en
Feedback
Ajeba Emmanuel united church

Ajeba Emmanuel united church

Open in Telegram

እውነት እላችኋለሁ፤ ቃሌን የሚሰማ፣ በላከኝም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ ከሞት ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም።” — ዮሐንስ 5፥24 (አዲሱ መ.ት)

Show more
259
Subscribers
-224 hours
-27 days
-430 days
Posts Archive
‹‹ነገር ግን ከእኔ ጋር የነበረ ቲቶ እንኳ የግሪክ ሰው ሲሆን ይገረዝ ዘንድ ግድ አላሉትም፤›› ገላ 2፡1-3 ድነት የክርስቶስ የመስቀል ላይ ስራ እንጂ በሰው ስራ ላይ የተንጠለጠለ ስጦታ አይደለም ፡፡ አዳኛችን ክብር ይሁንለት ፡፡ አሜን!! ይቀጥላል......

ክፍል አስር የገላቲያ ምዕራፍ ሁለት የመጀመሪያ ክፍል #በከንቱ_እንዳልሮጥ_ሮጬ_እንዳይሆን !! ገላ 2:1-3 አገልጋዮች ቆም ብለው ማስተዋል ያለባቸውን እውነት!! አማኞች ሊረዱት የሚገባው አካሄድ!! ሁሉ ሊያውቀው የሚያስፈልገውን መርህ !! ጳውሎስ በእዚህ ክፍል ጠቆም ያደርጋል ።ለመማር የፈለገ እንግዲህ ሜዳ ይኸውለት ! ‹‹ከዚያ ወዲያ ከአሥራ አራት ዓመት በኋላ ከበርናባስ ጋር ቲቶን ደግሞ ይዤ ወደ ኢየሩሳሌም ሁለተኛ ወጣሁ፤እንደ ተገለጠልኝም ወጣሁ፤ ምናልባትም በከንቱ እንዳልሮጥ ወይም በከንቱ ሮጬ እንዳልሆን በአሕዛብ መካከል የምሰብከውን ወንጌል አስታወቅኋቸው፤ ዋኖች ግን መስለው ለሚታዩ ለብቻቸው አስታወቅኋቸው።ነገር ግን ከእኔ ጋር የነበረ ቲቶ እንኳ የግሪክ ሰው ሲሆን ይገረዝ ዘንድ ግድ አላሉትም፤›› ገላ 2፡1-3 ከእዚህ ቀደም ጳውሎስ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ነበር በምራዕፍ አንድ ላይ ይህንን አሳውቋል ፡፡ አሁን ሁለተኛ ጉዞ ከአስራ አራት አመት በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም ይመለሳል ፡፡ ጳውሎስ ለአገልግሎት የተጠራው በዋናነት ለአሕዛብ በመሆኑ ብዙ ጊዜውን ያሳለፈው በአገልግሎት ከእስራኤል ውጪ ባለ ከተሞች ነበር አልፎ አልፎ ግን ወደ ኢየሩሳሌም ብቅ ይላል ፡፡ ጳውሎስ እንቅስቃሴው ሁሉ የሚያከናውነው ከወንጌል አግልግሎቱ አንጻር በመሆኑ በገላቲያ በተጠቀሱ የኢየሩሳሌም ጉዞዎች ውስጥ ያከናወናቸውን ጉዳዮች በጽሑፍ ያሳውቃል ፡፡ በሁለተኛ ምዕራፍ መግቢያ እንዲህ ነው የሚለው ። ይህ ክፍል በአዲሱ መደበኛ ትርጉም እንዲህ ይነበባል !! ‹‹ከዐሥራ አራት ዓመት