en
Feedback
Ajeba Emmanuel united church

Ajeba Emmanuel united church

Open in Telegram

እውነት እላችኋለሁ፤ ቃሌን የሚሰማ፣ በላከኝም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ ከሞት ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም።” — ዮሐንስ 5፥24 (አዲሱ መ.ት)

Show more
259
Subscribers
-224 hours
-27 days
-430 days
Posts Archive
ገላትያ ክፍል 12 #ለአፍታ_አልተገዛንላቸውም 🙏 #ለአንድ_ሰአት_እንኳ በቤተክርስቲያን ውስጥ ክብራችን እንዳይነካ የምንታገለውን ያህል ለወንጌል እውነት ታግለን ይሆን ?ለመታየት እንደምንጥረውስ ያህል ለእውነተኛ ወንጌል መታየት ለፍተን ይሆን? ኢየሱስ ከመድረክ ገሸሽ ሲል አንዘርዝሮን ያውቃል ?ሐሰተኞችን ለመታገል በጥበብ ፣በእውነት ታግለን ይሆን?ንፁህ ወንጌል እንዲሰበክ ምን ያህል አስተዋፆ አድርገናል? ጳውሎስ ግን ለወንጌል እውነት የታገለው ትግል የሚያስገርም ነው ። “የወንጌልም እውነት በእናንተ ዘንድ ጸንቶ እንዲኖር ለአንድ ሰዓት እንኳ ለቅቀን አልተገዛንላቸውም።” — ገላትያ 2፥5 "ለእነዚህ ሰዎች ለአንድ አፍታ እንኳ አልተገዛንላቸውም፤ ይኸውም፣ የወንጌል እውነት ከእናንተ ጋር ጸንቶ እንዲኖር ነው። ገላትያ 2:5" በገላትያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሁለት ጎራዎች ተፈጥረዋል። 🔸በእዚህ ጎራ ለእውነተኛ ወንገል የቆሙ በእምነት የእግዚአብሔር ልጅ የሆኑ የክርስቶስ ወታደሮች እንደ ጳውልስ አይነቶች አሉ ። 🔸በእዚያኛው ጎራ ክርስትናን ከሌላ ወንጌል ጋር ለመቀየጥ የሚንቀሳቀሱ የወንጌል ተቃዋሚ ሐሰተኞች አሉ። ከአንደኛው ጎራ የሆነ ጳውሎስ ስለ ወንጌል እውነት ጨክኖ ለአንድ ሰአት እንኳ አልተገዛንላቸውም ይላል ይህ ቃል ለወንጌል እውነት ትኩረት መስጠቱን የሚያሳይ ነው ። ጳውሎስ በገላቲያ መፅሐፍ ውስጥ የወንጌል እውነት የሚለውን አስቀምጧል ። ጳውሎስ የወንጌል እውነት የሚለው ሰፊ ቢሆንም ጥቂቱን ለማሳየት እሞክራለሁ ። 🔸1ኛ መዳን በእምነት እንጂ የሙሴን ሕግ የመቅደስ ስርአት በመጠብቅ አይደለም ። አይሁዳውያን በእግዚአብሔር የተለዩ የኪዳን ሕዝቦች ናቸው ጳውሎስ ይህንን ይመሰክርላቸዋል “እነርሱ እስራኤላውያን ናቸውና፥ ልጅነትና ክብር ኪዳንም የሕግም መሰጠት የመቅደስም ሥርዓት የተስፋውም ቃላት ለእነርሱ ናቸውና፤” — ሮሜ 9፥4 ነገር ግን በሙሴ ሕግ መሰረት የመቅደስ ስርአትን በመፈፀም የሚከናወነው የኃጢያት ማንፃት ስነ ስርዓት የመታደስ ዘመን ሲመጣ ማለትም አዲሱ ኪዳን ሲመጣ አብቅቶለታል ። “ይህም ለአሁኑ ጊዜ ምሳሌ ነው፥ እንደዚህም መባና መስዋዕት ይቀርባሉ፤ እነዚህም #እስከ_መታደስ ዘመን ድረስ የተደረጉ፥ ስለ ምግብና ስለ መጠጥም ስለ ልዩ ልዩ መታጠብም የሚሆኑ የሥጋ ሥርዓቶች ብቻ ናቸውና የሚያመልከውን #በህሊና_ፍጹም ሊያደርጉት አይችሉም።” — ዕብራውያን 9፥9-10 በህሊና ፍፁም ሊያደርግ የሚችለው ኪዳን መጥቷል ።ስለዚህም ለአዲሱ ኪዳን ቦታ መልቀቅ አስፈልጎታል ። "ነገር ግን ኢየሱስ መካከለኛ የሆነበት ኪዳን ከቀድሞው እንደሚበልጥ ሁሉ፣ የተቀበለውም አገልግሎት ከእነርሱ አገልግሎት ይበልጣል፤ ይህም የተመሠረተው በተሻለ የተስፋ ቃል ላይ ነው።የመጀመሪያው ኪዳን ምንም ጒድለት ባይገኝበት ኖሮ፣ ለሁለተኛው ስፍራ ባልተፈለገም ነበር። " ዕብራውያን 8:6-7 ጳውሎስ የወንጌል እውነት የሚለው ይህንን ነው ። በመቅደስ ስርአት የበግ እና የፍየል ደም በማቅረብ የሆነውን ሳይሆን በእምነት የሆነ የመዳን መንገድ።ፅድቅ የሚገኘው በክርስቶስ ነው ይህ የወንጌል እውነታችን የጳውሎስም የወንገል እውነቱ ነው ። “የእግዚአብሔርን ጸጋ አልጥልም፤ ጽድቅስ በሕግ በኩል ከሆነ እንኪያስ ክርስቶስ በከንቱ ሞተ።” ገላትያ 2፥21 🔸2ኛ የእግዚአብሔር ልጅነት በእምነት የእግዚአብሔር ልጅ መሆን የሚቻለው ወደ ክርስቶስ በመምጣት ነው ።እርሱን በማመን በመቀበል ነው ። ሐዋሪያው ዮሐንስ ይህንን ፅፎልናል “ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤” — ዮሐንስ 1፥12 ጳውሎስ በገላቲያ መልዕክቱም ይህንን ነግሮናል ። "ነገር ግን የተወሰነው ዘመን በደረሰ ጊዜ፣ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን፣ ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤ ይህም የሆነው የልጅነትን መብት እናገኝ ዘንድ ከሕግ በታች ያሉትን ለመዋጀት ነው። ልጆችም ስለ ሆናችሁ እግዚአብሔር፣ “አባ አባት” ብሎ የሚጮኽ የልጁን መንፈስ ወደ ልባችን ላከ።ስለዚህ ከእንግዲህ ወዲህ ልጅ ነህ እንጂ ባሪያ አይደለህም፤ ልጅም ስለ ሆንህ፣ እግዚአብሔር ወራሽ አድርጎሃል።" ገላትያ 4:4-7 ይህ ልጅነት በክርስቶስ በመሆን የሚገኝ ነው ። ይህም የወንጌል እውነታችን ነው ። 🔸3ኛ በክርስቶስ ነፃ መሆን በክርስቶስ ኢየሱስ የተገኘ ነፃነታችን ይህ የወንጌል እውነታችን ነው ። “በነጻነት ልንኖር ክርስቶስ ነጻነት አወጣን፤ እንግዲህ ጸንታችሁ ቁሙ እንደ ገናም በባርነት ቀንበር አትያዙ።” — ገላትያ 5፥1 ይህ ነፃነት በክርስቶስ ምክንያት የተገኘ ነፃነት ነው ። በነፃነት እንድንኖር ማለት ግን እንደፈለግን እንኑር የሚለውን የሚያሳይ ሳይሆን በክርስቶስ የዘላለም ሕይወት ማግኘታችንን የሚያሳይ እና ለእዚህ የሚያስፈልገው በክርስቶስ የተሰራ መሆኑን የሚያሳይ እንደሆነ ልብ ይሏል። 4ኛ በሕግ ማንም አይፀድቅም ። ጳውሎስ ሌላው የወንጌል እውነቱ ይህ ነው ። ማንም በሕግ አይፀድቅምና በሕግ ይፀደቃል አትበሉ ነው ። “ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎአልና ማንም በእግዚአብሔር ፊት በሕግ እንዳይጸድቅ ግልጥ ነው።” — ገላትያ 3፥11 እንደውም ይህ ነገር ግልጥ ነው ይላል ።መጽደቅ በክርስቶስ ስራ ነው ። ለእነዚህ ነው ቀደም ብሎ በምዕራፍ ሁለት ላይ እንዲህ ያለው ። “የእግዚአብሔርን ጸጋ አልጥልም፤ ጽድቅስ በሕግ በኩል ከሆነ እንኪያስ ክርስቶስ በከንቱ ሞተ።” — ገላትያ 2፥21 ስለ ወንጌል እውነት ከእነዚህ በላይ ብዙ መጥቀስ ይቻላል ። ጥያቄው ዛሬስ እኛ የሚለው ነው ። ለወንጌል እውነት የምንቆም ነን ወይ? ለእውነተኛ ወንጌል ታማኞች ነን ?ኢየሱስ ብቻ ገኖ እንዲታይ ምን አይነት ዋጋ እየከፈልን ነው ? በእውነት ኢየሱስ በጉባዬው በሕይወታችን ደምቆ ይታይ ።በክርስቶስ ከሆነልን ውጪ የሚሰብኩ ከእውነተኛ ወንጌል ዘነፍ የሚሉ ሁሉ በኢየሱስ ስም አይሳካላቸው ። ለእኛም ለእውነተኛ ወንጌል የምንነሳበት ቀን ይሁንልን ። አሜን ይቀጥላል..... !!! ✍️ Girum Difek

