادتهم، وكونهم يحسبون أنهم يحسنون صنعًا، ولم يتوقف أحدٌ من السلف في تكفيرهم لأجْل كونهم لم يفهموا. እንዲሁም ሰለፎች ከመጠን በላይ የቀደርን የሚክዱትን (غلاة القدرية) እና ሌሎችንም ካፊሮች መሆናቸውን በአንድ ድምፅ ተስማምተዋል፤ ይህም ምንም እንኳን እውቀት ቢኖራቸው፣ ኢባዳቸው ጠንካራ ቢሆን፣ እነርሱም ራሳቸውን መልካም ሥራ እየሠሩ እንደሆነ ቢያስቡም ነው። እነርሱ ማስረጃውን አልተረዱም በሚል ምክንያት ሰለፎች መካከል ማንም ከእነርሱን ካፊር ብሎ ከመፍረድ አልተቆጠበም። إذا علمتم ذلك، فإن هذا الذي أنتم فيه كفر، الناسُ يعبدون الطواغيت، ويعادون دين الإسلام، فيزعمون أنه ليس ردَّة، لعلهم ما فهموا الحجة، كل هذا بيِّن، وأظهر مما تقدم الذين حرَّقهم عليٌّ، فإنه يشابه هذا. ይህን ካወቃችሁ እንግዲህ፣ እናንተ ያላችሁበት ነገር ኩፍር ነው። ሰዎች ጧጉቶችን ያመልካሉ፣ የኢስላምንም ዲን ይጠላሉ፤ ከዚያም “ይህ ሪዳ (ከእስልምና መውጣት) አይደለም፤ ምናልባት ማስረጃውን አልተረዱም” ይላሉ። ይህ ሁሉ ግልጽ ነው፤ ከዚህ በፊት ዓሊይ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ከአቃጠላቸው ሰዎች ጉዳይ የበለጠ ግልጽ ነው፤ ምክንያቱም ይህ ከዚያ ጋር ይመሳሰላል። وأما إرسال كلام الشافعية وغيرهم، فلا يتصوَّر أن يأتيكم أكثر مما أتاكم، فإن كان معكم بعض الإشكال، فارغبوا إلى الله تعالى أن يزيله عنكم، والسلام. የሻፊዒዮችንና የሌሎችን ንግግር መላካችሁን በተመለከተ፣ ከደረሳችሁ በላይ አዲስ ነገር ይመጣላችኋል ብሎ አይታሰብም። አሁንም የሚያስቸግራችሁ ነገር ካለ፣ አላህን ለምኑት፤ እርሱም ያንን ከእናንተ እንዲያስወግድላችሁ። ሰላም። وقال الشيخ رحمه الله في رسالته إلى أحمد بن عبد الكريم:... وأما عبارة الشيخ التي لبَّسوا بها عليك، فهي أغلظ من هذا كله، ولو نقول بها لكفَّرنا كثيرًا من المشاهير بأعيانهم؛ فإنه صرَّح فيها بأن المعيَّن لا يُكفَّر إلا إذا قامت عليه الحجة، فإذا كان المعيَّن يكفَّر إذا قامت عليه الحجة، فمن المعلوم أن قيامها ليس معناه أن يفهم كلام الله ورسوله مثل فهم أبي بكر رضي الله عنه، بل إذا بلغه كلام الله ورسوله، وخلا من شيء يُعذر به، فهو كافر، كما كان الكفار كلهم تقوم عليهم الحجة بالقرآن. ሸይኹ (አላህ ይዘንላቸው) ወደ አህመድ ቢን ዐብዱልከሪም በጻፉት መልእክትም እንዲህ ብለዋል፦ “እነርሱ ባንተ ላይ ግራ ለማጋባት የተጠቀሙበት የሸይኹ አነጋገር፣ ከዚህ ሁሉ የበለጠ ጠንካራ ነው። እኛም እነርሱ እንደሚሉት ብንል፣ ከታዋቂ ሰዎች ብዙዎቹን በስማቸው ካፊር ብለን እንፈርድ ነበር። ምክንያቱም እርሱ በግልጽ የተወሰነ ሰው ካፊር ተብሎ የሚፈረድበት ማስረጃው በእርሱ ላይ ከተቋቋመ በኋላ ብቻ መሆኑን ገልጿል። ማስረጃው በእርሱ ላይ መቋቋሙ ማለት የአላህንና የመልእክተኛውን ቃል እንደ አቡ በክር (ረዲየላሁ ዐንሁ) መረዳት ማለት እንዳልሆነ ግልጽ ነው፤ ነገር ግን የአላህና የመልእክተኛው ቃል ከደረሰው፣ የሚያስተውልበት ሸርዒ ምክንያትም ከሌለው፣ እርሱ ካፊር ነው፤ ልክ ቁርአን በደረሳቸው ካፊሮች ሁሉ ላይ ማስረጃው እንደተቋቋመው። ይ               ቀ              ጥ                    ላ                          ል..... https://t.me/ebinabdillahargobi

2⃣  الردُّ على مَن يقول: "لا نُكَفِّرُ الجاهلَ حتى تُقامَ عليه الحُجَّةُ".