በኋላም፣ ዳግመኛ ወደ ኢየሩሳሌም ወጣሁ፤ በዚህ ጊዜ ከበርናባስ ጋር ነበርሁ፤ ቲቶንም ይዤው ሄጄ ነበር። ካገኘሁትም መገለጥ የተነሣ ወደዚያ ሄድሁ፤ በአሕዛብ መካከል የምሰብከውን ወንጌል ለእነርሱም ገለጥሁላቸው። ይሁን እንጂ፣ ምናልባት በከንቱ እየሮጥሁ ወይም ሮጬ እንዳይሆን በመሥጋት፣ ዋነኞች ለሚመስሉት ብቻ በግል ይህን አስታወቅኋቸው። ከእኔ ጋር የነበረው ቲቶ እንኳ የግሪክ ሰው ቢሆንም፣ እንዲገረዝ አልተገደደም ነበር። ›› ገላትያ 2:1-3 በእዚህ ጉዞ ውስጥ በርናባስና ቲቶ አብረውት ነበሩ ፡፡ በርናባስ በሐዋሪያት ስራ መፅሐፍ ውስጥ ከእርሱ ጋር የሚያገለግል እንደነበር የሚታውቅ ሰው ሲሆን ቲቶ ደግሞ ጳውሎስ መልእክት የፃፈለት ፍሬው ነው ፡፡ በእዚህ ክፍል ውስጥ ጳውሎስ ያስቀመጣቸውን ዋና ዋና ነገሮች እንመልከት ፡፡ 1ኛ ካገኘው መገለጥ የተነሳ ነው ጳውሎስ ነው ጳውሎስ ወደ ኢየሩሳሌም የሄደው ፡፡ ለሁሉ ጉዳይ ምሪት ካልተሰጠን ባይባልም ( ከወንበር ለመነሳት ውሃ ለመጠጣት….ሌላም ሌላም ) ነገር ግን በህይወታችን ምሪት የሚያስፈልጋቸው ጉዳዪች አሉ ።በፀሎት በመሆን ቃሉን በማጥናትና በማሰላሰል ምሪትና ከእግዚአብሄር መጠየቅ ያስፈልጋል ወይም እግዚአብሄር ወደ ሕወታችን የሚያመጣውን ምሪት መቀበል ይኖርብናል ፡፡ ጳውሎስም ይሁን የተቀሩት የአዲስ ኪዳን አገልጋዮች ብዙ በምሪት የተንቀሳቀሱባቸው ቦታዎች እና ጉዳዮች ስለ መኖራቸው የአዲስ ኪዳን መፅሐፍት ምስክር ናቸው ፡፡ እኛም በሕይወታችን የእግዚአብሄርን ፊት በመፈለግ ከአምላክ ምሪት መቀበል እጅግ የሚጠቅመን ጉዳይ እንደሆነ አስባለሁ ፡፡ 2ኛ በከንቱ እንዳሮጥ ወይም ሮጬ እንዳይሆን ( በከንቱ እየሮጥኩ ወይም ሮጬ እንዳይሆን አ.መ.ት ) ጳውሎስ ከሚያስገርሙ ባህሪያቱ መካከል አንዱ ይህ ነው ፡፡ ይህም ራሱን ቆም ብሎ ለመፈተሸ እና ለማይት የሚያደርገው ጥረት ነው ፡፡ ብዙ ሰው ካፈርኩ አይመልሰኝ ወይም ራሱን ላለማይት በማሰብ ትክክል ነኝ ብሎ ይገሰግሳል ፡፡ ሩጫው የከንቱ እንዳይሆን ቆም ብሎ ማስብ አይሻም ፡፡ እልህ ከመጠን ሲያልፍ ዋጋ እንደሚያስከፍል አያስብም ፡፡ ሁሉ ነገር በእኛ የተጀመረ የሚመስለን ብዙዎች ነን ፡፡ በእኛም የሚጨረስ የሚመስለን ጥቂቶች አይደለንም ፡፡ነገር ግን እውነታው ይህ ነው በእኛ ተጀምሮ በእኛ የሚያልቅ የክርስትና ጉዞ የለም ፡፡ ጳውሎስ ለወንጌል ያለው ጠንካራ የማይነቃነቅ አቋም እንዳለ ሆኖ የእውቀት ማነስ ሳይኖርበት ለማስመሰልም ሳይሆን በታላቅ ትህትና ለኢየሱስ ሐዋሪያት ለዋነኞቹም የመጣበትን መንገድ እና ትምህርት አስታወቃቸው ፡፡ #የማስተምረው_ይህ_ነው! ጳውሎስ በሚያስተምረው አያፍርም ደሞ ታላላቆችን መስማት መልካም ስለ ሆነ ትምህርቴ ይህ ነው ብሎ ለጰጥሮስ፣ለዮሀንስ ፣ለያህቆብ ዋነኞች የሚባሉት እነዚህ ስለሆኑ አስታወቃቸው ፡፡ ለምን ይህን አደረገ ?;- ሁለት ምክንያቶችን ያስቀምጣል 🔸1ኛ ወደፊትን ታሳቢ አድርጎ፡- በከንቱ እንዳሮጥ ይላል በከንቱ መሮጥ እንዴት ያለ ኪሳራ እንዴት ያለ ከባድ እንዴት ያለ ልብ ሰባሪ ነገር ነው ፡፡ ነጋዴው በንግዱ ከንቱ ሆኖ ሲከስር ተማሪው እንደዛው ሲሆን እንዴት ያለ ከባድ ነገር ነው ፡፡የእግዚአብሄርን መንግስት አገለግላለው ብሎ የተሰማራ አገልጋይስ በዘመኑ መጨረሻ ይህ ሲገጥመው ምን ሊሰማው የሚችል ይመስላቹኃል ? ጳውሎስ ከአስራ ሁለት ሺ ኪሎ ሜትር በላይ ተጉዞ እንዳገለገለ ይነገራል ፡፡ በአይን ህመም ውስጥ እየታገለ አገልግሎ፣ በተለያዩ እስር ቤቶች ተገላቶ ፣ በስንት ግርፊያ እና የድንጋይ መወገር ተሰቃይቶ፣ መርከብ እየተሰበረበት አገልግሎ ፣በሰው ሃገር እየተገላታ ኖሮ ብዙ ሆኖ ያገለገለ ጳውሎስ በከንቱ ሮጦ ቢሆን ምን አይነት ስብራት ይሆን ነበር ? ጳውሎስ ግን በታላቅ ትህትና ለበጉ ሐዋሪያት ስለሚያተምረው ወንጌል አስረዳቸው ለዋኖቹም አስታወቃቸው ፡፡ ለእኛ ይሄ ትልቅ ትምርት ነው ፡፡ እኔ ብቻ አውቃለሁ በበዛበት አለም ከእኛ በእድሜ የገፉትን በእውቀት የተሻሉትን በተለያየ መንገድ ያለፉትን መጠየቅ እጅግ እንድናተርፍ ይረዳናል ፡፡በተለይም አገልጋይ የሚያደርገውን ነገር ሁሉ ሲያደርግ ነገን ታሰቢ በማድረግ መሆን አለበት፡፡ 🔸2ኛ ከኋላ የመጣበትን መንገድ ለመገምገም ጳውሎስ ሁለተኛ ምክንያቱ የመጣበትን መንገድ ዞር ብሎ ለመቃኘት ነው ፡፡ያለፈውን መመለስ ባይቻል እንኳ የወደፊቱን ለማስተካከል እጅግ ይጠቅማል ፡፡ወደ ኃላ ነገሮችን በቅጡ ማውጠንጠን ወደ ፊት በመስፈንጠር ረጅም ሊያስኬድ ይችላል ። ጳውሎስ ወደ ኢየሩሳሌም በመምጣት ይህንን አድሬጓል!!ከእ #ቲቶ_ግሪኩ_ሰው ጳውሎስ ቲቶን ወደ ኢየሩሳሌም ይዞት ሄዶ ነበር ፡፡ቲቶ የግሪክ ሰው ስለሆነ እንደ አይሁድ ልማድ ክርስትና የሚቀጥል ከሆነ ቲቶን ሊገርዙት የግድ ያስፈልጋል ፡፡ ወይም ክርስትና እንደ አይሁድ ልማድ የሙሴን ሕግና የመገረዝ ስርአትን በመፈፀም ድነት ይገኛል የሚል ትምህርት የሚያስተምር ቢሆን ቲቶ አይሁዳዊ ባለመሆኑ ከልጅነቱ የመገረዝን ስነ ስርአትን ስላልፈፀመ አሁን ግድ መፈፀም (መገረዝ) አለበት ።ነገር ግን አንደዛ አልሆነም ፡፡ ለድነት የሙሴን ሕግ እና የግርዘትን ስነ ስርአት መፈፀም ሳይሆን ክርስቶስን ማመን ስለሆነ የሚያስፈልገው ሐዋሪያቱ ከጳውሎስ ጋር በመስማማት ቲቶን ለመግረዝ ግድ አላሉትም ነበር ፡፡