✒ እኛ የተጠራን፣የተወሰነን የክርስቶስን መልክ እንድንመስል እንጂ እንድነስመስል አይደለም። 📝ልጁ በብዙ ወንድሞች መካከል በኵር ይሆን ዘንድ፥ አስቀድሞ ያወቃቸው የልጁን መልክ እንዲመስሉ አስቀድሞ ደግሞ ወስኖአልና፤ — ሮሜ 8፥29 መልካም ቀን ደምቀችሁ ዋሉልኝ💚 📝Teka.E

🎯አምላክ በግ በመሆን የባሪያን መልክ በመያዝ ለእኛ ኖሯል! እኛ ለእርሱ ብንኖር ምንም አይደንቀንም። ✒ለኖረልን ለኢየሱስ ከምር መ-ኖ-ር ይሁንልን! ቀናችሁ ብሩህ ነው ዋሉልኝ 🙌 #Teka.E💚

የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የእምነት አቋም pdfን ለመውረድ/save ለማድረግ አልተቻለም ብላችሁ ነበረ አሁን መውረድ/save ማድረግ ትችላላችሁ! ለሌሎችም ሼር አድርጉ💚 ቀጣይ የሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን እምነት አቋም ይለቀቃል 🙌

አሁን🙏🙏

#እንግዲህ_በክርስቶሰ ኢየሱስ ላሉት አሁን #ኩነኔ የለባቸውም።🙌 --(ሮሜ 8:1)