➫ ጌታ ኢየሱስ በአንተ ውብ ፍቅር እንደመነደፍ ያለ ክብር የለኝም 👐🙋 ውድ በጌታ ፍቅር የተወደዳችሁ እህት ወንድሞቼ ፀጋ እና ምህረት ይብዛላችሁ! ➫ዛሬ ኢ-የ-ሱ-ስ በሚል በስሙ ፍቅር መነደፍ ይሁንላችሁ! ➫የምድርን ኮተት በሚያስንቅ ውብ በሆነው በኢ-የ-ሱ-ስ ፍቅር መነካት ይሁንላችሁ 🙌🙌 @AECHB_group መልካም ቀን 💚

በምንም የማትቀልብኝ ስጦታዬ ነህ🙏🙏 ኢ የ ሱ ስ💚

#መዳን! 👇👇👇 ደህንነት በኃጢአት ምክነያት በሰውና በእግዚአብሔር መካከል የተቋረጠው ቤተሰባዊ ህብረት በኢየሱስ ክርስቶስ ሞት እና ትንሳኤ እንደገና መታደሱን የሚያበስር ነው። ድነት የሚገኘው በክርስቶስ ነው እንጂ በሌላ በማንም በምንም የለም። 1.መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና። — ሐዋርያት 4፥12 #መዳን 👉በሰው ጥረት እና መልካም ሥራ የማይገኝ በራሱ በእግዚአብሔር የምሰጥ የእግዚአብሔር ሞጎስ ነው👇 ➫ኤፌሶን 2 ⁸ ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤ ⁹ ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም። እውነት➫ እውነት እላችኋለሁ፥ ቃሌን የሚሰማ የላከኝንም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፥ ከሞትም ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም።” — ዮሐንስ 5፥24 #መዳን 👉ሰው በራሱ ችሎታ ኃይል ሊያድርገው የማይችል የእግዚአብሔር ችሎታ ነው! 👉 ኤፌሶን 1 ⁵ በበጎ ፈቃዱ እንደ ወደደ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ሥራ ለእርሱ ልጆች ልንሆን አስቀድሞ ወሰነን። ⁶ በውድ ልጁም እንዲያው የሰጠን የጸጋው ክብር ይመሰገን ዘንድ ይህን አደረገ። #በደህንነት_ውስጥ_የሚካተት_መሠረታዊ_ነጥቦችን 👇 #እንቀጥላለን... ፀጋው ይብዛላችሁ! ❤ አገልጋይ ታምረት ሳሙኤል❤👇 አገልጋይ ተመስገን አድመሱ ❤👇