Ngerulgn Merdo.mp36.75 MB

የኢትዮጵያ_ቃለ_ሕይወት_ቤተክርስቲያን_የእምነት_አቋም.pdf14.59 MB

ክፍል አስራ አንድ #ባሪያ_ሊያደርጉን!! ከባርነት ነፃ መሆን ማለት በክርስቶስ የዘላለም ድነት ማግኘት ማለት ነው ፡፡ ‹‹ነገር ግን ባሪያዎች ሊያደርጉን በክርስቶስ ኢየሱስ ያለንን አርነታችንን ይሰልሉ ዘንድ ሾልከው በስውር ስለ ገቡ ስለ ሐሰተኞች ወንድሞች ነበረ።›› ገላ 2፡4 ‹‹ይህ ጒዳይ የተነሣው አንዳንድ ሐሰተኞች ወንድሞች በክርስቶስ ኢየሱስ ያገኘነውን ነጻነት ሊሰልሉና ባሪያዎች ሊያደርጉን ወደ እኛ ሾልከው በመግባታቸው ነው።›› ገላትያ 2:4 አ.መ.ት በገላቲያ መፅሐፍ ውስጥ በዋናነት የተነሳው ጉዳይ በእዚህ ምክንያት ነው ይላል ፀሐፊው ።በእዚህ ቁጥር ውስጥም ጳውሎስ ሶስት ነገሮችን በዋናነት ያነሳል!! 🔸1ኛ ባሪያዎች ሊያደርጉን 🔸2ኛበኢየሱስ ክርስቶስ ያገኘው ነፃነት 🔸3ኛ ሾልከው በስውር የሚገቡ ሐሰተኛ ወንድሞች እነዚህ ሶስት ሀሳቦች በራሳቸው ብዙ ሊያስብሉ የሚችሉ ናቸው ፡፡ነገር ግን አሁን የመጀመሪያው ላይ ትኩረት በመድረግ እንነጋገራለን ፡፡ #ባሪያዎች_ሊያደርጉን ጳውሎስ ሾልከው ወደ ገላቲያ ቤተ ክርስቲያን የገቡትን ሰዎች ወይም የሐሰት አስተማሪዎች በአማኝ ማሕበረሰብ ውስጥ ሊያደርጉ ከሚችሉት አንዱ ይህ ነው ይላል፡፡ ያለ ማንነታችን ሌላ ማንነት ይሰጡናል፡፡ ነፃ የነበረውን ማሕበረሰብ ወደ ባርነት ያግዙታል ፡፡ ጳውሎስ የሚያንገበግበው ይህ ነው ፡፡ በነፃነት እንድትኖሩ ነፃ ከወጣችሁ በኋላ እንደገና በሐሰት አስተማሪዎች የተነሳ ሪያ ልትሆኑ ትችላላችሁ ፡፡ የእነዚህ ሰዎች መጨረሻ እኛ ባሪያ ማድረግ ነው እያለ ጳውሎስ ይሞግታል ፡፡ ጳውሎስ በገላቲያ መፅሀፍ ውስጥ ባሪያ /ባርነት የሚለው ምንን ነው ? ይህን ጥያቄ ለመመለስ የገላቲያ መፅሐፍ ዞር ዞር ብሎ ማየት ይጠይቃል ፡፡ ጳውሎስ በገላቲያ መፅሐፍ ውስጥ በተደጋጋሚ ይህንን ቃልና ሐሳብ ያነሳዋል ፡፡ የተወሰኑ ጥቅሶች እንመልከት ‹‹ስለዚህ ከእንግዲህ ወዲህ ልጅ ነህ እንጂ ባሪያ አይደለህም፤ ልጅም ከሆንህ ደግሞ በክርስቶስ የእግዚአብሔር ወራሽ ነህ።ነገር ግን በዚያን ጊዜ እግዚአብሔርን ሳታውቁ በባሕርያቸው አማልክት ለማይሆኑ ባሪያዎች ሆናችሁ ተገዛችሁ፤አሁን ግን እግዚአብሔርን ስታውቁ ይልቅስ በእግዚአብሔር ስትታወቁ እንደ ገና ወደ ደካማ ወደሚናቅም ወደ መጀመሪያ ትምህርት እንዴት ትመለሳላችሁ? እንደ ገና ባሪያዎች ሆናችሁ ዳግመኛ ለዚያ ልትገዙ ትወዳላችሁን?›› ገላ 4፡7-9 በክርስቶስ ያመኑትን ልጆች እንጂ ባሪያዎች አይደላችሁም እያላቸው ነው ቅዱስ ጳውሎስ ፡፡ይህንን ክፍል በሰፊው ቦታው ላይ ስንደርስ እናብራራለን ፡፡ ነገር ግን ባርነት ከልጅነታችን የሚለይ ሕይወት መሆኑን መገንዘብ እንችላለን ፡፡ ባሪያ ሆንክ ማለት ልጅነት የለህም ማለት ነው ፡፡ እነዚህ ሾላካ የሐሰት አስተማሪዎች ፍላጎታቸው ከልጅነታችን ቦታ አውርደው ባሪያ እንድንሆን ነው ፡፡ በሌላ ቦታ እንዲህ ይላል !! ‹‹በእምነት በኩል ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጆች ናችሁና፤ከክርስቶስ ጋር አንድ ትሆኑ ዘንድ የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን ለብሳችኋልና።አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም፥ ባሪያ ወይም ጨዋ ሰው የለም፥ ወንድም ሴትም የለም፤ ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ ሰው ናችሁና።እናንተም የክርስቶስ ከሆናችሁ እንኪያስ የአብርሃም ዘር እንደ ተስፋውም ቃል ወራሾች ናችሁ።›› ገላ 3፡26-29 ጳውሎስ አሁን ስለ እግዚአብሄር ልጅነት ይናገርና በምድር ስርአት ባሪያ የነበሩ እንኳን አሁን ዘመን መጥቶላቸው የእግዚአብሄር ልጅ ሆነዋል በስራ ድርሻ በዘመኑ ባለው አኗኗር ባሪያ ቢሆኑም ይህ ስጦታ ግን አልተነፈጋነቸውም ፡፡ በሰው ስርዓት ለሰው ባሪያ የነበሩ ሰዎች የእግዚአብሄር ልጅነት አልተነፈጋቸውም ፡፡ ይህ ነፃነት ለሁሉ የሚያስፈልግ ነው፡፡ ደግሞ በሌላ ቦታም እንዲህ ይላል። ‹‹ነገር ግን እላለሁ፥ ወራሹ ሕፃን ሆኖ ባለበት ዘመን ሁሉ፥ ምንም የሁሉ ጌታ ቢሆን ከቶ ከባሪያ አይለይም፥ነገር ግን አባቱ እስከ ቀጠረለት ቀን ድረስ ከጠባቂዎችና ከመጋቢዎች በታች ነው።እንዲሁ እኛ ደግሞ ሕፃናት ሆነን ሳለን ከዓለም መጀመሪያ ትምህርት በታች ተገዝተን ባሪያዎች ነበርን፤›› ገላ 4፡1-3 ጳውሎስ አማኞች ሁሉ ከባርነት ስር የነበሩ መሆናቸውን በእዚህ ክፍል ይናገራል ፡፡የአማኝ ድሮ ሲታይ የሚያመፃድቅ አይደለም ምክንያቱም አህዛቡም ( ከእስራኤል ውጪ ያለው ማሕበረሰብ) አይሁዳውያንም ከባርነት በታች ነበሩና። ነገር ግን አሁን የብርሃን ዘመን በክርስቶስ መጥቶልናል ፡፡ ከባርነት ነፃ መሆን ማለት በክርስቶስ የዘላለም ድነትን መግኘት ማለት ነው ፡፡ ታዲያ ጳውሎስ እነዚህ የስህተት አስተማሪዎች ባሪያ ሊያደርጉን ሲል ምን እያለ ነው ? ወደ መጣንበት ህይወት ሊመልሱን ነው ፡፡ በትውልድ አይሁዳዊ የሆኑ ክርስቲያኖች አሉ ፡፡ ደግሞ በትውልድ አይሁዳዊ ያልሆኑ ከአይሁድ ማህበረሰብ ውጪ ያሉ ክርስቲያኖች አሉ ፡፡ ከእዚህም ከእዛም የመጡ እነዚህ የአይሁድ ክርስቲያኖች እና ከአይሁድነት ውጪ ያሉ ክርስቲያኖች ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ከመምጣተቸው በፊት ባሪያ ነበሩ ፡፡ ከእዚህ የባርነት ሕይወት ጌታ አውጥቷቸዋል ፡፡ ለእዚህ ነው ጰውሎስ እንዲህ የሚለቸው ፡፡ ‹‹በነጻነት ልንኖር ክርስቶስ ነጻነት አወጣን፤ እንግዲህ ጸንታችሁ ቁሙ እንደ ገናም በባርነት ቀንበር አትያዙ።›› ገላ 5፡1 እነዚህ በገላቲያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በልዩ ወንጌል አምጪነታቸው የተጠቀሱት ሰዎች አካሄዳቸው አማኞችን ወደ ባርነት መመለስ ነው፡፡ ከነፃነት ወደ ባርነት የሚደረግ ጉዞ ነው ፡፡ ‹‹ነገር ግን ባሪያዎች ሊያደርጉን በክርስቶስ ኢየሱስ ያለንን አርነታችንን ይሰልሉ ዘንድ ሾልከው በስውር ስለ ገቡ ስለ ሐሰተኞች ወንድሞች ነበረ።›› ገላ 2፡4 አገኝቶ ማጣት ይዞ መልቀቅ ቀምሶ አለማጣጣም ነግዶ አለማትፍ በልቶ አለመጥገብ ሰርቶ አለማትረፍ ከባድ ነገር ነው ፡፡ ለአማኞች ከእዚህ የባሰ ነገር አለ ፡፡ አማኞች በክርስቶስ ምክንያት ያገኙት ነፃነት እና በረከቶች አሉ ፡፡ ነገር ግን እንደ አለመታደል ሆኖ የሐሰት አስተማሪዎች ከእዚህ ሊያወርዱን ይችላሉ ፡፡ እና ወደ ባርነት ለከቱን ይችላሉ ፡፡ ጳውሎስ ‹‹ነገር ግን ባሪያዎች ሊያደርጉን በክርስቶስ ኢየሱስ ያለንን አርነታችንን ይሰልሉ ዘንድ ሾልከው በስውር ስለ ገቡ ስለ ሐሰተኞች ወንድሞች ነበረ።›› ገላ 2፡4 የሚለው ለእዚሁ ነው ። ታዲያ ምን ይሻላል ? እንግዲህ ፀንታቹ ቁሙ ከክርስቶስ ውጪ ሌላ መዳኛ አትፈልጉ ፡፡ ከእርሱ ውጪ ሌላ የዘላለም ሕይወት ማግኛ ፍለጋ አይናችሁን አታማትሩ ፡፡እርሱ ለዘላለም ህይወት በቂ ነውና ፡፡ ፀጋ እና ሰላም ይብዛላችሁ!! ይቀጥላል ....!! ✍️ Girum Difek