👉 #እኛ እና #እርሱ👈 #እውነቱ_ይኸው_ነው👇 #እኛ በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጢአት ያላወቀውን #እርሱን ስለ እኛ ኃጢአት አደረገው። — 2ኛ ቆሮ 5፥21

ክፍል ዘጠኝ ( የምዕራፍ አንድ የመጨረሻ ክፍል) #ጳውሎስ_ድሮ_እና_አሁን ገላ 1፡13-24 ጉባዬው በአንድ ሰው እየተገረመ ነው ፡፡ ደግሞ መልሶ ይህንን ሰው እየፈራ ነው፡፡ የሚያየውን ለማመን የተቸገረ ይመስላል ትላንት ያሳደደውን መልሶ ልክ ነው የሚል ሰው በመካከላቸው ቆሞ በጆሯቸውም እየሰሙት ነው ፡፡ እኔ ነበርኩ ጥፋተኛ ያሳደደኩት ልክ ነው እያለ እየሰበከ ነበር ይህ ሰው አስገራሚው ሰው ጳውሎስ ነው ፡፡መስበኩ ሳያንስ በብዙ ዋጋ መክፈል ይህንን ወንጌል እያስተማረ ይገኛል ፡፡ የአሕዛብ ሐዋርያ የሆነው የቀድሞ አሳዳጅ ጳውሎስ ፡፡ ስለ እራሱ ስለ ድሮ ሕይወቱ እንዲህ ሲል ይመሰክራል፡፡ ገላ 1፡13-14 ፊሊ 3፡ 5-6 🔸ቤተ ክርስቲያንን ያለ ልክ የሚያሳድድ 🔸ለአባቶች ወግ ለመጠን ይልቅ የመሚቀና 🔸በአይሁድ ስርአት ከብዙዎች የሚበልጥ 🔸ክርስትናን ያጠፋ የነበረ ‹‹በአይሁድ ሥርዓት በፊት እንዴት እንደ ኖርሁ ሰምታችኋልና፤ የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ያለ ልክ አሳድድና አጠፋ ነበር፥ለአባቶችም ወግ ከመጠን ይልቅ እየቀናሁ በወገኔ ዘንድ በዘመኔ ካሉት ብዙዎችን በአይሁድ ሥርዓት እበልጥ ነበር።›› በፊሊጲስዮስ መፅሐፍ ላይ ደግሞ እንዲህ ይነግረናል ፊሊ 3፡4-7 ‹‹እኔ ግን በሥጋ ደግሞ የምታመንበት አለኝ። ሌላ ሰው ማንም ቢሆን በሥጋ የሚታመንበት እንዳለው ቢመስለው፥ እኔ እበልጠዋለሁ።በስምንተኛው ቀን የተገረዝሁ፥ ከእስራኤል ትውልድ፥ ከብንያም ወገን፥ ከዕብራውያን ዕብራዊ ነኝ፤ ስለ ሕግ ብትጠይቁ፥ ፈሪሳዊ ነበርሁ፤ስለ ቅንዓት ብትጠይቁ፥ ቤተ ክርስቲያንን አሳዳጅ ነበርሁ፤ በሕግ ስለሚገኝ ጽድቅ ብትጠይቁ፥ ያለ ነቀፋ ነበርሁ።ነገር ግን ለእኔ ረብ የነበረውን ሁሉ ስለ ክርስቶስ እንደ ጉዳት ቈጥሬዋለሁ።›› ጳውሎስ ትለንቱ ይገርማል ያስፈራል እንዴት ሊሆን ቻለ? ያስብላል ፡፡ ነገር ግን እግዚአብሄር ለራሱ እቃ አድርጎ ተጠቀመው ፡፡ በእዚህ ምክንያት የይሁዳ ማህበርተኞች ስለ እርሱ እግዚአብሄርን አመስግነዋል ልክ ናቹ ያስብላል በእውነት ፡፡ ‹‹ስለ እኔም እግዚአብሔርን ያከብሩ ነበር።›› ገላ 1፡24 ጳውሎስ ከተለወጠ በኋላ ገላ 1፡15-24 ይህ ሰው እየተገረመ ስለ ራሱ ይናገራል ። የተነካበትን መነካት እያስታወሰ በምልሰት እንዲህ ይላል ። የሄደበት በማስታወስ ስለ ጉዞውም ይተርካል። ‹‹ነገር ግን በእናቴ ማኅፀን ሳለሁ የለየኝ በጸጋውም የጠራኝ እግዚአብሔር በአሕዛብ መካከል ስለ እርሱ ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ልጁን በእኔ ሁኔታ ሊገልጥ በወደደ ጊዜ፥ ወዲያው ከሥጋና ከደም ጋር አልተማከርሁም፥ ከእኔም በፊት ሐዋርያት ወደ ነበሩት ወደ ኢየሩሳሌም አልወጣሁም፥ ነገር ግን ወደ ዓረብ አገር ሄድሁ እንደ ገናም ወደ ደማስቆ ተመለስሁ።ከዚህ ወዲያ ከሦስት ዓመት በኋላ ኬፋን ልጠይቅ ወደ ኢየሩሳሌም ወጥቼ ከእርሱ ጋር አሥራ አምስት ቀን ሰነበትሁ፤ነገር ግን ከጌታ ወንድም ከያዕቆብ በቀር ከሐዋርያት ሌላ አላየሁም።ስለምፅፍላችሁም ነገር፥ እነሆ፥ በእግዚአብሔር ፊት ሐሰት አልናገርም።ከዚያ ወዲያ ወደ ሶርያና ወደ ኪልቅያ አገር መጣሁ።በክርስቶስም ያሉት የይሁዳ ማኅበሮች ፊቴን አያውቁም ነበር፤ነገር ግን። ቀድሞ እኛን ያሳድድ የነበረ፥ እርሱ በፊት ያጠፋው የነበረውን ሃይማኖት አሁን ይሰብካል ተብሎ ሲነገር ይሰሙ ነበር፤ስለ እኔም እግዚአብሔርን ያከብሩ ነበር።›› የተለወጠው ጳውሎስ 🔸 ወንጌል በየሀገራቱ እየሶረ ያስተምር ነበር !! 🔸ቤተ ክርስቲያናትን ይተክል ነበር!! 🔸ተተኪ ለማፍራት ይታገል ነበር !! 🔸አጋንትና ከህዝብ ላይ ያስወጣ ነበር !! 🔸 ለእውነተኛው የወንጌል አገልግሎት ራሱን የሚሰጥ ነበር !! በገላትያ መፅሐፍ ምዕራፍ አንድ ላይ የመጨረሻ ቃሉ ይህ ነበር። “ስለ እኔም እግዚአብሔርን ያከብሩ ነበር።” — ገላትያ 1፥24 እጅግ ደስ የሚል ቃል ነው ። እግዚአብሔር በእኛ ምክንያት ሲከበር ። ጳውሎስ ለክርስቲያኖች የስደት ምክንያት ነበር አሁን ግን ታሪኩ ተቀይሯል ። ድሮ እንዲያ ነበር አሁን ግን እንዲህ ነው ።የተለወጠ ሰው የተለወጠ ሕይወት ይኖረዋል የተለወጠ ሕይወት ያለው ለእግዚአብሔር መከበር ምክንያት ይሆናል ። ኢየሱስ በምድር ሲያስተምር እንዲህ ብሎ ነበር። “መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።” — ማቴዎስ 5፥16 ጳውሎስ መለወጡ በተግባር ታይቷል የተለወጠ ሕይወቱ ለምስጋና ምክንያት ሆኗል ። እግዚአብሔር በተለወጠ ሕይወት እንድንኖር ፀጋ ይብዛልን አሜን ። ይቀጥላል ....

ጳውሎስ በእዚህ ወንጌል እርግጠኛ ሆኖ እንዲሰብክ ያደረው እውነታ ይህ ነው ፡፡ እኛስ ለእዚህ ወንጌል እርግጠኞች ሆነን በድፍረት መመስከር እንችላለን ? ከሁሉ ርዕሶች በላይ ርዕስ እናደርገዋለን? ልመርቃችሁ እውነተኛው ወንጌል አጥብቃችሁ የምትይዙበት ፀጋ ይጨመርላችሁ ። አሜን ይቀጥላል ... ✍️ Girum Difek

ክፍል ስምንት #መላዕክትም_እኛም_ብንሆን ገላ 1፡8-12 ዘማሪ ሀና ተክሌ ከወዳጆቿ ጋር በመሆን እንዲህ ታዜማለች። ካንተ በፊት የቆሰሉ ብዙ አሉ ለወንጌሉ እንደኔ እና እንዳተ በነፃነት ዘመን ያልተፈጠሩ ... ወንጌል ከአሁኑ በባሰ ዋጋ የሚያስከፍልበት ዘመን ነበር ።አሁንም በአንዳንድ ቦታዎች ላይ ወንጌል ከፍተኛ ዋጋ ይከፈልለታል ይገባዋል !! ይህ የሚመጣው ለወንጌል ካለ እውነተኛ አቋምና ለወንጌል ካለ ትክክለኛ መረዳት ብሎም እርግጠኝነት ነው ። ደፋሩ ጰውሎስ ለእዚህ እውነት እንዴት በልበ ሙሉነት እንደሚናገር ተመልከቱ ‹‹ነገር ግን #እኛ_ብንሆን ወይም #ከሰማይ_መልአክ፥ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ፥ የተረገመ ይሁን።አስቀድመን እንዳልን እንዲሁ አሁን ሁለተኛ እላለሁ፥ ከተቀበላችሁት የተለየውን #ማንም ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን።ሰውን ወይስ እግዚአብሔርን አሁን እሺ አሰኛለሁን? ወይም ሰውን ደስ ላሰኝ እፈልጋለሁን? አሁን ሰውን ደስ ባሰኝ የክርስቶስ ባሪያ ባልሆንሁም።ወንድሞች ሆይ፥ በእኔ የተሰበከ ወንጌል እንደ ሰው እንዳይደለ አስታውቃችኋለሁ፤ኢየሱስ ክርስቶስ ገልጦልኛል እንጂ እኔ ከሰው አልተቀበልሁትም አልተማርሁትምም።›› ጳውሎስ የማይደራደርበት እውነት በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን የሚገኘውን የዘላለም ድነትን ነው ፡፡ ይሄን ለማስረዳት ከሰማይ ከምድርም የተለያዩ አካላትን ይጠቅሳል ፡፡ 🔸1ኛ የሰማይ መላዕክትና 🔸2ኛ የወንጌል አገላጋዮች ራሱንም ጨምሮ 🔸3ኛ ማንም ይህ ማለት ምን ማለት ነው ? 1ኛ የሰማይ መላዕክት ጳውሎስ የሰበከው ወንጌል እንደ ሰው ያለሆነ ወንጌል ነው፡፡ ‹‹ወንድሞች ሆይ፥ በእኔ የተሰበከ ወንጌል እንደ ሰው እንዳይደለ አስታውቃችኋለሁ›› 7ላ 1፡11 ይህ ማለት ሰማያዊና ክርስቶስ የገለጠለት ነው ፡፡ ስለዚህ ይህ በማንም አካለት ሊሻር የማይችል የከበረ እውነት ነው ማለት ነው ፡፡ ከሰማይ ቅዱሳን መላዕክት ወርደው ይሄ ወንጌል ስህተት ነው ቢሉ የተረገሙ ሊሆኑ ይችላሉ እንጂ እውነተኞች ሊሆኑ አይችሉም ፡፡ የእግዚአብሄር መላዕክት የሚሰሩትን የሚያውቁ ጥንቁቆች ናቸው ፡፡ በቅዱሳት መፅሀፍት በብሉያትም በአዲሳትም ይህ ተብረርቶ እናገኘዋለን ፡፡ እነዚህ ቅዱሳን መለዕክት ከሰማይ ኦርደር የሚቀበሉ ታማኞች ናቸው ፡፡ ነገር ግን ይህንን የተከበረ ስራቸውን ትተው ጳውሎስ ከሰበከው ውጪ ሌላ ወንጌል ቢያመጡ በፍፁም እውነተኞች ሊሆኑ አይችሉም ፡፡ የትላንት እውነተኛነታቸው ለዛሬ ልዩ መልዕክት ለማምጣታቸው ዋስትና ሊሆን አይችልም ፡፡ ይልቅ የተረገሙ ሊሆኑ እንደሚችሉ ጳውሎስ ይጠቁማል ወይም የእርግማን ቃል ይናገራል ፡፡ ይህ የሚነግረን ነገር የጳውሎስን ለወንጌል ያለው ቆራጥ አቋምና እርግጠኝነት ነው ፡፡ እርግጠኛ ያደረገው ነገር በክርስቶስ የተሰጠው ከክርስቶስ የተቀበለው መሆኑ ነው ፡፡ ‹‹ኢየሱስ ክርስቶስ ገልጦልኛል እንጂ እኔ ከሰው አልተቀበልሁትም አልተማርሁትምም።›› ገላ 1፡12 በእዚህ ውስጥ የምንማራቸው ቁም ነገሮች ብዙ ናቸው ፡፡ ጳውሎስ ለሰማው እውነተኛ ወንጌል ምን ያህል ታማኝ እንደሆነ እና አስገራሚ ድፍረቱን ነው ፡፡ በክርስቶስ ለተገለጠለት ወንጌል በምንም የማይደረደር መሆኑን ነው የምናየው ፡፡ 🔸 እኛስ እንዴት አይነት ሰዎች እንሆን? ለእዚህ እውነተኛ 🔸ወንጌል ምን ያህል ዋጋ ለመክፈል ዝግጁ ነን? 