እግዚአብሔር አምላክ በነገር ሁሉ መከናወንን ይስጣችሁ!! መልካም ቀን💚

🙏🙏

#የጽድቅን_ሥራ_ሳትሠራ እንዴት ጻድቅ ልትሆን ትችላለህ? ብለው ከጠየቁህ #ኢየሱስ ኃጢአትን ሳያደርግ እንዴት ኃጢአት ሆነ ብለ ጠይቅ🙌 #Teka.E💚

ስለ ክርስቶስ ስም ከነቀፏችሁ ከሰደቧችሁ #እድለኛ ናችሁ!! ክርስቶስ በእናንተ ምክንያት ከተሰደበ ግን ወየሁላችሁ!!!!                 መምህር አሰግድ ሳህሉ

ባንተ መገረሜን አልጨረስኩም ለፍቅሬ መግለጫ ቋንቋ ቢያጥረኝ እንኳ ግን ላዉራዉ ልናገረዉ ዝም ከማለት ቢሻል የገረመኝ መዳኔ ነዉ እያልኩኝ ሳወራ ድንቅህን አሳየኸኝ በዘመኔ በየተራ #ትገርማለህ_ታስገርማለህ #ትገርማለህ_አንተ Singer samiTM

ወንጌላዊ ጌታሁን ከሀላባ አማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን! ጌታ ድንቅ ጊዜ ሰጥቶናል 💚 ርዕስ:-ኢየሱስ ለምን ቆመ! 👇👇👇👇👇 ➫ኢየሱስ የቆመበት ምክንያት በርጤሜዎስ የመንግስቱ/የተልዕኮ አካል ስለነበረ ነው። ➫ኢየሱስ ስለእናንተ ይቆማል ፡ያዝናል ፡ይራራል..... አሜን ➫ማንም ላይፈልጋችሁ ይችላል ኢየሱስ ግን ይፈልጋችኃል። ➫ሰው አለበበስህን ማንነትህን አይቶ ነው የሚቀርበው... ኢየሱስ ግን ኃጢአተኞች ሆነን ሙታን ሆነን ቀርበን ጌታ ይመስገን ❤🙌 #ማርቆስ 10 ⁴⁶ ወደ ኢያሪኮም መጡ። ከደቀ መዛሙርቱና ከብዙ ሕዝብ ጋር ከኢያሪኮ ሲወጣ የጤሜዎስ ልጅ ዕውሩ በርጤሜዎስ እየለመነ በመንገድ ዳር ተቀምጦ ነበር። ⁴⁷ የናዝሬቱ ኢየሱስም እንደ ሆነ በሰማ ጊዜ፦ የዳዊት ልጅ ኢየሱስ ሆይ፥ ማረኝ እያለ ይጮኽ ጀመር። ⁴⁸ ብዙዎችም ዝም እንዲል ገሠጹት፤ እርሱ ግን፦ የዳዊት ልጅ ሆይ፥ ማረኝ እያለ አብዝቶ ጮኸ። ⁴⁹ ኢየሱስም ቆመና፦ ጥሩት አለ። ዕውሩንም፦ አይዞህ፥ ተነሣ፥ ይጠራሃል ብለው ጠሩት። ⁵⁰ እርሱም እየዘለለ ተነሣና ልብሱን ጥሎ ወደ ኢየሱስ መጣ። ⁵¹ ኢየሱስም መልሶ፦ ምን ላደርግልህ ትወዳለህ? አለው። ዕውሩም፦ መምህር ሆይ አይ ዘንድ አለው። ⁵² ኢየሱስም፦ ሂድ፤ እምነትህ አድኖሃል አለው። ወዲያውም አየ በመንገድም ተከተለው። ➫እርሱም በርጤሜዎስም የመንግስቱ አካል ነበረ 👍 ➫እኛም የመንግስቱ አካል ነን አሜንንንንንን🙇🙇 የመንግስቱ አካል ናችሁ🙌 ➫ወንጌላዊ ጌች ፀጋው ይብዛልህ ❤