🔸 የሰማይ መላዕክትን ሳይሆን አንድ ግለሰብን በወንጌል እውነት ለመሞገት ምን ያህል ታማኞች ነን ?ደፈሮች ነን? ብርቱዎች ነን ?የአቋም ሰዎች ነን?፡፡ ጳውሎስ ግን አስገራሚ ድፍረቱን ለሰማው ለክርስቶስ ወንጌል ታማኘረነቱን እናያለን ፡፡ አይ ጳውሎስ!! 2. እኛም ብንሆን ‹‹ ነገር ግን #እኛም ብንሆን ›› ገላ 1፡8 አ.መ.ት ጳውሎስ እኛም ብንሆን እያለ ነው ።ይህ አስገራሚው ነገር ነው ፡፡ እኛ ሲል ማንን እያለ ነው ካልን እርሱንና ከእርሱ ጋር ወንጌል የሚያገለግሉ ታማኝ አገልጋዮችን ነዋ !! የወንጌል እውነትነት የሰውን ማንነት መሰረት አያደርግም ሁሉ ለእዚህ እውነት ዝቅ ይላሉ እንጂ ወንጌል ለሰዎች ማንነት ዝቅ አይልም ፡፡ ጳውሎስ ራሱን ጨምሮ ነው የሚናገረው። ዛሬ ወንጌል ይህ ነው ብዬ ተናግሬ ነገ አቋም ብቀይር ዛሬ የተናገርኩት አይደለም ስህተት እኔ ነኝ አሁን ስህተት እያለ ነው ፡፡ ለምን ይህንን ወንጌል ጳውሎስ ከራሱ አፍልቆ የተናገረው ሳይሆን ከላይ ከክርስቶስ ከሰማይ ከመለኮት የሰማው ነው ፡፡ ክርስቶስ ደግሞ ሊሳሳት አይችልም ፡፡ ክርስቶስ ተሳስቼ ነው የመዳን መንገድን በጳውሎስ በኩል ያስታወኳችሁ አይልም ፡፡ የዛሬ የጳውሎስ እውነቱ ልክ ሲሆን ምናልባት የጳውሎስ የነገ ስህተቱ የዛሬውን እውነት ሳይነካ ስህተት ሆኖ ይቀጥላል እንጂ ጳውሎስ መጀመሪያ የሰበከው እውነት ነው ፡፡ ጳውሎስ እያለ ያለው ይህንን ነው ፡፡ ከእዚህ እውነት በኋላ የሐዋሪያት ሌላ አስተምህሮ ከመጀመሪያው የተለየ ቢያመጡ ስህተት ሊሆን ይችላል እንጂ የቀደመ ትምህርታቸው ስህተት ሊሆን አይችልም ፡፡ ክርስትና በተጋገጠ እውነት የመዳን ጉዳዩን የመሰረተ እንጂ ወደፊት የሚያረጋግጠው ያለቀ እውነት ማለትም ሌላ የመዳን መንገድ የለውም ፡፡ በእዚህ እውነት ወስጥ የምንረዳው ሌላ እውነት ደሞ ይህ ነው ፡፡ወንጌል በአገልጋዮች ማንነት ላይ አይመረኮዝም፡፡ ትላንት ዝነኛ የነበሩ አእማድ ሰዎች ዛሬ ሊስቱ ይችላሉ ፡፡ የትላንት ጉምቱነታቸው ትልቅ አገልጋይነታቸው የዛሬውን ስህተታቸውን አያፀድቅላቸውም ፡፡ ወንጌል ከዝነኛ ሰዎች በላይ እውነት ነው? ፡፡ በሃገራችን ትላንት እጅግ መልካም የነበሩ አገልጋዮች ዛሬ ስህተት ሆነዋል ፡፡ በቆሙበት አልጸኑምና ወድቀዋል ፡፡ ዛሬ እውነት የሆኑ ለነገ ያሰጋሉ ፡፡ በጳውሎስ የተሰበከው ወንጌል ግን በማንኛውም ጊዜ እውነት ነው ፡፡ 3. ማንም ቢሆን ‹‹ከተቀበላችሁት የተለየውን #ማንም ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን።›› ገላ 1፡9 ጳወሎስ ምንም ክፍተት አይተውም ፡፡ ማንም የሚለው ቃል ከላይ የጠቀሳቸውን ጨምሮ የሚያካትትና መጠቅለያ መደምደሚያ ክፍተት መዝጊያ የሚሆን ቃል ነው ፡፡ ማንም ማለት በየትኛውም አቅጣጫ የሚመጣውን የስህተት ትምህርት ከወንጌል ተፃራሪ ሀሳብ የሚመክት ቃል ነው ፡፡ በእዚህ ውስጥ ጳውሎስ ለወንጌል ያለውን ቁርጠኝነት እና ከምንም ጋር ለፉክክር የማያቀርበው የከበረው እውነታው እንደሆነ ነው ምንረዳው ፡፡ ጳውሎስ ለምን እንዲህ አለ? ጳውሎስ በቀጣይ ባሉ ሶስት ቁጥሮች ውስጥ ማለትም በቁጥር 10-12 ባለው ክፍል ውስጥ ሊል የቻለበትም ምክንያት በአጭሩ ይናገራል ፡፡ ‹‹ሰውን ወይስ እግዚአብሔርን አሁን እሺ አሰኛለሁን? ወይም ሰውን ደስ ላሰኝ እፈልጋለሁን? አሁን ሰውን ደስ ባሰኝ የክርስቶስ ባሪያ ባልሆንሁም።ወንድሞች ሆይ፥ በእኔ የተሰበከ ወንጌል እንደ ሰው እንዳይደለ አስታውቃችኋለሁ፤ኢየሱስ ክርስቶስ ገልጦልኛል እንጂ እኔ ከሰው አልተቀበልሁትም አልተማርሁትምም።›› 🔸1ኛ የክርስቶስ ባሪያ ስለሆንኩ ለሰው ደስታ አልሰብክም በሚል ነው 🔸2ኛ እንደ ሰው የሆነ ወንጌል አይደለም በእኔ የተሰበከው 🔸3ኛ ክስርስቶስ ገልጦልኛል እንጂ ከሰው አልተማርኩትምና ነው ፡፡

ርዕስ :-#ያልተገባ_ሞጎስ🙌🙌👇👇 ዘሌዋውያን 16 ⁶ አሮንም ለእርሱ ያለውን የኃጢአቱን መሥዋዕት ወይፈን ያቀርባል፥ ለራሱም ለቤተ ሰቡም ያስተሰርያል። ⁷ ሁለቱንም አውራ ፍየሎች ወስዶ በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ አጠገብ በእግዚአብሔር ፊት ያቆማቸዋል። ⁸ አሮንም በሁለቱ ፍየሎች ላይ ዕጣ ይጥልባቸዋል፥ አንዱን ዕጣ ለእግዚአብሔር ሌላውንም ዕጣ ለሚለቀቅ። ⁹ አሮንም የእግዚአብሔር ዕጣ የሆነበትን ፍየል ያቀርባል፥ ስለ ኃጢአትም መሥዋዕት ያደርገዋል። ¹⁰ የመለቀቅም ዕጣ የሆነበትን ፍየል ያስተሰርይበት ዘንድ፥ ለመለቀቅም ወደ ምድረ በዳ ይሰድደው ዘንድ በሕይወቱ በእግዚአብሔር ፊት ያቆመዋል። ¹¹ አሮንም ስለ ራሱ ኃጢአት የሚሠዋውን መሥዋዕት ወይፈኑን ያቀርባል፤ ለራሱም ለቤተ ሰቡም ያስተሰርያል፤ ስለ ኃጢአቱ የእርሱን መሥዋዕት ወይፈኑን ያርዳል። ¹² በእግዚአብሔርም ፊት ካለው መሠዊያ ላይ የእሳት ፍም አምጥቶ ጥናውን ይሞላል፥ ከተወቀጠውም ከጣፋጭ ዕጣን እጁን ሙሉን ይወስዳል፤ ወደ መጋረጃውም ውስጥ ያመጣዋል። ¹³ እንዳይሞትም የጢሱ ደመና በምስክሩ ላይ ያለውን መክደኛ ይሸፍን ዘንድ በእግዚአብሔር ፊት ዕጣኑን በእሳቱ ላይ ያደርጋል። ¹⁴ ከወይፈኑም ደም ወስዶ በስርየቱ መክደኛ ላይ ወደ ምሥራቅ በጣቱ ይረጨዋል፤ ከደሙም በመክደኛው ፊት በጣቱ ሰባት ጊዜ ይረጫል። ¹⁵ ስለ ሕዝቡም ኃጢአት የሚሠዋውን መሥዋዕት ፍየል ያርዳል፥ ደሙም ወደ መጋረጃው ውስጥ ያመጣዋል፤ በወይፈኑም ደም እንዳደረገ በፍየሉ ደም ያደርጋል፤ በመክደኛውም ላይና በመክደኛውም ፊት ይረጨዋል። ¹⁶ ከእስራኤል ልጆች ርኵስነት ከመተላለፋቸውም ከኃጢአታቸውም የተነሣ ለመቅደሱ ያስተሰርይለታል፤ እንዲሁም በርኩስነታቸው መካከል ከእነርሱ ጋር ለኖረች ለመገናኛው ድንኳን ያደርጋል። ¹⁷ እርሱም ለማስተስረይ ወደ መቅደሱ በገባ ጊዜ ለራሱ፥ ለቤተ ሰቡም፥ ለእስራኤል ጉባዔ ሁሉ አስተስርዮ እስኪወጣ ድረስ በመገናኛው ድንኳን ውስጥ ማንም አይኖርም። ¹⁸ በእግዚአብሔርም ፊት ወዳለው ወደ መሠዊያ ወጥቶ ያስተሰርይለታል፤ ከወይፈኑም ደም ከፍየሉም ደም ወስዶ በመሠዊያው ዙሪያ ያሉትን ቀንዶች ያስነካል። ¹⁹ ከደሙም በእርሱ ላይ ሰባት ጊዜ በጣቱ ይረጫል፥ ከእስራኤልም ልጆች ርኵስነት ያነጻዋል፥ ይቀድሰውማል።

Voice message03:08

#ኢየሱስ የፍቅር በኩር ነው🙌❤

በግል መዝሙር ወንድም ደሳለኝ ይቀጥላል....❤🙌